Mark Tech Info | Mark Technology Information
رفتن به کانال در Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
نمایش بیشتر6 218
مشترکین
-324 ساعت
-407 روز
-33730 روز
آرشیو پست ها
‼️እስከ ገና ድረስ ብቻ የሚቆይ አሪፍ ገንዘብ የምትሰሩበት AIRDROP ነው፣ ተጠቀሙበት 400,000 ዶላር ተዘጋጅቷል።
Check out this Christmas game on Telegram 🎄
If you join, we both get gifts! Then you can decide if you wanna keep playing or not :)
Here’s the link 👇👇👇
❗️ዲጂታል መታወቂያ እንድታወጡ
በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና የምትወስዱ ተማሪዎች የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ እንድታወጡ ይጠበቃል።
ማንኛውም ተማሪ የመልቀቂያ ፈተናውን ለመውሰድ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሊኖረው እንደሚገባ ትምህርት ሚኒስቴር መወሰኑ ይታወሳል።
በመሆኑም በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ የሆናችሁ ተማሪዎች በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ማውጫ ማዕከል በመመዝገብ መታወቂያውን ማውጣት ይኖርባችኋል።
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
‼️ከዚህ በኋላ ትምህርት ቤት ውስጥ
* Crazy Day
* Gentle Day
* Olds Day
* Valentine Day
* Color Day
* Pyjama Day
ማክበር አይቻልም
የትምህርት አዋኪ ድርጊቶችን የሚፈጽሙ ግለሰቦች እና ተቋማት እስከ 150,000 ብር የሚደርስ የገንዘብ ቅጣት እንደሚጠብቃቸው ተመላክቷል።
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
የተማሪዎች የሥነ ምግባር ረቂቅ መመሪያ በውስጡ ምን ምን አካቷል ?
➡️ " Crazy day ፣ olds day ፣ Valentine day " እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር ይከለክላል።
መመሪያው በመንግስት ፣ መንግስታዊ ባልሆኑ ፣ የግል ፣ በኃይማኖት ተቋማት የሚተዳደሩ ትምህርት ቤቶችና ከኢትዮጵያ ውጪ ባሉ ኮሚዩኒቲ ትምህርት ቤት በሚማሩ ተማሪዎች ላይ ተፈፃሚ ይሆናል።
በመመሪያው የተማሪዎች መብትና ግዴታዎች ሲቀመጡ በተማሪዎች ግዴታ ስር ፀጉርን በአግባቡ መሰራት/ማሳጠር፣ ከተፈጥሯዊ ጸጉራቸው ውጪ እንዳይጠቀሙ ተቀምጧል።
የሴቶቾ የትምህርት ቤት የደንብ ልብስ ቀሚስ ቁመት ከባት በታች መሆን ያለበት ሲሆን ከአካባቢው ባህል ጋር የማይቃረን ልብስ መልበስ የሚለውም ተካቷል።
በመመሪያው ከተከለከሉ ተግባራት መካከል ሲጋራ ማጨስ፣ አልኮል መጠጣት፣ ጫት መቃም፣ ዕፆችን መጠቀም/ማዘዋወር እንደዚሁም ሞባይልና የሙዚቃ ማዳመጫዎችን ወደ ትምህርት ቤት ይዞ መምጣት ይገኙበታል።
በትምህርት ቤት ግቢ ውስጥ ኃይማኖታዊ አምልኮ ስርዓትና የፖለቲካ እንቅስቃሴዎችን ማከናወንም በመመሪያው ተከልክሏል።
በመመሪያው ሀገራዊ እሴት ያልሆኑ መጤ ነገሮችን በሰውነት ላይ መነቀስ ሲከለከል፤ ሴት ተማሪዎች የጥፍር፣ የፀጉርና የከንፈር ቀለም ከመቀባትና ከመኳኳል እንደዚሁም አላስፈላጊ ጌጥ ከማድረግ ይከለክላል።
በተጨማሪም በረቂቁ በትምህርት ቤት ውስጥ አላስፈላጊ የሆኑ የኢትዮጵያዊነት ባህልን የማይገልፁ ያላቸውን ድርጊቶች ፦
• Crazy Day,
• Gentle Day,
• Olds Day,
• Baby Day,
• Fruit Day,
• Tomato Day,
• Valentine Day,
• April the full,
• Color Day,
• Pyjama Day…etc መፈጸም፤ እና ሌሎችም አላስፈላጊ የሆኑ ባህልን የማይገልፁ ድርጊቶችን ማክበር እንደማይቻል ተገልጿል።
የተከለከሉ ተግባራትን በሚፈፅመት ላይ የተለያያ የእርምት እርምጃዎች ሲቀመጡ ቀላል እርምጃ ሊያስወስዱ በሚችሉ ጥፋቶች ስር ከፀጉር ጋር የተያያዙ እና ሌሎች ቀላል ጥፋቶች ተካተዋል።
የትምህርት ቤት ፕላዝማና ኮምፒውተር ለሌላ አላማ መጠቀም፣ በአጥር መዝልና መሽሎክ፣ ከላይ የተጠቀሱ አላስፈላጊ ባህሎችን ማክበር፣ አሉታዊ ምልክቶችን መነቀስ፣ ድብድብ እንደዚሁም ኃይማኖታዊ ስርዓት መፈፀምና ፖለቲካዊ እንቅስቃሴ ማድረግ በከባድ ጥፋት ውስጥ ተካተዋል።
የቅጣት እርከኑ እንደ ተማሪዎች የትምህርት ደረጃና ጥፋቱ ሲለያይ ለከባድ የስነ ምግባር ግድፈት በመደበኛ ህግ መሰረት የህግ ተጠያቂነት ይኖራል።
መመሪያው የዲሲፕሊን ክስ አመሰራረት፣ የዲስፕሊን ኮሚቴ ስብጥር እንደዚሁም ተግባርና ኃላፊነትን በዝርዝር አስቀምጧል።
ከዚህ ባለፈ ፦
• ትምባሆ (ሲጋራ፣ ሺሻ)
• ጫት
• አልኮል
• የናርኮቲክ እና ሳይኮትሮፒክ ዝርያ ያላቸው አደገኛ ህገ ወጥ መድኃኒቶችና ሱስ አስያዥ ዕፆች በትምህርት ቤቶችና አካባቢ መገኘት፣ መጠቀም፣ መሸጥ፣ ማብቀል፣ ማምረት ወይም መለወጥ የተከለከለ እንደሆነ መመሪያው ላይ ተቀምጧል።
እንዲሁም ፦
• የአልኮል መሸጫና ማከፋፈያ ቤቶች
• የሲጋራ መሸጫ ሱቆች
• ሺሻ ቤቶች
• ጫት መሸጫና መቃሚያ ቤቶች
• ጭፈራ ቤቶች
• ቁማር ቤቶች
• የእንግዳ ማረፊያ ቤቶች
• የሰውነት መታሻ (ማሳጅ) ቤቶች
• የፊልም ማጫዎቻ ቤቶች
• ፕሌይ ስቴሽን ቤቶች
• ዲ.ኤስ.ቲቪ ቤቶች
• ከረንቡላ ፑል
• ጆተኒ
• ቢንጎ እና የስፖርት ቁማር መጫወቻ ቤቶችም እገዳ ተጥሎባቸዋል።
በተጨማሪም መመሪያው በየደረጃው ያሉ የባለድርሻ አካላትን ተግባርያ ኃላፊነትም ዘርዝሮ ሲያስቀምጥ ማንኛውም ትምህርት ቤት ያለ መሸኛ ተማሪዎችን ተቀብሎ መመዝገብንም ከልክሏል።
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
‼️የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ3ኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ በ2019 የትምህርት ዘመን ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
ለመምህራን የሚቀርበው ጥቅማጥቅምና ደመወዝ በቂ አለመሆን ለመምህራን እጥራት ምክንያት እንደሆነ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ይህም አዲስ መምህራንን በበቂ ሁኔታ ለማፍራት አስቸጋሪ እንዳረገው ገልፀዋል።
የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ግለሰቦች የአንድ ዓመት የማስተማር ዘዴ (Pedagogy) ኮርስ በመውሰድ ለመምህርነት ብቁ መሆን እንደሚችሉ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በዚህም የመምህራንን ቁጥር ለማሳደግ ይቻላል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ሲሰጡ፣ የበለጠ የመምህነነት ሙያ ፍቅር ሊያጎለብቱ እንደሚችሉም ገልፀዋል።
ባለፈው ዓመት ከቅድመ-መዋዕለ ህጻናት እስከ 12ኛ ክፍል በሀገሪቱ አጠቃላይ የመምህራን ቁጥር 625,000 የነበረ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት ቁጥሩን ወደ 700,000 ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል። #Fortune
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
‼️የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች የ3ኛ ዓመት ትምህርታቸውን ሲያጠናቅቁ ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት እንዲሰጡ የሚያስገድደው መመሪያ በ2019 የትምህርት ዘመን ተግባራዊ መሆን ይጀምራል።
ለመምህራን የሚቀርበው ጥቅማጥቅምና ደመወዝ በቂ አለመሆን ለመምህራን እጥራት ምክንያት እንደሆነ የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) ለምክር ቤት አባላት ተናግረዋል። ይህም አዲስ መምህራንን በበቂ ሁኔታ ለማፍራት አስቸጋሪ እንዳረገው ገልፀዋል።
የመጀመሪያ ዲግሪ ያላቸው ግለሰቦች የአንድ ዓመት የማስተማር ዘዴ (Pedagogy) ኮርስ በመውሰድ ለመምህርነት ብቁ መሆን እንደሚችሉ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል። በዚህም የመምህራንን ቁጥር ለማሳደግ ይቻላል ብለዋል።
የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ለአንድ ዓመት የማስተማር አገልግሎት ሲሰጡ፣ የበለጠ የመምህነነት ሙያ ፍቅር ሊያጎለብቱ እንደሚችሉም ገልፀዋል።
ባለፈው ዓመት ከቅድመ-መዋዕለ ህጻናት እስከ 12ኛ ክፍል በሀገሪቱ አጠቃላይ የመምህራን ቁጥር 625,000 የነበረ ሲሆን፤ በዚህ ዓመት ቁጥሩን ወደ 700,000 ለማሳደግ እየተሠራ መሆኑ ተገልጿል። #Fortune
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
+1
የ12ኛ ክፍል ፈተና የማለፊያ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር ዝቅተኛ የመሆኑ ምክንያት በጥናት ሊለይ ይገባል፡- ቋሚ ኮሚቴው
የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ50 በመቶ በላይ ውጤት የሚያስመዘግቡ ተማሪዎች ቁጥር ዝቅተኛ የመሆኑ ምክንያት በጥናት ሊለይ እንደሚገባ በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሀብት ልማት፣ ሥራ ስምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሜቴ አሳሰበ።
ቋሚ ኮሜቴው የትምህርት ሚኒስቴርን የ2018 ሩብ ዓመት እቅድ አፈፃፀም ገምግሟል።
ባለፉት አምስት ዓመታት በትምህር ሥርዓቱ የተደረገው ማሻሻያ የትምህርት ጥራትን በማስጠበቅ እና የአመለካከት ለውጥ በማምጣት ረገድ ውጤት ቢመዘገብበትም፣ የትምህርት ሥርዓቱ አሁንም መቶ በመቶ ከችግር መላቀቅ አልቻለም ተብሏል።
ከባለፉት ዓመታት አንፃር በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ ተማሪዎች ቁጥር ቢጨምርም፣ ለፈተና ከተቀመጡት ተማሪዎች ቁጥር አንፃር ሲታይ ግን ዝቅተኛ መሆኑ ተገልጿል።
በተጨማሪም ከዓመት ዓመት ለ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የሚቀመጡ ተማሪዎች ቁጥር እየቀነሰ መምጣቱም ተጠቅሷል።
የRemedial ፕሮግራም ምደባ‼️
በ2017 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ማጠቃለያ አገር አቀፍ ፈተና ወስዳችሁ ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል የሚያስችል ማለፊያ ውጤት ያስመዘገባችሁ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ከታች በተዘረዘሩት አማራጮች ማየት የምትችሉ መሆኑን እየገለጽን ተቋማት በሚያስተላልፉት ጥሪ መሰረት የ Remedial ፕሮግራሙን መከታተል ትችላላችሁ።
የተመደባችሁበትን ተቋም ለማየት የቀረቡ አማራጮች
1. Website: https://student.ethernet.edu.et
2. Telegram bot: @moestudentbot
‼️የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያን እንድታወጡ ትምህርት ሚኒስቴር አሳስቧል።
ማንኛውም ተማሪ ፈተና ላይ ለመቀመጥ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ሊኖረው እንደሚገባ መወሰኑ ይታወሳል።
በመሆኑም በ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ የሆናችሁ ተማሪዎች በአቅራቢያችሁ በሚገኝ የፋይዳ ዲጂታል መታወቂያ ማውጫ ማዕከል በመመዝገብ መታወቂያውን ማውጣት ይኖርባችኋል ተብሏል።
‼️የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ይዘቶች ይፋ ሆኑ፡፡
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ፤ ተማሪዎች፣ የተማሪ ቤተሰቦች፣ መምህራንና የትምህርት አመራር ለፈተና ዝግጅት በሚያደርጉበት ወቅት ፈተና የሚሸፍናቸው የይዘት አካባቢዎች ይፋ አድርጓል።
የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ከፍል ፈተና ዝግጅትና አስተዳደር የሚከተሉትን ያካትታል፡፡
1. የትምህርት ዓይነቶችን በተመለከተ
ለተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ኬሚስትሪ፣
- ፊዝክስና ባዮሎጂ
ለማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፦
- እንግሊዘኛ፣
- ሒሳብ፣
- እስኮላስቲክ አፕቲትዩድ፣
- ታሪክ፣
- ጂኦግራፊና ኢኮኖሚክስ ናቸው።
2. ፈተናው ከ9ኛ እስከ 12ኛ ከፍል ደረጃዎችን እና በተማሪው መጽሐፍ ላይ ያሉትን ሁሉንም ምዕራፎች ይሸፍናል፡፡
3. ከ10ኛ – 12ኛ ክፍል ሁሉም የትምህርት ዓይነት ፈተና በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት መሠረት እየተዘጋጀ ያለ ሲሆን የ9ኛ ክፍል ደግሞ የሁሉም የትምህርት ዓይነቶች ፈተናዎች ከቀድሞውና ከአዲሱ ሥርዓተ ትምህርቶች የጋራ ይዘቶችን ብቻ አካቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
4. ፈተናው ማንኛውም ተፈታኝ ተማሪ ከተማረው ሥርዓተ ትምህርትና ከተማሪው መጽሐፍ ላይ ብቻ ተመስርቶ እየተዘጋጀ ይገኛል፡፡
5. የፈተናው አስተዳደር በበይነ መረብና በወረቀት ጎን ለጎን የሚሰጥ ሲሆን አብዛኛው ተፈታኝ በበይነ መረብ እንዲፈተን እየተሠራ ያለ በመሆኑ ተፈታኞች እራሳቸውን በበይነ መረብ ለመፈተን ሊያዘጋጁ ይገባል፡፡
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ላይ ለመቀመጥ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ቅድመ ሁኔታ ተደረገ።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት " ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ለፈተና ለመቀመጥ ቅድመ ሁኔታ ነው " ብሏል።
" ማንኛውም የ2018 ትምህርት ዘመን 12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ተፈታኝ ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ከፈተና ምዝገባ ቀድሞ ማውጣትና በእጁ መያዝ ይገባዋል " ሲል አሳውቋል።
" ብሔራዊ መታወቂያ (National ID) የሌለው ተማሪ ለፈተና መመዝገብ ሆነ በማንኛውም ሁኔታ መፈተን አይችልም " ሲል አስገንዝቧል።
ተማሪዎች የብሔራዊ መታወቂያ (National ID) ይዘው እንዲገኙ ፦
- የተማሪ ቤተሰብ
- መምህራን
- የትምህርት አመራሮች
- የሚዲያ አካላት ተገቢውን ድጋፍ እንዲያደርጉ ጥሪ ቀርቧል።
Via : tikvah
❗️የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል ይሸፍናል፡፡ - MOE
ትምህርት ሚኒስቴር የ2018 ትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተናን በተመለከት ለሁሉም ክልሎች እና ለሁለቱ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮዎች እንዲሁም ለትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ትናንት ጥቅምት 10/2018 ዓ.ም ደብዳቤ ልኳል፡፡
በሚኒስቴሩ የስርዓተ ትምህርት ማበልጸጊያ መሪ ሥራ አስፈጻማ ቴዎድሮስ ሽዋርገጥ (ዶ/ር) የተፈረመው ደብዳቤው፤ የ2018 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ፈተና ከ9-12ኛ ክፍል እንደሚሸፍንና ተማሪዎች የተማሩትን ይዘቶች የሚፈተኑ መሆኑን ይገልጻል፡፡
ብሔራዊ ፈተናው ከ10ኛ እስከ 12ኛ ክፍሎች የአዲሱ ስርዓተ ትምህርት ይዘቶችን መሠረት ያደረገ እንደሚሆን ተጠቁሟል፡፡
በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትምህርት ቤቶች 9ኛ ክፍልን በአዲሱ ስርዓተ ትምህርት፤ ሌሎቹ ደግሞ በቀድሞው ስርዓተ ትምህርት የተማሩ በመሆኑ ፈተናው ከሁለቱ ስርዓተ ትምህርቶች የጋራ የሆኑ ይዘቶች ተጣጥሞ የሚወጣ መሆኑ ተገልጿል፡፡
በአጠቃላይ ትምህርት ስርዓተ ትምህርት ሪፎርም መሠረት የሁለተኛ ደረጃ አዲሱ ስርዓተ ትምህርት በ2015 ዓ.ም የሙከራ ትግበራ በማካሔድ ከ2016 ዓ.ም ጀምሮ ወደ ሙሉ ትግበራ መገባቱ ይታወቃል፡፡
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻
It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches.
⚡️ Place your ad here in three simple steps:
1 Sign up
2 Top up the balance in a convenient way
3 Create your advertising post
If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it.
Start your promotion journey now!
Enjoy our content? Advertise on this channel and reach a highly engaged audience! 👉🏻
It's easy with Telega.io. As the leading platform for native ads and integrations on Telegram, it provides user-friendly and efficient tools for quick and automated ad launches.
⚡️ Place your ad here in three simple steps:
1 Sign up
2 Top up the balance in a convenient way
3 Create your advertising post
If your ad aligns with our content, we’ll gladly publish it.
Start your promotion journey now!
የሪሜዲያል ፈተና የመግቢያ ነጥብን በተመለከተ በግል ተቋማት እና በትምህርት ሚኒስቴር መካከል አለመግባባት መከሰቱ ተገለጸ
👉 የግል ተቋማቱ 'የቁጥር መዛባት' ጥያቄ ሲያነሱ፤ ሚኒስቴሩ በበኩሉ የተቀመጠው ቁጥር 'አፈርማቲቭ አክሽን' ለሚሰጣቸው ክልሎች እና ዜጎች ብቻ የሚሰራ ነው ብሏል
በመጀመሪያው ፈተና የዩኒቨርሲቲ መግቢያ ውጤት ያላስመዘገቡ የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የድጋሚ እድል የሚያገኙበት የ'ሪሜዲያል' ፈተና የዚህ ዓመት ውጤት ላይ በግል ትምህርት ተቋማት እና ትምህርት ሚኒስቴር መካከል አለመግባባት መፈጠሩን የኢትዮጵያ የግል ከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ማህበር ገልጿል፡፡
ማህበሩ "በትምህርት ሚኒስቴር የተቀመጠው የቁጥር መጠን ከማለፊያ መቶኛ ጋር አለመጣጣሙ ግራ መጋባትን ፈጥሯል" በማለት ቅሬታውን ሲያቀርብ፤ ሚኒስቴሩ በበኩሉ ቁጥሩ የተስተካከለ መሆኑን አስታውቋል።
የግል ከፍተኛ ትምህርት፣ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ተቋማት ማህበር ሥራ አስኪያጅ አቶ ተፈራ ገበየሁ፤ ሚኒስቴሩ 'የሪሜዲያል ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት እና ብዛት ከ33 በመቶ እና ከዚያ በላይ ውጤት ማምጣት አለባቸው' የሚል ማስታወቂያ ማውጣቱ አስታውሰዋል።
ይሁንና፣ በተፈጥሮ እና ማኅበራዊ ሳይንስ ለወንዶች የተቀመጠው 216 የመግቢያ ነጥብ ወደ መቶኛ ሲቀየር 36 በመቶ እንደሚሆን ገልጸው፤ በመቶኛ እና በቁጥር መካከል ያለው ልዩነት ግርታን እንደፈጠረ ለአሐዱ ተናግረዋል።
አቶ ተፈራ፣ ጉዳዩን አስመልክቶ 36 በመቶ መሆኑን የሚያሳይ መረጃ ለተቋማት በኢ-ሜል መልዕክት መላኩን ገልጸዋል። "ነገር ግን ይህ መረጃ 'ይፋዊ አይደለም' መባሉ፤ የመረጃ መዛባት ስህተት እንዳያስከትል ስጋት ፈጥሮብናል" ሲሉም አክለዋል።
አሐዱ ጉዳዩን አስመልክቶ የትምህርት ሚኒስቴር የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ማስተባበሪያ ዴስክ ኃላፊ ኢዮብ አየነው (ዶ/ር)ን ጠይቋል።
ኃላፊው በምላሻቸው፣ "ቁጥሮቹ ይፋ ሲደረጉ መስተካከል ያለባቸው እንዳሉ ተረድተናል" ያሉ ሲሆን፤ ሆኖም ግርታ እንዳይፈጠር በሚል ለተቋማቱ በዚህ ሳምንት የማስተካከያ ደብዳቤ እንደሚጻፍ ተናግረዋል።
አክለውም፤ "የተቀመጠው '33 ከመቶ' የሚለው ቁጥር 'አፈርማቲቭ አክሽን' ለሚሰጣቸው ክልሎች እና ዜጎች ብቻ የሚሰራ ውጤት ነው" ብለዋል፡፡
በመንግሥት ወጪያቸው የሚሸፈነው እና የግል ተቋማት ውስጥ ገብተው የሚማሩት ተማሪዎች ግን፤ 36 ከመቶ ወይም ወንድ 216 ሴት ደግሞ 204 የመቁረጫ ነጥቡን ያመጡ ተማሪዎች ብቻ እንደሆኑ አስረድተዋል።
ለታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች በሁለቱም የትምህርት ዘርፎች እና ለሁለቱም ጾታ 198 ነጥብ ተቀምጧል።
በተጨማሪም መስማት የተሳናቸው የተፈጥሮ እና የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የዩኒቨርሲቲ መግቢያ 198 ሲሆን፤ ዓይነ ስውራን ደግሞ በሁለቱም የትምህርት ዘርፎች እና ጾታ 165 የማለፊያ ነጥብ ተወስኖላቸዋል። ይህ ቁጥርም በመቶኛ 33 ከመቶ ይሆናል ነው የተባለው።
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
ይጠንቀቁ‼️
የዩኒቨርሲቲ ምደባን በተመለከተ ጉዳይ እናስፈፅማለን፣ እንዲቀያየሩ እናደርጋለን ከሚሉ ግለሰቦች ይጠንቀቁ፡፡
“ከአንድ ዩኒቨርሲቲ ወደ ሌላ ዩኒቨርሲቲ እናቀያይራለን“፣ “ቅሬታዎ ተቀባይነት እንዲያገኝ“ እናስደርጋለን ከሚሉ የማኅበራዊ ሚዲያ አጭበርባሪዎች እንዲጠነቀቁ እናሳስባለን፡፡
ትምህርት ሚኒስቴር ከዩኒቨርሲቲ ምደባ ጋር የተያያዘ ማንኛውም ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ላላቸው ተማሪዎች ምላሽ እየሰጠ መሆኑን ለቲክቫህ አረጋግጧል፡፡
በመሆኑም ከምደባው ጋር የተያያዘ ማንኛውም ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ያላችሁ ተማሪዎች በቀጣይ ቀናትም ትምህርት ሚኒስቴር #በአካል በመሔድ ቅሬታዎን ያቅርቡ፡፡
‼️ከምደባ ጋር የተያያዘ ቅሬታ ላላቸው እየሰጠን ነው፡፡ ትምህርት ሚኒስቴር
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡና በመንግሥት ዩኒቨርሲቲዎች ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ትናንት ይፋ መደረጉ ይታወቃል።
በርካታ ውጤት ያመጡ ተማሪዎች ከዩኒቨርሲቲ ምደባው ጋር ተያይዞ ያላቸውን ጥያቄ አድርሰውናል፡፡ በጉዳዩ ዙሪያ ትምህርት ሚኒስቴርን ጠይቀናል፡፡
በዚህም በትምህርት ሚኒስቴር የተቋቋመ ኮሚቴ ከምደባው ጋር በተያያዘ ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ላላቸው ተማሪዎች ምላሽ እየሰጠ እንደሚገኝ የሚኒስቴሩ አመራር እና የኮሚቴው አባል ለቲክቫህ ዩኒቨርሲቲ ተናግረዋል፡፡
በኦንላይን ብቻ 350 የሚሆኑ ቅሬታዎችን መቀበላቸውን የገለፁት የኮሚቴው አባል፤ በአካል ወደ ትምህርት ሚኒስቴር ለሔዱ እጅግ በርካታ ተማሪዎች ተገቢ ምላሽና ማብራሪያ እየተሰጣቸው መሆኑንም ገልፀዋል፡፡
ክፍተቶች ካሉ እያየን ነው ያሉት አመራሩ፤ ከምደባው ጋር የተያያዘ ማንኛውም ጥያቄም ሆነ ቅሬታ ያላቸው ተማሪዎች በቀጣይ ቀናትም በአካል ማቅረብ ይችላሉ ብለዋል፡፡
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
የዩኒቨርስቲ ምደባ ይፋ ሆነ‼️
በ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል አገር አቀፍ ፈተና ወስደው የማለፊያ ውጤት ያስመዘገቡ እና ለትምህርት ሚኒስቴር ተጠሪ በሆኑ የመንግስት ዩኒቨርስቲዎች በወጪ መጋራት (ስኮላርሽፕ) ትምህርታቸውን ለሚከታተሉ የቅድመ ምረቃ መደበኛ ተማሪዎች የተቋም ምደባ ይፋ መደረጉን ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
ተማሪዎች ከአሁን ሰዓት ጀምሮ ፦
➡️ በዌብሳይት፦ https://student.ethernet.edu.et
➡️ በቴሌግራም ቦት @moestudentbot ምደባቸውን ማየት እንደሚችሉ ገልጿል።
የRemedial ፕሮግራም ምደባ በቅርቡ ይፋ እንደሚደረግ ትምህርት ሚኒስቴር አሳውቋል።
https://t.me/+uXs4lxNd76QyMThk
የሪሜዲያል መግቢያ ነጥብ ይፋ ሆነ‼️
ትምህርት ሚኒስቴር በ2018 የትምህርት ዘመን የመንግስት ዩኒቨርሲቲዎችን በተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ትምህርት መስኮች ከ49.5% በታች ያስመዘገቡ ነገር ግን ከዚህ በታች የተዘረዘሩትን የሚያሟሉ ተማሪዎች የRemedial ፕሮግራም ተጠቃሚ መሆናቸውን አሳውቋል።
1. በሁሉም አማራጮች (በግል እና በመንግስት ተቋማት) የ Remedial ፕሮግራም ለመከታተል ተማሪዎች እንደተፈተኑት የትምህርት አይነት ብዛት 33% ከመቶ እና ከዚያ የተቆረጠ መሆኑን።
2. ከላይ በተራ ቁጥር 1 የተገለጸው እንደተጠበቀ ሆኖ በመንግስት ተቋማት (ወጪያቸው በመንግስት ተሸፍኖ) የ Remedial ፕሮግራም የሚከታተሉ ተማሪዎች የመቁረጫ ነጥቡን ያሟሉ ብቻ ይሆናሉ።
የመቁረጫ ነጥብ ፦
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ወንድ ተማሪዎች 216
➡️ የተፈጥሮ እና የማህበራዊ ሳይንስ ሴት ተማሪዎች 204
➡️ ታዳጊ ክልል እና አርብቶ አደር አካባቢ የተፈጥሮ እና ማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ የማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ መስማት ለተሳናቸው ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 198
➡️ ማህበራዊ እና የተፈጥሮ ሳይንስ ዓይነስውራን ተማሪዎች ለሁለቱም ጾታ 165
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
