fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 063
مشترکین
-224 ساعت
-77 روز
+130 روز
آرشیو پست ها
የሆቴልና ሆስፒታሊቲ ኢንዱስትሪ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች እንዲመራ ኮሌጁ አስፈላጊውን ስራ እንደሚሰራ ገለጸ፡፡ #ዜና|የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሳምራት ሆቴል ባለሙያዎችን በአጫጭር ስልጠና በሆቴልና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ አስመረቀ፡፡ የሆቴልና ሆስፒታሊቲ ዘርፍ ክህሎትና እውቀት ያለው በቂ ባለሙያ የሚፈልግ ነው፡፡ ይህን ኢንዱስትሪ ለማሳደግ ደግሞ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአጫጭርና በረጃጅም ስልጠናዎች ባለሙያዎችን እያፈራ ይገኛል ያሉት የኮሌጁ ዲን ተወካይ አቶ ዘየደ ተክሌ ሲሆኑ አያይዘውም ድሬዳዋ ከተማ የንግድ፣ ኢንዱስትሪና ኢንቨስትመት እንደመሆኗ መጠን ከተማችን ባላት የቱሪዝም መዳረሻዎች ከተማዋን ለመጎብኘት የሚመጡ እንግዶችን ተቀብሎ ለማስተናገድ ብቃት ያላቸው ባለሙያዎች ያስፈልጋሉ ስለዚህ እነዚህን ባለሙያዎች ለማፍራት ደግሞ ኮሌጁ በትጋት እየሰራ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም በምርቃት መርሃ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የሳምራት ሆቴል ተወካይ አቶ መልካሙ እንዳሉት ሆቴሉ በፍጥነት እያደገችና ብዙ ታሪኮች ባላት ትልቅ ከተማ ከተለያዩ የሀገራችን ክፍሎች እንዲሁም ከውጪ ሀገራት የሚመጡ እንግዶችን እየተቀበለና ተገቢውን መስተንግዶ እየሰጠ የሚገኝ ትልቅ ሆቴል ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በዚህ ሆቴል ውስጥ እየሰሩ የሚገኙ ሰራተኞች ያላቸውን ሙያዊ ክፍተቶች ከኮሌጁ ጋር በመሆን ለመሙላት የተሰሩ ስራዎች እጅግ በጣም የሚያረካና በቀጣይም በተለያዩ ሙያዎች ከኮሌጁ ጋር አብረን እንድንሰራ የሚያነሳሳ ነው ብለዋል፡፡በመጨረሻም ይህን ስልጠና በአግባቡ ሲያሰለጥኑ ለነበሩ የኮሌጁ መምህራኖችና የኮሌጁ ኃላፊዎች ምስጋና አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም በምረቃት መርሃ ግብሩላይ መልእክት ያስተላለፉት በስራና ክህሎት ቢሮ የCOC ማእከል ተወካይ አቶ መኳንንት እንዳሉት የሆቴልና ሆስፒታሊቲ ዘርፉን ለማሳደግ ከሚሰጠው ትምህርት ስልጠና ጎን ለጎን ባለሙያዎች ብቁ መሆናቸውን የማረጋገጥ ስራ መስራት ያስፈልጋል ያሉ ሲሆን አያይዘውም የCOC ማእከሉ በተለያዩ ተቋማት የሚገኙ ባለሙያዎችን በአጫጭርም ሆነ በረጃጅም ሙያዎች የሰለጠኑ እንዲሁም በልምድ የተገኘ እውቀቶችን የመመዘን ስራዎችን የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡ይህም የስራ ዘርፎቹ ብቃት ባላቸው ባለሙያዎች እንዲመሩ ያስችላል ብለዋል፡፡ ኮሌጁ ያስመረቃቸው የሳምራት ባለሙያዎች በአጠቃላይ 80 የሚሆኑ ሰልጣኞች ሲሆኑ Front office, Food and Beverage service, Housekeeping እና Food Preparation ሙያዎች በስራ ቦታቸው ላይ በመሆን(in company Training ) ስልጠናውን መስጠት እንደተቻለ ለማወቅ ተችሏል፡፡በመጨረሻም በሆቴሉ የላቀ አፈጻጸም ላስመዘገቡ ሰራተኞች የእውቅና መርሃ ግብር ተከናውኗል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትልሞች በሦስት ዋና ጉዳዮች ያተኩራሉ - ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር)  የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትልሞች በዋናነት በሦስት ዋና ዋና ጉዳዮች ላይ እንደሚያተኩሩ ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) ገለጹ። ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) የዲጂታል ኢትዮጵያ 2025 ማጠቃለያ እና በዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 በይፋ የማስመጀመሪያ ሥነ-ሥርዓት ላይ ማብራሪያ ሰጥተዋል። በዚሁ ወቅትም የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዋና ራዕዩን ሰብሰብ አድርገን ስንገልጸው ሦስት ነገሮችን ለማሟላት ያለመ ነው ብለዋል። በዚህም መሠረት የመጀመሪያው አቅርቦት(አክሰስ) መሆኑን ገልጸው፤ ይህ ማለት ሁሉም ዜጎች ካሉበት ሆነው የሚፈልጉትን አገልግሎት ማግኘት የሚችሉበትን ዕድል መፍጠር መሆኑን አስረድተዋል። በመሆኑም ዜጎች እኩል እድል እና እኩል አገልግሎት እንዲያገኙ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 የመጀመሪያ ትልሙ አቅርቦት ነው ብለዋል። ሁለተኛው ዕድል(ኦፖርቹኒቲ) መሆኑን አመላክተው፤ እኩል እድል ባልሰጠንበት መስክና ሁኔታ እኩል ተጠቃሚ መሆን አይቻልም ነው ያሉት በማብራሪያቸው። በጾታ፣ በአካል ጉዳት ወይም በርቀት ምክንያት ዜጎች ሊያገኙ የሚገባውን እድል እኩል የሚያመቻች ሥርዓት መፍጠር እንደሚያስፈልግም ነው ያስገነዘቡት። ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 እንዲያሳካ ከሚፈለጉት ጉዳዮች አንዱ ለዜጎች እኩል እድል መስጠት መሆኑንም አመላክተዋል። ሦስተኛው ዲጂታል ኢትይጵያ 2030 እንዲያሳከው የሚፈለገው ትልም መተማመን(ትረስት) መሆኑን ተናግረዋል። በዚህም መሠረት በዜጎችና በተቋማት መካከል መተማመን ካልተፈጠረ፤ የገንዘብ ዝውውር፣ መማር ማስተማር፣ ለጤና ዳታ መስጠት፣ ደፍሮ ለሥራ ማመልከት፣ የግል መረጃን በክላውድ ላይ ማስቀመጥ የሚታሰብ አይደለም ሲሉ አብራርተዋል። ቴክኖሎጂ አሳላጭ መሆን ተስኖት በጥርጣሬ የሚታይና የሚፈራ ብሎም ዜጎች የማያምኑበት ከሆነ የምናስበውን ነገር አያሳካም ብለዋል ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) በገለጻቸው። ሦስቱ የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ትልሞች አቅርቦት፣ ዕድል እና መተማመን ተደምረው ለዜጎች በርከት ያለ የሥራ ዕድል መፍጠር ብሎም ለሀገር ዕድገት ማረጋገጥ አለባቸው ብለዋል። ሥራ እና ዕድገት ብቻውን በቂ እንዳልሆነ የጠቆሙት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር)፤ ሉዓላዊነትንም የሚያረጋግጥ መሆን እንዳለበት አስረድተዋል። ስለዚህ ዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ከላይ በተገለጹት ጉዳዮች ላይ አተኩሮ የኢትዮጵያን ብልጽግና ከሚያረጋግጡ ዋና ዋና ሴክተሮች(ምሠሦዎች) አንዱ ሆኖ ያገለግላል ተብሎ በመንግሥት መታሰቡን አውስተዋል። በመሆኑም በትብብር ከሠራን ይህን ራዕይ እንደምናሳካ ሙሉ እምነት አለኝ ሲሉም ተናግረዋል። ዘገባው የኢዜአ ነው። ታህሳስ 13/2018 ዓ.ም 🔗ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

የዲጂታል ኢትዮጵያ 2030 ስትራቴጂ ዋና ዋና አምዶች; ታህሳስ 12/2018 ዓ.ም 🔗ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtTbPZtDW1y

𝟮.𝟱 𝘆𝗲𝗮𝗿𝘀, 𝟭.𝟭 𝗠𝗶𝗹𝗹𝗶𝗼𝗻+ 𝘆𝗼𝘂𝘁𝗵 𝗥𝗲𝗮𝗰𝗵𝗲𝗱, 𝟯𝟮𝟱,𝟬𝟬𝟬+ 𝘆𝗼𝘂𝘁𝗵 𝗶𝗻 𝘄𝗼𝗿𝗸 𝗿𝗲𝗴𝗶𝘀𝘁𝗲𝗿𝗲
𝟮.𝟱 𝘆𝗲𝗮𝗿𝘀, 𝟭.𝟭 𝗠𝗶𝗹𝗹𝗶𝗼𝗻+ 𝘆𝗼𝘂𝘁𝗵 𝗥𝗲𝗮𝗰𝗵𝗲𝗱, 𝟯𝟮𝟱,𝟬𝟬𝟬+ 𝘆𝗼𝘂𝘁𝗵 𝗶𝗻 𝘄𝗼𝗿𝗸 𝗿𝗲𝗴𝗶𝘀𝘁𝗲𝗿𝗲𝗱, 𝗘𝗧𝗕 𝟯.𝟳𝟭+ 𝗕𝗶𝗹𝗹𝗶𝗼𝗻 𝗗𝗶𝘀𝗯𝘂𝗿𝘀𝗲𝗱. ----------------------------------------- The SEED Program, led by EDI in partnership with MastercardFoundation, is delivering measurable results for youth employment in Ethiopia. In just two and a half years the program has: ✅ Reached 1,167,804 youth. ✅ Connected 325,204 young people to sustainable work opportunities. ✅Supported 52,300 enterprises in scaling their operations. ✅Facilitated ETB 3.71 Billion in financing for 16,320 SMEs and startups through CBE. We have reached our 5-year goal early by reaching targeted youth ~(1.1 million) and training 1,022 TVT leaders (102.2% of target). Our commitment to equity remains firm: 78% of our outreach participants are women, and we have successfully integrated 3,270 vulnerable youth into the workforce.

የአሰልጣኝ መምህሩን አቅም መገንባት የስልጠና ጥራቱን ከማሻሻል አንጻር የላቀ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት በምሽት ስልጠና በተ
+7
የአሰልጣኝ መምህሩን አቅም መገንባት የስልጠና ጥራቱን ከማሻሻል አንጻር የላቀ ሚና እንደሚጫወት ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ሂደት በምሽት ስልጠና በተለያዩ ሙያዎች ስልጠና ለሚሰጡ አዲስ አሰልጣኝ መምህራን የማሰልጠን ስነ-ዘዴ (Training Methodology) ስልጠና ሰጠ:: ስልጠናው ለአሰልጣኝ መምህራኑ ከስልጠና ጥራት ጋር ተያይዞ የዘርፉን እሳቤ ተረድተው ስልጠናውን በሚፈለገው ደረጃ መስጠት እንዲያስችላቸው እንዲሁም ከምዘና ሂደት እና የምዘና ውጤት አገባብ ጋር ተያይዞ የሚስተዋሉ ክፍተቶችን ከወዲሁ ለማስቀረት ታሳቢ ያደረገ ስልጠና እንደሆነ የተገለፀ ሲሆን የሚነሱ ተያያዥ ቅሬታዎችንም ለመፍታት ያግዛልም ተብሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 11/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት ፆታን መሰረት ባደረገ ጥቃት ላይ እንዲሁም የአካባቢያዊ እና ማህበራዊ ጥበቃን አስመልክቶ ከተለያዩ ባለድርሻ አካላት ጋር ተወያየ። በመድረኩ ፆታን መሰረት ያደረገ ጥቃት (Gender-Based Violence) እና የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃ (Enviroment and Social safe guard) ጋር ተያይዞ በፕሮጀክቱ ቀጣይ ትግበራዎችና ተደራሽ የሚሆኑ ዝርዝር ተግባራት ላይ ለኮሌጁ የኢንዱስትሪ አድቫይዘሪንግ ቦርድ አባላት እንዲሁም የልህቀት ማዕከል ከሆኑት ሶስቱ ዲፓርትመንት ለተወጣጡ አሰልጣኝ መምህራን ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ተካሂዷል:: በEASE ፕሮጀክት በትኩረት እንዲሰራባቸው ከሚጠበቁ ጉዳዮች መካከል የስርዓተ-ፆታ እንዲሁም አካባቢያዊና ማህበራዊ ጥበቃ በዋነኛነት እንደሚጠቀሱ ያስታወሱት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ እክለውም ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ጋር በተመለከተ ፕሮጀክቱ የራሱ አያያዝና ሪፖርት አቀራረብ ሂደት ያለው በመሆኑ ግንዛቤን ለመፍጠር እንዲሁም በቀጣይ በፕሮጀክቱ የሚሰሩ የሪኖቬሽን ስራዎች የአካባቢ ጥበቃን ባማከለ ሁኔታ ተግባራዊ እንዲሆኑ በሚቻልበት አግባብ ከባለድርሻ አካላት ጋር ለመወያየት ይህ መድረክ መዘጋጀቱንም ገልፀዋል:: በዕለቱ በነበረው መድረክ በቅድሚያ በEASE ፕሮጀክት ትግበራ የእስካሁን አፈፃፀምና በቀጣይ የሚከናውኑ ቁልፍ ተግባራትን አስመልክቶ የፕሮጀክቱ ዋና አስተባባሪ የሆኑት ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ለተሳታፊዎች በዝርዝር ገለፆ አድርገዋል:: በመቀጠል በፕሮጀክቱ ትግበራ ወቅት ፆታን መሰረት ያደረጉ ጥቃቶች ሲፈጠሩ ጉዳዩ በሚስተናገድበት አግባብና ሪፖርት ከማድረግ ጀምሮ እስከ ሚሰጠው ውሳኔ ድረስ በፕሮጀክቱ ባህሪ መሰረት የተቀመጠውን የአሰራር ሂደት በዝርዝር ለተሳታፊዎች ግንዛቤ የሰጡት የEASE ፕሮጀክት የስርዓተ-ፆታና አካቶ ባለሙያ የሆኑት አቶ አዲስ አክሊሉ ሲሆኑ በተጨማሪም የፕሮጀክቱ የተለያዩ ትግበራዎች በሚከናወኑበት ወቅት የአካባቢና ማህበራዊ ጥበቃን ታሳቢ ባደረገ መልኩ እንዲከናወኑ በሚያመለክት ሁኔታ የተቀመጡ ዝርዝር ሂደቶችና ነጥቦች ላይም ሰፊ ገለፃን በመስጠት ለመድረኩ ተሳታፊዎች ግንዛቤ ፈጠረዋል:: በመጨረሻም በቀረቡ ጉዳዮች ላይ ከመድረኩ ተሳታፊዎች ጋር ውይይት የተካሄደ ሲሆን ለቀጠይ የፕሮጀክቱ ትግበራ ግብዓት የሚሆኑ ሀሳቦችም የተገኙበት መድረክ ነበር:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በተለያዩ ፕሮጀክቶች ለኮሌጁ የተሰጡ የተለያዩ ግብአቶች ከትምህርትና ስልጠናው በዘለለ ለኮሌጁ ገቢ የሚፈጥሩ ስራዎች ላይ እንዲውሉ መደረጉ የሚበረታታ ነው ተባለ፡፡ የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የICT የልህቀት ማእከል ግንባታንና የKFW ፕሮጀክትን የሚገመግም የባለሙያዎች ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመስክ ምልከታ አደረገ፡፡ በግምገማና ውይይት ሂደቱ ላይ በመገኘት እንግዶቹን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር ያደረጉት እና የኮሌጁን የተለያዩ ስራዎችን ያስጎበኙት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃድ ሲሆኑ በንግግራቸውም የSIFA ፕሮጀክት እንዲሁም የKFW ፕጀክቶች ለኮሌጁ ግብአትን ከማሟላት በዘለለ ለኮሌጁ የማሰልጠን ሂደቱን በዘመናዊ ማሰልጠኛዎች መስጠት እንድንችል አድርጎናል ያሉ ሲሆን የኮሌጁ ዲን አያይዘውም በኮሌጁ የሚተገበረው የSIFA ፕሮጀክት ወጣቶቻችን የሙያና የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ ትልቅ ፕሮጀክት ነው፡፡ በፕጀክቱ አማካኝነት በኮሌጁ የሚገነባው የልህቀት ማእከል ከተማችንን ብሎም ሃገራችንን የICT ማእከል የሚያደርጋት ነው ብለዋል፡፡በመጨረሻም በኮሌጁና በKFW መካካል ያለው ግንኙነትም በቀጣይ ተጠናክሮ እንዲቀጥል ኮሌጁ ቁርጠኛ ነው ብለዋል፡፡ በግምገማና ውይይቱ ሂደቱ ወቅት የSIFA እና የKFW ፕሮጀክቶች እስካሁን የደረሰበት የፕሮጀክት አፈጻጸም በአቶ መሳይ ጥላሁንና በአቶ መሃመድ አወልጠሃ ቀርቦ ውይይት የተደረገ ሲሆን በስተመጨረሻም በኮሌጁ ውስጥ እየተሰሩ ያሉ ስራዎችን ተዘዋወውረው ጎብኝተዋል፡፡ በጉብኝቱና በሪፖርቱ መሰረትም ልኡክ ቡድኑ የመሩት ዶ/ር አየለ ግዛቸው እንዳሉት ኮሌጁ የምስራቅ አፍሪካ የልህቀት ማእከል ለመሆን እየሰራ ያለውን ስራ አድንቀው በቀጣይ በኮሌጁ ውስጥ የሚገነባው የICT ልህቀት ማእከል ሲጠናቀቅ ደግሞ ለኮሌጁ ብሎም ለከተማው እንዲሁም ለሃገሪቱ የሚሰጠው ጥቅም ከፍተኛ ነው ብለዋል፡፡አያይዘውም በተለይ በተለያዩ ፕሮጀክቶች ለኮሌጁ የተሰጡ የተለያዩ ግብአቶች ከትምህርትና ስልጠናው እንዲሁም የበቃ የሰው ሃይል ከመፍጠር በዘለለ ለኮሌጁ ገቢ የሚፈጥሩ ስራዎች ላይ እንዲውሉ መደረጉ የሚበረታታ ነው ብለዋል፡፡ የልህቀት ማእከሉን ግንባታ በፍጥነት ተጀምሮ እንዲያልቅ አስፈላጊውን ስራ በKFW በኩል እንደሚደረግም ገልጸዋል ፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ

በአስተዳደሩ የሚገኙ የግልና የመንግስት የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች የአገልግሎት አሰጣጥ ለመገምገም ያለመ ድንገተኛ ሱፐርቪዥን ተካሄደ። የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል የቴክኒክና ሙያ ኮሌጆችን አገልግሎት አሰጣጥ ውጤታማነት ለማረጋገጥ የሚረዳ የኢንስፔክሽን ስራ መስራት ሲሆን በዛሬው ዕለትም በቢሮው ም/ኃላፊ እና በቴክኒክና ሙያ ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ የሚመራ ቡድን በአስተዳደሩ የግልና የመንግስት ቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ድንገተኛ ምልከታ አድርጓል። የድንገተኛ ምልከታ ዋንኛ አላማም ነባርና አዲስ ገቢ ሰልጣኞች በየኮሌጆቹ በስልጠና ላይ መሆናቸውን በተመሳሳይ የኮሌጅ አመራርና አሰልጣኝ መምህራን  በስራ ገበታቸው ተገኝተው ለዜጋው ተገቢውን አገልግሎት እየሰጡ ስለመሆናቸው ለማረጋገጥና በተጨማሪ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና አፈጻጸም ዙሪያ ያለውን ነባራዊ ሁኔታ ለመመልከት ሲሆን መሰል ድንገተኛ ምልከታዎች በሁሉም ኮሌጆች ተጠናክረው የሚቀጥሉ ይሆናል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ታህሳስ 10/2018 ዓ.ም ድሬዳዋ