cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

Inaya (ዒናያ) የመንዙማ ስንኞች ▢

💚💚💚💚💚💚💚💚 መላይካው በነቂስ ወከበ ዘለለ አርሽና ኩርስዩን ፈርሀን ተመየለ ዙልማት ተገፎ ኑር ኑርን አከለ ተወለዱ እያለ የጅብሪል ባለሟል :የኔ ነቢ ﷺ ... አስተያየት ካላቹ @Sadatochu https://t.me/+ayKCEp3lSvllMDNk

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
1 283
مشترکین
-224 ساعت
+17 روز
-530 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

#ኢስነይን🥰 "ለይል መቆምና ፆም ማብዛት ያመለጠው ሰው በነብዩ ሙሀመድ ሶለዋቱ ረቢ ወሰላሙሁ ዐለይህ ላይ ሶለዋት በማለት ነፍሱን መሽጙል ያድርግ::"💚💙 ኢብን ዐጧኢላህ አስ-ሰከንደሪ ቀደሰላሁ ሲረሁ 💚
نمایش همه...
🥰 7 2
#ለይለቱል ጁሙዐህ اللَّهمَّ صلِّ صلاةً كاملةً، وسلِّم سلامًا تامًّا، علىٰ نبيٍّ تنحلُّ به العقدُ، وتنفرجُ بهِ الكُرَبُ، وتُقْضَىٰ بهِ الحوائجُ، وتُنالُ بهِ الرَّغائبُ، وحسنُ الخواتيم، ويُسْتَسْقىٰ الغمامُ بوجههِ الكريم، وعلىٰ آلهِ.♥
نمایش همه...
3👍 1
#ኸሚስ_አመሻሹ_ላይ! ሙሐመድ ባለ‘ጣው አምሳያው የታጣው! ሲፈጥራቸው ገር አድርጎ ነው። ስብእናቸው ግሩም ነው። የልባቸው አሠራር እንኳን ሰሚን ታዳሚን ያደናገረ ነበር። ማዲሖቻችን "ሰው ነው ይላሉ እንጂ አይደለም እንደሰው" ይሉ ዘንድ የማንነታቸው ልክ ረቂቅ ነው። እንኳን የሚበልጣቸው አምሳያም አይገኝላቸውም። የመልካም ስነ‐ምግባር ቁንጮው እና ዓይነታው ተደርገዋል። ደግሞም ለእዝነት አባቱ ናቸውና ምስያ የላቸውም። ማንነታቸውን ወስፍልን ብለን ከባልደረባቸው አንዱን ብንጠይቀው እንዲህ ይለናል። ከእለታት አንድ ቀን አንድ አይ^ሁድ ሞቶ በአጠገባቸው ጀናዛውን ተሸከመው ሰዎች አለፉ። እኚህ አዛኝ ነቢ ታዲያ ነገሩን አወቁትና በእዝነትም በድንጋጤም ከተቀመጡበት ብድግ ብለው አለቀሱ። "ምነው የአላህ ነቢ?በክህደት ለሞተ ሰው ምን ቢሉ አለቀሱለት? " አሏቸው። "አንዲት ነፍስ ከእጄ አመለጠችኝ" ሲሉ ምክንያታቸውን ነገሯቸው። ይህ ወስፍማ አይበቃንም። ረጃእ መሰነቅን ለምትወድ ቀልብ ቀለብ ናቸውና እስቲ ሸራቡን በጥልቁ እንጎንጨው። ሰይድ ወሕሽይን እኚያ ነቢ ምን ቢሉህ ሰለምክ? እስኪ ወስፉን ሰጥርልን አንተ ወሕሽዩ ብንለው የኡሁድን ዘመቻ ያወሳል። የአላህን አንበሳ ሰይድ ሐምዛን በቀስቱ ወግቶ ከመሬት የጣለባትን ቅፅበት አይዘነጋም። የአላህን ነብይ ወንድም፣ አጎት፣ መከታ፣ ጋሻ ሩሕ በአንዲት ጦር ወደ ዘላለማዊ ሐገሯ ሸኛት። ወቅት አለፈና መካ በድል ተከፈተች። በነብዩ አስተዳደር ስር ወደቀች። ዳግም ወደ ሐኒፍ መንገዷ ተመለሰች። ዕለቱማ በሶሀቦች ዘንድ የበቀል እለት ነበረ። በአዛኙ ነብይ ዓይን ደግሞ የምህረት ቀን ነው። "ሒዱ፣ ከቅጣት ነፃ ናችሁ" በሚል የተስፋ እና የሀሴት ውሳኔ ነፃ አወጧቸው። በዚህ አላበቃም ለኢስላም ተጠሩ። ደግሞስ ቀላጣው ገበር የአላህን ሸእኑን ያውቁታልና ወሕሽዩን በግል አነጋገሩ፣ የኢስላምን ጥሪ አግራሩ፣ ሸሪዓውን አሳመሩ፣ በፀፀት የቆሰለ ደመኛቸውን በምህረት አሻሩ፣ ሐገርን አደናገሩ። ይበልጥ የዓጀበንማ የዚያ ምስኪን ጥቁር ድርጊት ነበረ። አራት የተለያዩ አንቀፆችን በእርሱ ሰበብ አስወረደ። ሙሉ ዋስትናን ከነብዩም ከአላህም እስኪያገኝ ድረስ ተሟገተ። ነብዬዋም ታግሰው የመሻቱን ሞሉለት። ሆነለት። ለእርሳቸውም ሆነላቸው። ሰይድ ሐምዛ ከሰይድ ወሕሽይ ጋር በጀነት ከተማ ሲተቃቀፉ አላህ በሹሁድ ዓለም ዘረጋላቸው። ከተጀሊው ባህር የጠለቁትን ስናወጋቸው በጣሙን ለጉድ አስዓጀቡን። ሰይዳችን መካን ሳይቆጣጠሩ ቀድመው ሱብሒ ሰግደው «የኔ ጌታ አላህዋ፣ የወንድሜን ደም ቀምሳለች፣ ከጉበቱ ጎርሳለች፣ ዛቱን ከዛቷ አዋህዳለች። የወንድሜን ደም የተሸከመች ነፍስ እና ጀሰድ ለእሳት አትዳርግብኝ» ብለው ተማፀኑ እና መልሱን ሰይድ ጅብሪል ይዘውላቸው መጡ። ከአላህ ዘንድ ማህተም ተመታላቸው። ተረጋገጠላቸው። ሂንድ ሰለመች። ተስፈኛው ነቢ ያሰቡትን የሰነቁትን ሁሉ ከአላህ አገኙ። ጨርሰውም አልደከማቸውም። አይታክቴው ነቢ መች በዚህ ያበቃሉ። ማዒዝ አል‐አስለሚይ ወደ ዘይኑል ውጁድ መጣና "ያ ረሱለሏህ ዝሙት ፈፅሜያለሁ እና የአላህን ቅጣት ፈፅምብኝ" አላቸው። ዝም አሉት። እርሱ ግን ደጋገመው። ይህኔ እጅጉን ራሩለትና "ምናልባት የአዕምሮ ህመም ይኖርብህ ይሆን? " አሉት። "የለብኝም" ቢላቸውም በጅ አላሉም ቤተሰቦቹን አስጠየቁና ደገሙላቸው። "ምናልባት ስመሃት ወይም ተነካክተህ ብቻ እንዳይሆን" ብለው ከሞት ሊታደጉት ጠየቁት። "የለም በትክክል ወቅዴያለሁ" አላቸው። የተቻላቸውን ሁሉ ከሞከሩ ኋላ ፍርድ ተፈፀመ። ሐድ ቆመበት። እንዲህ የሚራሩቱ ነብይ ሐለታቸው ከእለት እለት እየባሰ ቢሄድ ጊዜ የኸለቃቸው ጌታቸው ራሱ "እነርሱ አላመኑ እንደሆነ ታዲያ ራስህን በሀዘን ብዛት ልትጎዳ ነውን?" ሲል ወቀሳቸው። ይህም አልገደባቸውም ባዘኑ። "የኔ ውድ ነብይ የተቀረውን ኡመትህን በፍርዱ ዕለት ማልደኝ እማልድሃለው" ሲል በቃሉ አስደሳቸው። ይቅርታ የነገሰባቸው፣ ምሕረት የፈሰሰባቸው ውዱ ነብይ ሶለዋት እና ሰላም በዝቶ ይጉረፍባቸው። #ሶሉ_ዓለል_ሐቢብ! አሏሁመ ሶሊ ወሰሊም ወባሪክ ዓላ ሰይዲና ወመውላና ሙሐመድ ወዓላ አሊሂ ወሶህቢሂ ወሰለም!💚💚💚 Atiqa Ahmed Ali
نمایش همه...
👍 1 1🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
👍 6 2👌 2
ሰይድ አበራሙዝ ቀደሰላሁ ሲረሁ ለሙሪዶቻቸው ለአምዋት ሰደቃ መስጠት ወእዝ ሲያደርጉላቸው አንድ ሸህ ነበር ደረሶች ነበሩት ሁሉንም ደረሳዎቹን ቦታ ቦታ አስይዘዋል (ለሸህነት አድርሰዋቸዋል) አንዱ ደረሳቸው ሲቀር አንድ ጊዜ ሲታመሙ ያደረሳ ማልቀስ ይጀምራል እሳቸውም ለምን ታለቅሳለክ ብለው ሲጠይቁት ሁሉም ደረሶች ሸህነት ወተዋል እኔ ብቻ ስቀር እርሶም ደግሞ ሊያልፉ ነው አላቸው ሸሁም አብሽር አንተ ደሪሄ ላይ እየመጣክ ትቀራለክ ይሉታል.. ሸሁ ካለፉ በኋላ ደረሳው ወደ ደሪሀቸው እየሄደ ኪታብ ገልጾ ሲቀራ ይፈስሩለታል ታዲያ በመሀል አንድ ቀን ወደ ደሪሀቸው ተጠግቶ ያ የተለመደውን ቂርአቱን ሲጀምር ምንም ድምፅ አልሰማ አለው ደጋግሞ ቢቀራም የሸሁ ድምፅ ሌላ ቀን እንደለመደው አልሰማ አለው ተነስቶ ወደ ቤቱ ይመለሳል በንጋታው ኪታቡን ይዞ ወደ ደሪሁ ተጠግቶ ዝም ብሎ ቂርአቱን ሲጀምር ሸህየው ትላንት የት ነበርክ ብለክ አትጠይቀኝም እንዴ አሉት ሸህየው ትላንትማ አንድ ሰውዬ አንድ ባቄላ ቀቅሎ ለጀሚኧል አምዋት ብሎ ሰደቃ ሰጠው ከዛ ሰደቃ ድርሻዬን ልቀበል ሄጄ ነው ከሰደቃው 27/28 ቁና ነው የደረሰኝ አሉት ። በዛሬዋ በጁምዓ ቀን ቤተሰብ ዘመድ ጓደኛ ከኛ ጋር ለነበሩ ለተለዩን ሰዋብ እናድርስላቸው اللهم صَلِّ على سيدنا محمد صاحب المقام المحمود ، والمكان المشهود ، الموصوف بالكرم و الجود ، بإلهام من الملك المعبود عدد ما أحاط به علمك وجرى به قلمك وسبقت به مشيئتك وصلّت عليه ملائكتك ، صلاةً دائمة بدوامك باقية بفضلك وإحسانك إلى أبدِ الأبدِ ، صلاة تفتح لنا بها ما أُغلق علينا من أبواب المقاصد ، ويُلهِج لك ألسنتنا بأسنى المحامد ، وتحبّبنا بها الى كل ولي لك ذاكر حامد ساجد وعلى آله وصحبه وسلم تسليما...
نمایش همه...
4
رَبِّ اشْرَحْ لِي صَدْرِي بِماَ شَرَحْتَ بِهِ صُدُورَ الصَّالِحِينَ مِنْ عِبادِكَ ، ويَسِّرْ لِي أمْرِي بما يسرت به أمور الصَّالِحِينَ مِن عِبَادِكَ ، وَسَدِد لِسَانِي بِما سَدَدتَ بِهِ أَلسِنَة الصَّالِحِينَ من عبادك ، واهد قلبي بِما هَدَيتَ بهِ قُلوبَ الصَالِحِين من عبادك بِحَق سَيدنا مُحمَّد صلى الله عليه وسلم 📌📌አላህ ሆይ! የደጋጎችን ባሮችህ ልብ ባሰፋህበት ነገር ልቤን አስፋልኝ። የደጋጎች ባሮችህ ጉዳይ ባገራሕበት ነገር ጉዳዬን አግራልኝ። የደጋግ ባሮችህ ምላስ ባቃናህበት ነገር ምላሴን አቃናልኝ። የደጋጋግ ባሮችህ ልብ በመራህበት ነገር ልቤን ምራልኝ። ቢሐቂ ሰይዲና ሙሐመድ ሰለላሁ ዓለይሂ ወሰለም።
نمایش همه...
13
Jumea mubarek 💚
نمایش همه...
12👍 3