445
مشترکین
+124 ساعت
-17 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የ2019 በጀት ዓመት የደረጃ "ለ" ግብር ከፋዮች ዓመታዊ ግብር የመክፈያ ጊዜ ዛሬ በይፋ መጀመሩ ተገለፀ።
።።።።።።።።።።።።።።።
ሀምሌ 1/2018 ዓ.ም
በዚህ የማስጀመሪያ መርሀ--ግብር ላይ የክፍለከተማው ዋና ስራ አስፈጻሚ ዶክተር ምስክር ነጋሽ ተገኝተው መልእክት አስተላልፈዋል ዋና ስራ አስፈፃሚው በመልእክታቸውም የኢትዮጵያ ጀርባ አጥንት የሆናችሁ የግብር ከፋዮቻችን ለእናንተ የከተማ አስተዳደራችን ብሎም መንግስታችን ትልቅ ክብር አለው ካሉ በኋላ አንድ ሀገር የምትለማው በራሷ ዜጎች በሚከፈል ታክስ ነው ብለዋል፡፡
በተለይ በጣም ያደጉ ሀገሮች አሁን አደጉ ተመነጠቁ የምንለው ፍትሃዊ በሆነ መንገድ በተለይ ከዝቅተኛ ጀምሮ እስከ ከፍተኛው ግብር ከፉይ ድረስ በሚገብሩት ግብር ወይም ታክስ ነው ብለዋል በመልእክታቸው አስገንዝበዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለው የሌሎች ሀገሮች ግብር ከፋዮች ተሞክሮን ሲያነሱም ግብር ከፋዩ ለሚያስመዘግበው እድገት ከሚጠበቅበት በላይ ድጋፍ ያደርጋል ብለዋል፡፡ አዲስ አበባ ከዛሬ ስምንት አመት እና አሁን አነፃፅረን ብናይ በአይን የሚታይ በእጅ የሚዳሰሰኡ በርካታ ማህበራዊና ኢኮኖሚ ስራዎች እንዲሁም ሰው ተኮር ስራዎች የተሰሩበት ነው ያንን ደግሞ አለም ያረገጋገጠውና የመሰከረው እንደተሞክሮም የወሰደው ጉዳይ ነው ካሉም በኋላ ለዛ ደግሞ ምክንያቱ ግብር ከፋዩ የራሱ ድርሻ ሰላለው ነው ብለዋል፡፡
በመሰረተ ልማት በኮሪደር ልማት በወንዝ ዳርቻ ልማት በጣም ብዙ የሆኑ ከንጽህና እና ከፅዳት ጀምሮ ብዙ ስራዎች ተሰርተዋል። ይሄ በተከበረው በግብር ከፋያችን ጭምር የመጣ ለውጥ ነውም ብለዋል፡፡
ከዛሬ ስምንት አመት በፊት የአዲስ አበባ አጠቃላይ የገቢ እቅዷ 40 ቢሊየን ብር ያልበለጠ ነበረ ያሉት ዶክተር ምስክር ባለፈው አመት ብቻ ከ350 ቢሊየን ብር በላይ እቅድ ተይዞ በሰፊው የተከናወነ ሲሆን ይሄም የግብር ከፋዩ ሀገር ወዳድነት ያመጣው ስኬት ነው ብለዋል፡፡
ህብረተሰቡም የሚጠቀምበት አለም አቀፍ ደረጃውን የጠበቀ ሆስፒታል፣ ጤና ጣቢያ፣ የንፁህ መጠጥ ውሃ፣ መንገድ ማልማት የመሳሰሉት መገንባት የተቻለው በግብር ከፋዮቻቸእን የላቀ ተሳትፎ ነው ብለዋል፡፡ አዲስ አበባ የሀገራችን መዲና ብቻ ሳትሆን የአፍሪካ መዲና፣ ከኒውዮርክ እና ከጄኔቫም ቀጥላ ሶስተኛዋ የዲፕሎማቲክ መቀመጫ ከተማ ናት። ከዚህ አንጻር ግብር ለሰው ልጅ መብትና ግዴታም ነው። የመንግስት ሰራተኛውም፣ ነጋዴውም፣ በግል ተቋማት የተሰማራ ሁሉ መገበር አለበት።
ግብር ከፉዩ ሲገብር ፍትሃዊ በሆነ መንገድ ማህበረሰቡ ለሚጠቀምበት ለልማት ነው የሚገብረው፤ ሲገብር የመልካም አስተዳደር ችግሮችን ለመፍታት ነው የሚገብረው ያሉት ዋና ስራ አስፈፃሚው ከዚህ አንጻር "ግብር ለሀገር ክብር" በሚል ከአሁን በፊትም በክብርት ከንቲባችን በሚመራ ሰፊ ንቅናቄ አድርገን የግብር ከፋዩን መብትና ግዴታ እያሳወቅን በርካታ አኩሪ ተግባራት ተከናውኗል።
እናንተም ደግሞ ለሌሎች ግንባር ቀደም ሆናችሁ እናንተ ከፍላችሁ ሌላው እንዲከፍል በማነሳሳት በጣም አኩሪ ተግባር ሰርታችኋል ለዛም አክብሮታችን ከፍ ያለ ነው ብለዋል ፡፡
ህብረተሰቡ ይህንን አዲስና ዘመናዊ አሰራር በመገንዘብ ያለ ምንም እንግልት ባሉበት ቦታ ሆነው ግዴታቸውን እንዲወጡ ተቋሙ ጥሪ አቅርቧል።
ግብር የሚከፍለው ህብረተሰቡ ለራሱ ልማት ለራሱ ኑሮ መሻሻል መሆኑን በማወቅ በወቅቱ ግብርን መክፍል መቻል ይገባል ብለዋል ዋና ስራ አስፈፃሚው መልክታቸውን ባጠቃለሉበት ንግግራቸው፡፡
የግብር አሰባሰብ ስርዓቱን ሙሉ በሙሉ ዲጂታልና አውቶሜትድ (Automated) የሚያደረግ ‘ኢ-ታክስ’ (e-Tax) የተሰኘ አዲስ ሲስተም ወደ ስራ ተገብቷል።
ከዚህ ቀደም የነበረው በእጅ የሚሰራ (Manual) አሰራር ሙሉ በሙሉ በመቀየሩ ምክንያት ግብር ከፋዮች በየቢሮው በአካል በመገኘት በድንኳንና በረጅም ሰልፍ ውስጥ ማሳለፍ የሚገደዱበት አሰራር ማክተሙ ተነግሯል።
አዲሱ የኢ-ታክስ (e-Tax) ሲስተም የተለያዩ ተቋማትን መረጃዎች እርስ በርስ ያገናኘ በመሆኑ ግብር ከፋዮች ወደ ግብር አስገቢው መስሪያ ቤት መምጣት እንደማይጠበቅባቸውም ተገልጿል።
ተቋሙ የግብር ከፋዮችን መረጃ አስቀድሞ አጥርቶና አገናኝቶ ያጠናቀቀ በመሆኑ እያንዳንዱ ግብር ከፋይ የተመደበበት የግብር መጠንና የመክፈያ ማዘዣ ቁጥር በ775 አጭር የፅሁፍ መልዕክት (SMS) በቀጥታ በእጅ ስልኩ ላይ እንደሚደርሰውም ተገልጿል።
ግብር ከፋዩ ማስታወቂያው እንደደረሰው ባለበት ቦታ ሆኖ በኦንላይን ባንክ አማራጮች ክፍያውን መፈጸም እንደሚቻል ገልፀው የደረጃ ‘ለ’ ግብር ከፋዮች ከዛሬ ጀምሮ እስከ ሐምሌ 30 /2018 ዓ.ም ድረስ የአንድ ወር የጊዜ ገደብ ተሰጥቷቸዋልም ተብሏል።
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ወረዳ 10 የሌማት ትሩፋት ንቅናቄ ላይ ለ60 ተጠቃሚዎች የዶሮ እርባታ ግብዓቶች ተላለፈ
።።።።።።።።።።።
ሰኔ 30/2018
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የወረዳ 10 የህብረተሰቡን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥና ኑሮን ለማቃለል ያለመውን ሀገራዊ የሌማት ትሩፋት ንቅናቄ በስፋት እየተሰራ ይገኛል። ወረዳዉ በ5ኛው ዓመት በመጀመሪያው 90 ቀን ውስጥ ለ3ኛ ጊዜ ያዘጋጀውን የከተማ ግብርና ግብዓቶች ድጋፍ ዛሬ ለተጠቃሚዎች አስረክቧል።
በዚሁ የድጋፍ መርሃ-ግብር ለ60 ተጠቃሚዎች ምቹ እና ዘመናዊ የሆኑ ባለ 5 የብረት ኬጂዎች (የዶሮ ማሳደጊያ ቤቶች) 300 ቦባንስ ብራውንስ (Bovans Browns) የተባሉ፣ ከፍተኛ ምርት የሚሰጡ የ3 ወር እንቁላል ጣይ ቄብ ዶሮዎች፣60 ኩንታል የተመጣጠነ የዶሮ መኖ እና አስፈላጊ የዶሮ መድኃኒቶች በሙሉ ጥቅል ለነዋሪዎቹ ተላልፈዋል።
ይህ ድጋፍ የከተማ ግብርናን በየቤቱ በማስፋፋት የዶሮና እንቁላል ምርትን ለመጨመር፣ የኑሮ ውድነትን ለማቃለል እና ለሴቶችና ወጣቶች የስራ ዕድል ለመፍጠር ትልቅ አቅም እንደሚሆን ተገልጿል።
ተጠቃሚዎችም በተደረገላቸው ድጋፍ መደሰታቸውን ገልጸው፣ የተሰጣቸውን ግብዓት በአግባቡ በመንከባከብ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ቃል ገብተዋል።
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ ብር የሚያወጡ የአካል ድጋፍ ተበረከተ።
***
ሰኔ 24/2018 ዓ.ም
በዚህ ድጋፍ ከ30 በላይ ህፃናትና አረጋውያን ተጠቃሚ መሆናቸው ተገልጿል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት የአካል ጉዳት ያለባቸውን ወገኖች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ከከተማ አስተዳደሩና ከተለያዩ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ጋር በመቀናጀት ከአንድ ሚሊዮን ብር በላይ የሚያወጣ የዊልቸር ድጋፍ መደረጉን ገልጿል።
ፅህፈት ቤቱ በአዋጅ ከተቋቋመበት ዋና ዋና ተልዕኮዎች መካከል በክፍለ ከተማው የሚገኙ የአካል ጉዳተኞችን ማህበራዊ እና ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮቻቸውን በአግባቡ እንዲወጡ ሁኔታዎችን ማመቻቸት አንዱ በመሆኑ ይህንን ታሳቢ በማድረግ በበጀት ዓመቱ የተለያዩ መርሃ-ግብሮችን ቀርጾ ሲንቀሳቀስ መቆየቱ ተገልጿል።
በከተማ አስተዳደሩ በኩል የተሰጡትን 10 ዊልቸሮች ጨምሮ ፅህፈት ቤቱ በራሱ ጥረት ከተለያዩ የሀገር ውስጥና ዓለም አቀፍ ግብረ-ሰናይ ድርጅቶች ጋር ግንኙነት በመፍጠር ለ26 የአካል ድጋፍ ለሚያስፈልጋቸው ህፃናትና አረጋውያን የዊልቸር ድጋፍ ማድረጉ ታውቋል።
በድጋፍ አሰጣጥ ስነ-ስርዓቱ ላይ የክፍለ ከተማው ሴቶች ህፃናትና ማህበራዊ ጉዳይ ፅህፈት ቤት የስራ ኃላፊዎች፣ ድጋፉን በቀጥታ በማስተባበር ረገድ ከክፍለ ከተማው ጋር በቅንጅት የሰራው የሃንድ ኢን ሃንድ (Hand in Hand) ግብረ ሰናይ ድርጅት ኃላፊ እንዲሁም ድጋፉን ያበረከተው የአጋፔ ሞቢሊቲ ኢትዮጵያ (Agape Mobility Ethiopia) ድርጅት ኃላፊ ተገኝተዋል።
ከተበረከቱት ዊልቸሮች መካከል ለአካላቸው ተስማሚ መሆኑን ለማረጋገጥና የቅድመ ምርመራ ስራዎችን ለማገዝ የቢዜር (Be There) የተባለ የአሜሪካ ሲኤስኦ (CSO) ልዑካን ቡድን በቦታው በመገኘት ሙያዊ ድጋፍ ማድረጉም ተመልክቷል።
ፅህፈት ቤቱ ለተደረገው ሰብዓዊ ድጋፍ ምስጋና ያቀረበ ሲሆን የተጀመረው ማህበረሰብን የማገልገልና የመደገፍ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አስታውቋል።
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በተለያዩ ተቋማት በሚሰጠው የአገልግሎት አሰጣጥ መሻሻል የተሰማቸውን ደስታ ነዋሪዎች ገለጹ፡፡
****
ሰኔ 24/2018 ዓ.ም
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የህዝብን የእለት ተእለት እንግልት ለመቀነስ እና ተገልጋይን ያማከለ ቀልጣፋ አሰራርን ለማስፈን የጀመረውን ጥረት አጠናክሮ ቀጥሏል። ከዚሁ ጋር ተያይዞ በዛሬው ዕለት በክፍለ ከተማው ስር በሚገኙ የተለያዩ የአገልግሎት ሰጪ ተቋማት ይህንን እየተገበሩ ይገኛሉ፡፡
በዕለቱ በክፍለ ከተማ ደረጃ የሚገኙ ቁልፍ የህዝብ መስተናገጃ ጽህፈት ቤቶች እና በርካታ ተቋማት በሙሉ አቅማቸውና በተለየ ዝግጅት ለህብረተሰቡ ፈጣን አገልግሎት ሲሰጡ ውለዋል። የቢሮክራሲ ማነቆዎችን በማቃለል እና ፋይሎችን በአጭር ጊዜ ውስጥ ምላሽ በመስጠት ረገድ በዛሬው ዕለት የተከናወኑት ስራዎች ውጤታማ እንደነበሩም ተገልጿል።
በተለያዩ ተቋማት ተገኝተው የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑ የክፍለ ከተማው ነዋሪዎች እንደገለጹት ቀደም ሲል ይስተዋሉ የነበሩ መስተጓጎሎችና መጉላላቶች ተቀርፈው ዛሬ ያገኙት መስተንግዶ እጅግ ቀልጣፋ፣ ግልጽነትና ሰብዓዊነት የተሞላበት እንደነበር መስክረዋል።
ህብረተሰቡ በአገልግሎት አሰጣጡ ላይ የታየውን ይህንን በጎ ለውጥ በከፍተኛ ሁኔታ እንደሚያደንቅና በዚህ የተነሳ የተሰማውን ጥልቅ ደስታ ገልጿል።
የክፍለ ከተማው አስተዳደር የስራ ኃላፊዎች በበኩላቸው ይህ የአገልግሎት አሰጣጥ ቀን የአንድ ጊዜ ተግባር ብቻ ሳይሆን ተቋማቱ በየእለቱ ለህዝብ የሚሰጡትን ምላሽ የመገምገሚያና የማሻሻያ ስልት መሆኑን አብራርተዋል።
በቀጣይም ህዝብን በታማኝነትና በቅንነት ማገልገል የመንግስት ሰራተኛው ዋነኛ መገለጫ እንዲሆን በትኩረት እንደሚሰራ ኃላፊዎቹ አረጋግጠዋል።
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎት ማስጀመሪያ ታሳቢ ያደረገ በነጻ የሕክምናና ደም ልገሳ መርሃ-ግብር ተከናወነ።
****
ሰኔ 24/2018 ዓ.ም
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር ጤና ጽሕፈት ቤት እና የበጎ ፈቃድ ማስተባበሪያ ጽሕፈት ቤት በጋራ በመሆን ያዘጋጁት የክረምት በጎ ፈቃድ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር በዛሬው ዕለት በይፋ ተጀምሯል።
ይህ በሁለቱ ተቋማት አጋርነት የተሰናዳው መርሃ- ግብር የክረምቱን የበጎ ፈቃድ አገልግሎት በይፋ ለመክፈትና ማህበረሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ የጤና ሥራዎችን ጨምሮ ለማከናወን ያለመ መሆኑ ተገልጿል።
በዕለቱ በተከናወነው በዚህ ማስጀመሪያ መርሃ-ግብር ላይ ከስዊዝ ዲያግኖስቲክ ሴንተር ጋር የጋራ አጋርነት በመፍጠር ለነዋሪዎች ሰፊ የነጻ ሕክምናና ምርመራ አገልግሎት ተሰጥቷል።
በዚህ በተካሄደው የምርመራና ነፃ የህክምና አገልግሎትም የክፍለከተማው ነዋሪዎች የመንግስት ሰራተኞች ምርመራውና ነፃ ህክምናው በሚደረግበት ስፍራ ልዩ ልዩ የማህበረሰብ ክፍሎች የስኳር በሽታ ምርመራ፣ የጠቅላላ ደም ምርመራ እንዲሁም ሌሎች የነጻ ሕክምና ዕድሎችን ማግኘት ችለዋል።
ከነጻ ሕክምና አገልግሎቱ ጎን ለጎንም የብዙሃንን ሕይወት ለመታደግ ያለመ የደም ልገሳ መርሃ ግብር በስፋት የተካሄደ ሲሆን የክፍለ ከተማው አመራሮች፣ የበጎ ፈቃደኛ ወጣቶችና የአካባቢው ነዋሪዎች በነቂስ በመውጣት ደም በመለገስ አጋርነታቸውን አሳይተዋል።
የአዘጋጅ መሥሪያ ቤቶቹ የሥራ ኃላፊዎች እንደተናገሩት ከስዊዝ ዲያግኖስቲክ ሴንተር ጋር የተደረገው ይህ ቅንጅት የማህበረሰቡን የጤና ችግር ከመቅረፍ ባለፈ በክፍለ ከተማው የበጎ ፈቃድ ባህልን ለማሳደግ ከፍተኛ ሚና እንዳለው ገልጸው መሰል የደግነት ሥራዎች በክረምቱ ወራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ አረጋግጠዋል።
445
ማስታወቂያ
**
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት በአዋጅ ቁጥር 721/2004 እና ይህንን ለማስፈጸም በወጣው ደንብ ቁጥር 162/2016 መሠረት የሚከተሉትን ተግባራት የማከናወን ኃላፊነት ያለበት ተቋም መሆኑ ይታወቃል፡-
• ዓመታዊና ውዝፍ የሊዝ ዕዳ፡ የመክፈል ግዴታቸውን በማይወጡ የሊዝ ባለይዞታዎች ላይ ከማስጠንቀቂያ ጀምሮ በፍታሐብሔር ሕግ እስከ መጠየቅ፤
• ያለፈቃድ አገልግሎት መቀየር፡ በውል ከተሰጣቸው የይዞታ መጠቀሚያ አገልግሎት ውጭ፣ ያለ ጽሕፈት ቤቱ ዕውቅና አገልግሎት ቀይረው በሚጠቀሙ የሊዝ ባለይዞታዎች ላይ አስተዳደራዊ የቅጣት እርምጃ መውሰድ፤
• የግንባታ ጊዜ ገደብና ሕጋዊነት፡ ቦታ በምደባም ሆነ በጨረታ ወስደው በውል በተቀመጠላቸው ጊዜ ገደብ ግንባታ በማይጀምሩና በጊዜው በማያጠናቅቁ፣ ወይም ውል ሳያሻሽሉ ግንባታ በሚጀምሩ/በሚያጠናቅቁ ባለይዞታዎች ላይ ግንባታ ከማስቆም ጀምሮ ቦታ እስከ መንጠቅ የሚደርስ እርምጃ መውሰድ፤
• የስም ዝውውር (ካርታ ማዞር)፡ ከሪል እስቴት ወይም ከግለሰቦች ቦታ/ቤት ገዝተው በጽሕፈት ቤቱ ቀርበው ስም ያላዞሩ ግለሰቦችና ድርጅቶች ላይ፣ ወቅታዊ በሚደረግ የሊዝ ክፍያና የንብረት ዋጋ ተመን መሠረት ተጨማሪ ዋጋ ማስከፈል፤
• ሕገ-ወጥ ማስፋፊያ፡ ካላቸው ሕጋዊ ይዞታ ውጭ ሕገ-ወጥ በሆነ መንገድ አስፋፍተው የሚጠቀሙና በተቀመጠው አሠራር መሠረት ሕጋዊ የማያደርጉ ባለይዞታዎች ላይ፣ የመንግሥትን ይዞታ በሕገ-ወጥ መንገድ በመያዝ ወንጀል ከመጠየቅ ጀምሮ የመንጠቅ አስተዳደራዊ እርምጃ መውሰድ።
በመሆኑም ከላይ በተገለጹት ዝርዝር ጉዳዮች ላይ የሚጠበቅባችሁን ግዴታና ኃላፊነት ሕጋዊ በሆነ መንገድ ለተወጣችሁና ሕጋዊ መስመር ለምትከተሉ የክፍለ ከተማችን የሊዝ ባለይዞታዎች በሙሉ ልባዊ ምስጋናችንን እያቀረብን፤
እስካሁን ይህንን ግዴታችሁን ያልተወጣችሁ ባለይዞታዎች ግን ከሰኔ 17/2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ሰኔ 30/2018 ዓ.ም ድረስ (ቅዳሜን ጨምሮ) ባሉት ተከታታይ የሥራ ቀናት ውስጥ ቀርባችሁ ኃላፊነታችሁን እንድትወጡና ወደ ሕጋዊ አሠራር እንድትገቡ በጥብቅ እናሳስባለን።
የመቀበያ ቦታ፦ ባንቢስ አካባቢ፣ እሬቻ ፓርክ ፊት ለፊት፣ ማሪዎት ሆቴል አጠገብ በሚገኘው የክፍለ ከተማው አስተዳደር ሕንፃ ምድር ቤት (የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽሕፈት ቤት)።
«ንቁ ዜጋ በመሆን ግዴታችንን እንወጣ!!!»
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ መሬት ልማት እና አስተዳደር ቅርንጫፍ ጽ/ቤት
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ “ደረቅ ቆሻሻ የሀብት ምንጭ እንጂ የጎርፍ አደጋ ስጋት መሆን የለበትም” በሚል መሪ ቃል የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ፡፡
********
ሰኔ 16/2018 ዓ.ም
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ አስተዳደር “ደረቅ ቆሻሻ የሀብት ምንጭ እንጂ የጎርፍ አደጋ ስጋት መሆን የለበትም” በሚል መሪ ቃል ሰፊ ህዝባዊ ተሳትፎ የተደረገበት የተቀናጀ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል።
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ዋና ስራ አስፈፃሚ ዶክተር ምስክር በዘመቻው ወቅት ባደረጉት ንግግር ፅዳትና ውበት የሁሉም ነዋሪዎች የጋራ ኃላፊነት መሆኑን ገልፀው አካባቢን ከጎርፍ አደጋ ለመጠበቅና ጤናማ መኖሪያ ለመፍጠር ህብረተሰቡ በየደረጃው በሚዘጋጁ የፅዳት መርሃ-ግብሮች ላይ በቀጣይነትና በባለቤትነት ስሜት እንዲሳተፍ ጥሪ አቅርበዋል።
ዋና ስራ አስፈፃሚው አክለውም ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ በመለየትና በስርዓት በመሰብሰብ ወደ ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ወይም ወደ ሀብትነት መቀየር እንደሚቻል አስገንዝበዋል።
በየመንገዱና በውሃ ማፋሰሻዎች ውስጥ የሚጣል ቆሻሻ ለጎርፍ አደጋ መንስኤ ከመሆኑም በላይ የከተማዋን ገፅታ የሚያበላሽ በመሆኑ እያንዳንዱ ዜጋ ይህንን ድርጊት በጋራ ሊከላከልና ሊያወግዝ እንደሚገባ ዶክተር ምስክር አሳስበዋል።
በዚህ በቂርቆስ ክፍለ ከተማ በተከናወነው ዘመቻ በዋና ዋና መንገዶች፣ በየጎዳናዎቹ፣ በውሃ ማፋሰሻ ቦዮች እና በህዝብ መገልገያ ስፍራዎች ላይ ተከማችተው የነበሩ በርካታ ደረቅ ቆሻሻዎች የተነሱ ሲሆን ለአካባቢው ነዋሪዎችም ዘላቂ የንፅህና አጠባበቅን የተመለከቱ የግንዛቤ ማስጨበጫ ትምህርቶች ተሰጥተዋል።
ይህ የተካሄደው መጠነ ሰፊ ንቅናቄ ክፍለ ከተማዋን ከክረምት ወራት የጎርፍ አደጋ አስቀድሞ ለመጠበቅ፣ የአካባቢ ፅዳትን ለማሻሻል እና ደረቅ ቆሻሻን በአግባቡ ጥቅም ላይ የማዋል ባህልን በህብረተሰቡ ዘንድ ለማስረፅ ከፍተኛ አስተዋፅኦ እንደሚኖረው ታምኖበታል
445
መንግስት እየዘረጋው ያለው በቴክኖሎጂ የታገዘ ዘመናዊ አሰራር እና ለአገልግሎት አሰጣጡ ምቹ የሆኑ መሰረተ ልማት የተሟላላቸው ተቋማት የመልካም አስተዳደር ችግር መንስኤ የነበሩ የአሰራር ችግሮች በመቅረፉ ረገድ ከፍተኛ ሚና እየተጫወቱ እንደሚገኙ ተገለጸ፡፡
*************
ሰኔ 12/2018 ዓ.ም
የቂርቆስ ክፍለ ከተማ ምክር ቤት አባላት በክፍለ ከተማው አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ጉብኝት አደረጉ፡፡
በጉብኝታቸውም ተቋሙ ያካተታቸው የተገልጋዩን እንግልት እና ወጪ ያስቀሩ ዘመናዊ አሰራሮች እንዲሁም ለአገልጋዩና ተገልጋዩ ምቹ ተደርገው የተሰሩ ክፍሎች እና ተቋሙ ያካተተው መሰረተ ልማትን ተዘዋውረው ተመልክቷል፡፡
በተበታተነ መልኩ ሲሰጡ የነበሩ አገልግሎቶች በአንድ ማዕከል ተጠቃለው መገኘታቸው የተገልጋዩን ጊዜ፣ ወጪ እና መመላለስ የቀነሰ ሲሆን ከዚህ ጋር ተያይዞ የሚፈጠረው የመልካም አስተዳደር ችግር ሊፈታ የቻለ አሰራር መመልከታቸው የጉብኝቱ ተሳታፊዎች ገልጸዋል፡፡
ተቋሙ ያካተታቸው ቴክኖሎጂዎች የመረጃ አያያዙን በከፍተኛ ደረጃ አስተማማኝ ከማድረጉ ባሻገር የአገልግሎት አሰጣጡን በማቀላጠፍ የተቋሙ የጊዜ አጠቃቀም ውጤታማ እንዲሆን ማስቻሉና ለጽህፈት መሳሪያ ግብዓቶች የሚወጣው ከፍተኛ ወጪ በመቀነስ በሃገር ኢኮኖሚ ላይ ያለው አዎንታዊ አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑ መታዘባቸው የምክር ቤቱ አባላት ተናግሯል፡፡
ተቋሙ ከወረቀት እና ከክፍያ ንክኪ ነጻ መሆኑ ከግልጸኝነት ጋር ተያዠይዘው የሚነሱ ችግሮች እንደሚቀርፍ ሃሳብ የሰጡ ጎብኚዎች ዲጂታል የሆኑ የሃሳብ መስጫዎች የተገልጋዩን ገንቢ አስተያየት ለሚመለከተው አካል በማድረስ ለአገልግሎት አሰጣጡ መሻሻል የሚያበረክተው አስተዋጽኦ ከፍተኛ እንደሆነም ገልጸዋል፡፡
የአገልግሎት አሰጣጡ ለማሳለጥ የተቋማት መቹ ሆኖ መገንባት ያለው አበርክቶ ከፍተኛ መሆኑ በመግለጽ ተቋሙ በዚህ ረገድ ያለበት ደረጃ ከጠበቁት በላይ እንደሆነባቸው የምክር ቤቱ አባላት አስረድቷል፡፡
ተቋሙ የጎበኙ የምክር ቤቱ አባላት በተቋሙ ያደረጉት ጉብኝት ውጤታማ እንደነበረ ገልጸው አዲስ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት ስራ የጀመረው በቅርብ እነደመሆኑ ሌሎች ተመሳሳይ የሆኑ ጉብኝቶች እንዲደረጉና ለጉብኝቶች የሚድያ ሽፋን በመስጠት ማህበረሰቡ የዚህ ዘመናዊና ቀልጣፋ አሰራር ተጠቃሚ እንዲሆን የማስተዋወቅ ስራ በሰፊው ቢሰራ የሚል ሃሳብ ሰጥቷል፡፡
በጉብኝታቸው ወቅት ያገኘዋቸው ተገልጋዮች በማነጋገርም የአገልግሎት አሰጣጡ የተገልጋዩን እርካታ ማዓከል ያደረገ እንደሆነ መረዳታቸው የገለጹ ሲሆን ባገኙት አጋጣሚና መድረክ የአዲስ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ዘመናዊ አሰራር በማስተዋወቅ እንደሚጠቀሙበትም ተናግሯል፡፡
የጉብኝቱ ተሳታፊ የምክር ቤት አባላቱ በጉብኝታቸው መጨረሻ ወደዚህ ተቋም ያልተካተቱ ሌሎች አገልግሎቶች እንዲካተቱና ተቋሙ የማስተዋወቅ ስራ በሰፊው ቢሰራ የሚል ምክረ ሃሳብ ሰጥቷል፡፡
445
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና በሰላም መጠናቀቁን ተከትሎ ተማሪዎችና የፈተናው አስፈጻሚ አካላት ለችግኝ መትከያ የሚሆን የጉድጓድ ቁፋሮ መርሀ-ግብር ላይ መሳተፋቸው ተገለጸ፡፡
****************
ሰኔ 12/2018 ዓ.ም
በቂርቆስ ክፍለ ከተማ ስር በሚገኙ ሁሉም የፈተና ጣቢያዎች ሲሰጥ የነበረው የ8ኛ ክፍል ሚኒስትሪ ፈተና በሰላም መከናወኑንና መጠናቀቁን የክፍለ ከተማው ትምህርት ጽሕፈት ቤት አስታውቋል።
ፈተናው ፍጹም ሰላማዊ፣ ሂደቱን የጠበቀና ስኬታማ በሆነ መልኩ እንዲጠናቀቅ ከተማሪዎች፣ ከፈታኞች፣ ከወላጆችና ከጸጥታ አካላት ጋር የተቀናጀ ስራ መሰራቱ የተገለጸ ሲሆን ተማሪዎችም ያለምንም የጸጥታም ሆነ የቴክኒክ እክል ፈተናቸውን በራስ መተማመን ማጠናቀቃቸው ታውቋል።
የዘንድሮውን የፈተና ማጠናቀቂያ ልዩ የሚያደርገው ፈተናቸውን ያጠናቀቁ ተማሪዎች የመጨረሻውን የፈተና ወረቀት እንዳስረከቡ፥ ወዲያውኑ ወደ አረንጓዴ አሻራ መርሀ-ግብር በመሰማራት የችግኝ ጉድጓድ ቁፋሮ ማካሄዳቸው ነው። ይህም ተማሪዎቹ በቀጥታ ወደ አካባቢ ጥበቃና ልማት ስራ መሰማራታቸውን ያመላከተ ተግባር መሆኑ ተነግሯል።
"ትውልዱን በዕውቀትም በስነ-ምግባርም መገንባት" በሚል መሪ ቃል በተዘጋጀው በዚህ መርሀ-ግብር ላይ የ8ኛ ክፍል ተማሪዎች፣ ቺፎች፣ ሱፐርቫይዘሮች፣ ፈታኞች እንዲሁም የጸጥታ አካላት በጋራ በመሆን ተሳትፈዋል።
በትምህርት ቤቶች ቅጥር ግቢ ውስጥ ተማሪዎች ከክፍል ውስጥ ትምህርት ባሻገር በተግባራዊ የማህበረሰብ አገልግሎት ላይ ያላቸውን ከፍተኛ ተነሳሽነት ያሳዩበት መድረክ ሆኗል።
ከፈተና በኋላ የተደረገው ይህ የጉድጓድ ቁፋሮ መርሀ-ግብር ተማሪዎች ለተፈጥሮ ያላቸውን ፍቅር የሚያሳድግ ከመሆኑም በላይ በትምህርት ቤቶች አካባቢ አረንጓዴና ምቹ ሁኔታን የመፍጠር ትልቅ ዓላማ ያለው መሆኑ ተገልጿል።
