fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 069
مشترکین
+224 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+230 روز
آرشیو پست ها
#ዜና | በሀገራችን እንዲሁም በድሬዳዋ አስተዳድር መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ እና አለም አቀፍ ተወዳዳሪ አሽከርካሪዎችን ማፍረት እንደሚያስፈልግ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሁለተኛ ዙር ያሰለጠናቸውን መካኒክ አሽከርካሪዎችን በዛሬው እለት አስመረቀ፡፡ የትራፊክ አደጋ አምራች ኃይሉ ላይ ጉዳት የሚያደርስና ማህበረሰቡንም የሚጎዳ አስከፊ አደጋ ነው ያሉት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ ሲሆኑ የትራፊክ አደጋ በመንገድ ብልሽት፣በተሸከርካሪ ብልሽት፣ በእግረኛ የመንገድ አጠቃቀም ስህተት እንዲሁም በአሽከርካሪዎች ቸልተኝነት የሚደርስ ነው ስለዚህ ይህን የትራፊክ አደጋ ለመቀነስ ደግሞ ኮሌጁ አሽከርካሪዎችን በመካኒክነት ሙያ እንዲሁም በስነ ባህሪ በማብቃት አደጋውን መቀነስ በሚቻልበት ዙሪያ ስልጠናዎችን እየሰጠ ክፍተቶችን እየሞላ ይገኛል ብለዋል፡፡ አያይዘውም ለከተማችን ብሎም ለሃገራችን ብቁና ተወዳዳሪ አሽከርካሪዎችን ለማፍራት ቀጣይነት ባለው መልኩ በተለያዩ የሙያ መስኮች ስልጠናዎችን በመስጠት አሽከርካሪዎችን የማብቃት ስራ ኮሌጁ በሰፊው የሚሰራ ይሆናል ብለዋል፡፡በመጨረሻም እንኳን ለምርቃት ቀናችሁ አደረሳችሁ ብለዋል፡፡ በምርቃቱ መርሃ ግብር ላይ በመገኘት ንግግር ያደረጉት የቴክኒክና ሙያ ኤጀንሲ አሰልጣኝ ልማት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታሪኩ ለገሰ እንዳሉት ይህ ስልጠና ብቃት ያለው መካኒክ አሽከርካሪዎችን በማፈራት የትራፊክ አደጋን መቀነስ ዋናው አላማ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም በቀጣይ ይህንን ስልጠና በዘመናዊ መኪኖች መስጠት እንዲቻል የአሰልጣኞችን ብቃት የማሳደግ እና የማሰልጠኛ እቃዎችን የማሟላት ስራ ከኮሌጁ ጋር በመሆን ይሰራል ብለዋል፡፡ መካኒክ አሽከርካሪዎች ስልጠና ይህ የሁለተኛ ዙር ሲሆን በዚህም ስልጠና ከ47 በላይ አሽከርካሪዎች የተሳተፉበት እንደሆነና ሶስተኛ ዙር ስልጠናም በቀጣይ እንደሚጀመር በእለቱ ተገልጿል ፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 6/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ወጣቶችን በኢኮኖሚው እንቅስቃሴ የሚፈጠሩ በርካታ እድሎችን ተጠቃሚ በማድረግ ስራ አጥነትን ለመቅረፍ በሚደረገው ርብርብ የወላጆች እና የአካባቢው ማህበረሰብ ሚና የላቀ መሆኑ ተገለፀ:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ EASE ፕሮጀክት በ2ኛ ደረጃ ት/ቤቶች ለሚገኙ የወላጅ ኮሚቴዎች እንዲሁም በየወረዳው ለተመረጡ የመንደር ኮሚቴዎች በአዲሱ የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ:: የግንዛቤ መስጫ መድረኩን በንግግር የከፈቱት የስራና ክህሎት ቢሮ ም/ሀላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ ስተላፉት በመልዕክታቸው በተለምዶ ያደጉ እያልን የምጠራቸው ሀገራት ዛሬ ለደረሱበት እድገት መነሻ የሆናቸው በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ላይ ያሳደሩት እምነትና ዘርፉ ላይ በሰሩት ጠንካራ ስራ መሆኑን ጠቅሰው ወጣቱን በዚህ ረገድ ግንዛቤው ተፈጥሮለት የክህሎት ስልጠናዎች ላይ እንዲሰማራ እንዲሁም እንዱስትሪውን እንዲያንቀሳቅስ የማድረጉ ተግባርና ሀላፊነት ከወላጆች ጀምሮ የሁላችንም ድርሻ ነውም ብለዋል:: ወጣቶች አጠቃላይ የኢኮኖሚ እንቅስቃሴ ላይ ጉልህ ሚና እንዲኖራቸው ለማስቻል እና እየተፈጠሩ ያሉ እጅግ በርካታ እድሎችን ተጠቃሚ ለመሆን የመጀመርያ መግቢያ በሩ የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እንደሆነ የገለፁት የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ሲሆኑ አክለውም ወጣቶች ወደ ዘርፉን በሚፈለገው መጠን እንዳይቀላቀሉ ቴክንክና ሙያ ላይ በተለምዶ ያልተገባ ስም ተልጥፏል ያሉ ሲሆን እንደ ኮሌጅ ይህንን አመለካከት ለመቅረፍ በርካታ ስራዎች እየተሰሩ እንዳሉ ገልፀው ወላጆችን ጨምሮ ህብረተሰቡ ውስጥ ተሰሚነት ያላችሁ ሰዎች በተገኘው አጋጣሚ ለወጣቶች ግንዛቤ የመፍጠሩን ስራ ላይ መረባረብ ያስፈልጋልም ብለዋል:: በመድረኩ የተሻሻለውን የቴክኒክና ሙያ ፖሊሲ ሰነድ ለተሳታፊዎች ያቀረቡት የኮሌጁ የውጤት ተኮር ትምህርትና ስልጠና ም/ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ ባቀረቡት ሰነድም የቴክኒክና ሙያ እስፈላጊነት ጨምሮ ነባሩ ፖሊሲ ላይ የታዩ ክፍተቶች እንዲሁም የፖሊሲውን መሻሻል አስፈላጊነትን በዝርዝር ለመድረኩ ተሳቲፊዎች አቅርበዋል:: የEASE ፕሮጀክት ከአለም ባንክ ጋር የ5 አመት ፕሮጀክት እንዳለው የገለፁት ደግሞ የEASE ፕሮጀክት ዋና ኮርድኔተር ኢንጂነር ፋሲል ማዘንጊያ ሲሆኑ አያይዘውም ኮሌጁ መሰል ፕሮጀክቶችን በማፈላለግ አስፈላጊ የሚባለውን ሁሉ የሚያሟላው በከተማችን ያሉ ወጣቶችን አሰልጥኖ ከስራ ጋር ለማስተሳሰር እንደሆነም ጠቅሰው ወጣቶችን ወደዚህ እንዲመጡ ማበረታታት ያስፈልጋልም ብለዋል:: በመጨረሻም ከመድረኩ የተነሱ ጉዳዮችን መነሻ በማድረግ በተሳታፊዎች በርካታ ሀሳቦች ላይ ውይይት የተካሄደ ሲሆን በቀጣይ በቅንጅት በሚሰሩ ተግባራት ላይ ከመግባባት በመድረስ መድረኩ ፍፃሜውን አጊኝቷል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮምኒኬሽን መጋቢት 5/2017 ዓ.ም

#ዜና| ኮሌጁን ዘመናዊና ለሁሉም ተደራሽ የሆነ ለማድረግ በተለያዩ ሁነቶች የተገኙ ልምዶችን ለኮሌጁ ማህበረሰብ በማካፈል ምርጥ ተሞክሮ ያለው ተቋም እንዲሆን እየተሰራ እንዳለ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ
+5
#ዜና| ኮሌጁን ዘመናዊና ለሁሉም ተደራሽ የሆነ ለማድረግ በተለያዩ ሁነቶች የተገኙ ልምዶችን ለኮሌጁ ማህበረሰብ በማካፈል ምርጥ ተሞክሮ ያለው ተቋም እንዲሆን እየተሰራ እንዳለ ተገለጸ፡፡ የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማኔጅመንትና የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ከኢትዮጵያ አቬይሽን አካዳሚ የተቋም አሰራር ስርአት ያገኙትን መልካም ተሞክሮ ለተቋሙ ትምህርት ክፍልና የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ተጠሪዎች አካፈሉ፡፡ ኮሌጃችን ብዙ ለሌሎች እንደ ተሞክሮ የምንሰጣቸው መልካም ጎኖች አሉን ነገር ግን ወጥነት ያለው አተገባበር ባለመኖሩ የተለያዩ ክፍተቶች ይስተዋላሉ ያሉት የኮሌጁ ም/ዲንና የኢ/ኤ/ቴ/ሽ ኃላፊ የሆኑት ወ/ሮ ትግስት በዙ ሲሆኑ ም/ዲኗ አያይዘውም በዛሬው እለት የምናደርገው ይህ የልምድ ልውውጥ በተለያዩ ተቋማት የተገኙ መልካም ተሞክሮዎችን በመውሰድ እንዲሁም ለተቋማችን እንዲሆን በማድረግ ልንተገብራቸው ይገባል ብለዋል፡፡በመጨረሻም ኮሌጃችንን ዘመናዊና ለሁሉም ተደራሽ የሆነ ተቋም እንዲሆን ሁሉም አካላት በርብርብ ሊሰራ ይገባል ብለዋል፡፡ በዛሬው እለት ልምዳቸውን ያካፈሉት የኮሌጁ ማኔጅመንት አባላትና የትምህርት ክፍል ተጠሪዎች ከዚህ ቀደም ለ5 ቀናት በኢትዮጵያ አቬይሽን አካዳሚ የTvT leadership and management system ላይ ትኩረቱን ያደረገ ስልጠና መውሰዳቸው የሚታወስ ነው፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 5/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በሀገር አቀፍ ደረጃ ለ4ኛ ጊዜ ለሚካሄደው የክህሎት ውድድር ዝግጅቱን ማጠናቀቁን አስታወቀ፡፡ ኮሌጁ በ2017 ዓ.ም "ብሩህ አዕምሮዎች ፣በክህሎት የበቁ ዜጎች!" በሚል መሪ ሀሳብ ለሚካሄደው ሀገር አቀፍ የክህሎት ውድድር የቅድመ ዝግጅት ሥራዎች አጠናቆ ከመጋቢት 9 2017 ዓ.ም ጀምሮ ውድድሩ እንደሚካሄድ የገለፁት የኮሌጁ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ም/ዲን አቶ ተሾመ ሸዋዬ ሲሆኑ ውድድሩ ላይ የሚሳተፉ ተወዳዳሪዎችን ከመለየት አንስቶ የሚያስፈልጉ ግብዓቶች በሟሟላት የተለያዩ የቅድመ ዝግጅት ስራዎች መከናወናቸውንም ገልፀዋል:: በዘንድሮ ውድድር ኮሌጁን እንዲሁም ከተማ አስተዳደሩን በሀገር አቀፍ ውድድር ላይ የሚወክሉ አሰልጣኞች፣ሰልጣኞች እንዲሁም ኢንተርፕራይዞችን አወዳድሮ ለመለየት በኮሌጅ ደረጃ ከመጋቢት 9 ጀምሮ የሚደረግ ሲሆን ውድድሩም በ7 የሙያ ዘርፎች ተወዳዳሪዎችን እንደሚያሳትፍ ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 4/2017 ዓ.ም

#ዜና| የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የብየዳ እና የምህንድስና ብቃት ማእከል ለመሆን እየሰራ እንዳለ ተገለጸ፡፡ ከኢትዮጵያ የምህንድስና ብቃት ማእከል(CEE) የተውጣጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የብየዳ እና የምህንድስና ብቃት ማእከል የመስክ የስራ ጉብኝት አደረጉ፡፡ ከፍተኛ ባለሙያዎችን የተቀበሉትና የተቋሙን እንቅስቃሴ ያስረዱት የኮሌጁ ዲን አቶ ሰለሃዲን አብዱልሃሚድ እንዳሉት ኮሌጁ በተለያዩ የሙያ ዘርፎች የልህቀት ማእከል ለመሆን አልሞ እየሰራ ይገኛል ከነዚህም መካከል አንዱ ለምስራቁ የሃገራችን ክፍል ማገልገል የሚችል የብየዳ የልህቀት ማእከል አንዱ ነው ያሉ ሲሆን አያይዘውም ይህ የብየዳ ማእከል በተቋማችን መኖሩ ለምስራቁ የሀገራችን ክፍል ለሚኖሩ ኢንዱስትሪዎች እንዲሁም በተለያዩ ተቋማት ውስጥ የሚገኙ ወጣቶችን በሙያና በክህሎት የዳበሩ እንዲሆኑ ያስችላል ብለዋል፡፡ኮሌጁ በአስተዳደሩ በኩልም እንደ ተርኒኪ አይነት ፕሮጀክቶችን ተረክቦ እየሰራ እንዳለ ለባለሙያዎቹ ገለጻ አድርገዋል፡፡ በኮሌጃችን በተለያዩ ደረጃዎች የበቁ ከፍተኛ የብየዳ አሰልጣኞች ያሉት ኮሌጅ ነው ያሉት ደግሞ የኮሌጁ የማኑፋክቸሪንት ትምህርት ክፍል ተጠሪ አሰልጣኝ መምህር ዮሃንስ ተካ ሲሆኑ አያይዘውም ይህን በኮሌጁ ያለውን መልካም እድል በመጠቀም ለተለያዩ ኢንዱስትሪዎች በርከት ያሉ ድጋፎችን መስጠት ችላል እንዲሁም ለባለሙያዎቻቸው ደግሞ በየጊዜው ስልጠናዎችን መስጠት ችለናል ብለዋለል፡፡ የመስክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም የልኡካን ቡድኑ ጋር በነበረው የጋራ ውይይት ወቅት የተሳተፉ የልኡክ ቡድኑን አባላት እንዳሉት አጠቃላይ የኮሌጁ እንቅስቃሴ እጅግ በጣም ጥሩ የሚባልና በተለያዩ መስኮች የልህቀት መአከል ለመሆን እየሰራ ያለው ስራ የሚበረታታነው በቀጣይ ደግሞ የብየዳ ማእከሉ ሙሉ እውቅና አግኝቶ በኮሌጁ ውስጥ ሲቋቋም ድግሞ ተጨማሪ አቅምን ይፈጥራል ያሉ ሲሆን፡፡ ትምህርት ክፍሉም እየሰራ ያለው ስራ ለከተማው ብቻ ሳይሆን ለምስራቁ የሃገራችን ክፍል የሚተርፍ ስራ ነው ስራውም ለሌሎች ኮሌጆች እንደ አርአያ የሚወሰድ ነው ብለዋል፡፡ የመስክ የስራ ጉብኝቱ ዋናው አላማ ኮሌጁን የምህንድስና ልህቀት ማእከል ለማድረግ ያሰበ እንደሆነ በውይይቱ ወቅት ለማወቅ ተችሏል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን መጋቢት 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች ላይ የሚሰራውን ግንዛቤ የመፍጠር ስራ በማጠናከር በማርያም ሰፈር እና በመድሀንያለም አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ላይ ለሚገኙ የ11ኛ እና 12ኛ ክፍል ተማሪዎች ዘርፉን አስመልክቶ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ:: በግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኩ ላይ ተማሪዎች ስለ ዘርፉ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲኖራቸው ከማደረግ አኳያና እንደ ሀገር ከተያዘው የትኩረት አቅጣጫም አንፃር የቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ለወጣቱ በተለይም ከዚህ በኃላ ወደዘርፉ ለሚቀላቀሉ የ2ኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ብዙ መልካም እድሎችን የያዘ ዘርፍ መሆኑን በዝርዝር ማብራሪያ በመስጠት ሰፋ ያለ ግንዛቤ የመፍጠር ስራ መስራት ተችሏል:: የግንዛቤ ማስጨበጫውን ለተማሪዎች የሰጡት የኮሌጁ ዲኖች እንዲሁም የዲፓርትመንት ተጠሪዎች ሲሆኑ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ወደ ቴክኒክና ሙያ ተቋም ከመቀላቀላቸው አስቀድሞ ከወዲሁ በአስተሳሰብም ሆነ ለዘርፉ ባላቸው አረዳድ ዝግጁ እንዲሆኑ የሚያደርጋቸውን ምክረ ሀሳብና በኮሌጁ ያለውን ተሞክሮ ለተማሪዎች አካፍለዋል:: በቀጣይም የፈጠራ አቅም ያላቸውን ተማሪዎች የሳይንስና ቴክኖሎጂ ክህሎቶቻቸውን እንዲያዳብሩ የሚረዳቸውን የቴክኒክና ሙያ (STEM) ክበብ በየትምህርት ቤቶቹ በመቋቋም ላይ እንደሚገኙ የተገለፀ ሲሆን ይህም የአንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ቀደም ብለው ከቴክኒክና ሙያ ኮሌጆች ጋር ትስስር እንዲፈጥሩና በሲስተም ውስጥ እንዲያልፉ እድል እንደሚፈጥርላቸውም ተገልፇል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን መጋቢት 4/2017 ዓ.ም

”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” በሶስተኛው ዙር ሥራ ፈላጊ ወጣቶችን ወደ  ትግበራ ለማስገባት እንዲያስችል ለመልማይ እና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጀ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በዚህ ዓመት ቀበሌዎች ለሚተገበረው ”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት”  ውስጥ መሳተፍ ያለባቸውን ወጣት የሆኑ ነዋሪዎችን በመምረጥ በኩል የተጣለባቸውን ሃላፊነት በአግባበቡ መወጣት እንደሚገባቸው  ከየቀበሌው ለተመረጡ መልማይና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ገለጻ ተደርጓል፡፡ በሁለተኛው ዙር ”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” ተግባራዊ ተደርጎ እንደ አስተዳደር የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል ከተጠቃሚዎች ምልመላ ጀምሮ የታዩ የአሰራር ክትተቶችን በማሻሻል ወደ ምዝገባ መገባቱ ይታወቃል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” በሶስተኛው ዙር ሥራ ፈላጊ ወጣቶችን ወደ  ትግበራ ለማስገባት እንዲያስችል ለመልማይ እና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ግንዛቤ መፍጠሪያ መድረክ ተዘጋጀ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የሥራ ዕድል ፈጠራና አንድ ማዕከል ዳይሬክቶሬት በዚህ ዓመት ቀበሌዎች ለሚተገበረው ”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት”  ውስጥ መሳተፍ ያለባቸውን ወጣት የሆኑ ነዋሪዎችን በመምረጥ በኩል የተጣለባቸውን ሃላፊነት በአግባበቡ መወጣት እንደሚገባቸው  ከየቀበሌው ለተመረጡ መልማይና ቅሬታ ሰሚ ኮሚቴዎች ገለጻ ተደርጓል፡፡ በሁለተኛው ዙር ”ብቃት የወጣቶች የሥራ ላይ ልምምድ ፕሮጀክት” ተግባራዊ ተደርጎ እንደ አስተዳደር የተገኘውን ውጤት ለማስቀጠል ከተጠቃሚዎች ምልመላ ጀምሮ የታዩ የአሰራር ክትተቶችን በማሻሻል ወደ ምዝገባ መገባቱ ይታወቃል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 4/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

በኢ.ፌ.ዲ.ሪ መከላከያ ሚኒስቴር የጤና መምሪያ ስር የተደራጀው የምስራቅ እዝ ደረጃ-3 ሪፈራልና ማስተባበሪያ ሆስፒታል ውስጥ የተቋቋመው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ማሰልጠኛ ኮሌጅ በአዲሱ የነርሲንግ ሙያ ላይ ከደረጃ ሶስት እስከ ደረጃ አራት መደበኛ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና እንዲሰጥ ለአንድ አመት የሚቆይ የምዝገባ ፈቃድ ከድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ ተሰጠው፡፡ የምዝገባ ፈቃዱንም በቢሮው የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ታሪኩ ለገሰ በኩል ብ/ጀ ዶ/ር ሃይሉ ከፈኔ የጦር ሀይሎች ሆስፒታል አዛዥን ጨምሮ የሰራዊቱ ከፍተኛ አመራሮች በተገኙበት ሰርተፍኬቱን አበርክተዋል፡፡ ብ/ጀ ዶ/ር ሃይሉ ከፈኔ የምዝገባ ፈቃድ መሰጠቱን ተከትሎ ባስተላለፉት መልዕክት ሰራዊቱ ከጊዜው ጋር የሚሄድ አቅምን እንዲፈጥር ከክህሎትና ቴክኖሎጂ ጋር ያለው መስተጋብር እያሳደገ መሄድ ይገባዋል ያሉ ሲሆን ለዚህም የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና እውቅና መሰጠቱ የሚኖረው ፋይዳ ቀላል አለመሆኑን አስረድተዋል። አቶ ታሪኩ ለገሰ በበኩላቸው ማሰልጠኛው ፈቃድ እንዲሰጠው በጠየቀው መሠረት ከባለድርሻ አካላት ጋር በመቀናጀት ከግብዓት፤ ከሰውሃይል እና ስልጠናውን ለማካሄድ የሚያስፈልጉ ምቹ ሁኔታዎች መሟላታቸውን በማረጋገጥ ለአንድ አመት የሚቆይ የምዝገባ ፈቃድ ተሰጥቷቸዋል አፈጻጸም ታይቶም ከአንድ አመት በኋላ ለሶስት አመት የሚቆይ የዕውቅና ፈቃድ የሚሰጣቸው እንደሚሆን ገልጸዋል። በተያያዘ የማሰልጠን ስነ ዘዴ ስልጠና ወስደው ላጠናቀቁ አሰልጣኞች ሰርተፍኬት በተመሳሳይ የተበረከተ ሲሆን አጠቃላይ የኮሌጁን እንቅስቃሴ ተዘዋውረው በመጎብኘት በቀጣይም የአስተዳደሩ ሥራና ክህሎት ቢሮ የስልጠና ተቋሙን አቅም የሚያሳድጉ ተከታታይነት ያለውን ድጋፍ የሚያደርግ መሆኑን ዳይሬክተሩ አረጋግጠዋል። የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 3/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽን(Job fair) ዝግጅት ዙሪያ ከባለድርሻ አካላት ጋር የጋራ ምክክር ተደረገ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር ሥራና ክህሎት ቢሮ አሰሪና ሰራተኛ ዳይሬክቶሬት ይህን የምክክር መድረክ ሲያዘጋጅ የሥራና ሠራተኛ ማገናኛ ኤግዚብሽኖች አሰሪውና ስራ ፈላጊው በአንድ ቦታ የሚገናኙበትና ሥራ ፈላጊው አሰሪው ላቀረበው ክፍት የሥራ ቦታ የሚያመለክትበት ቀጣሪው ቃለመጠይቅ የሚያደርግበትን ሁኔታ ማመቻቸት ትኩረት እንደተሰጠው የዳይሬክቶሬቱ ዳይሬክተር አቶ መሀመድ ኢብራሂም ተናግረዋል፡፡ በዚህ የምክክር መድረክ ላይ ተሳታፊ የሆኑ ባለድርሻ አካላት በአጠቃላይ ሥራ ፈላጊውና (job seekers) እና ቀጣሪዎች (Employers) በቀላሉ መገናኘት እንዲችሉ መንግሥት ከሚሰጣቸው የስራ ስምሪት አገልግሎቶች መካከል ሥራና ሰራተኛ ማገናኘት ኤግዚብሽን (Job fair) ላይ የሚታዩ ክፍተቶችን በማስተካከልና በመናበብ ሊሰሩ በሚችሉበት አግባብ ላይ በሰፊው ተወያይተዋል፡፡ የሥራና ክህሎት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት መጋቢት 3/2017 ዓ.ም ድሬዳዋ

ክቡር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ "ትንሿ ኢትዮጲያ" ድሬዳዋ የእንኳን በደህና መጡ!
+7
ክቡር አብይ አህመድ (ዶ/ር) ወደ "ትንሿ ኢትዮጲያ" ድሬዳዋ የእንኳን በደህና መጡ!