fa
Feedback
Biruke Fact

Biruke Fact

رفتن به کانال در Telegram
6 958
مشترکین
-124 ساعت
-257 روز
-1030 روز
آرشیو پست ها
ፈርኦኖቹ ተደረማመሱ። የአንፊልድን ሜዳ ያንቀጠቀጡ የሞ ሳላ እግሮች በሞሮኮ ምድር ሳይጠበቁ ዝለዋል። የአባይን ውሀ እየጠጡ ያደጉት ፈርኦኖቹ ግብፆች በሴኔጋል የቁርጥ ቀን ልጅ በጥቁር አልማዙ በ se
ፈርኦኖቹ ተደረማመሱ። የአንፊልድን ሜዳ ያንቀጠቀጡ የሞ ሳላ እግሮች በሞሮኮ ምድር ሳይጠበቁ ዝለዋል። የአባይን ውሀ እየጠጡ ያደጉት ፈርኦኖቹ ግብፆች በሴኔጋል የቁርጥ ቀን ልጅ በጥቁር አልማዙ በ sedio mane ብትንትናቸው ወቷል። ከግማሽ ፍፃሜው የካይሮ ትኬታቸው የቆረጡት ፈርኦኖቹ የውድድሩ አሳዛኝ ተሸናፊ ሆነዋል። የማኔው ሴኔጋል ለፍፃሜው ጨዋታ ከወዲሁ ትኬታቸው ቆርጠዋል ማለፋቸውም በይፋ አረጋግጠዋል። ሴኔጋል ሀገር በደስታ እየተናወጠች ትገኛለች።

ሰበር አስደሳች መረጃ ‼️ ትብብራቹ አንድነታቹ በመጨረሻም ፍሬ አፍርትዋል። Popular electronics በይፋ 1 million ገብተዋል። በታድያ ብዙሀኑ ማህበረሰብ ቻለንጁን ላስጀመረው አዶናይ ም
ሰበር አስደሳች መረጃ ‼️ ትብብራቹ አንድነታቹ በመጨረሻም ፍሬ አፍርትዋል። Popular electronics በይፋ 1 million ገብተዋል። በታድያ ብዙሀኑ ማህበረሰብ ቻለንጁን ላስጀመረው አዶናይ ምስጋናቸው እያቀረቡ ሲሆን። ይህ እንዲሳካ ለተባበራቹ ሁላቹም  ታላቅ ምስጋና ይገባችኋል።

ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የልደት በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። መልካም የልደት በዓል
ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች መልካም የልደት በዓል እንዲሆንላችሁ እንመኛለን። መልካም የልደት በዓል

እጅግ አሳዛኝ መረጃ ተሰምቷል‼️ ከ30 በላይ ወጣቶች ህይወታቸውን ማለፉ ተሰምቷል። ሁላቹም ነፍስ ይማር በሉ ከድንገተኛ አደጋ ፈጣሪ ይጠብቀን። በዛሬው እለት ከጠዋቱ 11:00 ላይ በተሳቢ መኪና ቁጥ
+2
እጅግ አሳዛኝ መረጃ ተሰምቷል‼️ ከ30 በላይ ወጣቶች ህይወታቸውን ማለፉ ተሰምቷል። ሁላቹም ነፍስ ይማር በሉ ከድንገተኛ አደጋ ፈጣሪ ይጠብቀን። በዛሬው እለት ከጠዋቱ 11:00 ላይ በተሳቢ መኪና ቁጥራቸው ወደ 100 የሚጠጉ ህይወታችንን እንቀይራለን በማለት ልጅነታቸውን ትተው ለራሳቸው እና ለቤተሰባቸው የተሻለ ነገን ፍለጋ በማለት በህገ ወጥ መንገድ ወደ ሳዑዲ አረቢያ በመጓዝ ላይ እያሉ ሰመራ እየተገነባ ካለው አድሱ አደባባይ ላይ ወድቆ ከ30 በላይ የነገ ተስፋ ወጣቶች ተቀጥፈዋል። ቀሪዎቹ ወደ ዱብቲ ሆስፒታልለህክምና መወሰዳቸውን ዘመን ተሻጋሪው ከስፍራው መረጃውን አጋረሰቷ። ለሟቾች ነፍስ ይማር ለቤተሰቦች መፅናናትን እመኛለሁ።

አስቸኳይ_ማስጠንቀቂያ‼️ ሰሞኑን የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ እንዲሁም ሌሎች ባንኮች ባለንበት ሆነን የፈይዳ መታወቂያችንን በልንክ ገብተን ማስተሳሰር እንዳለብን ማሳወቃቸው ይታወሳል። ይሁን እንጂ ይህንን ገጠመኝ በመጠቀም አንዳንድ አጭበርባሪዎች የተለያዩ ልንኮችን በመላክ ፎርም ይሙሉ በማለት ብዞዎችን እያሳቱ ይገኛሉ። #ስለዚህ ለጥንቃቄ ያክል በምከተለው መንገድ መስተካካል ይቻላል:_ 1. ቅድመ ዝግጅት (ምን ያስፈልገዎታል?) ሥራውን ከመጀመርዎ በፊት እነዚህን ነገሮች ያዘጋጁ፦ ⏺ የባንክ ሒሳብ ቁጥርዎ፡ (ለምሳሌ፦ 1000...) ⏺ የፋይዳ ተለዋጭ ቁጥር (FAN): በመታወቂያው ላይ ያለ 16 አሃዝ ቁጥር። ⏺ ባንክ ቤት ያስመዘገቡት ስልክ፡ ለደህንነት ማረጋገጫ የሚላክላችሁን የሚስጥር ቁጥር (OTP) ለመቀበል። 2. የሂደቱ ዝርዝር ደረጃዎች ⏺1️⃣. የባንክ ሒሳብዎን ማረጋገጥ መጀመሪያ ሲስተሙ "ይህ የባንክ ሒሳብ የእርስዎ ነው?" የሚለውን ያረጋግጣል። ⏺ ሊንኩን (https://cbefayda.cbe.com.et/) ይከፍታሉ። ⏺ የባንክ ቁጥርዎን ሲያስገቡ ወደ ስልክዎ ባለ 6 አሃዝ ቁጥር (OTP) ይላካል። ⏺ ያንን ቁጥር ድረ-ገጹ ላይ ሞልተው ሲያረጋግጡ ወደ ቀጣዩ ክፍል ያልፋሉ። 2️⃣. የፋይዳ ቁጥርዎን ማገናኘት አሁን የባንክ ሒሳብዎን ከብሔራዊ መታወቂያዎ ጋር የማጣመር ሥራ ይሠራል፦ ⏺ የፋይዳ 16 አሃዝ ቁጥርዎን ያስገባሉ። ⏺ እንደገና ለደህንነት ሲባል ወደ ስልክዎ ሌላ የሚስጥር ቁጥር (OTP) ይላካል። ⏺ ያንን ቁጥር አስገብተው "Verify" እና "Allow" ይላሉ። ይህ ማለት "ባንኩ የፋይዳ መረጃዬን እንዲያይ ፈቅጃለሁ" ማለት ነው። ✅3️⃣. መጨረሻ ⏺ "Accept and Update" የሚለውን ሲጫኑ መረጃው ወደ ባንኩ ይላካል። ⏺ "Update complete. Pending Approval" የሚል መልእክት ካዩ ሥራዎን በትክክል ጨርሰዋል ማለት ነው። ባንኩ መረጃውን አይቶ በሲስተሙ ያጸድቀዋል። ✅ 3. ለምን ይህን ማድረግ አስፈለገ? ⏺ የመንግሥት ትዕዛዝ ስለሆነ፦ ከሕዳር 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ ያለ ፋይዳ መታወቂያ የባንክ አገልግሎት ማግኘት አይቻልም። ⏺ ባንክ ቤት ላለመሄድ፦ ይህ አማራጭ ባንክ ቤት ሄደው ሰልፍ ሳይይዙ ባሉበት ቦታ እንዲጨርሱ ይረዳዎታል። ⏺ የአካውንት ደህንነት፦ የባንክ ሒሳብዎ ከእርስዎ የጣት አሻራ እና የፊት ገጽታ መረጃ (Biometrics) ጋር ስለሚገናኝ ለደህንነትዎ እጅግ አስፈላጊ ነው። ⚠️ ወሳኝ ጥንቃቄ! ይህን ሂደት በሚያደርጉበት ጊዜ ወደ ስልክዎ የሚላከውን የሚስጥር ቁጥር (OTP) ለማንም ሰው በስልክም ሆነ በአካል አይስጡ። ባንኩ በስልክ ደውሎ ይህን ቁጥር አይጠይቅዎትም።

ኢትዮ ቴሌኮም በተለያዩ ጥቅሎች ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን በይፋ አስታወቀ‼️ እየታዩ ያሉትን የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎች፣ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች እየጨመሩ ያሉ የካፒታልና የሥራ ማስኬጃ ወጪዎችን
ኢትዮ ቴሌኮም በተለያዩ ጥቅሎች ላይ የዋጋ ጭማሪ ማድረጉን በይፋ አስታወቀ‼️ እየታዩ ያሉትን የማክሮ ኢኮኖሚ ሁኔታዎች፣ እንዲሁም በተለያዩ ምክንያቶች እየጨመሩ ያሉ የካፒታልና የሥራ ማስኬጃ ወጪዎችን ከግምት ውስጥ በማስገባት መጠነኛ የታሪፍ ማስተካከያ ተግባራዊ ማድረግ አስፈላጊ ሆኖ ተገኝቷል። ይህ ማስተካከያ ኩባንያችን ለደንበኞቹ የሚሰጠውን ሰፊ አገልግሎት ቀጣይነት ለማረጋገጥ እና በመላ አገሪቱ እያካሄድን ያለውን የቴሌኮሙኒኬሽን እና የዲጂታል መሠረተ ልማት መስፋፋትን በዘላቂነት ለማጠናከር እና ወደፊት ለማራመድ ነው። ይህ ማስተካከያ ሲደረግ የደንበኞቻችንን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ የሚከተሉት ነጥቦች ታሳቢ ተደርገዋል፦ የቴሌብር ልዩ ስጦታ፦ በቴሌብር ጥቅል ሲገዙ የነበረው የ10% ቅናሽ ወደ 20% ከፍ እንዲል ተደርጓል። ዋጋቸው ያልተቀየሩ ጥቅሎች፦ በርካታ ደንበኞች የሚጠቀሙባቸው 38 የተለያዩ ጥቅሎች ላይ ምንም ዓይነት የዋጋ ጭማሪ አልተደረገም። ዲጂታል አካታችነትን ለማስቀጠል፦ ዝቅተኛ ገቢ ያላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች የሚጠቀሙባቸው የ1 ብር፣ የ2 ብር፣ የ5 ብር እና የ1 ሰዓት ጥቅሎች ባሉበት ቀጥለዋል። ልዩ ጥቅል፦ ለአካል ጉዳተኞች፣ ለተማሪዎች እና ለመምህራን የተዘጋጁ ልዩ ጥቅሎች ላይ ምንም ዓይነት ጭማሪ አልተደረገም። ለዘወትር አብሮነታችሁ እያመሰገንን፣ የዜጎችን ኑሮ የሚያዘምኑ የዲጂታል መፍትሔዎችን ማቅረባችንን አጠናክረን እንቀጥላለን!

አሳዛኝ ዜና‼️ ዛሬ በገብርኤል ዕለት 5 ህፃናት ህይወታቸው ማለፉ ተገለፀ። ታህሳስ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት በዓድዋ በአሉላ ጣቢያ (እንዳ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ) በታላቁ የቅ
አሳዛኝ ዜና‼️ ዛሬ በገብርኤል ዕለት 5 ህፃናት ህይወታቸው ማለፉ ተገለፀ። ታህሳስ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በዛሬው ዕለት በዓድዋ በአሉላ ጣቢያ (እንዳ ገብርኤል ተብሎ በሚጠራው አካባቢ) በታላቁ የቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል ዕለት፣ በአጋጠመ አሳዛኝ አደጋ የ5 ህፃናት ሕይወት ማለፉን የዓድዋ ከተማ አስተዳደር አስታውቋል። ሕፃናቱ በመኖሪያ ቤታቸው ውስጥ ተኝተው ሳለ በከሰል ጭስ በመታፈን በድንገት ሕይወታቸው ሊያልፍ ችሏል። ከእነዚህም መካከል ሦስቱ የአንድ ቤት ልጆች ሲሆኑ፣ ሁለቱ ደግሞ የአባወራው እህት ልጆች መሆናቸው ተገልጿል።

እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ በመላ ሀገሪቱ በየደብራቱ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።
እንኳን ለቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብረ በዓል በሰላም አደረሳችሁ። ዓመታዊው የቅዱስ ገብርኤል በዓለ ንግስ በመላ ሀገሪቱ በየደብራቱ በድምቀት እየተከበረ ይገኛል።

ቲክቶከሩ አዶናይ በትግራይ በሕፃፅ በራብ ለተጎዱ ወገኖች አንድ ቀን ሳይሞላ 11 ሚልየን ብር በመቶ ብር ቻሌንጅ ማሰባሰብ ችሏል። ቲክቶክን እንዲህ ላለ በጎ አላማ ማዋሉ ወጣቱ ቲክቶከር ከብዙ ወገኖች
+1
ቲክቶከሩ አዶናይ በትግራይ በሕፃፅ በራብ ለተጎዱ ወገኖች አንድ ቀን ሳይሞላ 11 ሚልየን ብር በመቶ ብር ቻሌንጅ ማሰባሰብ ችሏል። ቲክቶክን እንዲህ ላለ በጎ አላማ ማዋሉ ወጣቱ ቲክቶከር ከብዙ ወገኖች ምስጋና ተችሮታል።

መረጃ‼️ በቲክቶክ የፈጠራ ስራዎች እና በባህል ጥበቃ ዙሪያ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጠ ማብራሪያ‼️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቲክቶክ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በሰጡት አዲስ ማብራሪያ፣
መረጃ‼️ በቲክቶክ የፈጠራ ስራዎች እና በባህል ጥበቃ ዙሪያ ከጠቅላይ ሚኒስትሩ የተሰጠ ማብራሪያ‼️ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ በቲክቶክ ማህበራዊ ሚዲያ አጠቃቀም ዙሪያ በሰጡት አዲስ ማብራሪያ፣ ወጣቶች ቴክኖሎጂውን ለፈጠራ ስራዎችና ለኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት እንዲያውሉት መንግስት ድጋፍ እንደሚያደርግ አስታወቁ። ይሁን እንጂ፣ ይህ ነፃነት * የሀገሪቱን ባህል፣ * ወግና * እሴቶች በጣሰ መልኩ መሆን እንደሌለበት በጥብቅ አሳስበዋል። ጠቅላይ ሚኒስትሩ በንግግራቸው፤ ወጣቶች ከውጭው ዓለም የሚመጡ ተጽዕኖዎችን ሲቀበሉ "ጠቃሚውን ብቻ" በመለየት መሆን እንዳለበት ጠቁመው፣ ከኢትዮጵያ ስርአት ውጪ የሚንቀሳቀሱ አካላት ላይ "መመከርና መገሰጽ" አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል። ቀጣዩ ትውልድ ሊታሰብበት ይገባል፤ መልካሙን ብቻ ማሳየት የሁላችንም ኃላፊነት ነው" ሲሉም ተናግረዋል።

ስለ ማስተር አብነት! በአሁኑ ወቅት ማስተር አብነት ከበደ በሀገራችን በሚገኝ አንድ ትልቅ ሆስፒታል ህክምናውን እየተከታተለ ይገኛል። በፈጣሪ እርዳታ አሁን ያለበት ሁኔታ ጥሩ የሚባል ነው። የሀኪሞችን
+2
ስለ ማስተር አብነት! በአሁኑ ወቅት ማስተር አብነት ከበደ በሀገራችን በሚገኝ አንድ ትልቅ ሆስፒታል ህክምናውን እየተከታተለ ይገኛል። በፈጣሪ እርዳታ አሁን ያለበት ሁኔታ ጥሩ የሚባል ነው። የሀኪሞችን ውሳኔ ተከትሎ በቀጣይ ከሀገር ውጪ አልያም በሀገር ውስጥ ህክምናውን ተከታትሎ በቅርቡ ወደ በጎ ስራው ይመለሳል ብለን ተስፋ እናደርጋለን። የሚኖረውን አዲስ ነገር የምናሳውቃቹ ይሆናል። አሁንም በፀሎት አስቡት። እናመሰግናለን። NB:- በማስተር አብነት እውቅና ለመላው ኢትዮጽያውያን የተላለፈ መልዕክት። Via brook news

የሴቶች አርተፊሻል ፀጉር ወይም ዊግ ወደ ሀገር እንዳይገባ ተከለከለ። የቡርኪናፋሶው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ አርቲፊሻል ጸጉር (በተለምዶ ዊግ በመባል የሚታወቁት) ወደ አ
የሴቶች አርተፊሻል ፀጉር ወይም ዊግ ወደ ሀገር እንዳይገባ ተከለከለ። የቡርኪናፋሶው መሪ ኢብራሂም ትራኦሬ ከውጪ ወደ ሀገር ውስጥ የሚገቡ አርቲፊሻል ጸጉር (በተለምዶ ዊግ በመባል የሚታወቁት) ወደ አገራቸው ቡርኪና-ፋሶ እንዳይገቡ መከልከላቸው ተሰምቷል። ትራኦሬ በንግግራቸውም አፍሪካ አህጉር እንጂ  "ሙዚየም አይደለችም" ሲሉ ተደምጠዋል።

በቲክ ቶክ ስሙ Lil_jay የተባለ ወጣት እና ባልደረባው ከኢትዮጵያ ባህልና ወግ ባፈነገጠ መልኩ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተጠርጥረው ታሰሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደገለፀው ከሆነ በቲክቶክ ስሙ L
በቲክ ቶክ ስሙ Lil_jay የተባለ ወጣት እና ባልደረባው ከኢትዮጵያ ባህልና ወግ ባፈነገጠ መልኩ ማህበራዊ ሚዲያን በመጠቀም ተጠርጥረው ታሰሩ የአዲስ አበባ ፖሊስ እንደገለፀው ከሆነ በቲክቶክ ስሙ Lil_jay ወይም ጎይጋር ኮት ውይዋል እና ከእርሱ ጋር የቲክቶክ አካውንት በመጠቀም አፀያፊ ድርጊት ስትፈጽም ነበረችው ያላትን ኸሊሌ ጊቦ አያና የተባሉ ዛሬ ታህሳስ 02 ቀን 2018 ዓ/ም በለሚ ኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 9 ልዩ ቦታው ፍሊንትስቶን ሆምስ ከሚባል ቦታ በቁጥጥር ስር ውለዋል ብሏል። በተመሳሳይ ነገር በመጠርጠር በቲክቶክ ስሙ ፕሬዚዳንት ማሜ ወይም ባህሩዲን ሙሰማን ዛሬ በቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 1 ልዩ ቦታው ቦሌ ሚካኤል ጃፋር መስጅድ አካባቢ በቁጥጥር ስር ውሏል ሲል ፖሊስ ገልፇል።

ጊፋታ‼️ የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ፡፡
ጊፋታ‼️ የወላይታ የዘመን መለወጫ በዓል "ጊፋታ" በተባበሩት መንግሥታት የትምህርት፣ የሳይንስና የባሕል ድርጅት (ዩኔስኮ) በዓለም ቅርስነት ተመዘገበ፡፡

breaking‼️ ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ሰኞ ግንቦት 24 ፣ 2018 እንዲሆን ጸደቀ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኞ ግንቦት 24፤ 2018 ሆኖ መጽደቁን
breaking‼️ ቀጣዩ ሀገራዊ ምርጫ ሰኞ ግንቦት 24 ፣ 2018 እንዲሆን ጸደቀ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ሰባተኛው ሀገራዊ ምርጫ የድምጽ መስጫ ቀን ሰኞ ግንቦት 24፤ 2018 ሆኖ መጽደቁን አስታወቀ። ቦርዱ ዛሬ ለመገናኛ ብዙሃን ይፋ ባደረገው የጸደቀ የምርጫ የጊዜ ሰሌዳ፤ የምርጫ ውጤት በቦርዱ ደረጃ ይፋ የሚደረገው ሰኔ 4 ቀን እንደሆነ ገልጿል። Via ኢትዮጵያ ኢንሳይደር

ተያዙ‼️ ከባህልና ስነ-ምግባር ያፈነገጠ አለባበስ ተያዙ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቅርቡ በ3ኛው የG-Power TikTok Creative Award ላይ በሕዝብ ፊትና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ላይ ከ
ተያዙ‼️ ከባህልና ስነ-ምግባር ያፈነገጠ አለባበስ ተያዙ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ በቅርቡ በ3ኛው የG-Power TikTok Creative Award ላይ በሕዝብ ፊትና በቴሌቪዥን ቀጥታ ስርጭት ላይ ከሀገሪቱ ባህልና መልካም ስነ-ምግባር ያፈነገጠ፣ ሰውነትን የገለጠ አስነዋሪ አለባበስ ለብሰው የታዩ ተጠርጣሪዎች ላይ ምርመራ መጀመሩን አስታውቋል። ፖሊስ ክስተቱ ከሕዝብ ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞን ማስተናገዱን ተከትሎ፣ ወዲያውኑ በክሱ የተጠረጠሩ ግለሰቦችን ከዝግጅቱ አቀናባሪዎችና ስፖንሰሮች ጋር በቁጥጥር ስር አውሏል። በተለይ ምርመራ የተጀመረባቸው ተጠርጣሪዎች፡- * ወንጌላዊት ገብረ እንድርያስ በርሄ * በርከት ፀጋዬ ጅፋር * መቅድም ደረጄ መንግስቱ * ግሩም ገዛሀኝ ቀጭኔ * ዮሃንስ መኮንን ሀ/ማርየም የፌደራል ፖሊስ ባወጣው መግለጫ፣ ከሕብረተሰቡ ባህልና እሴት ያፈነገጡ አለባበሶች እና መጤ ባህሎች ተስፋፍተው በትውልዱ ላይ አሉታዊ ተፅእኖ እንዳይፈጥሩ የሕግ ተጠያቂነትን ለማረጋገጥ ምርመራውን አጠናክሮ እንደሚቀጥል አሳስቧል። Via የፌደራል ፖሊስ

አሳዛኝ ዜና‼️ በርካቶቻቹ የምታውቁት ተወዳጁ ኮሜዲያን ወንደሠን አውራሪስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል። ለብዙ ዓመታት በሳቅ ሲያስቀን የኖረው ወንደሠን፣ በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት ሕይ
አሳዛኝ ዜና‼️ በርካቶቻቹ የምታውቁት ተወዳጁ ኮሜዲያን ወንደሠን አውራሪስ ከዚህ ዓለም በሞት መለየቱ ተሰምቷል። ለብዙ ዓመታት በሳቅ ሲያስቀን የኖረው ወንደሠን፣ በድንገተኛ የልብ ህመም ምክንያት ሕይወቱ ማለፉን ተሰምቷል። ለወንድማችን ነፍስ ይማር ለቤተሰቦቹ፣ ለጓደኞቹ፣ ለአድናቂዎቹ እና ለመላው ኢትዮጵያውያን በሙሉ መፅናናትን እንመኛለን።

የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአሸናፊዎች ዝርዝር 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ አነቃቂ አዶናይ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የህክምና ይዘት ተሸላሚ ዶክተር ዐቢይ ታደሰ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የላይቭ ስትሪመር ተሸላሚ ናሆም ፎንቲ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የማህበራዊ ኃላፊነት በመወጣት ተሸላሚ ዶክተር አብይ ታደሰ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የኢንፎርማቲቭ አሸናፊ ብሩክ ኒውስ (ብሩክ ጫላ) 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ ተስፋ የተጣለበት ቲክቶከር ባምሌ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ዳንሰኛ ተሸላሚ ዳዊት ታዬ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ የጉዞ ተሸላሚ ሰያ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ላይፍ ስታየል አሸናፊ አዶናይ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ የ STEM አሸናፊ መምህር ዳኒ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ የጭላሎ ቻሌንጅ አሸናፊ በረከት ታደሰ (ቤኪ 4kilo) 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የG-Power ቻሌንጅ አሸናፊ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ሴት ኮሜዲ ተሸላሚ ንጹ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ወንድ ኮሜዲ ዶሚኔት ኑሪ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ አጭር ፊልም አሸናፊ ቤንጂ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ሪቪው ይዘት ተሸላሚ ጃኒ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የስማይል ቻሌንጅ አሸናፊ ዩቲ ናስ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ ምርጥ ሚመር ተሸላሚ ፓትሮን 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ Life Time አሸናፊ ዩቲ ናስ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የስፖርት መረጃ ይዘት አሸናፊ አቢ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ ምርጥ አለባበስ በሴት አሸናፊ ዩቲ ናስ 📌የ2025 የቲክቶክ ክሬቲቭ አዋርድ የአመቱ ምርጥ ቲክቶከር አሸናፊ አዶናይ

መረጃ‼️ ዛሬ በማርበግር ቫይረስ የ2 ሰዎች ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደረገ። ህዳር 17, 2018 የማርበርግ ቫይረስ ወቅታዊ ሪፖርት በማርበርግ ቫይረስ ዙሪያ ያለው ሁኔታ በየዕለቱ እየተዘገበ ይገኛል።
+1
መረጃ‼️ ዛሬ በማርበግር ቫይረስ የ2 ሰዎች ህይወት ማለፉ ሪፖርት ተደረገ። ህዳር 17, 2018 የማርበርግ ቫይረስ ወቅታዊ ሪፖርት በማርበርግ ቫይረስ ዙሪያ ያለው ሁኔታ በየዕለቱ እየተዘገበ ይገኛል። የዛሬው ዘገባ የሚያሳየው መረጃ በሚከተለው ቅርጸት ቀርቧል፦ የዕለቱ መረጃዎች (ዛሬ የተመዘገበ) * የተደረገ የላብራቶሪ ምርመራ: 7 * ቫይረሱ የተገኘባቸው አዳዲስ ሰዎች: 2 * የሟቾች ቁጥር (ዛሬ): 2 ሰዎች አጠቃላይ የቫይረሱ ስርጭት (ከመጀመሪያው ጀምሮ) * በቫይረሱ የተያዙ ሰዎች ጠቅላላ ቁጥር: 12 ደርሷል * ህይወታቸው ያለፈ ሰዎች ጠቅላላ ቁጥር: 7 ደርሷል ማሳሰቢያ: ህብረተሰቡ ጥንቃቄውን እንዲያጠናክር እና ከጤና ባለሙያዎች የሚሰጡ መመሪያዎችን እንዲከተል ይመከራል። ምንጭ: MOH - Ethiopia

ዛሬ ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን ነው ​ይህ ቀን አስፈላጊ የሆነባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ። ቀኑ የወንዶችን መብቶች፣ የጤና እንክብካቤ እና የአዕምሮ ጤና ግንዛቤ ለመፍጠር በዓለም ዙሪያ ባሉ ብዙ አገሮ
ዛሬ ዓለም አቀፍ የወንዶች ቀን ነው ​ይህ ቀን አስፈላጊ የሆነባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ። ቀኑ የወንዶችን መብቶች፣ የጤና እንክብካቤ እና የአዕምሮ ጤና ግንዛቤ ለመፍጠር በዓለም ዙሪያ ባሉ ብዙ አገሮች ይከበራል። ​