fa
Feedback
ዝጉ መንገድ ሚዲያ

ዝጉ መንገድ ሚዲያ

رفتن به کانال در Telegram

''ዝጉ መንገድ ሚዲያ '' የዚህ ቻናል ዓላም ተከታዮቹን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው፤ በግል ስብዕናቸው፤ በቢዝነስ ሕይወታቸው እና በሙያዊ ሕይወታቸው ላይ የሚያስፈልጋቸውን እውቀትና ክህሎት እንዲሁም ጥበብ ለማጎልበት የሚሠራ ድንቅ ቻናል ነው። የ ''ዝጉ መንገድ ሚዲያ''አስተማሪ ቪዲዮችን ለምትፈልጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጫኑ!!! https://youtu.be/OIhbFJUy0Nw?si=6hhr3VOes5XEnZO

نمایش بیشتر
261
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
اوت '24
اوت '240
در 1 کانال‌ها
ژوئیه '24
+12
در 1 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '24
+11
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مه '24
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '24
+20
در 1 کانال‌ها
Get PRO
مارس '24
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '24
+9
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '24
+24
در 2 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '23
+26
در 1 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '23
+15
در 1 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+243
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
06 اوت0
05 اوت0
04 اوت0
03 اوت0
02 اوت0
01 اوت0
پست‌های کانال
2
"አንድ ነዳይ አጥብቆ እየለመነህ በቸልታ ትተኸው ስትሔድ እግዚአብሔርን አጥብቀህ በምትለምን ጊዜ ቢተውህ የሚሰማህን አስብ።" ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ https://t.me/dn_mez
277
3
  "ከላይ ሲሆኑ አይከብድም " _ #ዛሬ አንድ ጉዞ ነበረኝ። ጉዞው በኢትዮጵያ አየር መንገድ ነው። የሚሸኘኝ ሰው ወደ መሳፈሪያ ስፍራ እየወሰደኝ ሳለ እባክህ ትኬቱን እናስቀይረውና ጉዞህን ሌላ ቀን እናድርገው አለኝ። ለምን? ስለው አታየውም አየሩ ጥሩ አደለም አለኝ። ሳየው የቆየሁትን ሰማይ ደግሜ አየሁት፤ እውነትም ሰማዩ በጭጋግ ተሸፍኗል። ፀሐይ ወደ ምድር መድረስ ተስኗት ከጥቁሩ ደመና ጋር ትታገላለች። ሰማይና ምድር መካከላቸው በገባው ጥቁር ደመና ምክንያት መተያየት አቁመዋል። ቀና ብየ ደግሜ አየሁት፤ ያስጨንቃል። ፊቱን የዞረ ሰማይ በቆፈን የተወረረ ምድር። ምድር ሰማዩ ፊቱን ካላበራላት ጨለማ ናት። ለካ ብርሃናችን ከሰማይ ነው። ምድር አይኗን የምትገልጥበት ምንም የላትም። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። "የፈራ ይመለስ" የሚለው ስብከት ትዝ አለኝ። ነገር ግን መቅረት ስለማልችል እሄዳለሁ ብየ ጉዞየን ጀመርሁ። መሬቱን ለቀን ወደ ላይ አቀናን። አውሮፕላኑ ጥቁሩን ደመና አልፎ የተፈቀደለትን ከፍታ እስከሚይዝ ድረስ ያስፈራል። ከተሞች ከዐይናችን ተሰወሩ። አሁን በሰማይና በምድር መካከል ነን። ፍርሃቴ እየቀነሰ ሲመጣ ይሰማኛል። ምክንያቱም ጥቁሩን ደመና እያለፍነው ነው። ከደመናው በላይ ፀሐይ አለ። ብርዱ ያለ ከታች ነው። ከላይ ግን ሙቀት ነው። ጨለማው ያለ ከመሬት ነው ከላይ ግን ብርሃን ነው። ኔትዎርክ ኖሮ መነጋገር የሚፈቀድ ቢሆን ያንን የሸኝን ሰው ችግሩ ያለ ከታች በመኖራችን እንጅ ከላይ መልካም የሆነ ዓለም መኖሩን እነግረው ነበር። ነገር ግን ከታችኛው ዓለም ጋር መገናኘት አይቻልም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ከደመናው በላይ መልካም የሆነ ዓለም ካለ ከሰማዩ በላይ እንዴት ያለ መልካም ሀገር ይኖር ይሆን? ወደ ሰማያዊው ከተማ የገቡ ሰዎች ለአንድ ቀን ከኛ ጋር መገናኘት ቢፈቀድላቸው ምን ይሉን ይሆን? የላይኛውን ዓለም በእምነት መመልከት ላልቻሉ ሰዎች በዚህ መኖር መልካም ይመስላቸዋል። በክርስትና መንገድ ላይ የጀመሩትን የቅድስና ጉዞ አቋርጠው የተመለሱ ብዙዎች ናቸው። ምክንያቱም የጋረዳቸውን ደመና አልፈው መሄድ ስላልቻሉ ነው። ጭጋጉን እስክናልፍ የክርስትና ፈተናው ከባድ ቢሆንም በቅዱስ ወንጌል የተፈቀደላቸውን የሕይወት ከፍታ ይዘው ለሚጓዙ ክርስቲያኖች ግን መንገዱ አስቸጋሪ አይደለም። ፈተናው ያለ ስንወጣና ስንወርድ ብቻ ነው። ያስፈራል። ያስጨንቃል። ከላይ ስንሆን ግን የሚመራን ታላቅ ብርሃን አለ። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። አሁን ወደ ምድር ተመልሰናል። ምድርን ያጨለማት ደመና እዚህም አለ። ያው መመላለስ ነው። አንድ ጊዜ ወደ ላይ አንድ ጊዜ ወደ ምድር።
391
4
+5
بدون متن...
269
5
ምን ላቁም? አንድ ታዋቂ የአመራርና የማኔጅመንት አስተማሪ እንዲህ አለ፣ “መሪዎችን ስናሰለጥን ብዙውን ጊዜአችንን የምንፈጀው ማድረግ የሚገባቸው ነገር ምን እንደሆነ በመንገር ነው፡፡ መሪዎች ማቆም ያለባቸው ነገር ምን እንደሆነ ለመንገር ግን በቂ ጊዜን አናሳልፍም፡፡ ካገኘኋቸው መሪዎች መካከል ግማሾቹ ሊማሩ የሚገባቸው ማድረግ ያለባቸው ምን እንደሆነ አይደለም፡፡ በተቃራኒው መማር ያለባቸው ማቆም ያለባቸውን ነገር ነው”፡፡ ይህ አባባል የብዙዎቻችንን የሕይወት ዘይቤ አመልካች ነው፡፡ ሁል ጊዜ፣ “ምን ባደርግ ጥሩ ነው?” ከሚል ሃሳብ ጋር ስንሟገትና ይህንና ያንን ለማድረግ ስንሯሯጥ ምናልባት በመተው የምናከናውናቸው ነገሮች ያመልጡናል፡፡ አስተዳደጋችን አንድን ነገር አድርገን የማስመስከርን አቅጣጫ ብቻ አሳይቶን ነው ያደግነው፡፡ ስለዚህ መሻሻልን፣ ማደግን፣ ስኬትንና የመሳሰሉትን የምንመኛቸውን መልካም ነገሮች ለማግኘጥ ካለማቋረጥ እንጦዛለን፡፡ አንዳንድ ጊዜ ግን ስኬታችን ያለው ማቆም ያለብንን ነገር ከማቆም አንጻር ሊሆን ይችላል፡፡ አየህ፣ እጅግ በረዷማ በሆነ አካባቢ የሚኖሩ አንዳንድ እንስሶች፣ “የበረዶውን ወቅት ለማለፍ የሚያስችለኝን ምግብ እንዳገኝ ምን ላድርግ?” የሚለው ጥያቄ አላዛልቅ ሲላቸው፣ “የተመገብኩት ምግብ በቶሎ እንዳይቃጠልና ጉልበት እንዳላጣ ምን ማድረግ ላቁም?” በማለት “ሽሸጋ” (Hibernation) ውስጥ ይገባሉ፡፡ ባለማድረግ ይኖራሉ፣ በመተው ይሰነብታሉ፡፡ ዛሬ እስቲ ይህንን አስፈላጊና ወሳኝ ጥያቄ ራስህን ጠይቅ፣ “ማቆም ያለብኝ ነገር ምንድን ነው?”    “የተሻለ ገቢ ለማግኘት ምን ተጨማሪ ስራ ልጀምር?” የሚል ሰው ምናልባት፣ “የትኛውን አላስፈላጊ ወጪ ላቁም” በማለት ራሱን ቢጠይቅ፣ የተሻለ ገቢ እስከሚያገኝ ድረስ የተሻለ ገንዘብን የማጠራቀምና የማቆየት ስኬት ውስጥ ሊገባ ይችላል፡፡ “ከዚህ የተሻለ ሰላምና መረጋጋት እንዳገኝ ምን ላድርግ?” የሚል ሰው ምናልባት፣ “ከማን ጋር መገናኘት ላቁም?” ብሎ ራሱን ቢጠይቅ ሰላሙና መረጋጋቱ ይመለስለት ይሆናል፡፡ “ጊዜዬን በአግባቡ ለመጠቀም ምን ላድርግ?” የሚል ሰው ምናልባት፣ “ጊዜዬን በከንቱ እንዳላስበላ ማቆም ያለብኝ ጊዜ አባካን ሁኔታ ምንድን ነው?” ብሎ ራሱን ቢጠይቅ አንዱን የጊዜ አጠቃቀም ዘይቤ ይደርስበታል፡፡ አንዳንድ ጊዜ፣ “የት ልሂድ?” ከሚለው ጥያቄ ይልቅ፣ “ከየት ቦታ ልቅር?” የሚለው ጥያቄ የበለጠ ስኬታማ ያደርገናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ፣ “ከማን ጋር ላውራ?” ከሚለው ጥያቄ ይልቅ፣ “ከማን ጋር ያለኝን ንግግር ላቁም ወይም ልቀንስ?” የሚለው ጥያቄ የበለጠ ፍሬያማ ያደርገናል፡፡ አንዳንድ ጊዜ ከምንናገረው ይልቅ ዝም ለማለት የመርጠነው ነገር የበለጠ ስኬታማ ያደርገናል፡፡ ይህንን ምስጢር በሚገባ ስንገነዘብ ራሳችንን በመሰብሰብ፣ በመቀነስና በመልቀቅ ልቀን የምንገኝባቸው ሁኔታዎች ይበሩልናል፡፡ https://t.me/dn_mez
473
6
ፍቅር የሚሰጠውንም የሚቀበለውንም ይፈውሳል። ሁለቱ ወንድማማቾች በቤተሰቦቻቸው እርሻ ላይ አብረው ይሰራሉ። አንደኛው ያገባና ብዙ ቤተሰብ ያለው ሲሆን ሌላኛው ገና ያላገባ ነበር። ሁልጊዜ በቀኑ መጨረሻ ላይ ወንድማማቾቹ ምርቱን እና ትርፉን ሁሉንም ነገር እኩል ይካፈሉ ነበር። አንድ ቀን ብቻውን የሚኖረው ወንድም ለራሱ "ምርቱን እና ትርፋን እኩል መካፈላችን ትክክል አይደለም። እኔ የምኖረው ብቻዬን ነው ፤ የሚያስፈልገኝ ጥቂት ነው።" ብሎ  አሰበ። ከዚያ በእያንዳንዱ ምሽት ከራሱ ጎተራ አንዳንድ ጆንያ እህል ይወስድና በእርሱና በወንድሙ ቤት መካከል ያለውን ሜዳ አቋርጦ በወንድምየው ጎተራ ውስጥ ያስቀምጣል። ያገባው ወንድምም ለራሱ "ምርቱን ና ትርፋን እኩል መካፈላችን ፍትሀዊ አይደለም።  እኔ ለሚመጡት አመታት የሚንከባከቡኝ ሚስት ና ልጆች አሉኝ። ወንድሜ ግን ማንም የለውም ፤ወደፊት የሚንከባከበው የለም። "ብሎ አሰበ። ስለዚህ በየምሽቱ ከራሱ ጎተራ አንዳንድ ጆንያ እህል እየወሰደ ሳያየው ወንድምየው ጎተራ ወስጥ ያስቀምጥ ነበር። ሁለቱም ሰዎች ጎተራቸው ውስጥ ያለው እህል መጠኑ ባለመቀነሱ ለአመታት ይገረሙ ነበር። ከዚያ በአንድ ጨለማ ምሽት ሁለቱ ወንድማማቾች በድንገት ተጋጩ።  ቀስ በቀስ ምን እየተከሰተ እንደነበር ተረዱ ከዚያ ሁለቱም የተሸከሟቸውን ጆንያዎቻቸውን ጥለው በእንባ ተቃቀፉ። አስተማሪ ታሪክ ነውና ለወዳጅዎ አጋሩ
242
7
ፅናት!! "በዓለም ላይ የፅናትን ቦታ የሚተካ ምንም ነገር የለም። ብቃትም  አይደለም።  እንደውም ብቃት ያላቸው ስኬታማ እንዳልሆኑ ብዙ ቁጥር ያለው የለም።  የረቀቀ ዕውቀትም አይደለም እንደውም ሰዎች እንደማወቃቸው ስኬታማ አለመሆናቸው ቢታይ አስገራሚ   ትዕይንት ነው።መማርም አይደለም። ዓለማችን በተማሩና በማይሰሩ ሰዎች የተሞላች ናት። ጽናትና ቁርጠኝነት ግን ሁሉንም ነገሮች ናቸው።የአላማ ፅናት ያላቸው ሰዎች ከየትኛውም ቦታ ተነስተው  ያሰቡት ቦታ ለመድረስ ሊያቆማቸው የሚችል ምንም ነገር የለም።"                             ካልቬን ኮሌጅ "እያንዳንዱ ታላላቅ  የስኬት ታሪክ የትልልቅ ውድቀቶች ውጤት ነው ። ልዩነቱ ተሸናፊዎች በወደቁበት ተኝተው ሲቀሩ አሸናፊዎች ግን ከያንዳንዱ ውድቀታቸው በኀላ ዳግመኛ በታላቅ ብርታት መነሳተቸው ነው"                          -ፊዮዶር ዶስቶቭስኪ https://t.me/dn_mez
174
8
ገብርኤል በዓለ አብሣሪ ነው የብሥራት በዓላት 3 ናቸው ቅዱስ ያሬድ "ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ በዝንቱ ቁጽር ኮነ ዝንቱ ምክር ተፈነወ ገብርኤል መልአክ እምኀበ እግዚአብሔር..." በማለት ያመሠጠረውን ሊቃውንቱ በዚህ ዕለት ያመሰግኑበታል፡፡ ✔️ትርጉሙም፦ "በዚህ "ሃሌታ" ቁጥር ፍጻሜ ይህ ምክር ተደረገ፤ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ" ማለት ሲሆን ✔️ምሥጢሩ፦ በ5 ሃሌታ ☞ 5500 ዘመን ሲፈጸም (በ6ኛው ወር☞በ6ኛው ሺህ ዘመን) ገብርኤል ለብሥራት ተላከ የሚለውን የሚያመለክት ነው፡፡ 1. መጋቢት 21፦ ብሥራቱን የሰማችው የእመቤታችን በዓል፤ የተበሣሪዎቹ የእኛ በዓልም ጭምር ነው ፡፡ መልአኩ ለእመቤታችን ለቅድስት ድንግል ማርያም ወላዲተ አምላክ "ደስ ይበልሽ " ብሎ የነገራት የደስታ ቃል በሰው ልቡና እንደ ጥሩ ምንጭ እየፈላ እየመነጨ ይኖራል" በማለት መተርጉማን ያብራራሉ፤ የ15 ዓመቷ ብላቴና በጽድቅና በቅድስና እኛን ደካሞቹን ወክላን ደስታን ሰምታልናለች፡፡ በዚህም ምክንያት ♥️ሙኃዘ ፍሥሐ♥️ ትባላለች ፦ የደስታ መፍሰሻ ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ያሬድ ይህን ሁኔታ እንዲህ ይገልጸዋል፦ "...ገብርኤል ቦአ ቤተ መቅደስ ኀበ ማርያም ወይቤላ ተፈሥሒ ፍሥሕት ለዓለም ወለዓለመ ዓለም ወትቤሎ ድግም ድግም ዜናከ" ትርጉም፦ ገብርኤል ወደ ቤተ መቅደስ ገብቶ ማርያምን ደስተኛይቱ ሆይ ለዓለም ለዘለዓለም ደስ ይበልሽ አላት፤ እሷም "ድገመው ንግግርህን ድገመው" አለችው በማለት ያስደምመናል፡፡ እኛ ደሞ ቅዱስ ያሬድን "ድገመው" እንለዋለን!!! 2. መጋቢት 29፦ ብሥራቱ የተነገረለት የጌታ በዓል ነው፦ ይህም ማለት "ዘኒ ይትወለድ እምኔኪ ቅዱስ ውእቱ፦ካንቺ የሚወለደው ቅዱስ ነው" የተባለው ጌታ በዓል ነው፡፡ ፅንሱን በአዳም አካል፤ ሕፃናት በሚፀነሱበት የጊዜ መጠን ያደረገበትን ምሥጢር የምናደንቅበት የምናመሰግንበት በዓል ነው፡፡ 3. ታኅሣሥ 22፦ ብሥራቱን ለእመቤታችን የተናገረው መልአክ ቅዱስ ገብርኤል በዓል፡፡ ይህም ማለት "በ6ኛው ወር ወደ አንዲት ድንግል" የተላከው ፤ ከሰዎች መፈጠር አስቀድሞ "ሑር አብሥራ ለወለተ ሐና" (ሂደህ ለሐና ልጅ ማርያም ደስ ይበልሽ በላት) ተብሎ "ማኅተመ ብሥራት" በክንፉ የተሣለበት፤የተቀረጸበት መልአክ በዓል ነው፡፡ ይህ ጊዜ ሲፈጸም መልአኩ እንደተላከ ለማጠየቅ ቅዱስ ያሬድ "ሃሌ ሃሌ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሃሌ ሉያ በዝንቱ ቁጽር ኮነ ዝንቱ ምክር ተፈነወ ገብርኤል መልአክ እምኀበ እግዚአብሔር..." በማለት ያመሠጠረውን ሊቃውንቱ በዚህ ዕለት ያመሰግኑበታል፡፡ ✔️ትርጉሙም፦ "በዚህ "ሃሌታ" ቁጥር ፍጻሜ ይህ ምክር ተደረገ፤ ገብርኤል ከእግዚአብሔር ዘንድ ተላከ" ማለት ሲሆን ✔️ምሥጢሩ፦ በ5 ሃሌታ ☞ 5500 ዘመን ሲፈጸም (በ6ኛው ወር☞በ6ኛው ሺህ ዘመን) ገብርኤል ለብሥራት ተላከ የሚለውን የሚያመለክት ነው፡፡ ☞የአንዱን ቀን በዓል ለ3 ለ4 ከፍሎ ማክበር በቤተ ክርስቲያን የተለመደ ነው፡፡ ❖ይሁን እንጂ መጋቢት 21 ዐቢይ ጾም ላይ ስለሚውል እና መጋቢት 29 ደግሞ ሰሙነ ሕማማት ላይ የሚውልበትም ጊዜ ስላለ የ 3ቱም በዓላት ተሰብስቦ ታኅሣሥ 22 ቀን በድምቀት ይከበራል፡፡ ❖መታሰቢያነቱ ግን በ3ቱ ዕለታት የተቀመጠ መሆኑን ማስተዋል ነው፡፡ ከንጉሡ አፄ ናዖድ ጀምሮ ዐቢይ ጾም ላይ የሚውሉ አብዛኞቹ በዓላት በተለዋጭ ዕለታት እንደሚከበሩ የታወቀ ነው፡፡ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ደስ የሚያሰኘውን ነገር ሁሉ • ለሁላችን • ለሀገራችን ያሰማን! ብሥራተ ሥጋዌውን የሰማች የድንግሊቱ በረከት አማላጅነት አይለየን! አሜን! https://t.me/dn_mezmur
93
9
''ዝጉ መንገድ ሚዲያ '' የዚህ ቻናል ዓላም ተከታዮቹን በመንፈሳዊ ሕይወታቸው፤ በግል ስብዕናቸው፤ በቢዝነስ ሕይወታቸው እና በሙያዊ ሕይወታቸው ላይ የሚያስፈልጋቸውን እውቀትና ክህሎት እንዲሁም ጥበብ ለማጎልበት የሚሠራ ድንቅ ቻናል ነው። የ ''ዝጉ መንገድ ሚዲያ''አስተማሪ ቪዲዮችን ለምትፈልጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጫኑ!!! https://youtu.be/OIhbFJUy0Nw?si=6hhr3VOes5XEnZO
144
10
بدون متن...
166
11
እንኳን አደረሳችሁ ለጰራቅሊጦስ በዓል
252
12
+2
بدون متن...
255
13
አትፈልጉዋቸው ተዉዋቸው! በዙርያችሁ ያሉ ሰዎች ህልማችሁን እንዳትኖሩ እንቅፋት እንዲሆኑባችሁ አትፍቀዱላቸው። አብረውህ ለመሆን ስለፈለጉ ብቻ አብረሀቸው ለመሆን አትሞክር።ደካማ አስተሳሰባቸውን አንተ ላይ እንዲያሰርፁብህ አትፍቀድላቸው። ሁሌም ቢሆን አንተ ከእነሱ የተለየ የምትኖርለት ነገር እንዳለ አስብ።ከህልምህ ይልቅ ከነሱ ጋር መዞር እንዳለብህ የሚያስቡ ከሆነ ተዋቸው|ተሰናበታቸው። https://t.me/dn_mez
210
14
ያለ ጸሎት መንፋሳዊ ነኝ የሚል ሰው እሳት መካከል ገብቶ የሚጫወትን የእሳት ራትን ይመስላል፡፡ (ማር ይስሐቅ) ልጄ ሆይ አንተ በራስህ ላይ ስትፍረድ እግዚአብሔር ፍርዱን ያነሳልሃል፤ አንተ በራሰህ ላይ ባትፈርድ ግን እግዚአብሔር ይፈርድብሀል። (ታላቁ መቃሪዮስ) ክርስትና የሚጀምረው ከተግባር እንጂ ከወሬ አይደለም፡፡ ሕይወታችን በጥቅስ ተገንዞ በጥቅስ የተቀበረ ከሕይወትና ከሥራ የተለየ እንዲሆን አንፍቀድለት፡፡ /ቅዱስ ጎርጎርዮስ ዘእንዚናዙ/ ዘመን ማለት አንተ ነህ ፡፡ አንተ ሰላማዊ ስትሆን ሰላማዊ ትሆናለች፡፡ አንተ የከፋህ እንደሆነ ትከፋለች፡፡ / አንጋረ ፈላስፋ/ ራስህን ለማየት ወደ መስታወት ብትመለከት ውበትህን ወይም ጉድለትህን ያሳይሀል፡፡ ምንም ነገር እንዳታይ ታደርግ ዘንድ ከመስታወቱ መሰወር አትችልም፡፡ ማንም ሊያመልጥበት በማይችለው በፍርድ ቀንም እንዲሁ ይሆናል፡፡ /አንጋረ ፈላስፋ/
165
15
ውድ የ2016 ዓ.ም ተፈታኝ ተማሪዎች ይህንን መዝሙር እየዘመርን ተስፋችን ሁሉ በእናታችን በእመቤታንች ላይ እንጣል። ለመኑ እነግር ሀዘነ ልብየ እንበሌኪ እግዝእትየ #ትርጉም ለማን እነግራለው የልቤን ሀዘን የአምላክ እናት ከአንቺ በቀር ዲ/ን መዝሙሩ ንጉሴ ወልቂጤ፡ኢትዮጵያ 2016 ዓ . ም ዝጉ መንገድ ሚዲያ የማርያም ልጆች ነን https://t.me/dn_mezmur
169
16
ከነገ ጀምሮ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተመራቂ ተማሪዎች ግቢ ጉባኤያችን መልካም ፈተና ይሆንላችሁ ዘንድ ትመኝላችኋለች! ግቢ ጉባኤ እንዳስተማረቻችሁ ስጋታችሁን፣ ጭንቃችሁን ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ በመ
ከነገ ጀምሮ የመውጫ ፈተና የምትወስዱ ተመራቂ ተማሪዎች ግቢ ጉባኤያችን መልካም ፈተና ይሆንላችሁ ዘንድ ትመኝላችኋለች!  ግቢ ጉባኤ እንዳስተማረቻችሁ ስጋታችሁን፣ ጭንቃችሁን ሁሉ በእግዚአብሔር ላይ  በመጣል ፈተናችሁን ተረጋግታችሁ እንድትፈተኑ ይሁን ። ብሔራዊ ፈተና ስትፈተኑ ይህ  የመጀመሪያችሁ አይደለምና ልክ ከዚህ በፊት እግዚአብሔር ረድቷችሁ ያለፋችኋቸውን ፈተናዎች አሁን በእግዚአብሔር ክንድ ተደግፋችሁ እንደምታልፉ አምናችሁ የሚያስጨንቃችሁን ሁሉ በእርሱ ላይ ጣሉት። ቸሩ አምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ለእኛ የሚያስፈልገውን በጎ ነገር እኛ ሳንጠይቀው ያውቃልና ውጤቱ ምንም ይሁን ምን አንተ የወደድከው ለእኔ ይመቸኛል ብለን ልንቀበል ይገባል። ለዘመናት ያልተለየን ፣ የጠበቀን ፣በጉዟችን ሁሉ የረዳን እግዚአብሔር ዛሬም ከእኛ ጋር ነውና እምነታችንን ሁሉ በእርሱ ላይ ጥለን ሳንጨነቅ የሚቻለንን ብቻ  እናድርግ ትላለች እናት ግቢ ጉባኤያችን! ቅዱሳን አበውን በጉዟቸው ሁሉ የረዳ እግዚአብሔር እናንተንም በፈተናችሁ ረድቷችሁ መልካሙን ውጤት ለማየት ያብቃችሁ! እመብርሃን በምልጃዋ አትለያችሁ🙏 ❝ርሱ ስለ እናንተ ያስባልና፥ የሚያስጨንቃችኹን ዅሉ በርሱ ላይ ጣሉት። 1ኛ ጴጥ 5፥7❞ መልካም ፈተና! ✞ ✞ ✞ ወ▮ዩ▮ግ▮ጉ
178
17
❖ ሰኔ ፲፪ ❖ ✞ ቅዱስ ሚካኤል ሊቀ መላእክት [በነገዱ ውስጥ፥ በመላእክት ሁሉ ላይ አለቃ ሆኖ የተሾመበት..፣ በእስክንድርያ ከተማ ቅዳሴ ቤቱ የከበረበት..፣ የሞት መልእክት የተጻፈባትን የቅዱስ ባሕራንን ደብዳቤ የለወጠበት..፣ ቅድስት አፎምያን ያዳነበት..፣ ለሰው ልጆች ሁሉ ምሕረትን የሚለምንበት..በእለኚህ ምክንያት ነው በዓሉን የምናከብረው] ✞ "ሰላም ለሚካኤል መሐሪ ውእቱ፤ ወተአዛዚ ለሰብእ በዲበ ሠናይቱ፤ ለቀርነ ዝንቱ መልአክ በድምፀ ንፍሐቱ፤ በከመ ኮነ ቀዳሚ ውስተ ሰማያት ዕርገቱ፤ ለእግዚአብሔር ይከውን ዳግመ ምጽአቱ።"
158
18
+4
بدون متن...
230
19
+2
بدون متن...
198
20
https://t.me/dn_mezmur
238