cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ሁለገብ ኢስላማዊ ቻናል 🌙

Join @islamichanale ፈገግታ ሱና ነው 😊 አሰላሙአለይኩም ውድ የቻናሌ ቤተሰቦች ⚡ ኢስላማዊ ትምህርቶች ⚡ ኢስላማዊ ታሪኮች ⚡ ቁርአን አና ሀዲሶችንም ያገኙበታል ስለ ቻናሉ ሀሳብ አስተያየት ካላቹ 👉 @esmosmith

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
196
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

በ አላህ ፍቃድ ታሪካችንን ጨረስን እንዴት ነበር ታቃላቹ COMMENT ብርታት ነው ስለዚ ሀሳባቹን አካፍሉኝ
نمایش همه...
ቻው ማለት በጣም ስለሚጠላ << አፈቅርሻለሁ እያለ ነበር ስልኩ የተቋረጠው አለቀ በቃ የመጨረሻው የናፊ ድምፅ ነበር ይሄ ሪያድ ደሞ ሁሉንም መናዘዝ ጀመረ መጀመሪያ ስመጣ ናፊ ራሱ ነበር ያመጣው ሀሳብን አንተ እያትና ከወደድካት አብረሀት ትቆያለህ ነበር ያለኝ እኔም እሺ ብዬው መጣው የመጀመሪያው ቀን ነበር እ ከዚ ቡሀላም ትመጣለህ ሲለኝ አው አልኩት ላይብረሪ የሄድን ቀን እንዴት እንደሆነ እንጃ ግን ኤርፖርት ማድረግ ያለበት ነገር ነበር እኔም የዛን ቀን አልመጣም ስላለኝ ነበር ግን የሆነው ይሄ ነው << እና አንተ ትወደኛለህ ማለት ነው አልገባኝም>> << አዎ በዚ መንገድ ባልነግርሽ ደስ ይለኝ ነበር ግን አው >> << እኔኮ ለ አንድ ሰው ልቤን በታማኝነት የሰጠሁ ሰው ነኝ ያንን እምነቴን ማጉደል አልፈልግም >> ብዬው ተነስቼ ሄድኩ ከዛን ቀን ቡሀላ እሱ እንዳያገኘኝ መንገድ እየቀየርኩ መሄድ ጀመርኩ ይሄን አውቆ ወላጅ እየፈለገሽ ነው አስብሎ አስጠራኝ ምንም ልለው አልፈለኩም ግን እኔ አንቺን መውደድ አልችልም ሀጢያት ነው እንዴ የሰራሁት እ ብሎ አፋጠጠኝ እኔም ይሄንን ሲለኝ አላስችል አለኝ << ይሄ ባንተ በኩል ያለ ሀሳብ ነው ለኔ ግን ወንጀል እየሰራሁ ያለው ነው ሚመስለኝ >> << ይሄ ነው መልስሽ በቃ >> << እና ምን ልበ...>>ሳልጨርስለት <<በቃ በቃ እሺ ደና ዋይ>> ብሎኝ ሌላ ሳይጨመር ሄደ ከዛ ቡሀላ በመንገዶቼ አይጠፋም ነገር ግን ብቻውን አልነበረም ከ ሚያማምሩ ሴቶች ጋር ነው ማየው ብቻ ዋናው መገላገሌ ነው ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ አሁቱ ሪያዱ አልተወኝም ግን ሁለተኛውን መልስ የሰጠሁት ጠንከር አድርጌ ስለ ነበር ምንም አላለኝም ግን ከፊቴ ርቋል በወንድምነት አስቢኝ እሺ ብሎኝ ነበር ግን ይሄን አይነት ነገር እንደማያደርግ ናፊ አስረግጦ ነግሮኛል ወንድ ልጅ ሚወድሽ ሆኖ እንደ እህቱ ሊያስብሽ አይችልም ብሎኛል እና ይሄም እንደማይሆን ነግሬው ቆይ የናፊን አደራ እየበላሽ ነው ነበር ጥያቄው እሱ ህይወትሽን ቀጥይ ነው ያለኝ ስለዚ ህይወቴን መቀጠል ነው በቃ አለቀ ህይወቴ ውስጥ ሁሌም ማይጠፋው ብርሀን ናፊ ነው ሁሌም ብራስሌቴን ሳይ እሱን አስባለሁ ሁሌም እንደ አዲስ ያሳለፍናቸውን ነገሮች እደግመዋለሁ ብቻዬን እያሰብኳቸው እስቃለሁ በቃ መቼም መቼም አልረሳውም እሱ የህይወቴ ብርሀን ነው እህቴ እንዳለችው እሱ ለኔ ህይወቱን ሰጥቶኛል እኔ ጋር የመጣው የህይወቱን ምእራፍ እንድቀጥል ነው ናፊዬ ግን እስካሁን አልመጣም ምን ሆኖ እንደሆነም አላቅም ሪያዱንም አናግሬው ተመሳሳይ መልስ ነው የሰጠኝ ስልኩም እንደተዘጋና ማንም ወደነሱ ቤት እንዳልመጣ ነገረኝ ናፊ እንዲ ይለኛል °° ሁሌም ሚሆነው እኛ ስለፈለግን ሳይሆን እሱ ሲፈልግ ብቻ ነው °° #ተፈፀመ ⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩⩩ ታሪኩ ይሄንን ይመስል ነበር ሀሳብ አስተያየታቹ ያበረታታኛል መጥፎም ይሁን ጥሩ ምትሉትን ወይም ስለታሪኩ ያልገባቹ ቦታ ካለ ፃፋልኝ ✉️✉️ @Ben_riham 👈👈ላይወሰላሙ አለይኩም ወራህመቱላህ መልካም ምሽትን ተመኘሁላቹ 🥰🥰🥰😍😘
نمایش همه...
// ክፍል 35 // ፀሀፊ ✍ ኒ ሀ ል #ራህሚ እኔ ከዛች ሰአት ጀምሮ ምንም ሰላም ሚባል ነገር አጣሁ ይሄ ግን በቂ አልነበረም ነገም በተመሳሳይ ሰአት ናፊን እንዲያሳየኝ አላህን ለምኜ ሄድኩ ግን የተፈጠረ ለውጥ የለም ወረብ ምን ያህል እንደ ናፈቀኝ እንጃ ግን አላህዬን ላለማስከፋት በሚል ምንም ላለማድረግ ወሰንኩ ብቻ ሪይዱን ናፊስ ብቻ ነበር የጠየቅኩት እሱ ይሄን ጥያቄ አይወደውም መሰል ብቻ ፊቱ ሁሌ ይለዋወጥብኛል ናፊ ላይ እኮ አደለም ቂም ምንም በቃ እንከን አይወጣለትም የዛሬዋን ቀን እሱን ሳላይ ምንም ቀን ሳይመስለኝ አለፈ ዛሬ ብቻ ነው አይደገምም ብዬ ለራሴ ነገርኩት ናፊን ከራሴም በላይ ነው ማምነው እና ግን ነገ ይመጣል ብዬ ትራሴ ላይ ተደገፍኩ ለማን እንደማወራ ሳይገባኝ ያልመጣበትን ምክንያት ለራሴ መንገር ጀመርኩ ከዛ እራሴን በእንባ ረጥቤ አገኘሁት ምንም ላላመጣ alu ሳላስበው በሩን ከፍታ ገባችና አጠገቤ ተቀመጠች እኔም ሰው ያስፈልገኝ ነበር እሷ ላይ ሄጄ ተጠመጠምኩባት ምን ሆነሽ ነው ብላም ስጠይቀኝ ሁሉንም ነገር ምንም ሳላስቀር ነገርኳት በቃ ተቃቅፈን አለቀስን የዛን ቀን እዛው ባለንበት ተኛን ነገም ሌላ ቀን ነው ወፎቹ አዲስ የተወለደውን ቀን ለማብሰር መጯጯህ ሲጀምሩ ሳልጨርሰው ከእንቅልፌ ተነሳሁ እንዴት ልተኛ ነው ብዬ እራሴን እየጠየቅኩ ነበር አሁን ግን ራሴን በዚ ሁኔታ ማግኘቴ ደስ ብሎኛል ውዱእ አድርገን ሰገድን ሁለታችንም እረጅም ሰአት ዱአ አደረግን ይሄ የዛሬ ውሎዬን ከቀየረ በሚል ...................... ግን የተቀየረ ምንም ነገር የለም ከሪያድ ልብስ ውጪ በቃ መልመድ አለብኝ መሰለኝ ግን እንዴት ብዬ እንዲሁ እንዳለው አንድ ጠና ያለ ሰውዬ ልጄ እድልሽ ነው አሉኝ ግራ ተጋብቼ ምንማለቶት ነው ብዬ ስጠይቀው ሳይመልሱልኝ ሄዱ በዚ ሁኔታ አንድ ወር ሊሞላን ሆነ ሪያዱ አንድ ሰከንድ ከአጠገቤ ዞር እንዲል አይፈልግም አንዳንዴ እሱ በፍቅር ፍቅረኛ ሂሳብ ያየኝ ይሁን እንዴ እያልኩ ብዙ እንድጠረጥው ያደርገኛል የሆነ ቀን እንደውም ሀፊዛ የክፍላችን ልጅ << ኧረ ራህሚ ይሄም ብቻ ባሌ ነው እንዳትይኝ ቆንጆዎቹን ፈጀሻቸው >> << ኧረ ከሪያዱ ጋር ኖርማል ነን ካልደበረሽ አናግሪው >> ብያት ሪያዱ ያልሰደባት ነገር የለም እና የዛን ቀንም ከሷ ለማምለጥ ይሁን አላቅም ብቻ ፍቅረኛዬ ናት ብሏታል እኔም እንዳልሆንን እና በቃ ከሷ ጋር መሆን ስላልፈለገ እንደሆነ ነገርኳት ኧረ ተጠንቀቅ በይ ግን እሱ አይን ውስጥ የእውነት መውደድ ነው ያለው አለችኝ ብቻ አላውቅም ግን ሚያረጋቸው ነገሮች አንጀት ያቆስላሉ አጋጣሚ ብቻ ሚጠብቅ መንካት ማቀፍ በቃ እኔ ማልፈልጋቸውን ናፊ ሲመጣ ሚናደድባቸውን ነገሮች ያደርጋል ተሞሙቶም ቢሆን እና አንድ ወር ማለት ለኔ በቃ እንደ አንድ አመት የተለጠጠች ያህል ተሰማኝ አንድ ቀን ከተኛው እልልል ነው ሚባለው ዛሬም ምንገናኝበት ቦታ ቆሞ ተገናኘን ግን የተለየ ነገር ዛሬ እንዳለና እንዲ ነግረኝ ጠየቅኩት በጣም ደንግጦ ማን ነገረሽ አለኝ መልሴ ልቤ ሚል ነበር አው አለ ግን ምንን አስመልክቶ ብሎ ደግሞ ጠየቀኝ ናፊን ስለው በቃ አላውቅም ተደመመ ያደረግኩት ምን ነበር ብዬ እስካስብ ግን ምንም ሊነግረኝ ፍቃደኛ አልሆነም እኔም በምላሹ ከዚ ቡሀላ እንዳትመጣ ካልነገርከኝ ብዬ ቁርጥ ውሳኔዬን ነገርኩት ምንም ሳይለኝ እሺ አንድ ቀን ስጪኝ ብሎ ለዛሬ አብረን መጣን በነጋታው የኔና የናፊ መናፈሻ ውስጥ ይዞኝ ገባና የሆነ የውጭ ሀገር ስልክ ደወለ አንድ ሁለቴ ጠርቶ በሶስተኛው ተነሳ ምንም ሳልል ከስልኩ ሚወጣውን ድምፅ መጠባበቅ ጀመርኩ በጣም ነው ደስ ያለኝ የወጣው ድምፅ የናፊ ነበር << እ ሪያዱ አለህልኛ >> << አለሁልህ አንተስ >> << የኔ ሩህ እንዴት ናት በአላህ ደሞ አሁን ከሷ ጋር አደል እንዴ መሆን ያለብህ ?>> << ነኝ እኮ ባባ አውፍ በለኝ ግን አልቻልኳትም >> << እና አሁን አጠገብህ ናት እየሰማችኝ ነው >> እንባ አነቀው መሰል ዝም አለ << አው >> ብሎ ዞሮ አየኝ እንባዬ ከራሴ አልፎ እሱን አረጠበው ተጠጋግተን ነበር የተቀመጥነው << የኔ ሩህ >> << ሀያቴ >> << አለሽልኝ አደል >> << የለሁም የኔ ሩህ የለሁም >> << ተያ ጠንከር በይልኝ እንዲ አትሁኚብኝ በረብ >> << ለምን ግን ይሄ በኛ ላይ ሆነ ምን ሆነን ነው የተለያየነው ምንድን ነው እ ንገረኝ >> << አሁን የኔ ሀያት ሰአት የለኝም ግን ሪያዱን እንዲ ነግርሽ እነግረዋለሁ >> << አሁን እሺ ለምን ሰአት የለህም ?>> << ቀዶ ጥገና ላደርግ ነው አለኝ >> እሱ ከኔ ምንም ላለመደበቅ ሲል ነበር የነገረኝ ግን አልሆነም እኔም ራሴን መሆን አልቻልኩም ከዛ ሁሉም ነገር ጨለመ ሪያድ ከስልኩ ሚወጡ ራህሚ ራህሚ የሚል የስቃይ ድምፅ አለቀ አቤት ሳልል አይኔ ተከደነ ምን ያህል እንደቆየሁ እንጃ ግን ስነሳ <<ናፊ እ ሪያዱ ናፊ >> << እሺ ትንሽ ተረጋጊ ቆይ >> ሪያድ ነበረ << አው አታስብ አሁን ነቅታለች እሺ ይኸው >> ብሎ ስልኩን ወደኔ አስጠጋው << እኔ ልሙትልሽ እናቴ በኔ ምከንያት አሁንም አደል አሁንም በኔ ምክንያት እንድታዝኚ አደረግኩሽ አደል >> << ተው የቱም ምታወራው ልክ አደለም እወቃት አሁን የት ነህ እሺ ልምጣ ያለዚያ ቀስ እያልኩ እሞታለሁ እ >> << እንዴት ብለን ሀያቲ የኔ ዱዝ ስልኩን እይልኝ እስቲ አንዴ >> << አየሁት i phone ነው >> << ዱዝ ቁጥሩን ነው ምልሽ >> <<አየሁት እሱንማ መጀመሪያ ግን እዚ አደለሁም ልትለኝ አደለማ >> << ስልኩኮ የዲሲ ነው እዛ ካልሆንኩ አይሰራም >> << የምን ቀዶ ጥገና ነው ምን ሆነህብኛል ?>> << ምንም ሀያቲ ቀላል ነው >> << እኮ ምንድን ነው ??>> << እ የጭንቅላት እጢ ሀያቲ ቀላል ነው ትላንት ነበር ማደርገው ግን አንቺ ጥሩ ስሜት ላይ እንዳልሆንሽ ሳውቅ ለዛሬ አደረግኩት >> << እሺ >> << የኔ ሩህ ከህይወትሽ አስወጪኝ ልንገርሽ አንድም ቀን ያልኩሽን እንዳትረሺ ሌላ ራህሚ አለች አንቺ ውስጥ እሷን ሁኚ ይቺኛዋን ከሆንሽ አትችይውም ጠንካራ ነሽ አቃለሁ ይሄንንም ታልፊዋለሽ ሚሆነውን ግን አላህ ያውቃል አንቺ ያለኔ ህይወትሽን አስበሽ አታውቂም ግን ከዛሬ ጀምሮ አስቢ <<ይሄን ሁሉ ሲሆን ለምን አልነገርከኝም >> << ብነግርግሽ መጨነቅ ነው ምታተርፊው ሌላ የለውም ህመሜን ራሴ ነኝ መታመም ያለብኝ አንቺን ክፋ እንዲነካሽ አልፈልግም አንድ ነገር አድርጊልኝ ..... ኧረ ዛሬም አታስጩህብን ስልኩን ዘግተህ ና ከውጭ ሚመጣ ድምፅ ነበር << ምን ?>> << የመጀመሪያ ልጅሽን በኔ ስም ጥሪው>> << የአባቱ ስም ነው መሆን ያለበት >> ከሁለታችንም የታፈነ ድምፅ ነበር ሚወጣው አሁን ግን ድምፅ አውጥተን ማልቀስ ጀመርን << አትርሺ ሁሌም አላህ ያለው ነው ሚሆነው >> << እ እሺ >> << አፈቅርሻለሁ ሀያቲ የኔ እናት ከዚ ቡሀላ እንዳታለቅሺ >> << አንተም አታድርገው >>ብዙ መናገር ምፈልገው ነገር ነበር
نمایش همه...
//  ክፍል 34  // ፀሀፊ ✍ ኒ ሀ ል                      #ራህሚ እንዲም እንዲያም ብሎ ቦታዋ ጋር ልንደርስ ትንሽ ቀረንና ኢልሀሚን መንገዷ መገንጠያ ጋር ትቻት ተመለስኩና ወደ መንገዴ አዘገምኩ ቦታዋ ጋር ስደርስ አይኔን እስክትሰላች ድረስ እሱን እንድታሳየኝ ለመንኳትና ገ ከጨፈንኩበት ገለጥኳት እኔ ልመና ላይ እስከዚም ነኝ መሰለኝ አልተሳካልኝም ሪያድ ብቻውን አንገቱን ደፍቶ ቆሞ ነበር እንደ መመለስ እግሬን ወደ ኋላ ሰደድኩት ፊቴን ወደሱ አዙሬ ነገሩ የገባው ይመስል ከሄደበት ሰመመን ብርግግ ብሎ እኔን ይመስለኛል በአይኑ ፈለግ ፈለግ አደረገኝ ብዙ ሳይለፋ ፊት ለፊቱ ተገጣጠምን ወደኋላ የላኳትንም እግሬን መለስኳትና አረማመዴን አስተካከልኩ ከዛ ግን ፊቱን ማየት ነው አቀባበሉ ልክ በቃ የናፊን አይነት ሆነብኝ ግን እንደ ማልነካውም አስቀድሞ አውቆታል መንገዳችንን ከመጀመራችን በፊት ናፊን ለምን አልመጣም ብዬ ጠየቅኩት እሱም እንዳልተመቸውና ቀጠሮ እንዳለበት ነገረኝ ቀጠሮው አስፈላጊ መሆን አለበት መቼም አዎ ነው ነበር ያለኝ ምን ሊለኝ እንደ ፈለገ ግን አልገባኝም ከሱጋ ስዛዛግ መሄዱን አልወደድኩትም እና << ላይብረሪ መሄድ አለብኝ ዛሬ እና...... ገና ሳልጨርሰው << ታዲያ ምን ችግር አለው ቤት አረፈድክ ተብሎ ሚፈጠር ነገር የለ >> << እሺ በቃ እንሂድ እንደዛ ከሆነ >> << እድለኛ ነኝ >> የሚል ድምፅ ከበስተ ኋላችን ተሰማ << የኔ ሀያት 🥰🥰🥰 የሱ ድምፅ ነበር >> << የኔ ሩህ ❤️❤️❤️>> እየተጠጋጋን አጠገቡ ደረስኩ << ብዙ አስሮጥኩህ አደል >> << አደለም መሮጥ ከዛ ያለፈ ነገርም አደርጋለሁ >> << እሺ ሀያቲ ቀጠሮው አስፈላጊ ከሆነ እኮ ባትመጣም አብሰንት አላረግህም ነበር 😊 >> << ከዚ ብኋላ እኮ ማላይሽ እስኪመስለኝ ነበር ትናንት የከፋሽ ወይስ መስሎኝ ነው >> << የገባኝ ነገር ይሄ አባባልህ ለኔ መሆኑ ነው >> << ማታገኚኝ መስሎሽ ነበር ሀያቲ አንቺም ጋር ተጋባ አሁን መልመድ ሊኖርብን ነው በቃ >> እሱ እያወራኝ አይኔ ግን ሪያድ ላይ ነው... እንደ ማልሰማው ገብቶት ነው መሰለኝ ፊት ለፊቴ ግትር ብሎ ቆመ << ምንድን ነው ምታይው >> ፊቱን ፍም አደረገው << ኧረ ምንም ልጁ ምን ሆኖ ነው ብዬኮ .......>> ሳልጨርሰው << ታዲያ እኔ እያናገርኩሽአ እንዴ 😡 >> << እሺ የሆነ ነገር በለው >> << ሪያዱ ምን ሆነህ ነው እ >> << ምን ማለት ነው ይሄ ያልከኝ ምን ነበር >> << ተረዳኝአ አላስችል ብሎኝ ነው >> << ተረዳሁህ በቃ እሺ በሉ >> << እንዴ ልትሄድ ነው >> አልኩት ፈጠን ብዬ << እንድሄድ ካልፈለግሽ አልሄድም >> << አዎ ኧረ ይደብራል >> << እ በቃ እሺ አሁን ላይብረሪ ወዳልሽው እንሂድ 😊 >> << እ እ እሺ >> ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ላይብረሪ ብዬ ያልኳትን ቅፅበት ጠላኋት እኔ አሳይመንቴን ለመስራት በሚል ስለሄድኩ እንዳንረብሽሽ በሚል ትንሽ ራቅ ብለው ነበር የተቀመጡት እኔም የሆነ ርእስ ይዤ ተመስጫለው እንደድንገት ቀና ስል የሆነች ልጅ ልታማልለው ይሁን አላቅም ብቻ ቆማ ማውራት ጀምራለች አይኔ አይዋሸኝም እጁን ልትካው ስትል ይቅርታ ብሎ ወደኔ መጣ እኔም የወሰደችብኝ ያህል አይኔ አነባ አቅፎኝ አብሮ ማንባት ጀመረ ናፊን ሳውቀው እንዲ አልነበረም የሆነ የተፈጠረ ነገርማ አለ የሆነ ነገር ላሳይሽ አለና በሚያምር ፅሁፍ ራህሚ ብሎ ፃፈ እኔም በምችለው መልኩ አሳምሬ ናፊ ብዬ ፃፍኩኝ ዳግም እቅፋ ውስጥ አስገባኝ እንውጣ ብሎ ተያይዘን ወጣን እጄን ከፍ አደረገና << ይሄ እጅ የሆነ ነገር አይገባውም ?>> << ምን ????>> የሚያምር የእጅ ብራስሌት አደረገልኝ << በረብ ይሄንን ስትታጠቢም ምንም ቢሆን እንዳታወልቂው እ እሺ >> << እሺ ሀያቲ አላወጣውም ቃሌ ነው >> እንዲ እያለን የቅድሟ ልጅ መጣች << ኦ ይቅርታ ካንቺ ጋር አልመሰለኝም >> ብላኝ ሄደች እኛም ብዙ ሳንቆይ ሄድን መለያየታችን የመጨረሻ እስኪ መስል ድረስ ገና ከመሄዴ ነይልኝ በአላህ አንዴ እያለ ሁለት ሶስት ጊዜ በተመሳሳይ መልኩ ይሄን አደረገ << ሀቢቢ ምነው ግን እ ችግር አለ እንዴ ?>> << አይ እንዲሁ ስለምትናፍቂኝ ነው >> እንባው እየታገለው ይቺን ቃል እንደ ምንም አወጣት ለምን እንደፈራሁ አላውቅም ግን በቃ እሱን የማላየው እየመሰለኝ ሁሌም ስለየው ዛሬ የመጨረሻዬ ነው እያልኩ ነው ግን የዛሬው በጣም ተለየብኝ እንዲሁ መለያየቱን እየፈራን አለቀ በቃ ተለያይተን በመንገዳችን ገባን . . . . . . . . . . ⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⨳⋕ይቀጥላል ...
نمایش همه...
// ክፍል 33 // ፀሀፊ ✍ ኒ ሀ ል #ራህሚ የኔ ሀያት እነዛን ነጫጭ ጥርሶቹን ብቅ ብቅ አደረጋቸውና እንደ ህፃን ፍልቅልቅ እያለ ከፊቴ ጠፋ እሱን እያሰብኩ ሆነ ጉዞዬ የኔ ነገር ዛሬም የማሚ << ተመለሽ !>> ሚለው ቃል ነው ከሰመመኔ የቀሰቀሰኝ << አይ ማማ ይሄን ነገር እየረሳሁ እኮ ተቸገርኩ😊 >> << ነይልኝማ ያይኔ አበባ >> << እሺ ማማዬ ቆይኝማ >> ብዬ ጫማዎቼን አወላልቄ ሄድኩኝ አጠገቧ << የሆነ ልትነግሪኝ ምትፈልጊው ነገር አለ ?>> << ኧረ የለም ምን ልልሽ እችላለሁ ?>> << ምንም አትይኝም ?>> << ምን ልበልሽ ማማ እ >> << የተቀየረ ነገር የለም ?>> << አዎ ማማ የለም በአሳይመንት ስላጨናነቁን ነው ሰላምታ ሳልሰጥሽ ምገባው በቃ ሰላቴን ልስገድ >> ብዬ እሳት ከሚተፋው ጥያቄዋ ዘወር አልኩ ___ አይኑን ለማየት የጓጓሁትን ያህል ምንም ቢመጣልኝ ያን ጉጉቴን አያሽርልኝም ትምህርት ቤትም አላስቆም አላስቀምጥ ነው ያልኳቸው <<ዛሬ ብሶብሻል የድሮዋን ራህሚ ነው ምንፈልግው >> እስኪሉ ድረስ ነበር ያዛኳቸው በነገሬ ላይ ለኢልሀሚ ጭምጭምታ ነገር ነግሬያታለሁ ለዚም እንደሆነ ታውቃለች ጭራሽ እሷም እኔኑ ቁጭ ሆነች በቃ አስተማሪው አልቀረን ተማሪ አዛ አደረግናቸው ትንሽም ቢሆን ጊዜውን ገፋ አደረግነው አንደ ድንገት ሆኖ ኢልሀሚ ፌንት ወደቀችብኝ አብዝታ መደሰትም ሆነ ማዘኗ እንድትወድቅ ያደርጋታል በሷ ሁኔታ እየተዋከብን ሀፊዛ መጥታ << ኧረ ሰዎች ይሄ ሙድ ተበልቶበታል >> ብላን ሄደች በሷ ቤት አፀፋ መመለሷ ነው እኔም ዝም ያልኳት ለ ናፊ የገባሁለት ቃል ስላለ ነው ☑️ ሀፊዛ ማለት የክፍላችን ተማሪ ናት ናፊን ታዲያ ከሚወዱት ሴቶች አንዷ ናት የሷ የባሰው ፈጣጣነቷ ነው እኔን በምሳ እንደ ሚያገኘኝ ታውቃለች እኔ መሄዴን አልረሳሁትም ግን ቲዲ ሚባል የተረገመ ትምህርት ከሱጋር ስዛዛግ አጅሬ ሆዬ ሄዳ ማናገር እኔም አላወቅኩም ነበር እና የጨረስኩ ሰአት ነበር የሄድኩት እና መታጠፊያው ጋር ስለነበር ድምጿ በደንብ ይሰማኛል << እና እንደነገርኩህ ነው ያየሁህ ቀን በቃ ይሄ ልጁ የኔ ....... እያለች ተረት ተረት ጀመረች << እሺ አፍወን ግን የኔ ሴት እየመጣች ነው ሳታይሽ ብትሄጂ >> << አይ እሷ አትመጣም አሁን የምታስረክበው ነገር ስላላት አደርስም አታስብ አሁን ንገረኝ >> << አሀ ምን ልንገርሽ ፕሊስ ካየችሽ ጥሩ አይመጣም >> << ከመጣችም መጣች ነዋ አያገባኝም >> << እንድነግርሽ ምትፈልጊውን ልንገርሻ ?>> << አው እሺ >> <<እሷ ማለት የኔ ሩህ ናት በቃ ከሷጋር አልሆነ በቀር ልቤ ከየትኛውም ስብርባሪ ጋር አይሄድም ቢሄድም ሚሆነው አንድ መጥፎ ሰው ምንም ማልጠቅም ነው ምሆነው ምክንያቱም ሩሄ እሷ ጋር ሆኖ እንዴት ጥሩን ነገር መስራት እችላለሁ እንዲ ነው ልገልፅልሽ ምችለው የኔን ሀያት >> << እሺ ሩህህ እንዳለች ሆና እኔን ሁለተኛ ወይም የሆነ ቦታ ......... ሳትጨርሰው << የኔ ሀያት አረፈድኩብሀ >>እያልኩ ወደነሱ ተጠጋው ከዛም እሱን አቅፌ ሰላም አልኩትና ለእሷም አስከተልኩ ግን የንቀቷ ንቀት እጄ ላይ ፊቷን አዞረች የኔ ሀያትም ሁለቱንም እጆቼ አዘርግቶ መሀል ላይ ራሱን አስገባና አቅፎ አንጠለጠለኝ <<የኔ አበባ >> _______ ይሄንን ይዛ ነው እኛማ እንግዲህ ብቻ አላህ ረድቶን ተሽሏት ተነስታልናለች የኔ ጀግና እንዲ እንድትሆን ስላደረኳት በራሴ አዝኛለሁ << ኢልሀሚ አሁን ደና ነሽልኛ ?>> << አትጨነቂ አው ደና ነኝ ታቂ የል >> << እሺ በቃ አሁን ተነሺ ወደ ቤት እንሂድ >> << ሰአት ደርሶ ነው 😳 >> << አዎ ሀያቲ ተነሽ በይ >> << እሺ ውድዬ ☺️☺️☺️ >> እንዲም እንዲያም ብሎ ቦታዋ ጋር ልንደርስ ትንሽ ቀረንና ኢልሀሚን መንገዷ መገንጠያ ጋር ትቻት ተመለስኩ . . . . . . . #################ይቀጥላል ......
نمایش همه...
// ክፍል 32 // ፀሀፊ✍ ኒ ሀ ል #ራህሚ ግን ግራ አጋብቶኛል የምሩን ነው ሚያስተዋውቀኝ አሀ ልጁ እኮ ናፊ ነው አደለም ከሰው ጋር ሊያስተዋውቀኝ ይቅርና መንገድ ላይ ማንንም እያየሽ አትሂጂ በቃ እኔን ብቻ እይኝ ሚል ልጅ እኮ ነው አሁን ተነስቶ ሰው አስተዋውቅሻለሁ ያለኝ ይሄንን እሺ ብዬ ብቀበል እንኳ አላመመኝም ብሎኝ ነበር ስጠይቀው ታዲያ ይሄ ሁሉ መዋሸት እና ማስመሰል ምን አመጣው ........ << ተመለሺና ሰላሙ አሌይኩም ብለሽ ጊቢ !>> ከሄድኩበት ሰመመን ተመለስኩና እ እሺ ማሚዬ << አሰላሙ አሌይኩም ...>> <<አው እንደሱ ወአለይኩም ሰላም ወራህመቱላህ ነይልኝ እስቲ እዚጋ >> ብላ በእጇ ቦታውን መታ መታ አደረገችው እዛው ጋር ተቀመጥኩ << ማሚዬ ግን ሰው እያየሽው ሲደብቅሽ ምን ታረጊዋለሽ ?>> << ምንአይነት መደበቅ ራህሚ ?>> << አሁን ለምሳሌ እንዳመመው እያወቅሽ አላመመኝም ስትባይ >> << ታዲያ ይሄኮ አንቺን ላለማስጨነቅ ነው እኔም ብዙ ቀን ብዬሽ አውቃለሁ ግን ልዋሽሽ አደለም እንዳትጨነቂ ነው >> << መሆኑ እያስጠላሽ እንዲሆን ምታደርጊው ነገር አለ ?>> << አዎ አሁን ለምሳሌ ቤት መቀየር አልፈልግም ከጠየቅሽኝ ምጠላው ነገር ቢኖር እቃን ማንከራተት ነው 😁 ግን ከዚ የተሻለ ቤት ቢኖር መሄዴ አይቀርም ምክንያት ካልሽኝ ለሁሉም ስለ ሚበጅ >> ገባኝ ባንቺ ትርጓሜ ለኔ ሚበጀው እሱን መተዋወቅ ነዋ ~~~~ ከራሴ ጋር ነበርኩ << ምናልሸ ራህሚ >> << አይ ማሚዬ ላንቺ አደለም >> << አሁን ተነሺ ሰላት አያምልጥሽ >> << እሺ >> ብዬ ለመስገድ ተነሳው ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️ ዛሬ ልቤ እየፈራ ነው የምርም ሚያስተዋውቀኝ ከሆነ ማም እንዳለችው ከሆነ 😢 እያልኩ ብዙ ተጨናነቅኩ መምጣት ከነበረበት ሰአት ቆየ ነገር ግን እኔ እየጠበቅኩት ነው በስተመጨረሻም መጣ ግን እንደ ፈራሁት የሆነም ልጅ አብሮት አለ ቢረቢ ናስ አሁን እሺ ምን ላደርግ ነው አጠገቤ ደረሱ እና ቀለል ለማለት እየሞከርኩ ነው ናፊ ሁለት እጆቹን ዘርግቶ እቅፉ ውስጥ አስገባኝ ምን ሆነ ልጁ እስክል ድረስ አገላብጦ ሳመኝ መልቀቅ ራሱ አልፈለገም ወደ ጆሮዎቼ ተጠጋና << እንደዚህ እንቆይ ለትንሽ ደቂቃ ?>> አለኝ እኔም እሺ ብዬው ቆየሁ ግን አስተቃቀፉ ምቾት አልሰጠኝም ጥብቅ አርጎ ነበር የያዘኝ የት ምሄድ ይምሰለው እንጃ ብቻ በዛ ሀል ትንሽ ቆየን ከዛ የሆነ ብንን አለና ወይኔ ሪያድስ ? ብሎ እኩል ወደ ኋላ ዞርን ጭንቅላቴ ምን ሊያስብ እንደሚችል ታዘበ ሚገርመው ግን ልጁ እንደ ፋንዲሻ ፍልቅልቅ እያለ መሳቅ ጀመረ << አንተ አጁዛ አትሳቅ ባክህ እዚ አለው አትልም እንዴ ?>>አለው << አሀ አብረን አ እንዴ የመጣነው በነገራችን ላይ ተሳክቶልሻል >> << ምኑ >> ብዬ ፈጣን መልስ ሰጠሁት << ማስፈቃቀሩ ነው ሚባለው ብቻ እኔ ለማንም እንዲ ሲሆን አይቼው አላውቅም ወረብ አሀ እኔን ረሳኝ እኮ 😁😂>> << እኔ ምለው ተዋወቃቹ ግን እ ?>> << አውቃታለሁ እኮ እኔ ግን ያው ካልክ አይቀር >> ብሎ ሁለት እጆቹን ለማቀፍ አመቻችቶ ይዟቸው መጣ ናፊ በመሀል ገባና ታቀፈለት እኔ እዛው ድክም 😂😂😂አልኩ << ውይ አህባቢ እሷኮ ወንድ አታቅፍም >> << እኔም ጠርጥሬ ነበር >> << ምኑን ?>> << ወንድ አለመ......😁😂 >> በቃ አልቻልኩም እኔ መሬት ላይ ቁጭ አልኩና ሆዴን ይዤ ነፈርኩ ሁለቱም ወደኔ ዞሩና አይን አይኔን ማየት ጀመሩ ጤነኛ ናት ወይ ነው ሚመስለው ብዙ ሳቅኩ መሰለኝ ሆዴን አመመኝ ከዛ ገና እያስታወስኳቸው ድጋሚ መሳቄን ጀመርኩ ናፊ እንደኔው ተቀመጠና ፊቴን መዳበስ ጀመረ የምር የቀወስኩ እንደ ምመስል አልገባኝም ነበር ወዲያው ሳቄን ገታ አድርጌ << እህ እህ ሀቢቢ ምነው ? >> << ደና ነሽልኝ አደል 🥺>> << አው ምነው ግን ጤነኛ አልመስል ብዬህ ነዋ ?>> << አይ እንደዚ ስትስቂ ቀለል ይለኛል ለዛ ነው>> << አንተን ቀለል ይበልልኝ እንጂ ሁሌ እስቃለሁ እሺ 😘 >> << እሺ ውድድዬ አሁን ይሄን ቀውስ ተዋወቂው>> << እሺ ቆይ አንዴ ያዘኝ ልነሳ............. ራህመት እባላለሁ >> << እሺ ራህሚ እኔን ሪያድ ብለሽ ጥሪኝ ከፈለክሽ ግን ዬ ጨምሪበት ያለዚያ አይቆላመጥም 😇😂😅 >> << 😁 እሺ ሪያድዬ >> ናፊ ሊናደድ እንደ ሚችል ችላ አልኩ መሰለኝ ዞር ብዬ አየሁት አይኖቹ እንባ ቋጥረዋል ቅድም የነበረው ፊት አልነበረም ጭራሽ ብዬ ብዬ ጥዬው ነበር የሄድኩት << ናፊዬ የኔ ሩህ ምንሆንክብኝ መቼ እንዴት በምን አይነት ቅፅበት እንደሆነ አላቅም ብቻ ደረቱ ላይ ለተመኝና ማልቀስ ጀመረ እኔኮ አንቺን ማጣት አልፈልግም ለምን ግን ራህማኑ ይሄንን ፈቀደ ለምን ፃፈልኝ ነገሩ አልገባኝም ግን አብሬው ማልቀስ ጀምሬያለሁ ቀና አደረገኝና የኔ ሀያት አንድ እንባ በኔ ምከንያት እንዳታነቢ እሺ ወደፊትም ቢሆን እያለ አንድ በአንድ እንባዎቼን መጥረግ ጀመረ << አሞሀል አደል እንዳልጨነቅ አትነግረኝምአውቃለሁ ሁሉንም ነገር አትደብቀኝ ይሄኮ ለማንም ግልጽ ነገር ነው  ደሞ.....>> ሳልጨርሰው << እ ምንድን ነው ምታቂው ንገሪኝ ?????😳😳😳😳>> << አታካብዳ አሀ ደሞ ደነዝ ነው እንዴ ምመስልህ ደነዝ ምትለውም ያውቀዋል ይህንንማ እሺ አሁን ንገረኝ ምንህን ነው ያመመህ  ?>> <<ኡፉፉፉ ኧረ የምር ምኔንም አላመመኝም ነስሩ በቃ ከተፈጥሮ ነው ስወለድ ጀምሮ >> (የሆነ እየዋሸኝ እንደሆነ ስድስተኛው ስሜቴ ነግሮኛል ) << ኧረ ውይ እኔኮ ያመመህ ነበር የመሰለኝ >> ላለመጨቃጨቅ ነው እንዲ ሚፈልጋትን መልስ የሰጠሁት << አላመመኝም አታስቢ >> ዱዝ እየዋሸኝ መሆኑኮ ያስታውቃል ባለፈው አሞት ነዋ ያልመጣው ነስሩን ነበራ መልስ ይሁንሽ ያለኝ ታዲያ ዛሬ ምንድን ነው ሚለኝ << እኔ ምልሽ ሰፈርሽ ከዚ ይርቃል ራህሚ>>ሪያድ ነበር << እ ያን ያህል አይርቅም ደርሰናል ኧረ  እንደውም >> << ምልሽ ገጠር ነው ሚመስለው ሰፈራቹ😉😂>> << ዱዝ መርካቶ በላት እኮ ምን ታውቃለህ ለነገሩ 😞😁>> << በቃ ምታቂያት እሷ ነችኣ >> << አደለም ግን ለፒያሳም የአንድ ታክሲ መንገድ ነች እኮ << ታዲያ ለዚህ ብቻ ነው ገጠር ማትሆነው ?>> << አዋ ቀልድህ መሀል ከተማዋ ቅርቧ ናት እያልኩህ ነው እኮ ያለሁት >> << እንዴ መሀል ከተማዋ ፒያሳ ናት እያልሽኝ አደለም አ >>
نمایش همه...
<< በመሰለኝ አይሰራማዋና ከተማዋን አላቅም ንገረኝ ይባላል >> << እ ማን ናት ልትል ነው > <<እንደዛ አደለም ሚባለው ንገረኝ ደደብ ነኝ አላውቃትም እንደዚ እስቲ በይው 😂😂😂😅🤣🤣 >> << አትንገረኝ ዱዝ አልፈልግም >> << በቃ ድድብናሽ ይቅርና እንዲ በይ>> <<😳 >> << ለወሬ ሞች ነኝ በይ ከዛ ልንገርሽ ወላሂ >> << ቀቅለህ ብላው ዱዝ >>😂😂😂 እንዲ እያዛገኝ ቤት ደረስን ናፊ ስለዋሸኝ ቅጣቱ ነው ያላናገርኩት <<  አሁን መሰናበቻ ሰአት ነው ሰውዬው >> << ግቡ ሻይ ብና ምናምን ይባላል እሺ ለሌላ ጊዜሽ 😁>> << አንተን አስገብቼ እኔ ከቤት ልወጣ ያሰብኩት ቀን እልሀለሁ >>😁 << በይ በቃ ትናፍቂዋለሽ >> ዞር አልኩ ወደ ናፊ  አየሁት ግን እያየኝ አልነበረም እሱን ሳየው ሳያየኝ የመጀመሪያው ነው ናፊ አኮረፍክ እንዴ ብዬ ከአንገቱ ቀና አረኩት አይኖቹ የተራቡኝ ነው ሚመስሉት እዚም እዛም ያተራምሳቸው ጀመር <<  ገና ከአሁኑ ልትረሺኝ ነዋ አደል >> << አንተን ነው ምረሳው ወላሂ መቼም አልረሳልህም እዚጋ እዚጋ ( ደረቴን እየነካው )እዚ ውስጥ ነው ያለኸው እኮ እንዴት ያስችለኛል >> ምን እንደሆነ እንጃ ግን አልቅስ አልቅስ ሚለው ነገር አለ መሰለኝ ውስጡ እኔን ሲያየኝ ሁሌ ቢያለቅስ ይቀለዋል ካልሆነ ደምስሮቹ ግትርትር ይላሉ << ግን መቼም እንዳትረሺኝ እሺ እኔ የትም ብሆን ጀሰዴ እንጂ ሁሉ ነገሬ አንቺ ጋር ነው እንዳትረሺ እሺ>> << እሺ ሀያቲ መቼም አልረሳም >> <<ነይልኝ የኔ ህይወት >> አለና አጥብቆ እቅፋ ውስጥ አስገባኝ << ናፊ የኔ ሀያት ልትለየኝ ነው እንዴ ?>> << አላደርገውም አላህም አይበለው>> አለኝ እንባ በተናነቀው ድምፅ አሁን  ወላሂ አሁን እያመመኝ መጣ ከዚ ብሀላ ማላየው ነው እየመሰለኝ ያለው ብቻ አላህ ለኸይር ያርግልኝ ከአይኔ እስኪጠፋ ድረስ ቆሜ ሸኘኋቸው መታጠፊያው ላይ ናፊ ሁለቱን እጆቹን ከንፈሩን አስነክቶ ወደኔ መለሳቸውና ኡፍፍፍፍ አላቸው እኔም ወልዬ ተቀብዬው አፀፋውን መልሼ ድጋሚ ኡፍፍ ብዬ ላኩለት የኔ ሀያት እነዛን ነጫጭ ጥርሶቹን ብቅ ብቅ አደረጋቸውና እንደ ህፃን ፍልቅልቅ እያለ ከፊቴ ጠፋ . . . . . . . . ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️#ይቀጥላል
نمایش همه...
// ክፍል 31 // ፀሀፊ ✍ ኒ ሀ ል #ራህሚ እናቱ የራሷን ምርጫ መርጣ አጋብታዋለች ለዛ ነው ደሞም እራሱ ነው ይህን ያለኝ እስካሁንም የቆየሁት ለሱ ብዬ ነበር ይገርማል አንተ ብዙ ሚስጥር አለህ ብትበረበር << ይመስለኛል 😁 >> አለና እቅፍ አርጎ ውስጡ ወሸቀኝ ያው ይሄ የመታረቃችን ብስራት መሆኑ ነው ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️ ከዛች ቀን ቡሀላ ምንም አጣልቶን አያቅም መንገድ ላይ ከሚያዩኝ ሰዎች በቀር የማላቀቸው ሰዎች ናቸው ግን ሚሆነውን ነው ሚያሳጣው ሆኖም በዚህ ሰሞን መምጣት እየደበረው ይሁን ብቻ አላውቅም መምጣት አቁሟል ብል ይቀለኛል በሳምንት አንዴ ወይም ሁለቴ ቢመጣ ነው ምን ማድረግ እንዳለብኝ ግን እንጃ ዛሬም ከመጣ ነው እንግዲ ከት/ቤት ተለቀናል ሌላ ጊዜ ምጠብቅበት ቦታ ላይ ሆኜ እየጠበቁት ነው ግን አንዳችም ዝር ሚል ነገር የለም በመጨረሻም ተስፋ ቆርጬ መንገዴን ጀመርኩ መሬት መሬት እያየሁ ነበር አካሄዴ ሳላስበው ፊትለፊቴ መኪናው ገባና ሲጢጢጢጥጥ................. ሚል ድምፅ አሰማ ቀናም ብዬ ሳላይ መንገዴን አስተካክዬ ለመሄድ ወደ ቴራዞው እግሬን ሰደድኩ ግን መኪናው አልተንቀሳቀሰም እንደውም ይባስ ብሎ የሆነ መልኩ ለአይን ሚስማማ ወፎች ሚዘምሩለት ውበቱ ከፀሀይ ከራሷ ጋር ማይወዳደር አይምሮን የሚይዝ አይነት ልጅ ከውስጡ ወጣ ወደኔ ነበር የዞረው ገና ፊቱን እንዳየው የኔ ፀሀይ መሆኑ ገባኝ የዛሬው ሚለየው ልቤ ነበር ገፍትሮ ያጣበቀኝ እሱም አፀፋውን መለሰልኝ አይን አይኔን ማየት ጀመረ የኔ ሀያት እንዲ ሲያየኝ ነው እንደ ሚሳሳልኝ ማቀው አደለም ለኔ ለማንም ይታያል ዛሬ በመጣበት መኪና ነው እየሄድን ያለነው አልገባኝም ነገሩ እንደ ህፃን ልጅ አኮረፍኩት እንደ ለመድኩት ቸኮሌቴን ሰጠኝ << እንዲ ማይሆን ልምድ አስለምደኸኝ የት የት ነው ምትጠፋው ?>> ቸኮሌት እንደ ራሴ ያን ያህል አልወድም ግን ናፊ በጣም ነው ሚወደው እና እኔ ምንም ምክንያት የለኝም ምጠላበት በጣም ከመውደዴ የተነሳ በቀን እሱ ካለ 10 ካልሆነ የቻልኩትን << ወላሂ በጣም ነበር የናፈቅሽኝ 🥺>> << አሀ ገባኝ ናፋቂም ይረሳል ለካ 🤥>> <<የምር በረቢ እንዲ ስትይ ድጋሚ እንዳልሰማሽ >> << እሺ እሺ ግን ንገረኛ ለምንድን ነው እየጠፋህ........... ብዬ ሳልጨርስ ይነስረው ጀመር ኢላሂ የመአት ሶፍት አወጣ አልገባኝም ይሄ ሁሉ ለዚ ማለቴ ለነስሩ ነው ወረበል ደንግጫለሁ ግን ሶፍቱ የምር ከልቤ አስገርሞኛል የሆነ አስቦ ነው ያደረገው ሲቀጥል ደሞ እየጠረግነውም አያልቅም ደሙ ይፈሳል እንደው ይግረምሽ ብሎ ይሁን አላውቅም ያ መአት ያልኩት ሶፍት አልቆ ሾፌሩ ሌላ ገዝቶ መጣ እንደምንም ብለን ማስቆም ቻልን << ቅድም ለጠየቅሽኝ መልስ ነው ዛሬም ከ ማማ ጋር ተጣልቼ ነው የመጣሁት >> << አፍወን ግን አንተን ማየት ያስፈልገኝ ነበር እኮ 😧>> << እሱማ ሳይገባኝ ቀርቶ አደለም ግን ፀሀይ ስለሆነ እንደዚህ እንዳይፈጠር ብላኮ ነው ደሞ ማስተዋውቅሽ ሰው አለ>> << ማንን ነው ምታስተዋውቀኝ ?>> << ሪያድን >> << እንደከበደህ ያስታውቅብሀል ምንም ለመደበቅ አትሞክር ደሞ ከመቼ ጀምሮ እ >> << በአላህ ምንም አትበይ በቃ አስተዋውቅሻለው እሺ በይ >> << እንደዛ ከሆነ እሺ >> << ፈጠንሽ በጣም እ 🤬>> <<🤭😄 እንዲ ነው ያቃጠልከኝ እ 😉¡>> <<😂😂😂 የኔ ተንኮለኛ በቃ ያንቺን ስሜት መጋራት ግድ ይለኛል ማለት ነዋ ☺️>> << አዋ ቀልድህ በቃ አሁን ልሂድ እ ከዚ ቡሀላ ቅርብ ነው ቤት ለመግባት ካልሆነ በቀር 😌>> << እሱስ መች ይቀራል ግን እንዳረሺ ያልኩሽን እሺ ሩሂ ውድድድ አረግሻለሁ >> << እኔም ከልቤ ነው ውድድድድ ማረግህ አረሳውም ካልክ ይሁና እሺ >> . . . . . . . . . . ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️#ይቀጥላል...........
نمایش همه...
// ክፍል 30 // ፀሀፊ ✍ ኒ ሀ ል #ራህሚ << ሀያቲ እኔስ ያላንተ ያስችለኛል እንዴ >> ( አይኑ ላይ ማየት ምፈልገውን እየፈለግኩ ) ጠየቁት << እሱንማ አቃለው እና ግን ያደረኩትን ብነግርሽ እንጃ ምትቀበይው አይመስለኝም >> << እሱን ለኔ ተውልኝና አንተ ብቻ ንገረኝ >> << እሺ ማይሊኝ >> << አይ እንግዲህ አታናደኝ ንገረኝ >> << እሺ እሺ በቃ ይኸው ልናገር ይሄ መኪና የኔ ነው >> << ማለት 😳>> << እይኝማ አሁን ተረጋጊ ከዛ ልቀጥል >> << እየሰማሁ ነው ቀጥል >> << እሺ እና የሚነዳው ልጅ የሰፈር ጀለሴ ነው ረዳቱ ጋር ያን ያህል አንተዋወቅም ወረብ ይሄ ነው እውነቱ ምንም አልደበቁሽም >> << ምኑን ነግረኸኝ ነው ቆይ ያንተ ነው እሺ አወቅከው ከዛስ ረዳቱን አታቀውም እሺ እና ምን አደረክ አልገባኝም >> <<በቃ አውቄ ነበር ይሄን ሁሉ ያደረግኩት >> << ከመጀመሪያው ጀምሮ ነው ? >> << አው ስልሽ የመኪናውን >> << የወደቅከው ምናምን እሱ ......?>> << አው የወደቅኩት የሳምኩሰሽ በቃ በግልጽ እሺ ብለሽ እንደማትሳሚልኝ አውቃለሁ ለዛ ነው >> << እኮ አንተ የስሜትህ በልጦብህ ማለት ነው እ ? >> << እንደዛ አትበይ እንዲ እንደማይሆን በደንብ ታውቂያለሽ >> << ታዲያ ምንድን ነው ምትለኝ ?>> << በቃ የሆነ አጋጣሚ ላይ እኔ ካንቺ ጋር ልሆን አልችልም ለዚ ነው በቃ >> ( አምልጦት ነው ሚመስለው ) << እ ምን ማለት ነው ቆይ ይሄን ነገር በጣም ደጋገምከው አታወዛግበኝ እና በስነስርዓቱ አስረዳኝ >> << እ እ ማለቴ አው ሁሉንም ነገር አላህ አደለም ሚያቀው ዛሬም እኮ ልሞት እችላለሁ አደል ለዛ ነው ሲቀጥል ደሞ ሁሉንም ያደረግኩት አውቄና ፈልጌ ስለሆነ ይቅርታ አጠብቂ << ጥሩ እሺ >> ( ይሄን ብቻ ብዬው ቀጥ ብዬ ከመኪናው ወጣው ) ለሱ ማይረባ ድራማ ተብሎ ቤት ያሉት ሰዎች ምን እንደ ሚሉኝ ረስቼዋለው ብቻ አላህ ይርዳኝ እንደፈራሁትም ሁሉም ነበር የወረደብኝ ....... ግን ይበለኝ የራሴው ጥፋት ነው ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ እና ይኸው ተጣልተን ቀረን በመንገዴ ላይም ላለ መታየት የሚያደርጋቸውን ጥረት ሳላደንቅ አላልፍም አይኔ እሱን እየተራበ እምቢ ብሎ እንጂ መች አንጋጦ መሄዱን ፈለግኩት ግን አይኔ ባያስቸግርና ባያየው ኖሮ ናፍቆት በሚባለው በሽታ ተቃጥዬ እገኝ ነበር ያው አሁንም ናፍቆኛል ግን ቢያንስ ይሻላል እሱ ያልተገኘበት ብዙ ቀናቶች እንደ ቅጠል ረገፉ የደረቁ ሆነው ዛሬም ከዚህ የደረቀ ቀን ጋር አፋጦኛል ቀኔን እየረገምኩ ወደ ት/ቤት አዘገምኩ በተለይ ስሄድ ይከብደኛል ስመለስስ እሱን አላጣውም ጠዋት ባገኘው ብዬ ሁሌም ነው ምመኘው ምከንያቱም እሱ የቀኔ መብራት ነው እሱን ካየሁ ወዲ ቀኔ ይፈካል ት/ቤት ውስጥ ነኝ ግን የምር ተማሪ አልመስልም የ4 ልጆች ያሉባት ምታበላ ምታጠጣቸው የሌላት እናት ነው ምመስለው መልኬ ብሎ ላየኝ ብቻ በዞረበት ዞሮ ትምህርት አለቀ የነፃነቴን አዋጅ ሀ ብዬ አወጅኩ ቶሎ ለመውጣት ካለኝ ጉጉት የተነሳ እርምጃዬ ሩጫ ነው ሚመስለው እንደዛ እየተራመድኩ መታጠፊያው ጋር ደረስኩ ከመታጠፌ በፊት የተከበረ ሰው ምገናኝ ይመስል ራሴን አቆነጃጅቼ ምንም እንዳልቀረብኝ ካየሁ በኋላ ታጠፍኩ ገና ከመታጠፌ ፊት ለፊቴ እንደ ጅብራ ከተገተረው ልጅ ጋር ተገናኘን እንዲሁም ዝም ብሎ ልብ ተብዬው እየመታ ነው ከልቤ አስደነገጠኝ የአይን እርግብግቢቴን አንድ ሁለት ተርገብግቦ ዞር ስል ጅብራው ልጅ ናፊ ነበር ገና ሌላ የልብ ምት ከድሮውም የማን እንደሆንኩ የሚያውቀው ልቤ ^^ዷ^^ ^^ዷ^^ ^^ዷ ^^ የሚል ድምፅ ማሰማቱን ተያያዘው እየገፈተረኝ እንደሆነ ሰው ሚያውቅ እስኪመስለኝ ነበር የመታው ግን አጋጣሚ ስለሆነ ነው ሚመስለኝ አቅጣጫ ቀይሬ መራመዴን ጀመርኩ አስቆመኝ እና ብዙ ተጨቃጨቅን አው እኔ እሱ ሚላቸው ነገሮች ሳይገብኝ ቀርተው አደለም ሲያወራ ማዳመጡ ናፍቆኝ ነው በመጨረሻም በ አንድ ነገር ተስማማን እንዴት እንዳገኘኝ እንደ ሚነግረኝ ተስማምቶ ነበር በመጀመሪያ ግን ሀሳቤ የነበረው በባለፈው ቀን ስለሚያወራው በሽታ እንዲነግረኝ ስጠይቀው ምንም በሽታ እንደሌለበት አስረግጦ ነገረኝ ያው ባያሳምነኝም እሺ ነበር መልሴ አስከትዬም ይሄንን ጥያቄ ነበር የጠየቁት አሁን እንደ ሚመልስልኝ ነግሮኝ የሆነ መናፈሻ ገባን ቦታ አመቻችተን ከተቀመጥን ብሀላ ስለ ነገሩ መተረክ ጀመረ ........... እኔ ማውቅሽ ሰባተኛ ክፍል እያለሽ ነው እና የዛኔ አሚር ሚባል ልጅ ታውቂዋለሽ አደል? አዎ ብዬ አንገቴን ወደ ላይና ታች አደረኩት ትዝ ይለኛል አሁንም ድረስ የባቻችን ቆንጆ እሱ ነበር አሚሬ በጣም ይወድሽ ነበር እና ሁሌም ወሬው ስላንቺ ነበር ያወራቹትን ሪከርድ አርጎ አምጥቶ ያሰማን ነበር ሳታስቢውም ፎቶ ያነሳሽ ነበር ሁሉንም ሚያደርገው ፍቅሩን ሳይገልፅልሽ ነበር እና እኔንም ቀስ እያለ የዚህ ነገር ሰለባ አደረገኝ እኔም ድምፅሽን ሳልሰማው ስቀር እታመም ጀመርኩ የሞተው ሀያቴ ያንቺን ድምፅ ሲሰማ ሀይ መሆን ጀመርሽ የልቤን ወለል ሞላሽው ቃላቶችሽ አልሰለች አሉኝ ሌላ ሪከርድ ቀድቶ እስኪመጣ ይሄንኛውን አልጠግበውም ቀድቶ ሚመጣው እኮ ከ ሶስት ወይም ከ አራት ቀናቶች ብሀላ ነበር ድሮኮ ታቂያለሻ በስልክ አደለም ምንቀዳው የሆነች አለች በሷ ነበር እና እንዲ ነበር የማውቅሽ እልሻለሁ ከተመስጦዬ ብርግግ ብዬ እና የጓደኛህን ፍላጎት አትጠብቅም እንዴ ? ከሱጋር ስለማትገናኙ ነው እና የሆነ ጊዜ በሆነች አጋጣሚ ላንቺ ያለኝን ፍቅር ለ ፎቶሽ ስገልጽ ሰምቶኛል ግን እሱ ነው ይሄንን ያለኝ ያኔ አልተገጣጠምንም ነበር እናም ግን እናቱ የራሷን ምርጫ መርጣ አጋብታዋለች ለዛ ነው ደሞም እራሱ ነው ይህን ያለኝ እስካሁንም የቆየሁት ለሱ ብዬ ነበር ይገርማል አንተ ብዙ ሚስጥር አለህ ብትበረበር . . . . . . . . . ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️#ይቀጥላል .............
نمایش همه...
// ክፍል 28 // ፀሀፊ ✍ ኒ ሀ ል #ራህሚ ሰዉ........ .ሰዉ የሁለት ፊደሎች መጠሪያ የሆነ ግን በዉስጡ ብዙ የህይወት ምስቅልቅል የያዘ ትርጉም ነዉ ....ሰው ማለት ክቡር ፍጡር ነው፡ ከሰው በላይ ተውቦና ተከብሮ የተፈጠረ ፍጡር የለም፡፡ አላህ በተከበረዉ ቁርአኑ እንዲህ ይላል :- ወለቀድ ከረምና በኒ አደመ ወሀመልናሁ ፊል በሪ ወልበህሪ """"""የሰውን ልጅ አክብረንና አልቀን ፈጥረነዋል በባህርም በየብስም እንዲንቀሳቀስ አስችለነዋል"""" መልካም ስራ ሰርተው ጀነትን የሚወርሱ ሰወች ከመላኢካ በላይ ናቸው ምክንያቱም ጀነት ውስጥ ሲቀማጠሉ በተድላ ሲሞሉ ዝቅ ብለው የሚታዘዟቸው መላኢካወች ናቸውና እንኳን ሰውና በዚህ ምድር ያሉ ፍጥረታቶች በሙሉ እንደ እናንተው ፍጡር ናቸው ብሎ ሙሉ መብት ተሰጥቷቸዋል ፡፡ መቸም የሰው ልጅ ሁሉም ታሪክ አለው ጧት ተነስቶ የሚንቀሳቀሰው ሁሉ የእለት ታሪኩን በማህደሩ ላይ እያሰፈረ ነው፡፡ አቅም አጥቶ የሚለምነው ሀይል ኑሮት የሚቦርቀው አዛን ሰምቶ ወደ መስጅድ ገብቶ የመሰግደዉ እና የዱንያ አላማ ይጠቅምብኛል ብሎ መስገድ የሚተመው፡ ክርስቲያኑም የሚፀልየው፡ ሌባውም የሚሰርቀው ፡ መሪ ሆኖ የሚመራው፡ ታሞ አልጋው ላይ የቀረው ፡ አግኝቶ ያጣዉ፡ ሁሉም ፍጡር የራሱን ዲያሪ አዘጋጅቶ ባይፅፈውም ነገር ግን የእሱን ታሪኮች ልቅም አድርገው አንድ ሳያስቀሩ የሚመዘግቡለት ረቂብ እና አቲድ የሚባሉ የመላኢካወች ወኪሎች አሉት ፡፡ እኛ እዚህ ምድር የምንፅፈው የምናውቀውን እና የምናስታውሰውን ነው፡፡ ስንት የማናውቀው አላህ ጋር ተመዝግቦ የዕኛን ማለፍና መውደቅ ከባድ ሚና የሚጫወት ፈጣሪህ ጋር ሙተህ ተቀስቅሰህ ስተናገኝ በቀኝ ወይንም በግራ እጅ ልንቀበለው የምንችል የስራ ውጤታችን አላህ ዘንድ ተዘጋጅቷል፡፡ ይሄም የሚሰጠን መፅሀፍ እኛዉ የተናገርነዉ የተፃፈዉ አሪፍ ከሆነ በቀኝ እጃችን የስራ መዝገባችንን ተቀብለን....ሰወችን በደስታ አንብቡልን ብለን የምንጋብዘው ወደ ጀነት የምንገባበት ሲሆን .....ደግሞ በተዘዋዋሪ ዛሬ ላይ በቀልድ የምናወራዉ ..ሰዉ የምናማበት ..የማይጠቅም የማይጎዳ ንግግሮች አብዝተን ተዉበት እስቲግፋር ሳናደርግ የተፃፈዉ መጥፎ ከሆነ የስራ መዝገባችን ሳንወድ በግዳችን በግራ እጃችን ተቀብለን ..ዋ ጉዴ ዋ ኪሳራየ ምነው የስራ ውጤት መፀሀፌን ባልተቀበልኩት ??ብለን የምንፀፀትበት ዋና መዝገባችን ወደፊት ይሰጠናል..አላህ ይጠብቀን ...አላህ ለሁላችንም ከቀኝ እና ከግራ ያስቀመጣቸዉ መላኢካዎች አሉ ረቂብ እና አቲድ ረቂብ ኸይር ነገር ስንናገር ቶሎ በደስታ እንደሚፅፍ እና በተዘዋዋሪ አቲድ ደግሞ ወንጀል መጥፎ ነገር ስንናገር የአሏህን ቅጣት ጀሀነም እሳትን አስታዉሶ ጊዜ ልስጠዉ በተናገረዉ ነገር እስቲግፋር ያረግ ይሆን ??ብሎ ይጠብቀናል..ነገር ግን አቲድ ስቲግፋር ሳናደርግ ስንቀር አንዴ ከአላህ ታዟልና የስራ መዝገባችን ላይ ይፃፋል፡፡ አላህ የዛን ጊዜ ከከሳሪዎቹ ሳይሆን ከሚደሰቱት በቀኝ እጃችን የስራ መዝገባችንን የምንቀበል ያድርገን፡፡አሚን ያረበል አለሚን እኔም በህይወቴ ብዙ ቅጣቶችን ተቀጥቻለው በምንም አይደለም በፍቅር ነው እንጂ ብዙውን ማንነቴንም ያወቅሁት አልቃሻ አፍቃሪ አፍቃሪም ነኝ የምር የልቤን በር ለመክፈት ምንም ቁልፍ ራሱ አላስፈለገኝም ነበር ወለል አርጌ ምንም ተቀናቃኝ ሳያግደኝ በንፁህ ዘር አብቦ ብዙ ፍሬ እንዲያፈራ ነበር ሀሳቤ ግን አልሆነም አሁን ላይ ናፍያድ ሚባል ልጅን ለመርሳት በመሞከር ላይ ነኝ ግን የገዛ ጆሮዬ ራሱ እያስተጋባ ስንቴ አቤት እያልኩ እንደምዞር ምግብም አይጣፍጠኝም ብቻ ማይሆን አህዋል ላይ ነኝ ፨፨፨፨፨ለምን ????????? ይሄ ሁሉ እያላችሁ ይሆናል ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ ሁሌ እንደምናደርገው ታክሲ በመጠበቅ ላይ ሳለን በሚያስገርም መልኩ ቶሎ ታክሲ መጣና ገባን መጨረሻው ላይ ነበር የተቀመጥነው እሱ ደሞ ከጎኔ ሆኖ እኔ ከሱም ከ መስኮቱም አጠገብ ነበርን እናም እንደ ቀድሞው እያወራን ብቻ ማይሰለች አንደበት ነው ያለው እኮ ወረብ መጠን ያወራል ግን በቃ ከቀልብ አይጠፋም ብቻ በመጨረሻም መውረጃችን ደረሰና ሁሉም ወረደ እና የመጨረሻዎቹ እኛ ነበርን እናም ቀና ሲል የመኪናው አንፓሉ መታ አደረገውና ወደቀ ምን ማረግ እንዳለብኝ ግራ ቢገባኝ እግሬ አልንቀሳቀስ ቢለኝ ቆሜ ቀረሁ ረዳቱ ነው ምን ብሎኝ እንደሆን እንጃ ብቻ እንደምንም ብዬ ምን ማድረግ እንዳለብኝ ጠየኩት ብቻ ጫቴን በተርዚናው ወጥሮ ጉንጩን ተርትረን ካልወጣን ከሚሉት የጫት ቅርጣፊዎቹ መሀል እያሳየኝ ውሃ ይዞ መጣና ረጨነው ሆኖም ሊነቃልን አልቻለም ብዙ ሞከርን ነገር ግን ንቅንቅ ሚል ነገር አልታይ አለን ሰውየው ከአንድ ቦታ የሱ አለመነሳት ከሌላ ቦታ ሲያጨናንቁኝ በስርዓቱ ማሰብ አስቸገረኝ ናፊ አሁን ላይ ትንፋሹ ቁርጥ ቁርጥ ማለት ጀመረች በቃ ሚሞት መሰለኝ << እያየሁህማ እንዳታረገው በረቢ ሀቢቢ >> ለራሴ በድን ለታቀፈው እኔነቴ ይሄን ቃል መደጋገም ጀመርኩ ሆኖም ለውጥ የለም ማቀው የቀረኝ የቁርአን አያህ የለም እየደገምኩት ቢሆን እንጂ <<እሺ ምን ላርገው አይኔ እያየ... >> ብዬው ሳልጨርስ በዚሁ መሄድ እንደምንችል አሰብኩ << በረቢ ባልከው እስማማለሁ ወደ ሆስፒታል አዙረው >> << ሀሳቡ አሁን ነው የመጣልሽ ኧረ ባትከፊኝም አደርስሽ ነበር አልችልም መንዳት ደሞ ባሉካው የ ልጁን ት/ቤት ደሞዝ ሊከፍል ባንክ ገብቷል ሲመጣ እንሄዳለን >> <<እሺ አሁን ምን ላድርግ እ ምን ትመክረኛለህ >> << አሀ ትንፋሽ ስጪው እንጂ ከገባሽ አላቅም ግን ትንፋሹ እየተቋረጠ ነው >> <<ኧረ እኔኮ ሴት ነኝ ባይሆን አንተ አርገው በረብ >> << እንደው በዚ አፍ በ አላህ ኧረ ተይ >> ብሎ ወደ አፋ አሳየኝ አው መሆንም የለበትም አልኩና ራሴን አጀግኜ አፌን በአየር ሞልቼ አፋን ከፍቼ ሰጠሁት ደግሜ ደጋግሜ ይሄንኑ አደረኩ የሆነ ሰአት ግን ያላሰብኩትን ነገር ሆኖ አየሁት ከንፈሬን መመለስ አቃተኝ ምንድን ነው ብዬ ....... . . . . ⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️⚜️ ይቀጥላል ..........
نمایش همه...