fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 083
مشترکین
+924 ساعت
+207 روز
+1530 روز
آرشیو پست ها
ለሃገር አቀፍ የግብርና ናሙና ቆጠራ በቴክኖሎጂ ታግዞ የተደረገው የሰው ሃይል ምልመላን በተመለከተ የሥራና ክህሎት ሚኒስትር መስሪያቤት ከኢትዮጵያ ስታትስቲክስ አገልግሎት ጋር በመቀናጀት የቅጥር ስራውን ለማከናወን በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ አስተባባሪነት ለአስተዳደሩ የከተማና የገጠር ወረዳዎች የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያ ኃላፊዎችና ለፐብሊክ ሰርቪስ ኃላፊዎች ስልጠና ተሰጠ። ይህም ስልጠና በሚኒስትር መስሪያቤቱ ስር በለማው የኢትዮጵያ ሥራ ገበያ መረጃ ስርዓት E-LMIS ሲስተም በኩል 43,500 ሰራተኞችን ለመመልመል በታቀደው መሰረት ከ200 ሺህ በላይ አመልካች የተመዘገቡ ሲሆን የሚመለከታቸው አካላትም በአግባቡ የቅጥር ሥራውን ማከናወን የሚያስችላቸው የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ እንደነበር የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራዕድል ፈጠራ እና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል፡፡ ዳይሬክተሩ አክለውም ይህን የቅጥር ሂደት በአነስተኛ ወጪ፣ በጣም አጭር በሆነ ጊዜ ውስጥ፣ ብቁ ሠራተኛ በዚህ ከፍተኛ የሰው ሃይል ቁጥር ልክ ለማቅረብ አስቻይ ሁኔታን ከፈጠረው ከቅንጅት ስራው ጎን ለጎን  በሚንስቴር መስሪያ ቤቱ የለማው ቴክኖሎጂ የሥራ ዕድል ፈጠራ ሥራውን ቀልጣፋና ውጤታማ አድርጎታል ብለዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 10/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

Repost from N/a
photo content
+5

Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ "ክረምትን በክህሎት"በሚል በተዘጋጀው የክረምት ስልጠና ለመሰልጠን የተመዘገቡ የአስተዳደሩ ወጣቶች በኮሌጁ ተገተው ስልጣናቸውን ጀመሩ:: ወጣቶቹ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የክህሎት ስልጠና ለመሰልጠን የተመዘገቡ ሲሆን ወደ ስልጠና ከመግባታቸው አስቀድሞ በኮሌጁ ስለሚሰጡ ስልጠናዎችና በክረምቱ በሚወስዱት የሙያ ክህሎት ስልጠናዎች ዙሪያ በኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ሀላፊና በኮሌጁ ም/ዲን አማካኝነት ሰፋ ያለ ገለፃ ተደርጎላቸዋል:: የክረምት ሰልጣኞቹ ይበልጥ ግንዛቤው እንዲኖራቸው ትምህርትና ስልጠና የሚሰጥባቸውን ወርክሾፖች ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን በዚህም በትምህርትና ስልጠና ክፍሎቹ በሚገኙ አሰልጣኝ መምህራን ሙያዊ ገለፃና ማብራሪያ በመስጠት ግንዛቤ እንዲያገኙ ተደርጏል:: "የክረምትን በክህሎት" ሰልጣኝ ወጣቶች ቀጣዮቹን ወራት በኮሌጁ በመረጡት ሙያዊ ስልጠና እየወሰዱ የሚቆዩ ሲሆን በስልጠናው ማጠናቀቅያ ላይም ለቀጣይ ምዕራፋቸው መሰረት የሚሆናቸውን ሙያዊ ክህሎት ጨብጠው እንደሚወጡም ተገልፇል:: ኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ነሃሴ 7/2016 ዓ.ም

Discover how the “ICT Skills and TVET Centre of Excellence Development for Youth Employment” project is transforming lives in Ethiopia. 🌍💻 Implemented by Dire Dawa Polytechnic College, this project is boosting the employability of young people in the ICT sector by providing demand-driven skills training and entrepreneurship courses. Hear from Anisa Zenu Redwan, a TVET graduate who found success in the ICT sector thanks to the skills and opportunities provided by the project: “𝗔𝗳𝘁𝗲𝗿 𝗜 𝗴𝗼𝘁 𝘁𝗵𝗲 𝗷𝗼𝗯, 𝗺𝗮𝗻𝘆 𝘁𝗵𝗶𝗻𝗴𝘀 𝗰𝗵𝗮𝗻𝗴𝗲𝗱 … 𝗜 𝗵𝗮𝘃𝗲 𝗯𝗲𝗰𝗼𝗺𝗲 𝗺𝗼𝗿𝗲 𝘀𝗲𝗹𝗳-𝘀𝘂𝗳𝗳𝗶𝗰𝗶𝗲𝗻𝘁. 𝗡𝗼𝘄 𝗜’𝗺 𝗲𝗱𝘂𝗰𝗮𝘁𝗲𝗱, 𝘄𝗼𝗿𝗸𝗶𝗻𝗴, 𝗮𝗻𝗱 𝘀𝘂𝗽𝗽𝗼𝗿𝘁𝗶𝗻𝗴 𝗺𝘆 𝗳𝗮𝗺𝗶𝗹𝘆.” The SIFA-supported project has successfully developed occupational standards and curricula for three ICT and telecommunications courses. To date, 514 students have been trained in the new ICT curriculum, including 358 women 👩🏽💻. Looking ahead, the project aims to construct a new ICT training building equipped with state-of-the-art classrooms and laboratories to enhance training capabilities further. Join us in celebrating these milestones, and watch the video to learn more about how SIFA is supporting employment prospects in Africa. 🎥👇🏽

የቢሮውን የመልካም አስተዳደር ችግሮች በመለየት አቅዶ ለመፍታት የሚያስችል መድረክ አካሄደ፤ በመድረኩ የሥራና ክህሎት ቢሮ  ሰራተኞችና አመራሮች የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በተመለከተ በቀጣይ ዓመት በዕቅድ የሚቀረፉበትን ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር የሚመለከታቸው የቢሮው አካላት የጋራ አቋም ለመያዝ የሚጠቁም ውይይት ተደርጓል። ውይይቱን የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኤጀንሲ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የመሩት ሲሆን ተሳታፊዎችም የተመለከቷቸውንና ያስተዋሏቸውን ችግሮች አንስተው በቀጣይ ትኩረት ተሰጥቷቸው እንዲፈቱ አመላክተዋል፡፡ በዚሁ መድረክ ላይ እንደ አገር በተመረጡ ተቋማት ላይ ትኩረት አድርጎ የአገልግሎት አሰጣጥ ምን እንደሚመስል የሚያሳይ የተጠና የጥናት ሰነድ ቀርቦ ውይይት ማድረግ ተችሏል፤ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በማጠቃለያው እንደተናገሩት በተለይ የመልካም አስተዳደር ችግሮችን በመፍታት ለዜጎች የምንሰጠውን አገልግሎት ጥራቱን በጠበቀ አግባብ ለመሥጠት የሚያስችል ስራዎች ይሰራሉ ብለዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 7/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

እንኳን ደስ አለን!!✊
እንኳን ደስ አለን!!✊

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የማኔጅምንት አባላት በቢሮውና በኮሌጆች ቅንጅት የሚሰሩ የአቅመ ደካሞችን ቤት በአዲስ የመስራት መርሐ-ግብር አስጀመሩ፡፡ **** በዚህም አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ማኔጅመንታቸው በድሬዳዋ አስተዳደር በወረዳ 05 እና በወረዳ 08 የሚገኙ የአቅመ ደካሞችን ቤት የማደስ መርሐ-ግብር ዛሬ አስጀምረዋል። የቢሮ ኃላፊው የቤት እድሳት መርሐ-ግብሩን ባስጀመሩበት ወቅቱ እንደገለጹት፣ በአስቸጋሪ የኑሮ ሁኔታ ውስጥ የሚገኙ ነዋሪዎችን ሕይወትን ማሻሻል የመንግሥት ዋነኛው ትኩረት እንደሆነ ገልጸው የቢሮ ተልዕኮም ሰው ተኮር እንደመሆኑ መጠን በመሰል ተግባራት ላይ ቢሮው በመሳተፉ ደስተኛ መሆናቸውን ተናግረዋል። በመርሐ-ግብሩ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ እንዲሁም በአስተዳደሩ የሚገኙ የመንግስት ኮሌጆች የድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ እና የኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጆች በዚህ ክረምት በወረዳ 02 እና በወረዳ 01 የሚገኙ ጨምሮ 7 ቤቶችን በአዲስ የሚሰሩ ሲሆን የቤት ዕድሳት የተጀመረላቸው ነዋሪዎችም የተሰማቸውን ደስታ ገልጸዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 3/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

"የአድራ አይነት መሰል ፕሮጀክቶች እንደ አገር የተቀረጹ ፖሊሲዎችን ወደ ተግባር በማውረድ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረጉ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ላቅ ያለ ነው፡፡" አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ =============================== በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘውን ተፈጥሮ የለገሰችውን የጸሃይ ኃይል ያለ ምንም ጥቅም ለዘመናት ትርጉም ያለው ስራ ሳይሰራበት ቆይቷል ምስጋና ለአድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ ለሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን የማሰልጠኛ ወርክሾፕ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማዘጋጀት በመጀመሪያ አመት ትግበራው ቀላል የማይባሉ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ በትላንትናው ዕለትም አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በSolar PV Instalation ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ለሚገኙትን 48 ሰልጣኞች በተለያዩ Unit of Competency በማሰልጠን አስመርቋል ሰልጣኞቹ በንድፈ ሀሳብ ሲከተታተሉ የቆዩትን ስልጠና ስራ ቦታው ላይ በአካል ተገኝተው በተግባር የሰለጠኑ ሲሆን ይህም ሰልጣኞቹ በቀጣይ ወደስራ አለም ሲገቡ በእጅጉ የሚያግዛቸው ይሆናል:: አድራ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ላለፉት አመታት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በተለይ የነብስ አድንና ዜጎችን ህይወት መለወጥ ላይ ትኩረት አድርጎ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲሰራ የቆየና አሁንም እየሰራ ያለ ድርጅት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በቀጣይ ፕሮጀክቱ ተደራሽነቱን በሚያሰፋበትና በአስተዳደሩ ላይ በተመዘገበው ውጤታማ አፈጻጸም ጥራትን አስጠብቆ በሚቀጥሉበት አግባብ ላይ ከፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ እና የጀርመን ዳይሬክተሮች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 3/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

"የአድራ አይነት መሰል ፕሮጀክቶች እንደ አገር የተቀረጹ ፖሊሲዎችን ወደ ተግባር በማውረድ ዜጎች ተጠቃሚ እንዲሆኑ በማድረጉ ረገድ የሚጫወቱት ሚና ላቅ ያለ ነው፡፡" አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ =============================== በድሬዳዋ አስተዳደር የሚገኘውን ተፈጥሮ የለገሰችውን የጸሃይ ኃይል ያለ ምንም ጥቅም ለዘመናት ትርጉም ያለው ስራ ሳይሰራበት ቆይቷል ምስጋና ለአድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ ለሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን የማሰልጠኛ ወርክሾፕ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማዘጋጀት በመጀመሪያ አመት ትግበራው ቀላል የማይባሉ ስራዎችን ሰርቷል፡፡ በትላንትናው ዕለትም አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በSolar PV Instalation ስልጠናቸውን እየተከታተሉ ለሚገኙትን 48 ሰልጣኞች በተለያዩ Unit of Competency በማሰልጠን አስመርቋል ሰልጣኞቹ በንድፈ ሀሳብ ሲከተታተሉ የቆዩትን ስልጠና ስራ ቦታው ላይ በአካል ተገኝተው በተግባር የሰለጠኑ ሲሆን ይህም ሰልጣኞቹ በቀጣይ ወደስራ አለም ሲገቡ በእጅጉ የሚያግዛቸው ይሆናል:: አድራ ኢትዮጵያ መንግስታዊ ያልሆነ ድርጅት ላለፉት አመታት የተለያዩ የልማት ስራዎችን በተለይ የነብስ አድንና ዜጎችን ህይወት መለወጥ ላይ ትኩረት አድርጎ በተለያዩ የኢትዮጵያ ክፍሎች ሲሰራ የቆየና አሁንም እየሰራ ያለ ድርጅት መሆኑ የሚታወቅ ሲሆን የአስተዳደሩ የሥራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው በቀጣይ ፕሮጀክቱ ተደራሽነቱን በሚያሰፋበትና በአስተዳደሩ ላይ በተመዘገበው ውጤታማ አፈጻጸም ጥራትን አስጠብቆ በሚቀጥሉበት አግባብ ላይ ከፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ እና የጀርመን ዳይሬክተሮች ጋር ውይይት አድርገዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ሐምሌ 3/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

ዓመታዊ የአካባቢ እና ማህበራዊ ኦዲት ግኝት ሪፖርት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክንቺ ኮሌጅ ለEASTRIP ግንባታ ፕሮጀክት ቀረበ። በኦዲት ሪፖርቱ ላይ በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳ
+3
ዓመታዊ የአካባቢ እና ማህበራዊ ኦዲት ግኝት ሪፖርት በድሬዳዋ ፖሊ ቴክንቺ ኮሌጅ ለEASTRIP ግንባታ ፕሮጀክት ቀረበ። በኦዲት ሪፖርቱ ላይ በመገኘት መድረኩን በንግግር የከፈቱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ አቶሳሊም በንግግራቸው ይህ የEASTRIP ፕጀክት በኮሌጁ ሲገነባ በአለም ባንክና በኢትዮጵያ በጸደቀው የአካባቢ እና ማህበራዊ ደረጃዎች ላይ መሰረት አድርጎ ስራዎችን እየሰራ እንዳለና በግንባታው ወቅት የሚያጋጥሙ ችግሮችም ማህበረሰቡ ላይ ተጽእኖ ከማምጣጡ በፊት እየተከታተለ ለችግሮቹ መፍትሄ እየሰጠና ድጋፍና ክትትሎችን እያደረገ እንዳለ በሪፖርቱ ወቅት ገልጸዋል፡፡ ዓመታዊ የአካባቢ እና ማህበራዊ ኦዲት ግምገማው በድሬዳዋ አስተዳደር አካባቢ፣ደንና አየር ንብረት ለውጥ ባለስልጣን የተካሄደ ሲሆን በግምገማው መሰረት የግንባታ ፕሮጀክቱ በአለም ባንክ የአካባቢ እና ማህበራዊ ደረጃ እንዲሁም በኢትዮጵያ በጸደቀው አዋጅ እና በፀደቀው እየተተገበረ እንዳለ ተገልጿል። በኦሪት ሪፖርቱ ወቅት የተገኙ EFCC ባለስልጣን ተወካዮች አንዲሁም ተሳታፊ አካላት እንደ ተናገሩት ኮሌጁ እየተከተለ እንዳለው ስርአት መሰረት የመንግስት እና የግል ኮንስትራክሽን ፕሮጀክቶች በESIA መስፈርት እና አዋጅ መሰረት መተግበር አለበት ሲሉ አስተያየታቸውን ሰጥተዋል ። የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ነሀሴ 2/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

አድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) የኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በSolar PV Installation Maintenance በመጀመርያ ዙር ያሰለጠናቸውን ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው ዕለት አስመርቋል። የዛሬ ተመራቂዎች በአድራ ኢትዮጵያ(ድሬዳዋ) ከኢትዮ ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ጋር በመተባበር በአጫጭር ስልጠና በSolar PV Installation Maintenance ላለፉት 8 ወራት  ሲሰለጥኑ የቆዩ ሲሆን በዚህም 30 ወንድ እና 18 ሴት እንዲሁም 3 አካል ጉዳተኞች በድምሩ 48 ሰልጣኝ ተማሪዎች በዛሬው እለት ለምረቃ በቅተዋል:: ተመራቂ ተማሪዎቹ በሰለጠኑት ስልጠና የሶላር ሲስተም ጥገናን በሚፈለገው ልክ ተደራሽ ለማድረግ የብቃት ምዘና(COC) በብቃት በማጠናቀቅ ወደ ስራ አለም ለመግባት መዘጋጀታቸውም ተገልፇል:: በምረቃ መርሃ-ግብሩ ላይ ለመገኝት  የአድራ ኢትዮጵያ ዋና ዳይሬክተርን ጨምሮ የተለያዩ ሀላፊዎች ከአዲስ አበባ የተግኙ ሲሆን ከምረቃ ፕሮግራም መጠናቀቅ በኃላ የችግኝ ተከላ መርሃ-ግብር በኮሌጁ አካሂደዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፓሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ነሃሴ 2/2016 ዓ.ም