fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 089
مشترکین
+324 ساعت
+257 روز
+1730 روز
آرشیو پست ها
በኢንዱስትሪዎችና በኮሌጆች መካከል ያለውን ትስስር እንዲሁም የተማሪዎችና የትብብር ስልጠና እና የአሰልጣኝ መምህራኖች የኢንዱስትሪ አታችመንት (industry attachment) እና Internship ጥራትን ማስጠበቅ ላይ ያተኮረ ስልጠና በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር ላሉ የኢንዱስትሪ ባለድርሻ አካልት በዛሬው እለት ተሰጠ፡፡ ስልጠናው በዋናነት በኢንዱስተሪዎችና በኮሌጆች መካከል ያሉ ክፍተቶቸህነ በመሙላት እና ጠንክሮ በመስራት ክህሎትን ማሻሻል፣ ሙያዊ ማንነት፣ አመራር እና አስተዳደር ልማት፣ የትምህርት ድጋፍ፣ የደንበኞች ግልጋሎት እና የእውቀት ሽግግር እንዲመጣ የሚያስችል ስልጠና ሲሆን ፡፡ በተጨማሪም ተማሪዎች ኢንዱስትሪ ውስጥ ገብተው ተግባር ተኮር ስልጠናዎችን እንዲያገኙ ሲደረግ ከሰልጣኞች የሚገኝ አዲስ ሃሳብና የፈጠራ ውጤቶች ለኢንዱስትሪዎች ትልቅ ግበአት ሆኖ ተወዳዳሪ እንዲሆኑ ያስችላል ስለዚህም የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ትምህርትና ስልጠናቸው ተግባር ተኮር እንዲሆኑና ችግር ፈቺ ሰልጣኝ ተማሪዎች እንዲሆኑ ለማድረግ ሰልጣኞች ኢንዱስትሪዎች ውስጥ እየገቡ እንዲሰሩ እና እንዲሰለጥኑ ለማድረግ የታለመ ስልጠና እንደሆነ ከስልጠናው አስተባባሪዎች ለመረዳት ተችሏል፡፡ ይህ የመጀመሪያ ዙር ስልጠና CINOP እና AMBERO በተባሉ የውጪ ድርጅቶች አማካኝነት የተሰጠው ይህ ስልጠና ታህሳስ 22/2016 ዓ.ም በኢንዱስትሪዎችና በኮሌጆች መካከል በ industry attachment እና በትብብር ስልጠና እና Internship ላይ ያሉ ክፍተቶች ምን እንደሚመስሉ ከኢንዱስትሪ ከተውጣጡ ከባለድርሻ አካላት ጋር የተወያዩ ሲሆን ከውይይታቸው በመነሳት የዛሬው ስልጠና እንደተዘጋጀ ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 26/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

“ከዕዳ ወደ ምንዳ” በሚል ርዕስ ሲሰጥ የቆየው 5ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቀቀ። ላለፉት 4 ቀናት “ከዕዳ ወደ ምንዳ” በሚል ርዕስ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን የብልጽግና ፓርቲ አባላት የሆኑ የመንግሥት ሠራተኞች ሲሰጥ የቆየው 5ኛ ዙር የአቅም ግንባታ ስልጠና ተጠናቅቋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው ስልጠናው በተለያዩ ዓለም አቀፋዊ፣ ቀጠናዊ፣ ሀገራዊ እንዲሁም አስተዳደራዊ ነባራዊ ሁኔታዎችን መሰረት በማድረግ በተዘጋጁ የስልጠና ሰነዶች ዙሪያ ላይ ያተኮረ ሲሆን የፓርቲውን አባላት አቅም በማጎልበት ኢትዮጵያ ብሎም አስተዳደሩ ለጀመሩት የብልፅግና ጉዞ ወሳኝ ሚናቸውን እንዲወጡ የሚያስችላቸው የንድፈ ሀሳብ እውቀት የሚያስጨብጣቸው ግንዛቤ እንዲይዙ የሚያስችል አቅም የተፈጠረበት ስልጠና ነው ብለዋል።  በተመሳሳይ የድሬደዋ አስተዳደር ትራንስፖርት እና ሎጂስቲክስ ባለስልጣን ዋና ስራ አስኪያጅ ወ/ሮ ሽኩሪ አብዱረህማን የብልጽግና ፓርቲ የመንግሥት ሠራተኞችበአጠቃላይ ስልጠናው አባሉ ራስን ከመምራት ጀምሮ ህዝብን በሚገባ ማገልገል እንዲችልና በአባሉ ዘንድ የተግባርና የሀሳብ አንድነት በማምጣት ሀገራዊ ብልፅግና ለማረጋገጥ የሚያስችልና አባሉ ከተናጥል ትርክት ወጥቶ በወል እና ገዢ ትርክት ላይ ትኩረት እንዲያደርግ የሚያስረዳ ግንዘቤ መፍጠሩን ተናግረዋል። በስልጠናው ማጠናቀቂያ ሰልጣኞች እና የስልጠናው አዘጋጆች በጋራ በመሆን በአስተዳደሩ የሚገኘው የህጻናት ማቆያና ማገገሚያ ማዕከል በአካል በመገኘት በማዕከሉ ለሚገኙ ህጻናት የሚሆን ከ50 ሺህ ብር በላይ የሚገመት የምግብ፣ የንጽህና መጠበቂያ እና የአልባሳት ድጋፍ ያደረጉ ሲሆን በመጨረሻም በነጻንግድ ቀጠና ውስጥ የሚገኙ አምራች ኢንዱስትሪዎች መካከል ኤልአዉቶ እና ኤ ኤም የመኪና መገጣጠሚያ ፋብሪካ እንዲሁም ሃን ፕላስ ፋብሪካን የጎበኙ ሲሆን ሰልጣኞችም በተሰጣቸው የግንዛቤ ማጎልበቻ ስልጠና በጉብኝቱ መደሰታቸውን ገልጸው መንግስት የጀመረውን የብልጽግና ጉዞ እንዲያስቀጥል በማሳሰብ የበኩላቸውን አስተዋጽኦ ለማበርከትም ማሳሰባቸውን ዝግጁ መሆናቸውን ማወቅ ተችሏል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 25/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+3

👉ኢትዮ-ጣሊያን ቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ ለዳዊት አረጋውያን መርጃ የሙያ ድጋፍ አደረገ የኮሌጁ ውድ-ወርክ ቴክኖሎጂ ዲፓርትመንት ዳዊት አረጋውያን መርጃ ከለጋሾች ያገኛቸውንና አገልግሎት መስጠት የማይችሉ አልጋዎችና ወንበሮችን የሚያስፈልጉ ግብአቶችን አሟልቶ በመጠገን አስረክቧል። የጥገና ስራውን በመስራት በቅን መንፈስ ሙያዊ ድጋፍ ላደረጉት ለኮሌጁ የትምህርትና ስልጠና ምክትል ዲን አቶ ኤልያስ አህመድ እና የዲፓርትመንቱ ተጠሪ ለሆኑት አቶ ዮሴፍ እንዳልካቸው የአረጋውያን መርጃ ድርጅቱ ሀላፊ አቶ ዳዊት በቀለ በአረጋውያኑ ስም ምስጋናቸውን አቅርበዋል። Dawit Aregawiyan Merja ታህሳስ 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የተዘጋጀ የሞዴል ኢንተርፕራይዞች ኤግዚቢሽንና ባዛር ተጀመረ። ከታህሳስ 22-27/2016 ዓ.ም ድረስ በኢትዮጵያ ቀይ መስቀል ማህበር ድሬዳዋ ቅርንጫፍ ፊት ለፊት የሚገኘው ቦታ ላይ የሚካሄደውን ይህን ኤግዚቢሽን እና ባዛር የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ክቡር አቶ ከድር ጁሃር፣ የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ እንዲሁም የአስተዳደሩ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት በይፋ ተከፍቷል፤ በዚህም ኤግዚቢሽንና ባዛር ላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች ምርትና አገልግሎቶቻቸውን ይዘው የሚቀርቡ ሲሆን ወቅቱም በዓል ሰሞን እንደመሆኑ በቦታው በመገኘት የአስተዳደሩ ነዋሪ ሞዴል ኢንተርፕራይዞችን በማበረታታት ተጠቃሚ እንዲሆን  መልዕክት የቢሮው ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው መልክት አስተላልፈዋል፤ ኢንተርፕራይዞች ያመረቱትን ምርት ይዘው የሚቀርቡበት ገበያተኛውም በሚፈልገው ልክ ተገበያይቶ የሚወጣበት መድረክ መፍጠሪያ ዘዴ አንዱ ይህ በመሆኑ እንዲሁም  ያለውን የኑሮ ውድነት ለማረጋጋትም ከፍተኛ ሚና እደሚኖረው በቢሮው የሥራ ዕድል ፈጠራና የአንድ ማዕከል ማስተባበሪያ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ ተናግረዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 24/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ባለስልጣን የብልጽግና ፓርቲ የመንግሥት ሠራተኞች "ከዕዳ ወደ ምንዳ!" በሚል ርዕስ የሚሰጠው የአቅም ግንባታ ስልጠና ሁለተኛ ቀን ውሎውን ቀጥሏል፤ "የገዢ ትርክት ግንባታ" በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ የተዘጋጀው የስልጠና ሰነድ ላይ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ የሆኑት አቶ ሮቤል ጌታቸው ማብራሪያ በመስጠት እያሰለጠኑ ይገኛል። በሀገራዊ የጋራ ጉዳዮች የጋራ ግንዛቤ በመጨበጥ ለገዢ ትርክት ግንባታ በቁርጠኝነት ለመሥራት  የተግባርና የአመለካከት አንድነት እንደሚያስፈልግ ገልፀዋል። ሀገራችንና ዜጎቿን ከተስፋ ብርሃን ወደ ሚጨበጥ ብርሃን ለማሸጋገር በሚደረገው ርብርብ ለገዢ ትርክት ግንባታ በአርበኝነት መንፈስ አባሉ እንዲንቀሳቀስ ያስፈልጋል ብለዋል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 23/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ               

photo content
+7

Repost from N/a
photo content
+9

Repost from N/a
አድራ ኢትዮጵያ በሶላር ፒቪ የመንገድ መብራት ዝርጋታ እና ጥገና የእሴት ሰንሰለት ዙሪያ ተዘጋጅቶ በቀረበ ሰነድ ላይ ከባለድርሻ አካላት ጋር ውይይት አካሄደ:: አድራ ኢትዮጵያ ከአድራ ጀርመኒ ጋር በመተባበር በጀርመን መንግስት ድጋፍ ለሶላር ፒቪ ዝርጋታ እና ጥገና የሚሆን የማሰልጠኛ ወርክሾፕ በኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በማዘጋጀት ስልጠና እየሰጠ እንደሚገኝ የሚታወቅ ሲሆን በዘርፉ ያሉትን ማነቆዎች ለመቀነስ እና አዲሱን የGreen TVET Approach ለማሳወቅ ከፍተኛ ስራ እየሰራም ይገኛል። በዚህም መሰረት ከድሬደዋ TVET ኤጀንሲ ቢሮ ጋር በመተባበር በተሰራው የሶላር ፒቪ የመንገድ መብራት ዝርጋታ እና ጥገና የእሴት ሰንሰለት በድሬደዋ ከተማ (Value Chain Analysis On Solar PV Street Light Installation & Maintenance in DD city)በሚል ርዕስ ተዘጋጅቶ በቀረበው ሰነድ ላይ ዘርፉን የሚያነቃቃ ጠቃሚ እና ሰፊ ውይይት ከባለድርሻ አካላት ጋር በማድረግ ዘርፉ ላይ ያሉትን ክፍተቶች ወደ መልካም አጋጣሚ በመቀየር ለሰልጣኞች ሰፊ የስራ እድል መፍጠር የሚያስችል ሁኔታ መፍጠር እንደሚቻልም በመድረኩ ተመላክቷል። በዚህም ትልቁን ድርሻ ከሚወስደው የድሬደዋ መንገዶች ባለስልጣን ጋር አብሮ ለመስራት የሚያስችል ሁኔታዋችም መፈጠራቸው የተገለፀ ሲሆን በቀጣይም ስራውን በማስፋትና ወደ ገጠሩ አካባቢ በመውረድ ገጠሩን አካታች የሆነ የእሴት ሰንሰለት በመስራት አብሮ ችግሩን መቅረፍ የሚያስችል ሁኔታ እንዲፈጠርም አቅጣጫ ተይዟል። ኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ታህሳስ 22/2016 ዓ.ም

''ከዕዳ ወደ ምንዳ'' በሚል መሪ ሀሳብ የተዘጋጀው 5ኛው ዙር የፓርቲ አባላት ስልጠና በዛሬው ዕለት በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ እና የትራንስፖርትና ሎጅስቲክ ባለስልጣን የብልጽግና ፓርቲ አባላት መሰጠት ጀመረ፤ የፓርቲው አባላትም ዛሬን ጨምሮ ለሚቀጥሉት 4 ተከታታይ ቀናት "ሀብት እና ብልፅግናን መፍጠር እና ማስተዳደር፣ የገዢ ትርክት ግንባታ፣ አገልጋይና ስልጡን ሲቪል ሰርቪስን መገንባት እንዲሁም የሰላም ባህልና አመለካከት ግንባታ" በሚሉ ርዕሶች ስልጠና ይወስዳሉ። ስልጠናው ለተከታታይ አራት ቀናት ከታህሳስ 22-25/2016 ዓ.ም የሚሰጥ ይሆናል። የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

photo content
+8

#ዜና | በድሬዳዋ ከ15 ሺህ ለሚበልጡ ዜጎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው #DireTvአማርኛ | ታህሳስ 2016 ዓ.ም በድሬዳዋ ከ15 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ዜጎች የተለያየ የሥራ ዕድል ለመፍጠር ከሚመለከታቸው አካላት ጋር በቅንጅት እየተሰራ መሆኑን የአስተዳደሩ ከንቲባ ከድር ጁሃር ተናገሩ። በሀገር አቀፍ ደረጃ በተጀመረው "ብቃት ፕሮጀክት" 972 የድሬዳዋ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተጠቃሚ መሆናቸውም ተመልክቷል። የድሬዳዋ አስተዳደር ከንቲባ ከድር ጁሃር ለኢዜአ እንደተናገሩት፤ በገጠርና በከተማ የሚስተዋለውን የሥራ አጥነት ችግር ለመፍታት ዘንድሮ የተቀናጀ ጥረት እየተደረገ ነው። አስተዳደሩ የወጣቶችንና የነዋሪዎችን የሥራ ጥያቄ ለማቃለል ከፌደራል መንግስትና ከባለሀብቶች ጋር በቅንጅት እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል። በዚህም በተለይ የተማሩ ወጣቶችን ቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ ፍሬያማ ሥራ እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል። የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎት ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራ ዳይሬክተር አቶ ሰኢድ አሊ በበኩላቸው በዘንድሮው በጀት ዓመት ከሁሉም ወረዳዎች ከ15 ሺህ በላይ ሥራ ፈላጊዎች መመዘግባቸውን ገልጸዋል። ለነዚህ ሥራ ፈላጊዎች የሥራ ዕድል ለመፍጠር ከሁሉም ተቋማትና ባለሃብቶች ጋር የተቀናጀ ስራ እየተሰራ መሆኑንም አመልክተዋል። በኮንስትራክሽን፣ በብረታብረትና በእንጨት ሥራ፣ በከተማ ግብርና፣ በጨርቃጨርቅና በአልባሳት፣ በምግብ ዝግጅት እና ሌሎች መስኮች የሥራ ዕድል ለመፍጠር የተሰሩ ሥራዎች ውጤት እያስገኙ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይ የተማሩ ወጣቶች በድሬደዋ ነፃ የንግድ ቀጠናና በደረቅ ወደብና ተርሚናል የሚፈጠሩ የሥራ ዕድሎች ተጠቃሚ እየተደረጉ መሆናቸውን ነው ያስረዱት። አቶ ሰኢድ እንዳሉት ወጣቶች ያለባቸውን የአመለካከት፣ የሙያና የክህሎት ክፍተቶች ለመድፈን ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር የተናበበ ሥራ እየተሰራ ነው። እስካሁን ድረስ ለ2 ሺህ የተማሩና ሌሎች የህብረተሰብ ክፍሎች ቋሚ የሥራ ዕድል መፈጠሩን ተናግረው በቀጣይ ወራት የተሻለ ውጤት ለማስመዝገብ የቅደመ ዝግጅት ሥራ መጠናቀቁን ገልጸዋል። ከቋሚ የሥራ ዕድል ተጠቃሚዎች በተጨማሪ በሺህ ለሚገመቱ ወጣቶች ጊዜያዊ የሥራ ዕድል መፈጠሩንም ዳይሬክተሩ ተናግረዋል። በተለይ በአገር አቀፍ ደረጃ በመንግሥትና በዓለም ባንክ ድጋፍ በመተግበር ላይ በሚገኘው " በብቃት ፕሮጀክት" አማካኝነት 972 ወጣቶች ተገቢውን የህይወት ክህሎት ስልጠና ወስደው ከግል ተቋማትና ድርጅቶች ጋር የማስተሳሰር ስራ ተከናውኗል ብለዋል። ለፕሮጀክቱ ማስፈፀሚያ 40 ሚሊዮን ብር መመደቡንና ወጣቶቹ ከተመደቡበት ድርጅትና ተቋማት ውስጥ ለስድስት ወራት ነፃ አገልግሎት በመስጠት ወደ ቋሚ ሠራተኝነት እየተሸጋገሩ መሆናቸውን አቶ ሰኢድ አውስተዋል። እንደ አቶ ሰኢድ ገለፃ በማህበር ተደራጅተው ህይወታቸውን ለመለወጥ እየተጉ የሚገኙት ወጣቶች ለሚያነሷቸው የመስሪያ፣ የመሸጫ ቦታ እና የብድር ጥያቄዎች ምላሽ ለመስጠት ከሚመለከታቸው ተቋማት ጋር በቅንጅት እየተሰራ ነው። በተለያየ ጊዜያት ተገንብተው የተጠናቀቁ ውስን ሼዶች ተጠቃሚ ለማድረግም እየተሰራ መሆኑን አመልክተዋል። በዘንድሮው በጀት ዓመት ሥራ በጀመረ ፋብሪካ የሥራ ዕድል ተጠቃሚ የሆኑት ወይዘሮ ቆንጂት ለገሰ በበኩላቸው እንዳሉት፤ ለነዋሪው የሥራ ጥያቄ ምላሽ ለመስጠት አስተዳደሩ ከተለያዩ ተቋማት ጋር ተቀናጅቶ በመስራቱ የተሻለ ሥራ ማግኘታቸውን ገልጸዋል። "መሠረታዊ የህይወትና የሙያ ስልጠና አግኝቼ በሥራ ላይ ልምምድ ባሳየሁት ብቃት አሁን ቋሚ የፀጉር ሠራተኛ ሆኛለሁ" ያለችው ደግሞ የብቃት ፕሮጀክት ተጠቃሚ ወጣት ፌቨን አርአያ ናት። "በቀጣይ ብድር ከተመቻቸልኝ የራሴን ፀጉር ቤት በመክፈት ለሌሎች ወጣቶች የሥራ ዕድል የመፍጠር ዓላማ አለኝ፤ አስተዳደሩም ዜጎችን ለመደገፍ የጀመረውን ስራ ማጠናከር አለበት" ብላለች ። ዘንድሮ የድሬዳዋ አስተዳደር በተቀናጀ መንገድ በትኩረት እያከናወናቸው ከሚገኙት ሥራዎች አንዱ ለወጣቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር እያከናወናቸው ያሉ ተግባራት የሚጠቀሱ ናቸው ሲል ኢዜአ ዘግቧል።

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት በአዲስ  መልክ የተዘጋጁ እና የተሰራጩ ከደረጃ አንድ እስከ ደረጃ አራት ያሉ የሙያ ደረጃዎችን፤ ስርዓተ ስልጠናዎች(ስርኣተ ትምህርቶች) ፤ማስልጠኛ መርጃ መሳሪያዎች እና የአሰልጣኙ መምሪያዎች ላይ ለቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍ የግልና የመንግስት ኮሌጆች እንዲሁም በቢሮው ለሚገኙ አመራሮች እና ከፍተኛ ባሙያዎች  የተዘጋጀ  የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ተሰጠ፤ የስልጠናው ዋና አላማ በቢሮው በተለይም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ዘርፍን የሚመሩና የሚሰሩ አሰልጣኝ መምህራን፣ አመራሮችና ከፍተኛ ባለሙያዎች ጊዜው የሚጠይቀውን እና የሚፈልገውን ክህሎት ተላብሰው ተልዕኮ መፈጸም እንዲችሉ ታስቦ ስለ ሙያ ደረጃ ምንነት ፤እንዴት ይከለሳል እንዲሁም ማንስ ይከልሰዋል የሚሉና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ የተሰጠ መሆኑን የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት የሆኑት አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል፡፡ የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አክለውም የትኞቹ ሙያዎች ተዘጋጅተው ተሰራጭተዋል የሚለውን በማስተዋወቅና የአተገባበር ሂደቱን በመገምገም እና በተዘጋጁት ሰነዶች አተገባበር ሂደት ላይ ያጋጠሙ ችግሮች ላይ መፍትሄዎች እና ወደፊት የምዘና መሳሪያውን እንዴት እናዘጋጅ በሚሉ ጉዳዮች ላይ አሰልጣኝ መምህሩ  አመራሩ እና ከፍተኛ ባለሙያው በወሰዱት ስልጠና እራስን የማብቃት ስራ በዚህ ስልጠና የሚጠናቀቅ እንዳልሆነና አቅምና ክህሎታቸውን ለማዳበር ቢሮው መሰል ስልጠናዎችን በየጊዜው እንደሚያዘጋጅም ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 18/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ስር የሚገኘው ቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት የኮሌጆችን አቅም ለማሳደግና የአሰልጣኝ መምህራንን የክህሎት ክፍተት መሙላት የሚያስችል ስልጠና ለኢትዮ-ጣልያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት አስልጣኝ መምህራን ከታህሳስ 4 ጀምሮ መሠረታዊ የArduino programming and python with machine learning ላይ ስልጠና በመሰጠት ላይ ይገኛል፤ በዚህም ስልጠናው በትምህርት ክፍሉ ትምህርትና ስልጠናን በተሻለ መልኩ ለመስጠት እንዲያስችል አሰልጣኝ መምህራኑን በፌደራል ቴክኒክና ሙያ ስጠልና ኤጀንሲ ውስጥ  ለ15 ተከታታይ ቀናት ስልጠና በወሰዱ መሪ አሰልጣኞች አማካይነት ሲሆን በዳይሬክቶሬቱ በተያዘው ዕቅድ መሰረት አሰልጣኞች የእውቀት እና ክህሎት ሽግግር እንዲያደርጉ የሚያስችላቸው  ይሆናል፤ በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ እንደተናገሩት ይህ ስልጠና በመዘጋጀቱ በኮሌጁ አሰልጣኝ መምህራን ዘንድ ያለውን የክህሎት ክፍተት መሙላት ከመቻሉ ባሻገር በቀጣይ በ2016 ዓ.ም ትምህርትና ስልጠና ዘመን ዝግጁ ማድረግ የሚያስችል መሆኑንና በተመሳሳይ ከድሬዳዋ ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኤሌክትሪካል ኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት በቀረበው የስልጠና ፍላጎት መሰረት የውጭ አሰልጣኝ በመጋበዝ የሚቀጥል ፕሮግራም መኖሩን ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 17/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ