917
مشترکین
+124 ساعت
+57 روز
-330 روز
آرشیو پست ها
ሚያዚያ 16/2018 ዓ/ም
ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ የኢትዮጵያ ግሎባል ቴካንዶ ፌደሬሽን ፕሬዝዳንት ለገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እግር ኳስ ክለብ የመለያ ድጋፍ አደረገ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በድጋፉ እና በርክክብ ወቅት የወረዳው ምክትል አስተዳደሪ ወ/ሮ ዘይነብ ወራቄ፣ የወጣቶችና ስፖርት አመራሮችና ባለሙያዎች እንዲሁም እስፖርተኞች ተገኝተዋል።
በድጋፉ ጊዜ ኢንስትራክተር ሳቦም መሀመድ መኪ ለስፖርተኞቹ በስፖርቱ ዘርፍ ጠንክረው እንዲሰሩና የአካባቢያቸው ስም ከፍ ብሎ እንዲጠሩ እንዲሁም በወረዳው የሚገኙ ስፖርተኞች በሊግ እንዲሁም በብሄራዊ ቡድን ሊሳተፉ የሚችሉ ተጫዋቾች መፍለቂያ መሆን እንዳለበት ጠቅሰው እንዲሁም ልምዳቸውን በማካፈል ቀጣይም ክለቡ ለመደገፍ ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል።
ስፖርተኞችም ለተደረገው ድጋፍ አመስግነው ቀጣይ የተጣለባቸውን ሀላፊነት ዝግጁ መሆናቸውን ገልፀዋል። የወረዳው ምክትል አስተዳዳሪ ወ/ሮ ዘይነብ ወራቄ ለተደረገው ድጋፍ በወረዳው መንግስት ህዝብ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ሚያዝያ 15/2018 ዓ.ም
ባለፉት 5 ዓመታት በመንግስት፣ በባለሀብት፣ በግብረ ሰናይ ድርጅቶችና በማህበረሰብ ተሳትፎ ከ224 ሚሊዮን ብር በማሰባሰብ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ፅህፈት ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ውሃ ማዕድን ኢነርጂ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ አብድል ጀሊል ቱሉ እንደገለፁት፤ ባለፉት አምስት ዓመታት የወረዳችንን የንፁህ መጠጥ ውሃ ለማሻሻልና የማህበረሰቡን የውሃ መሠረተ ልማት ጥያቄዎችን ደረጃ በደረጃ ለመመለስ ከመንግስት፣ መንግስታዊ ካልሆኑ ድርጅቶች፣ ከልማታዊ ባለሀብቶችና ከማህበረሰቡ ተሳትፎ በተሰራው ከፍተኛ ስራ በዘርፉ አበረታች ውጤት እየተመዘገበ መሆኑን ገልፀዋል።
ባለፉት አምስት ዓመታት ከመንግስት፣ ከባለሀብት፣ ከግብረሰናይ ድርጅቶችና በማህበረሰብ ተሳትፎ ከ212 ሚሊዮን ብር በላይ ብር በማሰባሰብ የተለያዩ ስራዎች ሲሰሩ መቆየታቸውን ገልፀው፣ ከነዚህም የጥልቅ ጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ፣ የታንከር ግንባታ፣ የምንጭ ውሃ ማጎልበትና የትቦ ዝርጋታ ስራ በመስራት ህብረተሰቡን የንፁህ ውሃ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
አቶ አብድልጀሊል አክለውም ባለፉት አምስት አመታት በወረዳ በጀት ከ33.5 ሚሊዮን በላይ በጀት በመመደብ የተለያዩ ሰራዎችን መስራቱ ገልፀው ከተሰሩ ስራዎች መካከል ወለጋዲሴ የምንጭ ግንባታና ማስፋፊያ፣ፍቴ ምንጭ ግንባታ፣የገሬኖ የጥልቅ ጎድጓድ ውሃ እና ዝርጋታ፣ዘ/ሰፋቶ ውሃ ማስፈፊያ፣አበዘት ጤና ጣቢያ ቦኖ፣ሁትር ቀበሌ ነባር ውሃ፣የኢንጌ ከተማ የውሃ ታንከር እና የውሃ መስመር ዝርጋታ ፣የጅማ ከተማ ውሃ ወደ መብራት መቀየር ፣የአረዳ የምንጭ ግንባታ፣መጎራጉር የምንጭ ግንባታ፣ጠይብ ምንጭ ግንባታ፣የከብር ሚዴ የውሃ ቱቦ፣ እሬሶ የምንጭ ግንባታና ማስፋፊያ፣ቀቻ ውሃ ማስፋፊያ፣እንደብዮ ውሃ ግንባታ ፣ገርጋራ ታንከር ግንባታ ከነ ቦኖ እና ዘልዋን ሰፋቶ ማስፋፊያ ውሃ ባለፉት አምስት አመታት መገንባታቸው ተናግረዋል።
በክልሉ መንግስት ከ18 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ደነብ ቀበሌ ዘመናዊ መስኖ ተገንብቶ አገልግሎት እየሰጠ መሆኑን ጠቅሰው የዞኑ መንግስት ከ4 ሚሊዮን ብር በላይ የገሬኖ ቦልጫመኝ የጥልቅ ጉድጓድ ውሃ በ40 ሚሊዮን ብር መገንባቱን ተናግረዋል።
በአካባቢው ተወላጅ ባለሃብትና የሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስራስኪያጅ በአቶ ጀማል አህመድ አማካኝነት ከ140 ሚሊዮን ብር በላይ ብር በመመደብ ለመሀል አምባና ዙሪያው ላሉ አካባቢዎች ሶስት የጥልቅ ጉድጓድ ውሃ ቁፋሮ፣2 የታንከር ግንባታ፣12 ኪ.ሜ መስመር ዝርጋታና 3 ትራንስፎርመር ሙሉ ወጪ መሸፈን የህብረተሰቡን የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግር መቅረፍ መቻሉን ገልፀዋል።
በሚዛን ሰላም ማህበር ግብረ ሰናይ ድርጅት ከ10 ሚሊዮን ብር በላይ ለከንትዋት ቀበሌ ጥልቅ የንጹህ መጠጥ ውሃ እና ሰልማ የተሰኘ ኢስላሚሚክ ግብረ ሰናይ ድርጅት በ700 ሺህ ብር ለዘልዋን ሰፋቶና ቦሮቦር ሰፋቶ ቀበሌዎች ነባር ውሃ ማስፋፊያ በማድረግ ሰፊ የማህበረሰብ ችግር የነበረውን የንጹህ መጠጥ ውሃ በመቅረፍ የአካባቢው ህብረተሰብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል።
በዋን ወሽ ፈንድ ከ18 ሚሊዮን በላይ ብር ድጋፍ በማድረግ የኮምበል የንፁህ መጠጥ ውሃ ችግርን በዘላቂነት ለመፍታት የጥልቅ ጉድጓድ ቁፋሮ ተከናውኖ የመስመር ዝርጋታ ለማከናወን በሂደት ላይ መሆኑንም አቶ አ/ጀሊል ገልጸዋል።
ከ4 መቶ 88 ሺህ በላይ ብር በህብረተሰብ ተሳትፎ እሬሶ ምንጭ ግንባታ ማስፋፊያ ፣ጥላሞ ምንጭ ግንባታ ፣ቀቻ ምንጭ ግንባታ ፣ሰፋቶ ቀርሳ እና የጠይባ ቀበሌ የምንጭ ግንባታ እና ማስፋፊያ ስራ መሰራቱን ተመላክቷል።
በወረዳው የውሃ ተቋም ባለባቸው የገጠር ቀበሌዎች ውስጥ ለሚገኙ ለጤና ፣ለትምህርት እና ለእምነት ተቋማት የንፁህ መጠጥ ውሃ ተጠቃሚ እንዲሆኑ መደረጉን የገለጹት አቶ አ/ጀሊል በወረዳው የመንግስት ድጋፍ በጀነሬተር የሚንቀሳቀሱ የኢንጌ እና የጅማ ከተማ የውሃ ተቋማት ወደ ትራንስፎርመር የመቀየር ስራ መሰራቱንም አስታውቀዋል።
በመጨረሻም የውሃና ማዕድን ኢነርጂ ጽ/ቤት ኃላፊ አቶ አብድል ጀሊል ቱሉ የንፁህ መጠጥ ውሃ ተደራሽነትን ለማስፋትና የንፁህ ውሃ ተጠቃሚነትን ለማረጋገጥ በትኩረት እንደሚሰራ ገልፀው፤ የህብረተሰቡን የንፁህ ውሃ ችግር በዘላቂነት ለመፍታት በየደረጃው ላሉ ተወላጅ ባለሀብቶች፣ የግብረሰናይ ድርጅቶችና ማህበረሰቡ ላደረጉት አስተዋፅኦ አመስግነው
እንደ ወረዳ የንፁህ መጠጥ ውሃ ሽፋን 31.74% በመሆኑ በቀጣይ መሰል ድጋፎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ሁሉም የበኩሉን እንዲወጣ ጥሪ አስተላልፈዋል።
ሚያዝያ 13/2018 ዓ.ም
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ጉባኤ ተካሄደ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ያለፉት 9ወራት ያከናወናቸው ተግባራትና የቀሪ ዓመታት ዕቅድ ማፅደቅ ላይ ያተኮረ ከምክር ቤቱ አባላት ጋር ውይይት አደረገ።
የዕለቱ የመወያያ ዕቅድና ሪፖርት በአቶ ናስር ጫካ
ቀርቦ ባለፉት 9 ወራት በእስልምና ጉዳይ ምክር ቤት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት በወረዳው ውስጥ የሚገኙ መስጂዶች ፣የመቃብር ስፍራ የዳዕዋ ትምህርት ተቋማትና መርከዞች ያሉበት ሁኔታ ቅኝት በማድረግ ሀይማኖታዊ አስተምህሮት ለማጠናከር የቁራዓን፣ የሀዲችና ሀይማኖታዊ መፅሐፍት እጥረት በማሰባሰብ እጥረት ላለባቸው አከባቢዎች ተደራሽ ማድረግ መቻሉ ፤ሙስሊም የህብረተሰብ በአገልግሎት እጦት እንዳይገላታ የቀብርና የመስጂዶች በመጡ ጥያቄዎች መሰረት ምላሽ መስጠት መቻሉ፤ከሁሉ ቤተ እምነቶች ጋር የተቀናጀ ውይይት መደረጉ በሪፖርቱ ተመላክቷለ።
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ እስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ዋና ሰብሳቢ ሼህ አብድልበር ዘይኑ በጉባኤው ባስተላለፉት መልዕክት ባለፉት ዓመታት ለሕዝበ ሙስሊሙ ብቻ ሳይሆን እንደ ወረዳ የሚጠቅሙ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ተናግረዋል። በወረዳች ውስጥ ያሉ መስጂዶች ያለባቸው የግብዓት እጥረት ለማሟላት ሁሉም የምክር ቤቱ አባል ወክለው ከመጡበት አከባቢና ህብረተሰብ ጋር ሀብት የማሰባሰብ
ስራ ግንዛቤ በመፍጠርና ሀብት የማሰባሰብ ስራ መሰራት መቻል እንዳለባቸው ፤ተናግረው እንደ ወረዳ ምክር ቤት የራሱ መስሪያ ቤት እንዲሁም የቲሞች ዚያራ ለተለያዩ ተግባራትን ለማስፈፀም እንደሚያስፈልግ ጠቅሰው ይህንን ለማሳካት አቅም በፈቀደ መልኩ ጥረት ማድረግ እንደሚገባ አስታውቀዋል ።
ምክር ቤቱ ቀጣይ ላይ በተጠናከረ መልኩ ሪፖርትቶች ተገምግመው ውሳኔ ለማሳለፍ የሚካሄደውን ጉባኤ ወሳኝ በመሆን ለጉባኤው መሳካት የምንሰራቸው ሀይማኖታዊ ተግባር አጠናክሮ ማስቀጠል ይገባል ሲሉ ተናግረዋል።
በገጠሩ የህብረተሰብ ክፍል እና በወረዳችን ያሉትን የእስልምና ልህቀት ማእከላትን የማጠናከር ስራ ለነገ የማይባል በመሆኑ ድጋፍና ክትትል ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
ሚያዚያ 13/2018 ዓ.ም
የወረዳችን ሰላም እና ደህንነት ለመጠበቅ የሀይማኖት ተቋማት ኃላፊነት የጎላ በመሆኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ
በሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው በገ/ጉ/ወ/ወረዳ በሰላምና ጸጥታ ጽ/ቤት አማካኝነት የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ በቀበሌ ለሚገኙ የሀይማኖት አባቶችና ባለድርሻዎች ያሳተፈ የግንዛቤ መድረክ በተካሄደበት ወቅት ነው።
የፅህፈት ቤቱ የሃይማኖት ዕምነት ጉዳዮች እሴት ግንባታ ዋና ስራ ሂደት አስተባባሪ ወይዘሮ አስቴር ዮሐንስ ለመድረኩ የተዘጋጀ መወያያ ሰነድ አቅርበው ውይይት የተደረገ ሲሆን ከሌሎች እምነት ተከታዮች ጋር በምንም ምክንያት ወደ ግጭት መግባት እንደማያስፈልግ፣ መከባበርን ይበልጥ አጠናክረን በማስቀጠል ለሰላም እሴቶች ግንባታ የሚጠበቅብንን እንወጣለን፣ሰርግ ቤቶች እስከ ሌሊት ጭፈራ መኖሩን፣ስለ ሰላም መስበክ የዕለት ተዕለት ተግባር መሆን እንደሚገባና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ መፍጠር እንደሚያስፈልግ እንደሚገባ ተሳታፊዎች ጠይቀዋል
የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ሰላምና ፀጥታ ፅፈት ቤት ኃላፊ አቶ ሙሰማ በድሩ በመድረኩ ተገኝተው ባስተላለፉት መልዕክት ለወረዳችን እድገት መሰረት የሆነውን ሰላም ለመጠበቅ ፀጥታን የሚያደፈርሱ ጉዳዮች አስቀድሞ በመለየትና የመፍትሄ እርምጃ በመውሰድ ረገድ ከሀይማኖት ተቋማትና ከህብረተሰቡ ጋር በቅርበትና በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን ገልፀዋል ።
አቶ ሙሰማ አክለው ህግ ለማስከበር የዕምነት ተቋማት ለመንግስት አጋዥ በመሆናቸው ከዘረኝነትና ጎጠኝነት ገለልተኛ መሆን አንደሚገባቸው አስታውሰው ፤መንግስት አጥፊዎችን የመቅጣት ህግን የማስከበር ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል ተናግረዋል።
የወረዳው የሃይማኖት ተቋማት ህብረት ሰብሳቢና የእስልምና ምክር ቤት ሰብሳቢ ሼህ አብድልበር ዘይኑ ከመድረክ ለተነሱት ሃሳብና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መካሄድ ከጀመረበት ጊዜ አንስቶ ዘርፈ ብዙ ተግባራት መከናወናቸውን ጠቅሰው ፣ሴት ልጅ ጠለፋ ላይ የተሰማሩ ደላሎች መኖራቸውና ይህ ለሰው ልጅ ክብር የሚነካ ተግባር በመሆኑ የእምነ አባቶች መሰል ድርጊቶችን ለመካከል ሚናቸው ከፍተኛ በመሆኑ በትኩረት መስራት አንደሚገባ አሳስበዋል
ሁለንተናዊ ትብብር በማጎልበት የወረዳችንና የሃገራችን ልዕልና ከዳር ማድረስ ይጠበቃል ያሉት ሼኸ አብድልበር ዕምነታችን የማይፈቅደው ተግባር በመተው ፤ሁሉም በየ እምነቱ በመከባበር እምነቱ መጠበቅ እንደሚገባ ጠቅሰው ዕምነትን እንደ ሽፋን በመጠቀም የራሳቸው አጀንዳ ለማራመድ የሚንቀሳቀሱ አካላት በተለያዩ አከባቢዎች ለሚፈፀመው ግፍና በደል በፅኑ አውግዘዋል።
የወረዳው የሃይማኖት ተቋማት ህብረት ምክትል ሰብሳቢ መጋቢ ሀይማኖት ሀብታሙ የኔው በበኩላቸው ጉባኤተኞች የግንኙነት አግባባቸውን በማጠናከር ጸረ-ሰላም ሃይሎች ሊያስከትሉ የሚችሉትን የሰላም እጦት አስቀድሞ መከላከል እንደሚገባ መልዕክት አስተላልፈዋል።
ፈጣሪ የሚያዘውን መልካም ስራ ልንሰራ እንደሚገባ የጠቆሙት ሀብታሙ የኔው፣በያለንበት እምነት ለሰዎች ሁሉ በጎ ስራን ልንሰራ ያስፈልጋል ሲሉ ምክራቸውን ለግሰዋል።
ሚያዚያ 12/2018 ዓ/ም
ከአጎራባች ወረዳዎች ጋር በቅንጅት መስራት ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከልና የህግ የበላይነት ለማረጋገጥ ሚናው ከፍተኛ እንደሆነ ተገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
ይህ የተገለጸው በኦሮሚያ ክልል ደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ፣ በማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በቀቤና ልዩ ወረዳና በጉራጌ ዞን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ አዋሳኝ ቀበሌያት ዘላቂ ሰላምና ወንጀልን አስቀድሞ ለመከላከልና የህግ የበላይነት ዙሪያ በጋራ በቅንጅት ለመስራት የሚያስችል የሶስትዮሽ ውይይት በዛሬው ዕለት ኢንጌ ከተማ ላይ በተከሄደበት ወቅት ነወ።
ከአጎራባች ወረዳዎች በድንበር አከባቢ በተለያዩ ምክንያቶች የሚፈጠሩ ወንጀሎችና የጸጥታ መደፍረስ ለመቆጣጠርና ቀጠናዊ ሰላምን ለማስፈን የውይይት መድረኩ ወሳኝ መሆኑ በመድረኩ የገለጸ ሲሆን ይህ አይነት የምክክር መድረክ ተጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባ ተመላክቷል።
የጋራ ጉዳይ የሆነውን ሰላምን ለማረጋገጥ ሁሉ ዓቀፍ ትብብርን አጠናክሮ ማስቀጠል ከሶስቱም አጎራባች ወረዳዎች እንደሚጠበቅ እና የማህበረሰቦችን በጋራ አብሮ የመኖር መስተጋብር በፅኑ መሰረት ላይ የተገነባ እንዲሆን ቅንጅታዊ አሰራርን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ በውይይት መድረኩ ተገልጿል፡፡
በምክክር መድረኩ ላይ የደቡብ ምእራብ ሸዋ ዞን ወሊሶ ወረዳ፣ የቀቤና ልዩ ወረዳና የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ
የፖሊስ አመራሮች፣የቀበሌ ሚሊሻዎች እንዲሁም የቀበሌ አመራሮች ተሳትፈዋል።
መረጃው የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ፖሊስ ጽ/ቤት ነው።
ሚያዚያ 11/2018 ዓ/ም
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኢንጌ ከተማ ለሚገነባው የኢርሻድ ኢስላማዊ ኮሌጅ የመሠረት ድንጋይ በዛሬው እለት ተቀመጠ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
በጉራጌ ዞን ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ፣ ኢንጌ ከተማ በ10 ሺህ ካሬ ሜትር መሬት ላይ ለሚያርፈው አዲስ ኢስላማዊ ኮሌጅ ግንባታ የሚያስችል የመሠረት ድንጋይ በዛሬው ዕለት በይፋ ተቀምጧል።
የኮሌጁን የመሠረት ድንጋይ ያስቀመጡት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ አብዱልከሪም በድረዲን ሲሆኑ፤ የአዲስ አበባ እና የወረዳው መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች እንዲሁም ታላላቅ ኡለሞች እና የወረዳው አመራሮች በስነ-ስርዓቱ ላይ ተገኝተዋል።
በዚህ ፕሮግራም ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤት ተቀዳሚ ምክትል ፕሬዝዳንት ሸይህ አብዱልከሪም በድረዲን በሀገራችን በተለያዩ አካባቢዎች በሙስሊሙ ማህበረሰብ ላይ የመብት ጥሰት እየፈጸሙ የሚገኙ አካላት ከድርጊታቸው እንዲቆጠቡ በጥብቅ አሳስበዋል።
በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የወረዳው ዋና አስተዳዳሪ አቶ ሚፍታህ ሁሴን ባስተላለፉት መልዕክት በመንፈሳዊ ትምህርት የታገዘ ዜጋ ለሀገሪቱ እድገት ወሳኝ ሚና እንዳለው በማስገንዘብ፣ አስተዳደሩ የኮሌጁን ግንባታ በሁሉም መስክ ለመደገፍ ዝግጁ መሆኑን ቃል ገብተዋል።
የዚህ ግዙፍ ኢስላማዊ ኮሌጅ መገንባት፤ የዲን ትምህርት ፍለጋ ወደ አዲስ አበባ እና የተለያዩ አካባቢዎች የሚንከራተተውን የአካባቢውን ህዝበ ሙስሊም በአቅራቢያው እውቀትን እንዲያገኝ ከማስቻሉም በላይ፣ ማህበረሰቡን ሃይማኖታዊ እውቀት የሚያስጨብጡ ብቁ ዳኢዎችን ለማፍራት የጎላ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በዕለቱ ተብራርቷል።
የፌደራል እና የአዲስ አበባ መጅሊስ ከፍተኛ አመራሮች
በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚገኙትን ኢስላማዊ ተቋማት እና መስጂዶች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን፤ በተለይም የሚድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ ስራ አስኪያጅ አቶ ጀማል አህመድ ለአባታቸው መታሰቢያ ያስገነቡትን የበይተል ሙሀባ መስጂድና መድረሳን እንዲሁም የቁባ መስጂድን በዕለቱ ጎብኝተዋል።
የሳምንቱ አበይት ዜናዎች
ሚያዚያ 11/2018 ዓ.ም
🎤 በጉራጌ ገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ በኢንጌ ከተማ ለሚገነባው የኢርሻድ ኢስላማዊ ኮሌጅ የመሠረት ድንጋይ ተቀመጠ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በባለፉት 5 አመታት በወረዳው በሁሉም የማዘጋጃ ከተሞች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ የሚያደርጉ በርካታ ስራዎች ማከናወኑን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ከተማ ልማትና ኮንስትራክሽን ፅ/ቤት ገለፀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በጉራጌ ዞን በገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ የሚወዳደሩ የብልጽግና ፓርቲ እጩዎች በወረዳው የተለያዩ ቀበሌዎች የሚገኙ መሰረተ ልማቶችን በመዘዋወር ጎበኙ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 የተማሪዎች ስነ-ምግባር በማሻሻል ተወዳዳሪና ብቁ ዜጋ ለመፍጠር የመምህራን ሚና ከፍተኛ መሆኑ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ፅህፈት ቤት ገለጸ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 ባለፉት 5 አመታት ከ24,081 በላይ ወጣቶችን በቋሚና ጊዜያዊ የስራ ዕድል መፍጠር መቻሉ የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ስራ ዕድል ፈጠራና ኢንተርፕራይዝ ልማት ፅ/ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
🎤 በባለፉት 5 አመታት በህበረተሰቡ፣ በተወላጅ ባለሀብቶች፣ በመንግስትና ከ620 ሚልዮን ብር በላይ ሀብት በማሰብሰብ የትምህርት መሰረተ ልማት ማሻሻል መቻሉን የገደባኖ ጉታዘር ወለኔ ወረዳ ትምህርት ቤቶች ፅህፈት ቤት አስታወቀ።
፨፨፨፨፨///፨፨፨፨፨
