Mark Tech Info | Mark Technology Information
رفتن به کانال در Telegram
Buy ads: https://telega.io/c/MarkTechInfo ለአስተያየት ፣ ጥቆማ ፣ ለማስታወቂያ እና ለጥያቄዎች በዚህ ያናግሩን። 👇👇👇👇👇👇👇👇 @MarkTechInfoBot
نمایش بیشتر6 218
مشترکین
-324 ساعت
-337 روز
-31730 روز
آرشیو پست ها
+3
❗️በ18 ተማሪዎች ፈተናውን በፈተና ማጭበርበር የእስር ቅጣት ተላለፈባቸው!
የጋምቤላ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፈጣን ምድብ ችሎት የ12 ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና በማጭበርበር ለመፈተን ሲሞክሩ በተያዙ 18 ተማሪዎች ላይ የእስር ቅጣት ዉሳኔ አሳለፈ።
የጋምቤላ ከተማ ፍትህ መምሪያ ከፍተኛ ዐቃቢ ህግ በተከሳሽ እነ ዋው ጊዉ (ዘጠኝ ) ሰዎች እና በነ ሯች ጆክ (ዘጠኝ ) ሰዎች በፈጸሙት በጋምቤላ ዩንቨርስቲ በሌላ ተማሪ ስም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን ሲሞክሩ በተደረገ ፍተሻ በቁጥጥር ስር መዋላቸዉ ተመልክቷል ።
ዐቃቢ ህግም ጉዳዩን ወደ ጋምቤላ ከተማ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ፈጣን ምድብ ችሎት በማቅረቡ በተከሳሾቹ ላይ በተከሰሱበት አታላይነት ወንጀል ላይ የተሳተፉትን 18 (አስራስምንት ) ተማሪዎች ላይ ፍርድ ቤቱ በቀን 05/11/2017ዓ/ም በዋለዉ ችሎት በእያንዳዳቸዉ ተከሳሾች ላይ አንድ ዓመት ጽኑ እስራትና የሶስት ሺ ብር ብር የገንዘብ መቀጮ እንዲቀጡ መወሰኑ የጋምቤላ ክልል ፍትህ ቢሮ አስታውቋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
‼️የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት መቼ ይገለጻል?
የትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ፣ የ12ኛ ክፍል ፈተና ውጤት በጳጉሜን ወር 2017 ዓ.ም እንደሚገለፅ ተናግረዋል፡፡
"በማረሚያ ቤት ያሉ የሕግ ታራሚዎች፣ በአማራ ክልል ፈተናውን መውስድ ያልቻሉ ተማሪዎች እንዲሁም ዘግይተው ትምህርት ለጀመሩ ተፈታኝ ተማሪዎች የመልቀቂያ ፈተናውን በነሐሴ ወር ከሰጠን በኋላ ጳጉሜን ላይ ውጤት እናሳውቃለን" ብለዋል፡፡
ሁሉም ውጤት የሚያመጡ ተማሪዎች መስከረም 08/2018 ዓ.ም ወደ ዩኒቨርሲቲዎች ይገባሉ ያሉት ሚኒስትሩ፤ ከመስከረም እስከ ሰኔ የሚለው የትምህርት ካላንደር በ2018 ትምህርት ዘመን ሙሉ በሙሉ እንደሚተገበር ገልፀዋል፡፡
ዘንድሮ ውጤት አምጥተው ወደ ዩኒቨርሲቲ የሚገቡ ተማሪዎች ቁጥር ባለፈው ዓመት ከነበረው 5.4% የተሻለ ቁጥር ያላቸው ተማሪዎች እነደሚያልፉ ተስፋ እንደሚያደርጉ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗700 ትምህርት ቤቶች ምንም ያላሳለፉ 12ኛ ክፍል
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና አስፈትነው ምንም ተማሪ ለማያሳልፉ 700 ትምህርት ቤቶች በ2018 ዓ.ም ለአንድ ዓመት የሚቆይ ልዩ የማጠናከሪያ ስልጠና ሊሰጥ ነው፡፡
ለ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ዝግጅት ከክልል ትምህርት ቢሮዎች ጋር በመነጋገር ለተመረጡ 400 ትምህርት ቤቶች የማጠናከሪያ ድጋፍ መደረጉን ትምህርት ሚኒስትሩ ብርሃኑ ነጋ (ፕ/ር) አስታውሰዋል፡፡
በቀጣይ ዓመት የተሻለ የማጠናከሪያ ድጋፍ ለማድረግ መታቀዱን ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
በዚህም የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና ውጤት ይፋ ከሆነ በኋላ፣ ምንም ተማሪ ለማያሳልፉ 700 ትምህርት ቤቶች ልዩ ማጠናከሪያ ስልጠና ይሰጣል ብለዋል።
በተያያዘም በ2018 ዓ.ም አምስት ተጨማሪ አዳሪ ትምህርት ቤቶችን ገንብቶ ወደ ሥራ ለማስገባት መታቀዱን ሚኒስትሩ ገልፀዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚገባበት እለት መሆኑ ተነገረ
መስከረም 8 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ የቀጣዩ አመት የዩኒቨርስቲ ት/ት ይጀመራል ሲል ትምህርት ሚኒስቴር አስታውቋል።
የዘንድሮው የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የፈተና ውጤት ጳጉሜ ላይ ይፋ ይሆናል በማለት እስከዚያም ድረስ የሚቆየው ፈተና ያልወሰዱና በመጪው ነሐሴ ወር ለፈተና የሚቀመጡ ቀሪ ተፈታኝ ተማሪዎች በመኖራቸው መሆኑን የትምህርት ሚኒስትሩ ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ ተናግረዋል።
በተለያየ ምክንያት ዘግይተው ትምህርት የጀመሩ በመኖራቸው ነው ፈተና እኩል ያልወሰዱ ተፈታኞች ያሉት በማለትም በመሆኑም ጳጉሜ ወር ላይ የ12ኛ ክፍል የፈተና ውጤት ከታወቀ በኋላ መስከረም 8 ቀን ሁሉም ተማሪ ዩኒቨርስቲ የሚጀምርበት እለት እንደሚሆን ሚኒስትሩ ገልጸዋል።
የትምህርት ካላንደርን በአግባቡ አክብሮ በመስራት የፈተና ጊዜያትንም ላለመሻማት ይሰራል ሲሉ ያከሉት ፕሮፌሰር ብርሃኑ ከመስከረም ጀምሮ ጥብቅ አሰራር እንደሚኖር ገልጸዋል።
እንደ ሀገር እኩል ውጤት ተናግሮ በእኩል ትምህርት ለማስጀመር ሲባል ቀሪ ያልተፈተኑ ተፈታኝ ተማሪዎችን ጠብቆ ማስጨረስ እንደሚገባ የተናገሩት የትምህርት ሚኒስትሩ በራሳቸው ፈቃድና ምክንያት አስቀድመው ፈተና ላይ ካልተቀመጡት በቀር ሌሎቹ የመመዘኛ መስፈርቱ አካል መሆናቸውን ገልጸዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗ትምህርት ሚኒስቴር የ2017 ዓ.ም የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተናን አስመልክቶ ዛሬ መግለጫ ሰጥቶ ነበር።
የትምህርት ሚንስትሩ ፕ/ሮ ብርሃኑ ነጋ " ባለፉት ሶስት አመታት በተወሰነ መልኩ ያጋጥሙ የነበሩ የጸጥታ ችግሮች፣ የፈተና ስርቆት ሙከራዎች፣ የፈተና ስርዓትና አስተዳደር የዲሲፒሊን ግድፈቶች በዘንድሮው አመት ቀንሰው ተገኝተዋል " ብለዋል።
ለዚህም " የበይነ መረብ የፈተና ሽፋን በአንድ አመት ውስጥ በአራት እጥፍ ማደጉ፤ የፈተና ግብረ ሀይሉ ያልተቆጠበ ጥረት፤ እንዲሁም ተማሪዎች ሰርቶ ውጤት ማምጣት አማራጭ የሌለው መፍትሄ መሆኑን መገንዘባቸው " ምክንያቶች ናቸው ሲሉ ገልጸዋል።
የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) በበኩላቸው " ፈተናው በ4 ዙሮች እንዲሠጥ ነው የተደረገው። በአራቱም ዙሮች የተሰጡ ፈተናዎች ተቀራራቢ (አቻ) ናቸው " ብለዋል።
በ2017 የትምህርት ዘመን በአጠቃላይ ከተመዘገቡ ተፈታኞች 608,742 መካከል 581,905 (95.6%) ፈተናውን እንደወሰዱ አመልክተዋል። ከነዚህም ውስጥ 134,828 (23.2%) በበይነ መረብ ብቻ የተፈተኑ መሆናቸውን ገልጸዋል።
በአማራ ብሔራዊ ክልል ያሉ እና የተወሰኑ የህግ ታራሚዎች በድምሩ 4,966 ተፈታኞች ከነሐሴ 26-28/2017 ዓ/ም በሁለተኛ ዙር የተዘጋጀላቸውን ፈተና በወረቀት እንደሚወስዱ አመልክተዋል።
የ70 ዓመቱ የ12ኛ ክፍል ተፈታኝ
የ70 ዓመት አዛውንቱ አቶ ዋሬ ጎበና፣ በቡሌ ሆራ ዩኒቨርሲቲ የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና እየወሰዱ ከሚገኙ ተማሪዎች መካከል አንዱ ናቸው፡፡
በሱሮ በርጉዳ ወረዳ ነዋሪ የሆኑት አቶ ዋሬ፤ ሰባት ልጆቻቸውን ለማስተማር ሲሉ እሳቸው ከትምህርት ቤት መቅረታቸውን አስረድተዋል።
ትምህርት ዕድሜ አይገድበውም የሚሉት አቶ ዋሬ፤ በተለያየ ምክንያት ትምህርታቸውን ያቋረጡ ወደ ትምህርት እንዲመለሱ ጥሩ ምሳሌ ናቸው።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
‼️ሀገር አቀፍ የ2ኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ሰርተፊኬት ፈተና የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች ፈተና ተጀምሯል።
ለተፈታኞች መልካም የፈተና ጊዜን እንመኛለን
ምስል፡ ዲላ ዩኒቨርስቲ
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗የሶሻል ሳይንስ ተማሪዎች የፈተና ፕሮግራም
በወጣው መርሐግብር መሰረት ነገ ሐምሌ 01/2017 ዓ.ም የእንግሊዝኛ እና የሒሳብ ትምህርት ፈተናዎች በጠዋት እና በከሰዓት ፈረቃዎች ይሰጣሉ።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው የማኀበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ፈተና፤ ከሐምሌ 01-08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ ሲጓዝ የነበረ መኪና የትራፊክ አደጋ አጋጥሞት በሰዉና በንብረት ጉዳት መድረሱን የብርብር ከተማ አስተዳደር ፖሊስ አዛዥ ረዳት ኢንስፔክተር ምትኩ ፉላሞ ለቲክቫህ ኢትዮጵያ ተናግረዋል።
አደጋዉ የደረሰዉ ከቦሮዳ ወረዳ ሀገር አቀፍ ወደ ዩኒቨርሲቲ መግቢያ ፈተና ለመዉሰድ ወደ አርባምንጭ ዩኒቨርሲቲ የሚሄዱ የ12ኛ ክፍል የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ይዞ ሲጓዝ የነበረ የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-09846 ደሕ የሆነ FSR መኪና ከአርባምንጭ ወደ ወላይታ ሶዶ ከተማ ይጓዝ ከነበረ ኮድ 3-32326 ኦሮ ከሆነ የሕዝብ ማመላለሻ ጋር በመጋጨቱ እንደሆነ አዛዡ አስታዉቀዋል።
በአደጋው በ5 ሰዎች ላይ ከባድ እና በ23 ሰዎች ላይ ቀላል የአካል ጉዳት መድረሱን የገለፁት አዛዡ ተጎጅዎችም በብርብር መጀመሪያ ደረጃ ሆስፒታል ለህክምና መወሰዳቸዉን ገልፀዋል።
" ከቦታዉ ዳገታማነትና ከመኪኖቹ ፍጥነት አንፃር ሊደርስ ይችል የነበረዉ አደጋ ዘግናኝ ይሆን ነበር " ያሉት ፖሊስ አዛዡ " ፈጣሪ ጠብቋቸዉ የሞት አደጋ እስካሁን አልተከሰተም " ብለዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
የ2017 ዓ.ም የማኅበራዊ ሳይንስ መስክ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና ተፈታኞች ወደየተመደቡበት ዩኒቨርሲቲ በዛሬው ዕለት መግባት ጀምረዋል።
በሦስተኛ እና አራተኛ ዙር ፈተናቸውን ለሚወስዱ የማኅበራዊ ሳይንስ ተፈታኞች አቀባበል ሰኔ 28 እና 29/2017 ዓ.ም እንደሚካሔድ ከዚህ ቀደም በወጣ መርሐግብር መገለፁ ይታወቃል።
የማኅበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ከሐምሌ 01-08/2017 ዓ.ም በሁለት ዙር ይሰጣል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
በአዲስ አበባ ከተማ የ2017 ዓ.ም የ6ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ከወሰዱ ተማሪዎች መካከል 95 % ያህሉ 50% እና ከዛ በላይ በማምጣት ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ኃላፊ ዘላለም ሙላቱ (ዶ/ር) አስታውቀዋል።
በ2017 ዓ.ም ፈተናውን ከወሰዱ 79,034 ተማሪዎች መካከል 75,085 ተማሪዎች ማለትም 95 በመቶ የሚሆኑ ተማሪዎች 50% እና በላይ አስመዝግበው ወደ ቀጣዩ የክፍል ደረጃ መሸጋገራቸውን ገልጸዋል።
ዘንድሮው በከተማ ደረጃ ከፍተኛ ውጤት ካስመዘገቡ ተማሪዎች መካከል ከ1 እስከ 4 የሚሆኑት ከመንግስት ትምህርት ቤቶች መሆናቸው አመልክተዋል።
" በግልና በመንግስት ትምህርት ቤቶች መካከል ያለዉን የውጤት ልዩነት እጅግ እየተቀራረበ መጥቷል " ሲሉ ገልጸዋል።
ተፈታኝ ተማሪዎች ከታች የተቀመጠውን ሊንክ በመጠቀም ከዛሬ ጀምሮ ውጤታቸውን ማየት ይችላሉ ተብሏል።
LINK ፦ https://aa6.ministry.et/#/result
Telegram Bot : @emacs_ministry_result_qmt_bot
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
" ትናንት የተሰጠውን የእንግሊዘኛ ትምህርት ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎች ሌሎች ትምህርት ፈተናዎችን ከወሰዱ በኋላ ይፈተናሉ " - የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት
ትናንት በተሰጠው የመጀመሪያ ቀን ፈተናዎች ላይ የተወሰነ የኃይል እና የሲስተም መቆራረጥ አጋጥሞ እንደነበር የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር እሸቱ ከበደ (ዶ/ር) ለኢትዮጵያ ቴሌቪዥን ተናግረዋል።
" ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በመሆን ችግሩን በፍጥነት በመፍታት ፈተናውን ማስቀጠል ተችሏል " ሲሉ ተደምጠዋል።
" በሲስተምና በኃይል መቆራረጥ ችግር ትናንት የተሰጠውን የእንግሊዘኛ ትምህርት ፈተና ያልተፈተኑ ተማሪዎች ሌሎች ትምህርቶችን ከተፈተኑ በኋላ ይፈተናሉ " ብለዋል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና የሁለተኛ ቀን ፈተናዎች በመላ ሀገሪቱ እየተሰጡ ነው።
የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች በዛሬ ጠዋት መርሐግብር የስኮላስቲክ አፕቲትዩድ ትምህርት ፈተና እየወሰዱ ሲሆን፤ ከሰዓት የፊዚክስ ትምህርት ፈተና ይሰጣል።
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗️የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና መሰጠት ጀመረ!
የ2017 ዓ.ም የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ መልቀቂያ ፈተና በተቀመጠው የጊዜ ሰሌዳ መሰረት በሁሉም የመፈተኛ ማዕከላት መሰጠት መጀመሩን፤ የትምህርት ምዘናና ፈተናዎች አገልግሎት አስታውቋል፡፡
ማጠናቀቂያ ፈተናው በኦንላይን እና በወረቅት በመሰጠት ላይ የሚገኝ ሲሆን፤ የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ፈተና በዛሬው ዕለት በሁሉም የመፈተኛ ጣቢያዎች መሰጠት ጀምሯል።
በዚህም መሠረት ዘንድሮው በተፈጥሮ ሳይንስና በማህበራዊ ሳይንስ በአጠቃላይ 608 ሺሕ 588 ተማሪዎች ፈተናውን እንደሚወስዱ የተገለጸ ሲሆን፤ 140 ሺሕ የሚጠጉ ተማሪዎች ፈተናውን በኦንላይን እንሚወሰዱ ተመላክቷል፡፡
የዘንድሮ የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ የማጠናቀቂያ ፈተና በአራት ዙሮች የሚሰጥ ሲሆን፤ ከሰኔ 23 ጀምሮ እስከ ሐምሌ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ድረስ ይሰጣል፡፡
በዚህ መሠረት የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች ከሰኔ 23 እስከ 30 ድረስ እንዲሁም፤ የማህበራዊ ሳይንስ ተማሪዎች ደግሞ ከሐምሌ 1 እስከ 8 ቀን 2017 ዓ.ም ፈተናውን እንደሚወስዱ ተገልጿል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
❗️ነገ የሚጀመረው የ2017 ዓ.ም ሀገር አቀፍ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርት መልቀቂያ ፈተና የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የመጀመሪያ እና የሁለተኛ ዙር የፈተና መርሐግብር
በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው ብሔራዊ ፈተና ከሰኔ 23 እስከ ሐምሌ 08/2017 ዓ.ም ይቆያል።
ፈተናውን ለመውሰድ 608 ሺህ ተማሪዎች የተመዘገቡ ሲሆን፤ 150 ሺህ የሚሆኑት በበይነ መረብ የሚፈተኑ ናቸው።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ፈተና ለመፈተን በኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለተመደቡ ተማሪዎች ፈተናቸውን በውጤታማነት ለማከናወን እንዲችሉ ቅድመ ማስገንዘቢያ ተሰጥቷል።
የኢንስቲትዩቱ ፎካልፐርሰን አቶ ታምራት ፈቃደ እንደገለጹት ኢንስቲትዩቱ በዲጂታል መንገድ ፈተና የሚሰጥባቸው ኮምፒውተሮች፣ የኢንተርኔት እና ሌሎች መሠረተ ልማቶች ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ከዚህም በተጨማሪ አስፈላጊ እገዛ የሚያደርጉ ሙያተኞች መኖራቸውን ገልጸዋል።
የጸጥታ አካላት ስርዓቱን ለማስጠበቅ እና ደህንነቱ በተጠበቀ ሁኔታ ፈተናው እንዲከናወን የጸጥታ አካላት በተጠንቀቅ እንደሚሰሩ ተገልጿል።
ተማሪዎች በቆይታቸው ማሟላት የሚገቧቸውን እና የሚያገኟቸውን አገልግሎቶች በተመለከተ በኦረንቴ
በኢንስቲትዩቱ ከ4 ትምህርት ቤቶች 813 ተማሪዎች እንደሚፈተኑ ለማወቅ ተችሏል።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
❗12ኛ ክፍል ፈተና -መልስ መስጫው ላይ እንዴት እንደሚሞላና እንደሚቀባ የሚያብራራ ቪዲዮ።
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
+1
❗የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ22/10/2017 ዓ.ም በኦላይን ፈተና መስጫ ጣቢያ በሚሰጠው የፈተና ገለጻ/Orientation/ ላይ መገኘት እንደሚገባቸው ተገለጸ፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ትምህርት ቢሮ ምክትል ቢሮ ሀላፊ አቶ ዲናኦል ጫላ በከተማ አስተዳደሩ የ2017 የትምህርት ዘመን የ12ኛ ክፍል መልቀቂያ ብሔራዊ ፈተናን በኦላይን ለመስጠት ዝግጅቶች መጠናቀቃቸዉን እንዲሁም ፈተናው ከሰኞ ጀምሮ እንደሚሰጥ የገለጹ ሲሆን ተማሪዎች በፈተና መስጫ ጣቢያዎች በወጣው መርሀ ግብር መሰረት በመገኘት ፈተናዉን ሊወስዱ ይገባል ብለዋል፡፡
አቶ ዲናኦል አክለዉም የፈተና አሰጣጡን አስመልክቶ ገለጻ በፈተና ጣቢያዎች የሚሰጥ መሆኑን የጠቀሱ ሲሆን የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ ፈተና የመጀመሪያ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ22/10/2017 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ፣ የሁለተኛ ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ22/10/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 ፣ የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ29/10/2017 ዓ.ም ጠዋት 2፡30 ፣ የሁለተኛ ዙር የማህበራዊ ሳይንስ ተፈታኝ ተማሪዎች እሁድ በ29/10/2017 ዓ.ም ከቀኑ 7፡30 በኦላይን ፈተና መስጫ ጣቢያዎች በመገኘት የሚሰጠውን የፈተና ገለጻ/Orientation/ መከታተልና የመፈተኛ ቦታቸዉንና ክፍላቸዉን ማየት እንደሚገባቸው አሳስበዋል፡፡
🖥 ለተጨማሪ የ12ኛ ክፍል መረጃዎች 🖥
●▬▬▬▬▬ ๑۩۩๑ ▬▬▬▬▬●
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
📌 👉 t.me/grade12results 👈 📌
●▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬▬●
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
