cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

RemnantsOfGod|🌍| RoG👑📖

“በእኔ ብትኖሩ ቃሎቼም በእናንተ ቢኖሩ የምትወዱትን ሁሉ ለምኑ ይሆንላችሁማል።” — ዮሐንስ 15፥7

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
263
مشترکین
-124 ساعت
-27 روز
-530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

= = = = = = =🕊🕊🕊= = = = = = = 🕊 እጅግ ውድ ሆኖ በገንዘብ የማይገዛ፤ በኮተታ ኮተት ብዛት የማይገኝ፤ ብዙዎች ለመቁጠር የሚያዳግት ገንዘብ ተከበው💵💰💸💴💰💸💵 ፤ሊገዙት ግን ያልቻሉት እና ፈፅሞም የማይችሉት፤በአማርኛ ፊደል ሶስት ሆኖ በቃል አንድ የሆነ፤ በውስጡ ግን በጣም ብ...ዙ ...ነገሮችን የያዘ በምድር ላይ ካሉ ወሳኝ እና ትልቅ ነገሮች አንዱ ብቻ ሳይሆን ዋነኛውም ጭምር ነው... ። 🕊 🕊 🕊 እጅግ ውድ ሆኖ 🤔 በየቀኑ በየዜናው መጀመሪያና እና መጨረሻ በሀገራችን ብቸኛው በነፃ የሚሰጡን ፤ ከየሰዉ አፍ የሚሰማ ተራ የሚመስል: ግን በምድር ለታደሉት ብቻ ፤በሰማይ ደግሞ ዋና መፍለቂያ እና መገኛው የሆነ: እሱ ባለበት. . . ድህነት፤ ረሀብ፤ስደት ፤ጦርነት ማይኖርበት :: አንድ መስሎ በውስጡ ግን ...ሀሴት፤ደስታ፤ የማይቋረጥ እረፍት... የያዘው እውቁና ትልቁ ነገር ሰላም እና ሰላም ብቻ ነው 🤔። * * * * * * * * * * * "ሰላምን እተውላችኋለሁ፥ ሰላሜን እሰጣችኋለሁ፤እኔ የምሰጣችሁ ዓለም እንደሚሰጥ አይደለም።ልባችሁ አይታወክ አይፍራም።" _ዮሐንስ 14፥27 . . . ✍ 1/9/2016 ዓ.ም 🕊 🤗🙏
نمایش همه...
1
እግዚአብሔር የነገርን ምስጢር እና አደራረግ የሚገልጥ አምላክ ነው፡፡ ዳንኤል 2 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹⁹ የዚያን ጊዜም ምሥጢሩ በሌሊት ራእይ ለዳንኤል ተገለጠለት፤ ዳንኤልም የሰማይን አምላክ አመሰገነ። ²⁰ ዳንኤልም ተናገረ እንዲህም አለ፦ ጥበብና ኃይል ለእርሱ ነውና የእግዚአብሔር ስም ከዘላለም እስከ ዘላለም ይባረክ፤ ²¹ ጊዜያትንና ዘመናትን ይለውጣል፤ ነገሥታትን ያፈልሳል፥ ነገሥታትንም ያስነሣል፤ ጥበብን ለጠቢባን እውቀትንም ለአስተዋዮች ይሰጣል። ²² የጠለቀውንና የተሠወረውን ይገልጣል፤ በጨለማ ያለውን ያውቃል፥ ብርሃንም ከእርሱ ጋር ነው። ²³ ጥበብንና ኃይልን የሰጠኸኝ፥ እኛም የለመንንህን ነገር አሁን ያስታወቅኸኝ፥ አንተ የአባቶቼ አምላክ ሆይ፥ የንጉሡን ነገር አስታውቀኸኛልና እገዛልሃለሁ አመሰግንህማለሁ። … ²⁸ ነገር ግን ምሥጢር የሚገልጥ አምላክ በሰማይ ውስጥ አለ፥ እርሱም በኋለኛው ዘመን የሚሆነውን ለንጉሡ ለናቡከደነፆር አስታውቆታል። በአልጋህ ላይ የሆነው ሕልምና የራስህ ራእይ ይህ ነው። … ³⁰ ነገር ግን ይህ ምሥጢር ለእኔ መገለጡ ፍቺው ለንጉሡ ይታወቅ ዘንድ፥ አንተም የልብህን አሳብ ታውቅ ዘንድ ነው እንጂ በዚህ ዓለም ካሉ ሰዎች ይልቅ በጥበብ ስለ በለጥሁ አይደለም።
نمایش همه...
የምታምነውን እወቅ | የእግዚአብሔር ባህርያት | ፓስተር አስፋው በቀለ |www.operationezra.com
نمایش همه...
ኢሳይያስ 51 ¯¯¯¯¯¯¯¯¯¯ ¹ እናንተ ጽድቅን የምትከተሉ እግዚአብሔርንም የምትሹ፥ ስሙኝ፤ ከእርሱ የተቈረጣችሁበትን ድንጋይ ከእርሱም የተቈፈራችሁበትን ጕድጓድ ተመልከቱ። ² ወደ አባታችሁ ወደ አብርሃም፥ ወደ ወለደቻችሁም ወደ ሳራ ተመልከቱ፤ አንድ ብቻውን በሆነ ጊዜ ጠራሁት፥ ባረክሁትም አበዛሁትም። ³ እግዚአብሔርም ጽዮንን ያጽናናል፤ በእርስዋም ባድማ የሆነውን ሁሉ ያጽናናል፥ ምድረ በዳዋንም እንደ ዔደን በረሀዋንም እንደ እግዚአብሔር ገነት ያደርጋል፤ ደስታና ተድላ ምስጋናና የዝማሬ ድምፅ ይገኝበታል። ⁴ ወገኔ ሆይ፥ አድምጠኝ፤ ሕዝቤ ሆይ፥ ስማኝ፤ ሕግ ከእኔ ይወጣልና ፍርዴም ለአሕዛብ ብርሃን ይሆናልና። ⁵ ጽድቄ ፈጥኖ ቀርቦአል፥ ማዳኔም ወጥቶአል፥ ክንዴም በአሕዛብ ላይ ይፈርዳል፤ ደሴቶች እኔን በመተማመን ይጠባበቃሉ፥ በክንዴም ይታመናሉ። ⁶ ዓይናችሁን ወደ ሰማይ አንሡ፥ ወደ ታችም ወደ ምድር ተመልከቱ፤ ሰማያት እንደ ጢስ በንነው ይጠፋሉ፥ ምድርም እንደ ልብስ ታረጃለች፥ የሚኖሩባትም እንዲሁ ይሞታሉ፤ ማዳኔ ግን ለዘላለም ይሆናል፥ ጽድቄም አይፈርስም። ⁷ ጽድቅን የምታውቁ ሕጌም በልባችሁ ያለ ሕዝብ ሆይ፥ ስሙኝ፤ የሰውን ተግዳሮት አትፍሩ፥ በስድባቸውም አትደንግጡ። ⁸ እንደ ልብስም ብል ይበላቸዋል፥ እንደ በግ ጠጕርም ትል ይበላቸዋል፤ ጽድቄ ግን ለዘላለም ማዳኔም ለትውልድ ሁሉ ይሆናል። ⁹ የእግዚአብሔር ክንድ ሆይ፥ ተነሥ፥ ተነሥ፥ ኃይልንም ልበስ በቀድሞው ወራትና በጥንቱ ዘመን በነበረው ትውልድ እንደ ሆነው ተነሥ። ረዓብን የቈራረጥህ ዘንዶውንም የወጋህ አንተ አይደለህምን? ¹⁰ ባሕሩንና የታላቁን ጥልቅ ውኃ ያደረቅኸው፥ የዳኑትም ይሻገሩ ዘንድ ጠሊቁን ባሕር መንገድ ያደረግህ አንተ አይደለህምን? ¹¹ እግዚአብሔርም የተቤዣቸው ይመለሳሉ ወደ ጽዮንም ይመጣሉ፤ የዘላለምም ደስታ በራሳቸው ላይ ይሆናል፤ ደስታንና ተድላን ያገኛሉ፥ ኀዘንና ልቅሶም ይሸሻል። ¹² የማጽናናችሁ እኔ ነኝ፥ እኔ ነኝ፤ የሚሞተውን ሰው እንደ ሣርም የሚጠወልገውን የሰው ልጅ ትፈራ ዘንድ አንተ ማን ነህ? ¹³ ሰማያትንም የዘረጋው ምድርንም የመሠረተውን ፈጣሪህን እግዚአብሔርን ረስተሃል፤ ያጠፋ ዘንድ ባዘጋጀ ጊዜ ከአስጨናቂው ቍጣ የተነሣ ሁልጊዜ ቀኑን ሁሉ ፈርተሃል፤ የአስጨናቂው ቍጣ የት አለ? ¹⁴ ምርኮኛ ፈጥኖ ይፈታል፤ አይሞትም ወደ ጕድጓድም አይወርድም፥ እንጀራም አይጐድልበትም። ¹⁵ ሞገዱም እንዲተምም ባሕርን የማናውጥ አምላክህ እግዚአብሔር እኔ ነኝ፥ ስሜም የሠራዊት ጌታ እግዚአብሔር ነው። ¹⁶ ሰማያትን እዘረጋ ዘንድ ምድርንም እመሠርት ዘንድ፥ ጽዮንንም፦ አንቺ ሕዝቤ ነሽ እል ዘንድ ቃሌን በአፍህ አድርጌአለሁ፥ በእጄም ጥላ ጋርጄሃለሁ። ¹⁷ ከእግዚአብሔር እጅ የቍጣውን ጽዋ የጠጣሽ ኢየሩሳሌም ሆይ፥ ንቂ፥ ንቂ፥ ቁሚ፤ የሚያንገደግድን ዋንጫ ጠጥተሻል ጨልጠሽውማል። ¹⁸ ከወለደቻቸው ልጆች ሁሉ የሚመራት የለም፥ ካሳደገቻቸውም ልጆች ሁሉ እጅዋን የሚይዝ የለም። ¹⁹ እነዚህ ሁለት ነገሮች ሆነውብሻል፥ ማንስ ያስተዛዝንሻል? መፈታትና ጥፋት ራብና ሰይፍ ናቸው፤ እንዴትስ አድርጌ አጽናናሻለሁ? ²⁰ ልጆችሽ ዝለዋል፤ በወጥመድ እንደተያዘ ሚዳቋ በአደባባይ ሁሉ ራስ ላይ ተኝተዋል፤ በእግዚአብሔር ቍጣና በአምላክሽ ተግሣጽ ተሞልተዋል። ²¹ ስለዚህም ያለ ወይን ጠጅ የሰከርሽ አንቺ ችግረኛ፥ ይህን ስሚ፤ ²² ስለ ወገኑ የሚምዋገት አምላክሽ ጌታሽ እግዚአብሔር እንዲህ ይላል፦ እነሆ፥ የሚያንገደግድን ጽዋ የቍጣዬንም ዋንጫ ከእጅሽ ወስጃለሁ፤ ደግመሽም ከእንግዲህ ወዲህ አትጠጪውም። ²³ ነፍስሽንም፦ እንሻገር ዘንድ ዝቅ በዪ በሚሉአት በአስጨናቂዎችሽ እጅ አኖረዋለሁ፤ ጀርባሽንም ለሚሻገሩት እንደ መሬትና እንደ መንገድ አደረግሽላቸው።
نمایش همه...
👏 1
በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል የወጣቶች የድራማና የስነፅሁፍ ህብረት የተሰናዱ ሁለት ዝግጅቶች #ብኤርለሃይሮኢ ቀን: ነገ ማክሰኞ ሚያዚያ 29 ቦታ:በሀዋሳ አዲስ ከተማ ሙሉ ወንጌል ሰዓት: 11:00 #ሎዶቅያዊት ቀን: ግንቦት 02 ቦታ:በሀዋሳ ሕይወት ብርሃን ቤተክርስቲያን ሰዓት: 11:00
نمایش همه...
“ለኃጢአት ሞተን ለጽድቅ እንድንኖር፥ እርሱ ራሱ በሥጋው ኃጢአታችንን በእንጨት ላይ ተሸከመ፤ በመገረፉ ቁስል ተፈወሳችሁ።” — 1ኛ ጴጥሮስ 2፥24 አሜን🙏
نمایش همه...
🔥 1
Hawaz Tegegn        መዳፉ የፋሲካ መዝሙ🎸 😭😭 ያ እኔን በፍቅር ያቀፈበት እጆቹ በችንካር ተመቱ እኔ ያስጠጉኝ ጉኖቹ ውስጥ ጦር ገባባቸው😭😭 በዚህ ሰዓት የውዴ የተተለተለው ስጋውና የፈሰሰው ደሙ ከእንግዲህ ጭለማ " በቃ " ሞት " በቃ "ባርነት " በቃ "  ሲሉኝ ሰማኃቸው፤ ውዴም በታላቅ ድምፅ ተፈፀመ  ብሎ ጮኽ። “ኢየሱስም ሆምጣጤውን ከተቀበለ በኋላ፦ ተፈጸመ አለ፥ ራሱንም አዘንብሎ ነፍሱን አሳልፎ ሰጠ።”   — ዮሐንስ 19፥30 የፈሰሰው  ደሙ  ከሩቅ  እየጠራኝ አስነባኝ  መከራው   ያምላኬ እንዳላዝን    አዝኖ  እንዳልደማ   ደምቶ  እስከሞት  ወዶኛል  ጌታዬ በጥፊ  የመቱት  ምራቅ  ቢተፉበት መች  ሰለቸው  ይሆ  የኔ  አባት😭 ከዚህም  በላይ  አልፎ  ቤዛ  ሆኖልኛል ጌታዬ  እስከሞት  ወዶኛል🙌 ከዘባነ  ኪሩብ  መስቀል  ያስመረጠው ሌላ  ምንም   አይደል  ፍቅር  ነው ተከሳሹ   ድኜ   ዳኛው   ተከሰሰ ሊያከብረኝ  ውድቀቴን   ለበሰ ሁሉም  ሲዝቱበት   ይሰቀል   እንደሚሸለት  በግ  ዝም  አለ ሸክሜን  ተሸክሞ  ቢያቀረቅርልኝ ወንበዴው   ፀድቄ  ቀና አልኩኝ “ተጨነቀ ተሣቀየም አፉንም አልከፈተም፤ #ለመታረድ #እንደሚነዳ #ጠቦት፥ በሸላቶቹም ፊት #ዝም እንደሚል በግ፥ እንዲሁ አፉን አልከፈተም።”   — ኢሳይያስ 53፥7 መች  ሰለቸው  ይሆ  የኔ  አባት😭 ከዚህም  በላይ  አልፎ  ቤዛ  ሆኖልኛል ጌታዬ  እስከሞት  ወዶኛል🙌 ከዘባነ  ኪሩብ  መስቀል  ያስመረ ያ የሮማ   ጅራፍ   ጀርባህን   ያረሰው ፅድቄን   የፃፍክበት  ብዕር  ነው ትሁት  አካልህን   ደጋግሞ  ጠቀሰው ደምህ  እንደ ቀለም  ሊሆነው ተዘርግተህላት  #ነፍሴ  አነበበችህ🥺 በሰንበር  ተከፍለው  ገፆችህ አማረብኝ  ጎንህ  ውሃ  ደም  ሲያነባ  ጠውልገህ  የቆላው  አበባ ተባረኩበት❤
نمایش همه...
1
እዩ ተመልከቱት ፤ የክርስቶስን መስቀል ዛሬም ሲፈውስ ፤ የነፍስን ቁስል። © ቢቶ
نمایش همه...