Secrets of Truth - 𝘽𝙮 𝙍𝙚𝙨𝙝𝙖𝙙
رفتن به کانال در Telegram
● ዲናችንና በሚመለከት ወቅታዊ መረጃዎችን ➶ Current information about Muslims and Islam 🔗 ሌሎችንም አንገብጋቢ ጉዳዮችን የምንተዋወስበት Channel ነው‼️ ➞ በወቅታዊ ጉዳዮች ላይ አጠር ያሉ ስንኞች (በተለይም ስለ ፈለስጢን 🇵🇸) 🎯 አላማዬ:- የእውነትን ሚስጥሮች ማጋለጥ ነው‼️ #Free_Palestine 🇵🇸
نمایش بیشتر213
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-17 روز
-430 روز
آرشیو پست ها
“ከመልካም ስራዎች በላጩ ተግባር በሙእሚን ወንድምህ ልቦና ውስጥ ደስታን ማስገባት፣ ወይም እዳውን መክፈል፣ ወይም ምግብ ማብላት ነው።”
ረሱል ﷺ
#አላህ_ሆይ ለፍሊስጢኖች ድልን አጎናፅፋቸው🤲🤲
በትናንትናው እለት ልብ የሚነካው ዱዓ ለፍሊስጢኖች
የሸይኽ_ሱደይስ ዱዓ በመስጅድ አልሀረም
🌙🌙 ቀን ✅✅
ረሱል (☪) እንዲህ ብለዋል፦
﴿مَنْ قَامَ لَيْلَةَ الْقَدْرِ إِيمَانًا وَاحْتِسَابًا ، غُفِرَ لَهُ مَا تَقَدَّمَ مِنْ ذَنْبِهِ،﴾
“የለይለተል ቀድርን በኢማንና ከአላህ አጅር በመፈለግ የቆመ ከዚህ በፊት የሰራው ወንጀል በሙሉ ይማርለታል።”
📚 ቡኻሪ (1901) ሙስሊም (760) ዘግበውታል
➖➖➖➖➖➖➖➖➖
✔️ በነዚህ አድራሻዎች ይከታተሉን፦
🌐፦ https://bit.ly/4ayf0xJ
💬፦ https://bit.ly/486xnrS
🌐፦ https://bit.ly/41zEZkk
🌐፦ https://bit.ly/4arMbTx
🌐፦ https://bit.ly/41tIUPv
🌐፦ https://bit.ly/3UTTSwh
አላህ ሰሚ ነው፣ ተመልካች ነው፣ ጥበበኛ ነው፣ ታጋሽ ነው፣ አሸናፊ ነው፣ አዛኝ ነው፣ አዋቂ ነው፤ ፈራጅና ፍትሐዊ ጌታ ነው፣ ልዕለ ኃያልና አየያዘ ብርቱ ነው።
ወራሪዋ እስራኤል በአሜሪካ ይሁን ባይነት በዚህ በተከበረ ወር ሴትና ህፃን ሳትል በጋዛዊያን ላይ ማዝነብ የቀጠለችውን እሳት አላህ ያያል። ትክክለኛ ፍርድንና እገዛን ከርሱ ብቻ እንከጅላለን። እርሱ በርግጥም ከልብ ለተማመኑበት ባሮቹ በጠበቁበት ያገኙታል።
የአሸናፊዎች አሸናፊ የሆነው አላህ በቂያችን ነው፤ ትክክለኛ መጠጊያም ነው። ምን ያምር መጠጊያ‼
አደራ! ከልባችን በዱዓችን አንርሳቸው።
ነብዩ ሰለላሁ አለይሂ ወሰለም ፊት ለፊት አገኘሀቸው ና እንበል ምን ትላቸው ነበር? ምላሹ ልብ ይነካል ❤ እናንተስ ብትሆኑ ምላሻችሁ ምን ይሆን ነበር?
የረመዳን ቁጥሮች፡ በመስጂደል ሐረም እና መስጂድ አን ነበዊ
የረመዳን ወር ዛሬ ሰኞ 17ኛ ቀን ላይ ደርሷል፡፡ በእነዚህ ቀናት በቢሊዮን ከሚቆጠሩ ምዕመናን በተለየ በቅዱሳኑ መካ እና መዲና ከተሞች ለመገኘት የታደሉም አሉ፡፡ በመካ የሚገኘው መስጂደል ሐረም እና የመዲናው መስጂድ አን ነበዊ ምዕመናን በመጀመሪያዎቹ የረመዳን 15 ቀናት የቀረበው የኢፍጣር ገበታ እና የታደለው የዘምዘም ውሃ ምን ያክል ነው? የምዕመናን መስተንግዶስ እንዴት ያለ ነበር? ለሚለው ‘ሐረመይን’ የተሠኘው ድረ ገጽ ያጋራውን የቁጥር መረጃ እንደሚከተለው አቅርበነዋል፡-
የኢፍጣር ገበታ
በመጀመሪያዎቹ የረመዳን 15 ቀናት በሁለቱ መስጂዶች 10 ነጥብ 8 ሚሊዮን የኢፍጣር ገበታ ለምዕመናን ቀርቧል፡፡ ከምግብ ገበታው ተጨማሪ 10 ነጥብ 2 ሚሊዮን የቴምር ጥቅል እንዲዳረስ ተደርጓል፡፡
የዘምዘም ውሃ ዕደላ
በመስጂዶቹ የተገኙ ምዕመናን የተጠቀሙት የዘምዘም ውሃ አጠቃላይ ሥሌት 17 ሺሕ 512 ኪዩቢክ ሜትር ነው፡፡ የተዳረሰው የዘምዘም ውሃ በኩባያ ሲሰላ 100 ነጥብ 6 ሚሊዮን ይደርሳል፡፡ 405 ሺሕ 548 የዘምዘም ጠርሙሶች እንዲቀርብም ተደርጓል፡፡
+4
ከጀግኖቹ መንደር💪🏼
የዛሬው የሰሜናዊ ጋዛ የኻን ዩኑስ ንጋት እንደሌሎቹ አይደለም። በዚህ ግቢ በመቶዎች የሚቆጠሩ ወጣቶች ተሰባስበዋል። እኚህ ወጣቶች ቁርአንን በህሊናቸው ያስቀመጡ ባለዘውዶች ናቸው። በመሆኑም በዚህ የተከበረው ወርና በዛሬው ንጋት በቃላቸው የያዙትን ሙሉ ቁርአን ከንጋት ጀምሮ ሙሉ በሙሉ ያስደምጣሉ።
ፈለስጢን ሆይ ጋዛ ሆይ ባነገብሺው የቁርአን ፍቅር የጌታሽ እርዳታ ጦርና ቀስት ይሁንሽ❤️
እሰኪ አንድ ጥያቄ ልጠይቃችሁ፦
ሶላት ላይ ተሽሁድ ስንቀመጥ የምንለዉ
’’አተሂያቱ’’ ትርጉም ምን እንደሆነ የምናዉቀዉ ስነቶቻችን ነን?
’’አተሂያቱ’’ በእለት ተእለት ሰላታችን ዉስጥ
የምንፈፅመዉ ምርጥ ዱአ ነዉ፡፡ እኔ አታህያቱን ተሽሁድ ላይ ስቀራ በጣም ሃሴት ይሰማኛል፡፡ ምክኒያቱም ከንግግሮች ሁሉ የላቀ ንግግር፤ በፈጣሪያችን አላህ(ሱወ) እና ለአለማት እዝነት በሆኑት ሃቢቡና ሙሰጠፋ ሰለዋቱ ረቢ ወሰላሙን አለይሒ መካከል የተደረገ እዝነትና መተናነስ የተሞላበት እፁብ ድንቅ ንግግር በመሆኑ ነዉ፡፡
ይህም ነቢያችን (ሰዐወ) በኢሰራዕ ወል ሚዕራጀ ጉዞዋቸዉ ወቅት ነበር፡፡
ትርጉሙም እነደሚከተለዉ ነዉ፡-
ነቢያችን (ሰዐወ) በኢሰራዕ ወል ሚዕራጀ ጉዞዋቸዉ ወቅት አላህ (ሱወ) ሲገናኙ አሰላሙ አለይኩም አላሉትም ምክኒያቱም አላህ(ሱወ) ከኛ የሰላም ምኞት የተብቃቃና የሠላም ሁሉ ምንጭ በመሆኑ ይህ ሰላምታ አይገባዉም፡፡
እናም ነቢያችን (ሰዐወ) እነዲህ ነበር ያሉት
’’ አታህያቱ ሊላሂ ወሰለዋቱ ፤ ወጠይባ’’ ’’ .....
ክብር ሁሉለአላህ ነዉ፡፡ ሰላቶች እና መልካም ተግባራቶችም ለአላህ ሲባል የሚደረጉ ናቸዉ አሉ::
አላህም፤- መለሰላቸዉ ’’አሰላሙ አለይካ አዩሀነቢዩ
ወራህመቱላ ወበረካቱ’´ ’’አነተ ነብይ ሆይ! ሰላም
ባንተ ላይ ይዉረድ፡፡ የአላህ እዝነትና ዉዴታም ይስፈንብህ አለ።
ነቢያችን (ሰዐወ) እንዲህ በማለት መለሱ፤-
’አሰላሙ´አለይና ዋኣላ ኢባዲላሂ አሳሊሂነ’’´
በእኛ እና በአላህ ቅን ባሪያዎችም ላይ ሰላም ይስፈን። አሉ!
ይህንን የሰላምታ ቃለ ምልልስ እየሰሙ የነበሩ መላይካዎች እንዲህ አሉ፦
’’አሽሃዱ አንላኢላሃኢለላህ ዋአሽሃዱ አነ
ሙሃመደን አብዱሁ ወረሱሉሁ’’´
’’ከአላህ ዉጪ ሌላ አምላክ እንደሌለ እመሰክራለሁ፡፡ ሙሃመድም የአላህ ባሪያና መልዕክተኛዉ እነደሆነ አመሰክራለሁ፡፡ አሉ!!
እንግዲህ ይህ ነዉ በጌታችንና በነቢያችን (ሰዐወ)
መካከል የተደረገዉ የሰላምታ ልዉዉጥ፡፡ ጥበብ የተሞላበት የነቢያችን (ሰዐወ) ኡመትን ሁሉ ያካለለ ቅዱስ ንግግር ነዉ፡፡
▮ ልብ ብላችሁ ከሆነ አላህ (ሱወ)’’ « ነብይ ሆይ! ሰላም ባነተ ላይ ይዉረድ፡፡ የአላህ እዝነትና ዉዴታም ይስፈንብህ ሲላቸዉ » ፤ « በእኛ እና በአላህ ቅን ባሪያዎችም ላይ ሰላም ይስፈን » ነበር ያሉት።
〽️ ነቢያችን (ሰዐወ) በእኔ ላይ ሰላም ይስፈን አላሉም፣
ይልቁንስ በእኛ የሚለዉን ቃል ነዉ የተጠቀሙት፡፡
ለዚህም ነዉ ተሸሁድ ስቀመጥ አታህያቱን ስቀራ
በተመስጦ የምቀራዉ፡፡ ከዚህ በፊት ትረጉሙን የማታዉቁ ሰዎች ካሁን በኋላ እነደኔ አይነት ስሜት ይኖራችሁዋል ብየ አሰባለሁ፡፡
ወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላሂ ውብረካቱ ፡፡
Via--- Copy
👇𝐉𝐨𝐢𝐧 & 👇𝐒𝐡𝐚𝐫𝐞
YouTube.com/@SecretsofTruth
tiktok.com/@secretsof_truth
Twitter.com/Secretsof_Truth
Instagram.com/secretsof_truth
t.me/Secretsof_Truth
Fb.com/SecretsofTruth1
ለየትኛውም ለአስታየትና ድጋፍ:-
t.me/ReshadMuzemil
► ቀልባችንን የሚያረጋጋን!
► ውስጣችንን በሀሴት የሚሞላን!
► እሱን በማንበባችን ብቻ አጅር የምናገኝበት
► መጥፎውን ከጥሩ፣ ሀላልን ከሃራም፣ ቢድዓን ከሱና፣ ከሽርክን ከተውሒድ የሚለይልን!
► እውነትን የሚያስተምረን!
► ከአርሽ በለይ የሆነው የጌታችን የአላህ ቃል *ቁርዓን።*
#ጋብዤያችኋለሁ።
ጣፋጭ እና ቆንጆ ምክር የያዘ ግጥም ነው
👌በአላህ ላይ ብቻ መደገፍ እንዳለብን
📲لمتابعة القناة على التليجرام
الدال على الخير كا فاعله
💬 ሼር በማድረግ የአጅሩ ተካፋይ እንሁን
ተሌግራማችንን ተቀላቀሉ👇👇👇
t.me/ReshadIbnuMuzemil
⭕️ Fb.com/InspiresWorldWide
⭕️ Fb.com/ReshadIbnuMuzemil
⭕️ Fb.com/ReshadMuzemil2
⭕️ Fb.com/ReshadIbnuMuzemil1
«ኢትዮጵያ- ውለታ ዋለች ወይንስ ተዋለላት⁉️
ኢትዮጵያ ውስጥ በስፋት ከሚተረኩ ትርክቶች መካከል አንዱ ኢትዮጵያ ለስደተኞቹ የነብዩ መሃመድ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሰሃባዎች መጠግያ በመስጠት ለአለም ሙስሊሞች ታላቅ ውለታን ውላለች የሚለው ታሪክ ነው። ለስደተኞቹ ሰሃቦች ንጉሷ አል ነጃሺ አስሃማ ኢብኑ አብጀር መጠለያ መስጠቱ እውነት ነው፣ ነገር ግን ይህ ጉዳይ መመዝገብ ያለበት ኢትዮጵያ ለኢስላም እንደዋለችው ታላቅ ውለታ ወይንስ አላህ ለኢትዮጵያ እንደዋለላት ታላቅ ውለታ ነው? የሚለው በአግባቡ መዳሰስ ያለበት ጉዳይ ነው፡፡ ነብዩላህ ዩኑስን በአሣ ነባሪ ሆድ ውስጥ መጠለያ የሰጠ ፈጣሪ የነብዩን ሰሃባዎች ሲሻው እዚያው መካ ውስጥ፣ አለበለዚያም አካባቢው ባሉ ግዛቶች ውስጥ ወይንም ወዳጄ አቅል አይምሮ እንዳለው ጃፓን ወስዶ ሊያስጠልላቸው ይችል ነበር። ነገርግን በሃበሻ ምድር ላይ በ አል ነጃሺ ጥላ ሥር እንዲጠለሉ መረጠ! ይሄ ለሃበሻ ምድር ትልቅ ክብር ነው። ለዚህ ታላቅ ክብር በመታጨቷ የሃበሻ ምድር ኩራት ሊሰማትና ለዚህ ክብር ያጫትን ፈጣሪ ልታወድስ፣ የዚህም ከፍተኛ ክብር ባለቤት ትሆን ዘንድ በመምረጥ ለዋለላት ውለታ አብዝታ ልታመሰግን እንጂ ተመስጋኝ ካልሆንኩ ብላ ልትቀውጥ አይገባም።
.
ነብዩ መሃመድ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) መካን በተቆጣጠሩ ጊዜ የመዲና ሰዎች - “እነሆ ነብዩ መሃመድ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) የትውልድ ሃገራቸውን (መካን) ተቆጣጥረዋል፣ ምርኮውንም ለመካ ሰዎች አከፋፍለዋል ከአሁን በኋላ ከተማቸውን ለቀው አይወጡም” - በማለት ማጉረምረም ይጀምራሉ፡፡ ታድያ ነብዩ መሃመድ (ሶለላሁአለይሂ ወሰለም) ይህንን ሲሰሙ የመዲና ሰዎችን ሰብስበው - “የመካ ሰዎች የተከፋፈሉት ቅራቅንቦዉን (ቁሳቁስ) ነው፡፡ እናንተ ግን ነብዩን ይዛችሁ ነው የምትመለሱት፣ በዚህ አትብቃቁምን?” - ሲሉ ጠየቋቸው። የመዲና ሰዎችም “እርሶንማ ይዘን የምንመለስ ከሆነ በቂያችን ነው!” ሲሉ ደስታቸውን ገለጹ። የተሰራላቸውንም ውለታ ተገነዘቡ።ለዚህ ከፍተኛ ክብር በመብቃታቸውም ፈጣሪያቸውን አመሰገኑ። መዲናም የታላቁ ነብይ ነብዩ መሃመድ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) የማረፊያ ቦታ ሆነች። በዚህም ምክንያት በቁዱስ ከተማነት ተሰየመች። እነሆም በየአመቱ በአሥርተ ሚሊዮን የሚቆጠሩ ምእመናን የሚጎበኟት ከተማ ለመሆን በቃች። የተሰራልህን ውለታ ስትረዳና አመስጋኝ ስትሆን እንዲህ ነው! - በዱንያም በአኬራም (በዚህም ሆነ በመጪው አለም)፣ በመንፈስም፣ በቁስም አትራፊት ሆናለህ። ውለታ ቢስ ስትሆን ግን ሥራህ ከንቱ፣ ልፋትህ ኪሳራ እንጂ ትርፍ የሚያመጣ አይሆንም።
.
ወደ ኢትዮጵያ ስንመለስ እሺ መቸም ሙስሊም ያልሆኑት ዜጎች የተዋለላቸውን ውለታ በላመረዳታቸውና ውለታ በዚህም ምክንያት ዉለታ ቢሶች ሆነው ከዚህ ከፍተኛ ክብር ሊገኝ የሚችለውን መንፈሳዊም ሆነ ቁሳዊ ጥቅም ሳያገኙ መቅረታቸው ሳያንስ በተለዋጩ የፖለቲካ ጥቅም ለማግኘትና ሙስሊሙን በገዛ ሃገሩ መጤ፣ ባይተዋር እንደሆነ አድርጎ በመሳል አንገቱን ለማስደፋትና መብቱን ለመጋፋት ይመቻቸው ዘንድ “ለኢስላም ውለታ ውለናል! እኛ ባንኖር ኢስላም ያበቃለት ነበር! ከእነአካቴው ይጠፋ ነበር!” ብለው ይቀውጡት፤ ሙስሊሞችስ የምን ቤት ሆነን ነው ይህንኑ የተንሸዋረረ ትርክት የምናስተጋባው? ለአንድ ሙስሊም ከኢስላም የበለጠ ነገር አለ እንዴ? ኢስላምን ካገኝን በኋላ ሌላ ምን አይነት ሽልማት ነው ከፈጣሪያችን የምንሻውና ነው “ሃገራችን ለኢስላም ውለታ ውላለች” ብለን አካኪ ዘራፍ እያልን ያለነው? ደግሞ ይህንን የተንሸዋረረ ትርክት በአደባባይ እያስተጋቡ ያሉት ወንድሞች እኮ ኢስላምን ተውና የዶላር ቢሊየነሮች ሁኑ ቢባሉ እኮ እሺ የሚሉ አይደሉም። ኢስላምን ትተው ባለፀጋ ከመሆን ይልቅ እስልምናቸውን ይዘው ድሆች ሆነው ኖረው ወደ አኬራ ቢሄዱ የሚመርጡ ሰዎች እኮ ናቸው። ታዲያ እንዴት ነው እሱ ይህንን ያህል ከፍተኛ ዋጋ ያለውን ምንዳ በመለገስ ከፍተኛ ውለታ የዋለላቸውን ሃይማኖት ውለታ ሰርተንለታል ብለው ደፍረው የሚናገሩት? እንደ እኔ እንደ እኔ የሃበሻ ሙስሊሞች ሊሉ የሚገባው “አላህ ሱብሃነሁ ወተዓላ ከምድር በሙሉ የሃበሻን ምድር መርጦ ለነብዩ መሃመድ (ሶለላሁ አለይሂ ወሰለም) ሰሃባዎች መጠጊያ በማድረግ ለሰራልን ውለታ አመስጋኞች ነን። ለዚህም ከፍተኛ ክብር በመብቃታችን ደስተኞች ነን። ይህንን ከፍተኛ ክብር መሸከም የሚያስችል አቅም ስጠን፣ አሚን” ነው።»
©: RN05
𝐒𝐮𝐫𝐚𝐡 𝐀𝐭-𝐓𝐚𝐰𝐛𝐚𝐡 (𝟗:𝟓𝟏)
قُل لَّن يُصِيبَنَآ إِلَّا مَا كَتَبَ ٱللَّهُ لَنَا هُوَ مَوۡلَىٰنَاۚ وَعَلَى ٱللَّهِ فَلۡيَتَوَكَّلِ ٱلۡمُؤۡمِنُونَ
Say, “Never will we be struck except by what Allah has decreed for us. He is our Protector, and upon Allah let the believers rely.”
Sprich: “Uns wird nur das treffen, was Allah für uns bestimmt hat. Er ist unser Schutzherr. Auf Allah sollen sich die Gläubigen verlassen.“
+3
250 umbrellas in the courtyards of Masjid Al Nabawi, which operate automatically.
ጠበቃ ሙሉጌታ በላይ ልጅ ያሬድን የቤተክርስቲያን ክብር ደፍሯል በማለት ለፍርድ ያቀረበና ለሌሎች የቤተእምነቱ የህግ ጉዳይ ላይ ቀዳሚ ተሰላፊ የሆነ የህግ ባለሞያ ነዉ። የእፎይ ጉዳይም እንዲህ አብራርቶታል አዳምጡት!
ለበለጠ ወቅታዊ መረጃወችን ለማገኘት
የቴሌግራም ቻናላችን ከስር በሊንኩ ይቀላቀሉ👇
https://t.me/+UAKV32q7U2HKzEMf
ረመዿን 15
🌙 فضل قيام الليل 🌙
የሌሊት ሰላት ትሩፋት
የደጋጎች ልማድ የሆነው የሌሊት ሰላት ትሩፋት በቁርዓን እና በሐዲስ የተጠቀሱት ተቆጥረው አያልቁም
የሌሊት ሰላት የዕውቀት ባልተቤቶች መለያ ነው ፤ እውቀት ያላቸው ሰዎች ከሌላቸው ሰዎች ጋር ይስተካከላሉን?
ሙስሊም በሆነ አካል ላይ ነገ የትንሣኤ ዕለት ነፃ የሚያወጣውን እንዲሁም የሚጠቅመውን መልካም ስራዎችን በማዘውተር ላይ ሊበረታ ይገባል
እነዚህንም ሲያከናወን አላህ ፊት የተዋረደ ሆኖ ሊተናነስ እና ሌላው ከእሱ ውጭ ያሉት ያልገራላቸውን ሰዎች መናቅ እና ከራሱ አሳንሶ መመልከት የለበትም
ሌላው ወንዶችም ሆነ ሴቶች እነዚህን ወደ አላህ የሚያቃርቡን በሆኑ አምልኮች ላይ አላስፈላጊ የሆኑ ነገሮችን፤ ከእሱ ሊያርቀን ከሚችሉ አንዳንድ ሀራም የሆኑብን ነገሮችን ከመጨመር ልንጠነቀቅ ይገባል
አንዳንድ ሰው ወደ መስጅድ ለሰላት ይመጣል፤ ነገር ግን በሰዎች ክብር ላይ ይረማመዳል በራሱ ይደነቃል ሌላም ሌላም ወንጀሎችን ይፈፅማል
አንዳንድ ሴቶችም እንዲሁ ትልቅ ኢባዳን ለመፈፀም ክልክል የሆኑትን አንዳንድ ወንጀሎችን ይፈፅማሉ፤መህረም ካልሆነ ባዕድ አጅነቢ ከሆነ ወንድ ጋር አብሮ መሄድ የለባትም
ለመልካም ነገር ጉጉት ቢኖራትም እንኳን ከተቃራኒ ፆታ ጋር ብቻዋን መንቀሳቀስ ክልክል ነው
አላህ ዘንድ ያለው ምንዳ እሱን በማስቆጣት አይደለም የሚገኘው!
🔈 ሸይኽ አብዱልከሪም አል-ኹደይር አላህ ይጠብቃቸውና
One of the Shortest Duas By Sheikh Bandar Baleelah On The 15th Night Of Ramadhan.
Join Our Channel For More Updates : https://t.me/haramainsharif
