fa
Feedback
ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/

ኢትዮ - ኮን ሬድዮ ፕሮግራም/Ethio con radio program/

رفتن به کانال در Telegram

በግንባታው ዘርፍ ላይ ትኩረት የሚያደርግ ሳምንታዊ የባለሙያዎች የሬድዮ ፕሮግራም የኢትዮጵያ የኮንስትራክሽን ሥራ ተቋራጮች ማህበር ከአሀዱ ሬድዮ 94.3 ትብብር ዘወትር ሰኞ ምሽት ከ2፡00-3፡30 ሰዓት የሚተላለፍ ሳምንታዊ ፕሮግራም ነው።

نمایش بیشتر
4 236
مشترکین
-724 ساعت
-147 روز
-430 روز
آرشیو پست ها
የዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ 👷🕵️🧑🔧 👨💼👩🔧 የእንግዳ ሰዓት 🏢🏨🏫 በእንግዳ ሰዓት ከመንግስት ግ
የዛሬ ሰኔ 8 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ 👷🕵️🧑🔧 👨💼👩🔧 የእንግዳ ሰዓት 🏢🏨🏫 በእንግዳ ሰዓት ከመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር ከወ/ሮ መሰረት መስቀሌ ጋር የተደረገ ልዩ ቆይታ እናቀርባለን። በህንፃና መሠረተ ልማት ፕሮጀክቶች ዙሪያ የመንግስት ግዥ ሂደቶችና የንብረት አያያዝ ሁኔታ ምን ይመስላል? ከዋና ዳይሬክተሯ ጋር ያደረግነውን ቆይታ ይከታተሉ። ▪️በወቅታዊ ፕሮግራም በኮንስትራክሽን ሥራ ላይ የጤናና ደህንነት (Health and Safety) ጉዳይ ምን ያህል ትኩረት እያገኘ ነው? በኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ቴክኖሎጂ እና ማናጅመንት  ባለሙያዎች ማህበር አማካኝነት የተዘጋጀውን ፕሮግራም በወቅታዊነት እናነሳዋለን። የማህበሩ ፕሬዘዳንት አነጋግረናል። በግንባታ ቦታዎች ላይ ደህንነትን ለማስጠበቅ ምን እየተሰራ ነው? ተግዳሮቶቹስ ምንድናቸው? መልሱን ከፕሬዘዳንቱ ቃል እንሰማለን። 📞☎️📩 የምታነሱት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄ 👉 0974466655 ላይ አድርሱን፡፡ https://t.me/ethioconradio

🛩✈️ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አፍሪካም እንደምትችል ለዓለም የምናሳይበት ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አፍሪካም ማሰብ፣ ማቀድና መስራት እንደምትችል ለዓለም የምናሳይበት ግዙፍ ፕሮጀክት ነው አሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ ሒደት ያለበትን ሁኔታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁና በሚወጣለት ሀብት እንዲሁም በሚያንቀሳቅሰው ማሽነሪ በአፍሪካ ደረጃም ቢሆን ቀዳሚው ነው ። በብዙ ሀገራት ብሎም በኢትዮጵያ የሥራ ሐሳብና ሀብት ቢኖርም፥ የፕሮጀክት አመራር ችግር ስላለ ፕሮጀክቶች መቼ ተጀምረው መቼ እንደሚጠናቀቁና እንዴት ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው በቂ ግንዛቤ አለመኖሩን አንስተዋል፡፡ አሁን ላይም ይህንን የቆየ ልማዳዊ አሰራር በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት መቀየር ተችሏል ነው ያሉት፡፡ በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ ከ8 ሺህ በላይ ሠራተኞች እንደሚገኙና እስከ 4 ሺህ የሚጠጉ ማሽነሪዎችና መኪናዎች በ30 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ሌሊትና ቀን እንደሚንቀሳቀሱ አብራርተዋል፡፡ የፕሮጀክቱ እንቅስቃሴ እንደ አንድ ትንሽ ከተማ ማለት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ለማሽኖቹ በቀን ከ650 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ፤ በ10 ቀን ውስጥ ደግሞ ከ6 ነጥብ 5 እስከ 7 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ ጥቅም ላይ እንደሚውል አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት በስኬት ለመምራት የነዳጅ፣ ማሽነሪና ተሽከርካሪ በብቃት ለማስተናገድ ዘመናዊ ሥርዓት መዘርጋቱን አብራርተዋል። አውሮፕላን ማረፊያውን መገንባት ብቻ ሳይሆን የ4 ሺህ መኪናዎችን ዕለታዊ እንቅስቃሴ በቁጥጥር ማዕከል፣ በዳሽ ቦርድና በድሮን ቴክኖሎጂ የታገዘ ኦፕሬቲንግ ሲስተም በመጠቀም በብቃት ማስተናገድና መረዳት ለአመራሩ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ጅማሮ ላይ ብዙዎች አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ስራውን መምራት አይሆንላችሁም፣ ለምን ታስባላችሁ የሚል የተስፋ መቁረጥ ምልከታ እንደነበራቸው አስታውሰው÷ እኛ ደግሞ እንችላለን፤ ይገባናል እያልን ነው፤ ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜ ሲደርስ እናያለን ሲሉም አክለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ይህ ኤርፖርት ከዚህ ቀደም እንደነበሩት ፕሮጀክቶች ሳይሆን በከፍተኛ ክትትል የሚመራ በመሆኑ ባልነው ጊዜ እንጨርሰዋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። (FBC)

🛩✈️ የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አፍሪካም እንደምትችል ለዓለም የምናሳይበት ነው – ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ኢትዮጵያ ብቻ ሳትሆን አፍሪካም ማሰብ፣ ማቀድና መስራት እንደምትችል ለዓለም የምናሳይበት ግዙፍ ፕሮጀክት ነው አሉ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) የቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት ግንባታ ሒደት ያለበትን ሁኔታ ተዘዋውረው ተመልክተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በዚህ ወቅት እንዳሉት ÷ ፕሮጀክቱ በኢትዮጵያ ታሪክ ትልቁና በሚወጣለት ሀብት እንዲሁም በሚያንቀሳቅሰው ማሽነሪ በአፍሪካ ደረጃም ቢሆን ቀዳሚው ነው ። በብዙ ሀገራት ብሎም በኢትዮጵያ የሥራ ሐሳብና ሀብት ቢኖርም፥ የፕሮጀክት አመራር ችግር ስላለ ፕሮጀክቶች መቼ ተጀምረው መቼ እንደሚጠናቀቁና እንዴት ቁጥጥር እንደሚደረግባቸው በቂ ግንዛቤ አለመኖሩን አንስተዋል፡፡ አሁን ላይም ይህንን የቆየ ልማዳዊ አሰራር በቢሾፍቱ ዓለም አቀፍ አውሮፕላን ማረፊያ ፕሮጀክት መቀየር ተችሏል ነው ያሉት፡፡ በአሁኑ ወቅት በፕሮጀክቱ ከ8 ሺህ በላይ ሠራተኞች እንደሚገኙና እስከ 4 ሺህ የሚጠጉ ማሽነሪዎችና መኪናዎች በ30 ኪሎ ሜትር ራዲየስ ውስጥ ሌሊትና ቀን እንደሚንቀሳቀሱ አብራርተዋል፡፡ የፕሮጀክቱ እንቅስቃሴ እንደ አንድ ትንሽ ከተማ ማለት ነው ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ÷ ለማሽኖቹ በቀን ከ650 ሺህ ሊትር በላይ ነዳጅ ፤ በ10 ቀን ውስጥ ደግሞ ከ6 ነጥብ 5 እስከ 7 ሚሊየን ሊትር ነዳጅ ጥቅም ላይ እንደሚውል አስረድተዋል። በኢትዮጵያ ታሪክ የመጀመሪያ የሆነውን ይህንን ግዙፍ ፕሮጀክት በስኬት ለመምራት የነዳጅ፣ ማሽነሪና ተሽከርካሪ በብቃት ለማስተናገድ ዘመናዊ ሥርዓት መዘርጋቱን አብራርተዋል። አውሮፕላን ማረፊያውን መገንባት ብቻ ሳይሆን የ4 ሺህ መኪናዎችን ዕለታዊ እንቅስቃሴ በቁጥጥር ማዕከል፣ በዳሽ ቦርድና በድሮን ቴክኖሎጂ የታገዘ ኦፕሬቲንግ ሲስተም በመጠቀም በብቃት ማስተናገድና መረዳት ለአመራሩ ወሳኝ መሆኑን አስገንዝበዋል። በፕሮጀክቱ ጅማሮ ላይ ብዙዎች አትችሉም፣ ገንዘቡም አይገኝም፣ ስራውን መምራት አይሆንላችሁም፣ ለምን ታስባላችሁ የሚል የተስፋ መቁረጥ ምልከታ እንደነበራቸው አስታውሰው÷ እኛ ደግሞ እንችላለን፤ ይገባናል እያልን ነው፤ ማን እንደሚያሸንፍ ጊዜ ሲደርስ እናያለን ሲሉም አክለዋል። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ (ዶ/ር) ይህ ኤርፖርት ከዚህ ቀደም እንደነበሩት ፕሮጀክቶች ሳይሆን በከፍተኛ ክትትል የሚመራ በመሆኑ ባልነው ጊዜ እንጨርሰዋለን ሲሉም አረጋግጠዋል። (FBC)

🔲 የግድብ (Dam) ንድፍ(design) ደረጃዎች ወይም Steps 1. የፕሮጀክት መለየት እና የተፈጻሚነት ጥናት (Feasibility Study) 🚧ዓላማ: ፕሮጀክቱ ቴክኒካዊ፣ ኢኮኖሚያዊ እና አካባቢያዊ የሚቻል መሆኑን ለማረጋገጥ ▪️የፕሮጀክቱን ዓላማ መግለጽ (መስኖ፣ ኃይል ማመንጨት፣ የጎርፍ መቆጣጠር፣ የውሃ አቅርቦት) ▪️የመጀመሪያ የቦታ ምርጫ ሲቀጥል የሃይድሮሎጂ እና የመሬት ካርታ ጥናት የወጪ ግምት እና የጥቅም–ወጪ ትንተና የአካባቢ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናት 2. የቦታ ምርመራ (Site Investigation) 🚧ዓላማ: የዳሙን ቦታ የአካላዊ ሁኔታ ለመረዳት። a) የመሬት ካርታ ጥናት (Topographic Survey) የመሬት ኮንቱር ካርታ ማዘጋጀት የሬዘርቫር መጠን እና ከፍታ ግንኙነት መወሰን b) የጂኦሎጂ እና የጂኦቴክኒካል ጥናት የአፈር እና የድንጋይ አይነት መለየት የመሠረት የመሸከም አቅም መወሰን የውሃ መስረቅ (permeability) መለካት የስንጥቅ እና የድንጋይ ጉድለት መለየት የውሃ ሹልኪያ ጥናት 3. የሃይድሮሎጂ ትንተና (Hydrological Analysis) 🚧ዓላማ: የውሃ መጠን እና የጎርፍ መጠን ለመወሰን። ▪️የካችመንት አካባቢ ጥናት ▪️የዝናብ–ፍሰት ትንተና ▪️የንድፍ ጎርፍ መጠን መወሰን ▪️የሬዘርቫር አቅም ትንተና ▪️የደለል (sediment) ጥናት 🚧ዋና ውጤቶች: ▪️መደበኛ የውሃ ደረጃ (NWL) ▪️ከፍተኛ የውሃ ደረጃ (MWL) ▪️የንድፍ ጎርፍ ደረጃ (MFL) 4. የዳም አይነት ምርጫ (Selection of Dam Type) 🚧የሚመረጠው በሚከተሉት መሰረት ነው: ▪️የመሠረት ሁኔታ ▪️የንብረት አቅርቦት ▪️የሸለቆ ቅርጽ ▪️የኢኮኖሚ ሁኔታ የተለመዱ አይነቶች: ▪️ግራቪቲ ዳም ▪️አርች ዳም ▪️በትረስ ዳም ▪️የአፈር ዳም ▪️የድንጋይ ሙሌት ዳም 5. የሃይድሮሊክ ንድፍ (Hydraulic Design) 🚧ዓላማ: የውሃ ፍሰትን መቆጣጠር። ያካትታል: ▪️የስፒልዌይ ንድፍ ▪️የውሃ መውጫ ንድፍ ▪️የመግቢያ መዋቅር ▪️የውሃ ማስቀየሻ ስራ 6. የመዋቅር ትንተና (Structural / Stability Analysis) 🚧ዳሙ ደህንነቱ እንዲጠበቅ ይህ ይደረጋል። የሚታሰቡ ጭነቶች: ▪️የራሱ ክብደት ▪️የውሃ ግፊት ▪️የከፍታ ግፊት (uplift) ▪️የደለል ግፊት ▪️የመሬት መንቀጥቀጥ ▪️የንፋስ እና የማዕበል ግፊት 🚧 የሚመረመሩ: ▪️መገልበጥ (Overturning) ▪️መንሸራተት (Sliding) ▪️የመሠረት ግፊት ▪️የጭነት ስርጭት 7. የውሃ ሾልኮ ትንተና (Seepage Analysis) በተለይ ለአፈር ዳም አስፈላጊ ነው። ▪️የውሃ ፍሰት ትንተና ▪️የphreatic line መወሰን ▪️የpiping መከላከል የሚካተቱ: ▪️ፊልተሮች ▪️ድሬን ▪️cutoff wall 8. የመሠረት ንድፍ (Foundation Design) ▪️ደካማ አካባቢ ማሻሻል ▪️ግራውቲንግ ▪️cutoff trench ንድፍ 9. የሬዘርቫር እና ደለል ትንተና (Reservoir & Sedimentation Analysis) ▪️የደለል መጠን መወሰን ▪️የdead storage ንድፍ ▪️የuseful storage መወሰን 10. የመሬት መንቀጥቀጥ ትንተና (Seismic Analysis) ▪️የመንቀጥቀጥ ጭነት ትንተና ▪️የዳሙ መረጋጋት መርመር 11. የአካባቢ እና ማህበራዊ ተፅዕኖ ጥናት (Environmental & Social Impact) ▪️የአካባቢ ተፅዕኖ ▪️የህዝብ ማፈናቀል ጥናት ▪️የአካባቢ ጥበቃ(ተፅእኖ) ጥናት 12. የግንባታ እቅድ (Construction Planning) ▪️የግንባታ ደረጃዎች ▪️የውሃ መቀየሪያ ▪️የንብረት አቅርቦት ▪️የወጪ ግምት 13. የክትትል እና መለኪያ ንድፍ (Instrumentation & Monitoring) https://t.me/ethioconradio

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚኒሱ ማንኛው ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው ተገለፀ የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር  የኮንስትራክሽን ዘርፍ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆንና ዘርፉ ሰፊ እና ውስብስብ እንዲሁም ብዙ ሀብት የሚንቀሳቀስበት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የሚኒሱ ጥያቄዎችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል   ውይይት ተካሂዷል፡፡ የውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት ክቡር ሚ/ዲኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በዘርፉ የወጡ አዋጆች ደንቦች እና መመሪያዎች በማጣራት  ተመጋጋቢ እና ተናባቢ በማድረግ ወጥነቱን አስጠብቆ መሬት በማውረድ ከጥያቄ ባለፈ ተግባራዊ ማድረግ እንደምገባ ተናግረዋል ፡፡ በውይይቱ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ሙሉዓለም ደበበ ለህንጻ ስራ ተቋራጮች፣ ለሙያ ማህበራትና ለአማካሪዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የስራ ክፍሉ በሰጠው ስልጠና የተነሱ ጥያቄዎች፣ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የኮንስትራክሽን የምዝገባና የብቃት ማረጋገጫ መመሪያ ረቂቅ እንዲሁም ከኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የመወያያ ሰነዶች አቅርበዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት በማፋጠን የመሰረተ ልማት አውታሮችን በመዘርጋትና ለዜጎች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ ያለው ከፍተኛ ድርሻ ከግምት ውስጥ በማስገባት በዘርፉ የሚከናወኑ የግንባታ ፕሮጀክቶች የሚጠበቅባቸውን ጥራት፣ ደህንነት እና የወጪ ቆጣቢነት መርህ ተከትለው እንዲከናወኑ ለማድረግ ዘመናዊ ወጥ የሆነ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ የኮንሰትራክሽን ኢንዱስትሪ መረጃዎችን እና ግብዓቶችን  በአንድ ቋት ማግኘት የሚያስችል እና የዘርፉ ከ20 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ችግር የሚፈታ ሲስተም በሚዲያ ላይም ዘርፉ ከማስተዋወቅ ጋር በተያያዘ በርካታ ስራዎችን እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል ፡፡ በውይይቱ ላይ የተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች እና የዘርፉ አመራሮች ተሳትፈዋል። (ከመልሚ) https://t.me/ethioconradio

በኮንስትራክሽን ዘርፍ የሚኒሱ ማንኛው ጥያቄዎች ምላሽ ማግኘት እንዳለባቸው ተገለፀ ) የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር  የኮንስትራክሽን ዘርፍ አለም አቀፍ ተወዳዳሪ እንዲሆንና ዘርፉ ሰፊ እና ውስብስብ እንዲሁም ብዙ ሀብት የሚንቀሳቀስበት ከመሆኑ ጋር በተያያዘ የሚኒሱ ጥያቄዎችን ምላሽ መስጠት የሚያስችል   ውይይት ተካሂዷል፡፡ የውይይት መድረኩ ላይ የተገኙት ክቡር ሚ/ዲኤታ የትምጌታ አስራት (ዶ/ር) በዘርፉ የወጡ አዋጆች ደንቦች እና መመሪያዎች በማጣራት  ተመጋጋቢ እና ተናባቢ በማድረግ ወጥነቱን አስጠብቆ መሬት በማውረድ ከጥያቄ ባለፈ ተግባራዊ ማድረግ እንደምገባ ተናግረዋል ፡፡ በውይይቱ የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪ ልማት መሪ ስራ አስፈፃሚ ኢንጅነር ሙሉዓለም ደበበ ለህንጻ ስራ ተቋራጮች፣ ለሙያ ማህበራትና ለአማካሪዎች በተለያዩ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ የስራ ክፍሉ በሰጠው ስልጠና የተነሱ ጥያቄዎች፣ ከኢትዮጵያ ኮንስትራክሽን ባለስልጣን የኮንስትራክሽን የምዝገባና የብቃት ማረጋገጫ መመሪያ ረቂቅ እንዲሁም ከኮንስትራክሽን ማኔጅመንት ኢንስቲትዩት የመወያያ ሰነዶች አቅርበዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም የኮንስትራክሽን ኢንዱስትሪው የሀገሪቱን የኢኮኖሚ ዕድገት በማፋጠን የመሰረተ ልማት አውታሮችን በመዘርጋትና ለዜጎች ሰፊ የስራ እድል በመፍጠር ረገድ ያለው ከፍተኛ ድርሻ ከግምት ውስጥ በማስገባት በዘርፉ የሚከናወኑ የግንባታ ፕሮጀክቶች የሚጠበቅባቸውን ጥራት፣ ደህንነት እና የወጪ ቆጣቢነት መርህ ተከትለው እንዲከናወኑ ለማድረግ ዘመናዊ ወጥ የሆነ የቁጥጥር ስርዓት መዘርጋት ያስፈልጋል ተብሏል፡፡ የኮንሰትራክሽን ኢንዱስትሪ መረጃዎችን እና ግብዓቶችን  በአንድ ቋት ማግኘት የሚያስችል እና የዘርፉ ከ20 እስከ 30 በመቶ የሚሆነውን ችግር የሚፈታ ሲስተም በሚዲያ ላይም ዘርፉ ከማስተዋወቅ ጋር በተያያዘ በርካታ ስራዎችን እየተሰራ እንደሆነ ገልጸዋል ፡፡ በውይይቱ ላይ የተጠሪ ተቋማት የስራ ሀላፊዎች እና የዘርፉ አመራሮች ተሳትፈዋል። (ከመልሚ) https://t.me/ethioconradio

የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት 50 ሺህ ብር መደለያ የተቀበሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ህንፃ ውስጥ ነው። ዘነበ ንጉሴ የተባ
+2
የግንባታ ፈቃድ ለመስጠት 50 ሺህ ብር መደለያ የተቀበሉ ግለሰቦች በቁጥጥር ስር ዋሉ ግለሰቦቹ የወንጀል ድርጊቱን የፈፀሙት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 8 አስተዳደር ህንፃ ውስጥ ነው። ዘነበ ንጉሴ የተባለው ግለሠብ በጉለሌ ክፍለ ከተማ አስተዳደር የግንባታ ፈቃድ የህንፃ መጠቀሚያ ባለሙያ ሲሆን፣ የግል ተበዳይ የግንባታ ፍቃድ ለማውጣት 100 ሺህ ብር ተጠይቀው በድርድር 50 ሺህ ብር ይዘው እንዲመጡ ተስማምተዋል። የግል ተበዳይ የደረሰባቸውን በደል ለክፍለ ከተማው ፖሊስ የወንጀል መከላከል መምሪያ በሰጡት ጥቆማ ተጠርጣሪው በክትትል አባሎች ገንዘቡን ሲቀበል እጅ ከፍንጅ ተይዟል። ከጉዳዩ ጋር ተሳትፎ የነበረው በክፍለ ከተማው የግንባታ ፈቃድ የመጠቀሚያ ፈቃድ ባለሙያ የሆነው አድምቀው ውቤ የተባለው ግለሰብ የግል ተበዳይን ጉቦ ካልከፈልክ አገልግሎት እንደማይሰጠው በመንገርና ለአንድ ወር በማጉላላት 50 ሺህ ብሩን እንዲሰጥ በማድረግ የማግባባት ስራ ሲስራ እንደነበር ፖሊስ ገልጿል። ህብረተሰቡ መብቱን በገንዘብ መግዛት እንደሌለበት ያሳሰበው የአዲስ አበባ ፖሊስ ዋና ጠቅላይ መምሪያ መሰል የወንጀል ድርጊት ሲፈጸም ጉዳዩን በእጅ ስልኮች የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (citizen engagement application) በመጠቀም መረጃ መስጠት እንደቻልም የከተማው ፖሊስ በፌስቡክ ገጹ አስታውቋል፡፡ (የ.ፌ.ሥ.ሙ.ኮ)

https://www.facebook.com/share/v/18b3qfqhKT/ 👉 ኢትዮ ኮን ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም የቀጥታ ስርጭት ፕሮግራም

👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ ▪️▪️ልዩ ፕሮግራም▪️ 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘመናዊ መሠረተ
👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ ▪️▪️ልዩ ፕሮግራም▪️ 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘመናዊ መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም መሐንዲስ የነበሩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬን የምናስታውስበት ልዩ የሬድዮ ፕሮግራም ይዘን እንቀርባለን። 🔲 በፕሮግራሙ ውስጥ፦ ✔️ የህይወት እና የሙያ ጉዟቸው ✔️ ከቤተሰቦቻቸው የተሰሙ ትዝታዎች ✔️ ከስራ ባልደረቦቻቸው የተገኙ ምስክርነቶች ✔️ ለሀገር ያበረከቱት አሻራ 🗓 ቀን፡ [ ሰኔ 1 ቀን 2018 ] ⏰ ሰዓት፡ [ሰዓት 2፡20—3፡30] አይለፍዎ! ▶️ በወቅታዊነት የምናነሳው ነጥብ ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአዲስ መልክ ሌሎች የስራ መስኮች ላይ ሊሰማራ መሆኑን አስታውቋል። የራሱን ባለሙያዎች ጨምሮ የበላይ አካላትን እና የደንበኞቹን ሙያዊ ብቃትና የሥራ አፈጻጸም አቅም ለማሳየት የሚስያችል የሥልጠና ማዕከል በማደራጀት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል። ስለማሰልጠኛ ተቋሙ ግንባታ ሂደት ሌሎቸም ጉዳዮች ጋር ከተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ጋር ቆይታ አድርገናል። 📞☎️📩 የምታነሱት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄ 👉 📞0974466655 ላይ አድርሱን፡፡ ⏰⏱️📻ከ2፡00 — 3፡30 ሰዓት በአሀዱ ሬድዮ 94.3 ላይ በቀጥታ ስርጭት ፕሮግራሞቻችንን ትከታተሉ ዘንድ ከወዲሁ በአክብሮት እጋብዛለሁ፡፡                      መልካም ምሽት! https://t.me/ethioconradio

👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ 👩‍🔧👩‍💼👩‍🦰ልዩ ፕሮግራም 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘ
👉 የዛሬ ሰኔ 1 ቀን 2018 ዓ.ም "ኢትዮ ኮን" ምሽት የቀጥታ ስርጭት መሰናዶዎቻችንን ከወዲሁ እናስተዋውቃችሁ፡፡ 👩‍🔧👩‍💼👩‍🦰ልዩ ፕሮግራም 🎙 ልዩ የመታሰቢያ ፕሮግራም የኢትዮጵያ ዘመናዊ መሠረተ ልማት ግንባታ ግንባር ቀደም መሐንዲስ የነበሩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬን የምናስታውስበት ልዩ የሬድዮ ፕሮግራም ይዘን እንቀርባለን። በፕሮግራሙ ውስጥ፦ ✔️ የህይወት እና የሙያ ጉዟቸው ✔️ ከቤተሰቦቻቸው የተሰሙ ትዝታዎች ✔️ ከስራ ባልደረቦቻቸው የተገኙ ምስክርነቶች ✔️ ለሀገር ያበረከቱት አሻራ 🗓 ቀን፡ [ ሰኔ 1 ቀን 2018 ] ⏰ ሰዓት፡ [ሰዓት 2፡20—3፡30] አይለፍዎ! ▪️ በወቅታዊነት የምናነሳው ነጥብ ይኖረናል፡፡ ኮሜርሻል ኖሚኒስ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ማህበር በአዲስ መልክ ሌሎች የስራ መስኮች ላይ ሊሰማራ መሆኑን አስታውቋል። የራሱን ባለሙያዎች ጨምሮ የበላይ አካላትን እና የደንበኞቹን ሙያዊ ብቃትና የሥራ አፈጻጸም አቅም ለማሳየት የሚስያችል የሥልጠና ማዕከል በማደራጀት ለአገልግሎት ዝግጁ አድርጓል። ስለማሰልጠኛ ተቋሙ ግንባታ ሂደት ሌሎቸም ጉዳዮች ጋር ከተቋሙ ዋና ስራ አስፈፃሚ ኮማንደር ጥላሁን ፀጋዬ ጋር ቆይታ አድርገናል። 📞☎️📩 የምታነሱት ሀሳብ አስተያየትና ጥያቄ 👉 📞0974466655 ላይ አድርሱን፡፡ ⏰⏱️📻ከ2፡00 — 3፡30 ሰዓት በአሀዱ ሬድዮ 94.3 ላይ በቀጥታ ስርጭት ፕሮግራሞቻችንን ትከታተሉ ዘንድ ከወዲሁ በአክብሮት እጋብዛለሁ፡፡                      መልካም ምሽት! https://t.me/ethioconradio

👉 የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዋና ዋና ስኬቶች
👉 የከተማና መሠረተ ልማት ሚኒስቴር የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ዋና ዋና ስኬቶች

🔲 AFRICA HALL GUIDED TOUR
🔲 AFRICA HALL GUIDED TOUR

✴️ጨረታ አዲስ ዘመን ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid
✴️ጨረታ አዲስ ዘመን  ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ. ም ዕትም ላይ የተወሰደ https://t.me/ethioconbid

🏗 የግንባታ ወጪን የሚቀንሱ 5 መንገዶች 1. የተሟላ ፕላን ከስራ መጀመርዎ በፊት ያዘጋጁ። 2. ቁሳቁስን በአግባቡ ያከማቹ፡፡ 3.የሰራተኞችን ስራ በየቀኑ ይቆጣጠሩ። 4. የቁሳቁስ ብክነትን ይቀንሱ፡፡ 5. የጥራት ቁጥጥርን ከመጀመሪያው ይተግብሩ። 👉 ከመጀመሪያው የተሰራ የጥራት ስራ ከኋላ ከሚደረግ እርማት ያነሰ ወጪ ይጠይቃል። ለተጨማሪ የግንባታ እውቀቶች ቻናላችንን ይከታተሉ! https://t.me/ethioconradio

🔵 በውል አስተዳደር (Contract Management) የሚከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት 🔷  ውል ከተዋዋሉ ቀን ጀምሮ የተሸናፊና አሸናፊ ተጫራቾች የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) እንዲመለስ ይደረጋል፣ የጨረታ ማስከበሪያ (Bid Bond) ጊዜውን እየጠበቀ የማራዘሚየ ደብዳቤ እያዘጋጀ እንዲራዘም ይደረጋል፡፡ 🔷  የውል ማስከበሪያ (Performance Bond) ይቀበላል፣ ይይዛል፣ያስተዳድራል፣ 🔷  በአገር ውስጥ ጨረታ ጊዜ ዕቃውን ከተረከበ በኋላ ከ5 እስከ 10 ባሉት ቀናት ውስጥ አስፈላጊውን የክፍያ ሁኔታ ያመቻቻል ወይም እንዲመቻች ያደርጋል፡፡ 🔷  በአለም አቀፍ ጨረታ የሚፈፀም ግዥ (ICB) ከሆነ ሌተር ኦፍ ክሬዲት (l/C) ይከፍታል፣ወይም በተጠቃሚ መ/ቤቶች እንዲከፈቱ አስፈላጊውን ነገር ሁሉ ያመቻቻል፣ ሂደቱንና ዕቃውን ከተጫነበት አንስቶ እስከ ርክክብ ያለውን ሁኔታ እየተከታተለ መረጃዎችን ለተጠቃሚው መ/ቤት ያቀብላል፡፡ 🔷 የትራንዚትና ክሊሪንግ ሥራዎችን ተከታትሎ ያስፈፅማል፣ ሰነዶችንም በአግባቡ ይይዛል፣ ያደራጃል፣ 🔷  ለመ/ቤቶች የተገዙትን ዕቃ በሚፈለገው ስፔሲፊኬሽን መሰረት መቅረቡን በባለሙያ አስፈላጊውን ምርመራ እንዲደረግ ሁኔታዎችን ያመቻቻል፤ ከምርመራ በኋላ አስፈላጊውን የዕቃ ርክክብ እንዲፈፀም ያደርጋል፤ 🔷 በአገልግሎቱ የተገዙት ዕቃዎች (አገልግሎቶች) በውሉ መሰረት ለተጠቃሚዎች መድረሳቸውን ይከታተላል፣ ያረጋግጣል። https://t.me/ethioconradio

🔲 የዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ዓላማዎች ምንድን ናቸው? ▶️ የዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ዋና ዓላማ የመንግስት ወጪ ዘላቂ ልማትን እንዲደግፍ ማድረግ እና የመንግስት ገንዘብ ተመጣጣኝ ዋጋ (Value for Money) እንዲያገኝ ማስቻል ነው፡፡ ይህ በእንዲህ እንዳለ ሌሎች ዝርዝር ዓላማዎች ይኖሩታል፡፡ እንዚህም የመንግስትን ሀብት በብቃት መጠቀምን ማበረታታት፣ አካባቢን መጠበቅ፣ ማህበራዊ ፍትሃዊነትን እና የሰብአዊ መብቶችን መደገፍ፣ ዘላቂ የኢኮኖሚ ዕድገትን ማበረታታት፣ ግልጽነትን እና ተጠያቂነትን ማጠናከር፣ ፈጠራን እና አረንጓዴ ቴክኖሎጂዎችን ማበረታታት፣ ሀገር በቀል ተቋማትን እና አነስተኛ ድርጅቶችን መደገፍ እና ሌሎች ተያያዥ ጉዳዮችም ሊጠቀሱ ይችላሉ፡፡ ▶️ ስለሆነም ይህ የግዥ ስርዓት የመንግስት ተቋማት የሚጠቀሙት ዕቃዎችን እና አገልግሎቶችን ለማግኘት ብቻ ሳይሆን ሰፋ ያሉ የብሔራዊ ልማት ግቦችንም ለማሳካት ጭምር እንደሆነ የሚያስገነዝብ ነው። በዋናነት የዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ ነው። ዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ሦስት ዋና ዋና ጉዳዮችን ታሳቢ ያደረገ ነው ሲባል ምን ማለት ነው? ▶️ ዘላቂ የመንግስት ግዥ (Sustainable Public Procurement) ከአንድ አቅጣጫ ብቻ የሚታይ አይደለም፡፡ ማለትም ግዥውን ለመፈጸም ዝቅተኛ ዋጋን እንደ መስፈረት መውሰድ በቂ አይደለም፤ የእቃውን ጥራትም እንደ ግዥ መስፈርት ወስዶ ግዥውን መፈጸም በቂ አይደለም፡፡ ይልቁንም ግዥውን ለመፈጸም ከላይ ከገለጸናቸው መስፈርቶች በተጨማሪ ያለውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሚታ፣ በአካባቢ ላይ ተጽዕኖ የማያሳድር መሆኑ፣ ማህበራዊ አገልግሎት ላይ ያለው አስተዋጽዖ፣ አረንጓዴ ልማትን መድገፍ የሚያስችል መሆኑና ሌሎች መሰል መስፈርቶች ከግምት ውስጥ የሚገቡ ናቸው፡፡ በዝርዝር ለመመልከት ያህል፦ ▶️ የኢኮኖሚ ዘላቂነት (Economic sustainability)፦ የኢኮኖሚ ዘላቂነት በምርቶች እና በአገልግሎቶች የህይወት ዑደት ውስጥ ለተከፈለው ገንዘብ ተመጣጣኝ ዋጋ (Value for Money) ማረጋገጥ ላይ ያተኩራል። ይህም የወጪ ውጤታማነትን (Cost efficiency)፣ የጥራት ማሻሻያን (Quality improvement)፣ ዘላቂነትን (Durability)፣ የጥገና ወጪ መቀነስን  (Reduction of maintenance costs) እና የረጅም ጊዜ የፋይናንስ ቁጠባን (Long-term financial savings) መሰረት ያደረገ ነው፡፡ ስለሆነም በዚህ ሂደት ውስጥ የግዥ ባለሙያዎች የመግዣ ዋጋ ላይ ብቻ  አያተኩሩም ይልቁንም ከመግዣ ዋጋው በተጨማሪ የሥራ ማስኬጃ ወጪዎችን፣ የጥገና ወጪዎችን እና የማስወገጃ ወጪዎችንም ግንዛቤው ውስጥ ያስገባሉ። ▶️ የአካባቢ ዘላቂነት (Environmental sustainability)፡- የአካባቢ ዘላቂነት የግዥ ሂደቶች ግዥው በአካባቢ ላይ የሚያስከትለውን አሉታዊ ተፅዕኖ መቀነስ ላይ ያተኩራል። ከላይ ለመግለጽ እንደሞከርነው የሚገዙ ግዥዎች በአካባቢ ላይ ብክለትን የማያስከትሉ መሆናቸው መረጋገጥ ይኖርበታል፡፡ ይህን ስንል የሚገዙ ምርቶች ብክለትን የሚቀንሱ፣ ኃይልን የሚቆጥቡ፣ እንደገና ጥቅም ላይ ሊውሉ የሚችሉ ቁሳቁሶችን የሚጠቀሙ፣ የግሪን ሀውስ ጋዞችን የሚቀንሱ እና ታዳሽ ኃይልን የሚያበረታቱ መሆናቸው ግንዛቤ ውስጥ መግባት ይኖርበታል፡፡ ምክንያቱም የአካባቢ ተስማሚ ግዥ (Environmental Sustainability Procurement) የአየር ንብረት ለውጥን ለመቀነስ እና የተፈጥሮ ሀብቶችን ለመጠበቅ አስተዋፅኦ ያደርጋል። ▶️ ማህበራዊ ዘላቂነት (Social Sustainability):-  ማህበራዊ ዘላቂነት የማህበራዊ ደህንነትን ለማሻሻል እና ሥነ-ምግባራዊ የንግድ አሠራሮች ማረጋገጥ ላይ የሚያተኩር ሲሆን ፍትሃዊ የሥራ ልምዶች፣ የሰብአዊ መብቶች ጥበቃ፣ የሥራ ቦታ ደህንነት፣ የፆታ እኩልነት፣ የሥራ ዕድል ፈጠራ እና ለተጋላጭ ቡድኖች ድጋፍ መስጠትን የሚያበረታታ ነው፡፡ (መግባ) https://t.me/ethioconradio

* ዜና ዕረፍት * በደርግ ዘመነ መንግሥት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በመምራት የሚታወቁት አቶ ካሳ ገብሬ ከዚህ አለም በሞት ተለዩ። አቶ ካሳ በ92 ዓመት እድሜያቸው ይኖሩበት በነበረው አሜሪካ ሀገር ህይወታቸው ያለፈው በዛሬው እለት ነው። ኢንጂነር ካሳ ገብሬ ከኢትዮጵያ ህንፃ ኮሌጅ በሲቪል ምህንድስና ካናዳ ሀገር በሚገኘው የብሪቲሽ ኮሎምቢያ ዩኒቨርሲቲ የአንድ ዓመት የድህረ ምረቃ ትምህርታቸውን መከታተላቸውን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። በትምህርት ሚኒስቴር በዋና መሃንዲስነት፣ በቤቶችና ከተማ ልማት ሚኒስቴር ሚኒስትርነት፣ በኤርትራ የጠቅላይ ግዛቱ ዋና መሃንዲስ፣ በሕንጻ ኮንስትራክሽን ሚኒስትርነት እና በተለያዩ ከፍተኛ የመንግሥት ኃላፊነቶች እስከ ደርግ ስርዓት ማብቃት ድርስ አገልግለዋል።  ኢንጂነር ካሳ በደርግ ስርዓት ወቅት የተሰሩ ትላልቅ ፕሮጀክቶችንም መርተዋል። በሶማሌ ወረራ ጦርነት ወቅት ህዝባዊ ሠራዊት የሰለጠንበትን የታጠቅ ጦር ሜዳ ግንባታ  በአጭር ጊዜ ውስጥ ማዘጋጀታቸው  ከሚጠቀስላቸው ስራዎቻቸው መከከል ይገኝበታል። የጀግኖችና ህፃናት አምባ ምስረታዎች ወቅት የግንባታ ዘርፉን መርተዋል። የጣና በለስ ግድብ፣ የቀይ መስቀል ሕንጻ፣ ዋቢ ሸበሌ ሆቴል፣ ፍልውሃ ሕንጻዎች፣ አክሱም ጽዮን ቤተክርስቲያን፣ በርካታ የከተማ ፕላኖችና ድልድዮች ከታላላቅ ሥራዎቻቸው መካከል ይጠቀሳሉ። በዚህም ጉልህ አስተዋጿቸው ለዘመናዊቷ ኢትዮጵያ ግንባታ ከመሠረት ጣዮች መካከል አንዱ ተደርገውም ይነሳሉ። አገሪቷ ከፍተኛ የድርቅ አደጋ ውስጥ በገባችበት ወቅትም ዜጎችን ድርቅ ካለበት ወደ ድርቅ ወደሌለበት አካባቢ በማዛወር ከእልቂትና ከረሃብ አደጋ በመታደግ ትልቅ ሰብዓዊ አስተዋፅኦ ማበርከታቸውምን የህይወት ታሪካቸው ያስረዳል። ኢንጂነር ካሳ በኢህአዴግ መንግሥት ዘመን 12 ዓመት ከ3 ወር ታስረዋል። ከእስር ከተፈቱ በኋላ አብዛኛውን ኑሯቸውን ያደረጉት በአሜሪካ ሀገር ሲሆን መጽሐፍ ጽፈው አጠናቅቀው፣ ግን ለሕትመት ሳይበቃ አረፈዋል። አቶ ካሳ ገብሬ የሁለት ወንዶች እና የሁለት ሴቶች ልጆች አባትም ነበሩ።   በ92 ዓመት እድሜያቸው ዛሬ ከዚህ ዓለም በሞት የተለዩት ኢንጂነር ካሳ ገብሬ የቀብር ስነስርዓታቸው በአሜሪካን ሀገር ዋሺንግተን ዲሲ በሚገኘው ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ካቴድራል፣ ሰኞ ግንቦት 24 ቀን 2018 ዓም፣ በአገሩ ሰዓት አቆጣጠር ከጠዋቱ በ3:30 ሰዓት የሚፈፀም ሲሆን በአዲስ አበባ የመታሰቢያ መርሃግብር በቀጣይ ቀናት ይደረግላቸዋል ተብሏል። 👉 ለቤተሰቦቻቸው፣ ለወዳጅ ዘመዶቻቸው መፅናናትን እንመኛለን። https://t.me/ethioconradio

👉 ኢ/ር ካሳ ገብሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።
👉 ኢ/ር ካሳ ገብሬ ከዚህ ዓለም በሞት ተለዩ።