fa
Feedback
Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

Bureau of Labor and Skills-Dire Dawa

رفتن به کانال در Telegram
1 085
مشترکین
+924 ساعت
+207 روز
+1530 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለሚማሩ ተማሪዎች የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::  የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ከሁለተኛ ደረጃ ት/ቤቶች ጋር በጋራ የሚሰራውን ስራ አጠናክሮ በመቀጠል ያልፉትን 2ቀናት በሳቢያን ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ሰፋ ያለ ግንዛቤን የመፍጠር ስራ ሰርቷል:: የግንዛቤ ማስጨበጫው የተሰጠው በት/ቤቱ ለሚገኙ የ10ኛ ክፍል ተማሪዎች ሲሆን መድረኩ በኦሮምኛ ቋንቋ ትምህታቸውን የሚከታተሉትንም ያማከለና በሁለት መድረክ የተሰጠ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክም ነበር:: የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠናውን ለተማሪዎቹ የሰጡት የኮሌጃችን ዋና ዲን አቶ ታደለ አሰፋ እንዲሁም የኮሌጁ ምክትል ዲን አቶ ኤሊያስ አህመድ ሲሆኑ በመድረኩ ተማሪዎቹ ስለ ቴክኒክና ሞያ ዘርፍ ያላቸውን የተሳሳተ አመለካከት የሚቀርፍና የቴክኒክና ሞያ ነባራዊ ሁኔታን ቁልጭ አርጎ በሚያሳይ መልኩ በመተንተን ዘርፉ ለተማሪዎቹ የሚያስገኘውን ምቹ አጋጣሚ ሰፋ ባለ ማብራሪያ የሰጧቸው ሲሆን ተማሪዎች የነገ መዳረሻችውን ከዚሁ ትኩረት ሰተው በጥንቃቄ መምረጥ እንደሚገባቸውም ምክር ለግሰዋል:: በተጨማሪም በአዲሱ የትምህርት ፖሊሲ መሰረት እነዚህ ተማርዎች 11 እና 12 ላይ የቴክኒክና ሞያ ትምህትና ስልጠናዎችንም አያይዘው የሚሰለጥኑ በመሆኑ በዘርፉ የሚሰጡትን የስልጠና አይነቶች በግልፅ እንዲረዷቸው በማድረግ ከፍላጎታቸው ጋር የሚጣጣመውን የስልጠና አይነት ለይተው ምርጫቸው እንዲያደርጉ የሚረዳቸውን ግንዛቤ መስጠት ትችሏል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ግንቦት 29/2016 ዓ.ም

ድሬን በጋራ እናልማ!! በክቡር ከንቲባችን የተጀመረውን ድሬን እናልማ የልማት ጥሪ ሁሉም የቢሯችን እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች እንድትቀላቀሉ ጥሪዬን አቀርባለሁ። ድሬ የሁላችንም ቤት Lit
+1
ድሬን በጋራ እናልማ!! በክቡር ከንቲባችን የተጀመረውን ድሬን እናልማ የልማት ጥሪ ሁሉም የቢሯችን እና ተጠሪ ተቋማት አመራሮችና ሰራተኞች እንድትቀላቀሉ ጥሪዬን አቀርባለሁ። ድሬ የሁላችንም ቤት Little Ethiopia አቶ ሮቤል ጌታቸው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ኃላፊ

ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የሚገጥማቸውን የገበያ ተደራሸነትን ለመቅረፍ በሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በሚመራው የኢትዬጵያ ሥራ ገበያ  መረጃ ስርአት ፕሮጀክት ለምቶ ተግባራዊ የሆነው  መተግበሪያና ድህረገፅ ላይ በሰፊው እንዲመዘገቡ እየተደረገ መሆኑ ተገለጸ፡፡                                                                                                                                                                                                                     ምዝገባውን እያካሄደ የሚገኘው የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የኢንተርፕራይዞች ልማት ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ሙሉጌታ ኃ/ማርያም እንደተናገሩት ሞዴል ኢንተርፕራይዞች  ምርታቸውን ለሀገር ውስጥም ሆነ ለውጭ ሀገራት  ኦንላይን በማስተዋወቅ የሚሸጡበትና ክፍያ የሚቀበሉበት  የኢንተርፕራይዞቸን የገበያ ፍላጎት ችግርን በመፍታት ተደራሸነትን ከማሳደግ ባለፈ ገበያን ለማረጋጋትና የውጭ ምንዛሬንም ለማምጣት በሚያግዘው በዚህ መተግበሪያ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ታሳቢ ያደረገ መሆኑንና ሁሉም ኢንተርፕራይዞች በወረዳ አንድ ማዕከላት በመቅረብና በመመዝገብ የአገልግሎቱ ተጠቃሚ እንዲሆኑ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 27/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የ EASTRIP ፕሮጀክት የልህቀት ማእከል የህንጻ ግንባታ የስራ አፈጻጸም ከስራና ክህሎት ሚንስቴር እና ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ በተውጣጣ የSupervision
+6
የ EASTRIP ፕሮጀክት የልህቀት ማእከል የህንጻ ግንባታ የስራ አፈጻጸም ከስራና ክህሎት ሚንስቴር እና ከEASTRIP National Project Coordinator ቢሮ በተውጣጣ የSupervision team ግምገማ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተከናወነ፡፡ በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስር መተግበር ላይ ያለው የEASTRIP ፕሮጀክት ከስራና ክህሎት ሚኒስቴር የተውጣጡ ኃላፊዎችና ባለሞያዎች የልህቀት ማዕከሉን የህንጻው ግንባታ አፈጻጸም በዛሬው እለት ገመገሙ፡፡ ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታና የፕሮጀክቱን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግግራቸውም በኮሌጁ እየተተገበረ ያለው ይህ የ EASTRIP ፕሮጀክት መሳካት በኮሌጁ ማኔጅመንት ትልቅ ድጋፍና ክትትል እየተደረገበት አሁን ላለበት ደረጃ ደርሷል ሆኖም ግን በሚፈለገው ፍጥነት ልክ ተሰርቶና በአግባቡ ተጠናቆ ለታለመለት አላማ እንዲውል የከተማ አስተዳደሩ በቅርበት እየተከታተለው እንዲሁም የተለያዩ ድጋፎችን እያደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡ በመቀጠልም ስለ ልህቀት ማእከሉ የህንጻ ግንባታ እንዲሁም አሁን ያለበትን ሁኔታና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች የአማካሪ ድርጅቱ መሐንዲስ ዮሃንስ እቁባይ አማካኝነት ቀርቧል፡፡ ከሪፖርቶና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን የሰጡ ሲሆን በመጨረሻም በፕሮጀክቱ የስራ አፈጻጸም ላይ የSupervision ቡድኑ አቅጣጫ ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 27/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የICT የልህቀት ማእከል ያለበት ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክቱ የአ
+6
በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት የICT የልህቀት ማእከል ያለበት ደረጃ ለመገምገም የፕሮጀክቱ የአፍሪካ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ምክትል ቡድን መሪ ሚስተር ስቴፈን ጆን እና የፕሮጀክቱ የኢትዮጵያ ማስተባበሪያ ጽ/ቤት ኃላፊ ዶ/ር አየለ የተመራ ልኡክ ቡድን በዛሬው እለት የፕሮጀክቱን አሁናዊ ሁኔታ በኮሌጁ በመገኘት ግምገማ አደረገ፡፡ ለግምገማው የመጣውን ልኡክ ቡድን የተቀበሉትና የእንኳን ደህና መጣችሁ ንግግር እንዲሁም የኮሌጁን ሁኔታ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን ሲሆኑ በንግራቸውም ይህ በAUDA NEPAD እና EU የገንዘብ ድጋፍ እየተተገበረ የሚገኘው የ Skill Initiative For Africa(SIFA) ፕሮጀክት ሙሉ በሙሉ ተግባራዊ ሲደረግ እንደ ሀገር የሚጠቅመው ጥቅም የላቀና ብዙ ወጣቶችን የክህሎት፣የስራ ባለቤት እንዲሁም የስራ ፈጣሪ የሚያደርግ እንደሆነ እና ከተማችንን ደግሞ ዲጂታል አሰራሮች የሚያሳድግ ፕሮጀክት እንደሆነ ለልኡክ ቡድኑ ያብራሩ ሲሆን በመቀጠልም ስለ ልህቀት ማእከሉ አሁን ያለበትን ሁኔታ እና በቀጣይ የሚሰሩ ስራዎች በአቶ መሳይ ጥላሁን አማካኝነት ቀርቧል፡፡ከሪፖርቱና ከመስክ ጉብኝቱ በኋላ በቀረበው አፈጻጸም ላይ ልኡክ ቡድኑ የተለያዩ ገንቢ አስተያየቶችን ሰጥተዋል፡፡ የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 26/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በክረምት በንቅናቄ የሚሰሩ ስራዎች ዕቅድ ላይ ከቢሮውና በስሩ ከሚገኙ ኮሌጆችና የወረዳ የሥራና ክህሎት ማስተባበሪያዎች ጋር ውይይት ተካሄደ፤ የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ በክረምት የሚከናወኑ አበይት ተግባራት ለይቶ ዕቅድ አዘጋጅቷል በዚህም የተቋም አቅም ግንባታ፣ የክህሎት ልማት፣ ክህሎት መር የስራ እድል ፈጠራ፣ የአሰሪና ሰራተኛ ግንኙነት እንዲሁም የክረምት በጎ ፍቃድ ስራዎች የሚተገበሩ ይሆናል፡፡ በውይይት መድረኩ ላይ የቢሮ ኃላፊው አቶ ሮቤል ጌታቸው ይህ ዕቅድ በመደበኛ ከሚፈጸመው ተጨማሪ ቁርጠኝነት ታክሎበት የሚፈጸም መሆኑና በተለይ በቅንጅትና በመናበብ አዲሱን የዘርፉን እሳቤ መሠረት በማድረግ የመረጃ ልውውጥና የክትትልና ድጋፍ ስርአትን በመዘርጋት የቢሮው የስራ ክፍሎች፣ ኮሌጆች እና ወረዳዎች የራሳቸውን ዕቅድ አዘጋጅተው ወደ ስራ የሚገቡ እንደሚሆን ገልጸዋል። የቢሮው ም/ኃላፊና የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ ወ/ሮ ፈጡም ሙስጠፋ በበኩላቸው  በቀረበው ዕቅድ ላይ ተግባብቶ ወደ ትግበራ መግባቱ ወሳኝ መሆኑን ገልጸው በተለይ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናውን ሁለቱ የመንግስት ኮሌጆች የከተማ እና የገጠር ወረዳዎችን በመከፋፈል ሁሉን አቀፍና ተደራሽ የሆኑ ስራዎችን ለመስራት መታቀዱን ተናግረዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 23/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት በአስተዳደሩ ከሚገኙ የግል ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኮሌጅ አመራሮችና የሚመለከታቸው አካላት ጋር የድጋፍና ክትትል ግብረመልስ መስጫ መድረክ አካሄደ። በዚህም የተቋማት ትምህርትና ስልጠና ጥራትን ለማስጠበቅ የተከናወነው ይህ የድጋፍና ክትትል ግብረ-መልስ በአስተዳደሩ የሚገኙ የግል ኮሌጆች በዘርፉ ያላቸውን አስተዋጽኦ ከፍ ባለ እና ጥራቱን በጠበቀ አግባብ አገልግሎት መስጠት እንዲያስችላቸው ቢሮው በተከታታይ የሚያደርገው ድጋፍ አካል መሆኑን በቢሮው የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የአሰልጣኝ ልማትና ተቋማት ጥራት ቁጥጥር ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር የሆኑት አቶ ታሪኩ ለገሰ ተናግረዋል፤ በግብረ-መልሱ በተመላከቱት ክፍተቶች እና መስተካከል የሚገባቸው ከትምህርትና ስልጠና አሰጣጥ ጋር ተያያዥ የሆኑ አጠቃላይ ጉዳዮች ላይ በማተኮር በመስጠት በአጭር ጊዜ ውስጥ ማስተካከያ በማድረግ ጥራትን ከማረጋገጥ  አንፃር ትኩረት አድርጎ መስራት እንደሚጠበቅባቸውና ውስንነት የተገኘባቸው ኮሌጆችም የቅርብ ክትትል በማድረግ የታየባቸውን ውስንነት የመሙላትና የማስተካከል ስራዎችን እንደሚሰራ በመግለጽ በቀረበው የኢንስፔክሽን ሪፖርት ላይ ሰፊ ውይይት ማካሄድ ተችሏል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

የድሬዳዋ አስተዳደር የስራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ  የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት በቴክኒክና ሙያ ተቋማትና የተቋም ምዘናን እና ማጠናቂያ ምዘናን መሠረት ተደርገው የተዘጋጁ የምዘና መሳሪያዎች አተገባበር ላይ በኢትዮ ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፍና ክትትል አደረገ፡፡ በዚህም ድጋፍና ክትትል በኮሌጁ የሚገኙ ዲፓርትመንቶች ማለትም በአውቶሞቲቭ፣ በኤሌክትሪካል፣ የኢንፎርሜሽን ኮሚኒኬሽንና ቴክኖሎጂ፣ በኮንስትራክሽን፣ በማኑፋክቸሪንግ፣ ሆቴልና ቱሪዝም እንዲሁም በቢዝነስ ዘርፎች የምዘና መሳሪዎች መዘጋጀታቸው የሚታወስ ሲሆን ይህም የሰልጣኞችን ብቃት የሚያሻሽል እና በገበያው ተወዳዳሪ የሚያደርጋቸው መሆኑ በምልከታው ትኩረት ተደርጎበታል። በመሆኑም የምዘና መሳሪያዎቹ ዝግጅት ብቻ ሳይሆን ትግበራውም ለትምህርትና ስልጠናው ያለው ጠቀሜታ ከፍተኛ በመሆኑ በሌሎችም ሙያዎች ተዘጋጅተው በስራ ላይ እንዲውሉ ማድረግ ላይ ትኩረት ተሰጥቶት ሊሰራ የሚገባው ስራ መሆኑን በተለይም እንደ አገርም በሙያ ደረጃ  ያልተሰራላቸውን ሙያዎች በዚህ ልክ አዘጋጅቶ ወደ ስራ መገባቱ እንደሚበረታታ የሰልጣኝ ልማትና ተቋማት አቅም ግንባታ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ ጀማል አደም ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 22/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ

በኮሌጁ የተጀመሩ የሪፎርም እና የመደበኛ ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ ባለመውና ከሥራና ክህሎት ሚንስቴር መስሪያ ቤት የተውጣጣ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ የክዋኔ
+8
በኮሌጁ የተጀመሩ የሪፎርም እና የመደበኛ ሥራዎች ተግባራዊነትን ለመከታተልና ለመደገፍ ባለመውና ከሥራና ክህሎት ሚንስቴር መስሪያ ቤት የተውጣጣ ልኡክ ቡድን በድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ድጋፋዊ የክዋኔ ኦዲት እና የስራ ጉብኝት በዛሬው እለት አከናወነ:: የድሬዳዋ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዲን አቶ ሳሊም ኡስማን በውይይቱ ወቅት ሲገልጹ በባለፉት ግዜያት በኮሌጁ የተከናወኑ የልማት ስራዎችን በተለይም የትምህርትና ስልጠና፣የኢንተርፕራይዝ ድጋፍ እንዲሁም የቴክኖሎጂ ልማትና የኢንዱስትሪዎችን የተለዋጭ ምርት ማምረት ላይ ኮሌጁ ያለውን ተሞክሮ ትኩረት በማድረግ እየሰራ እንደሚገኝ ለልኡክ ቡድኑ በመስክ ምልከታ ወቅት እና በግብረመልስ ስብሰባ ወቅት በበቂ ሁኔት አስረድተዋል። የመሰክ ምልከታውን መሰረት በማድረግም ልኡክ ቡድኑ ኮሌጁ ያለበትን ደረጃ በበቂ ሁኔታ መረዳት እንደቻሉ እንዲሁም ከትምህርትና ስልጠና፣ከኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ እዲሁም ከኢንዱስትሪዎች ጋር ኮሌጁ ባለው ትስስር አመርቂ ውጤት እያስመዘገባ እንዳለ መረዳት ችለናል ይህን ተሞክሮ ደግሞ ለሌሎች ተቋማት ማስፋት ያስፈልጋል ብለዋል፡፡ የመስክ ምልከታው ዓላማ በዋናነት መልካም አፈፃፀሞችን ማስፋት፣ ማነቆዎችን መፍታት እና ድጋፍ የሚፈልጉ ሥራዎችን ለይቶ በመደገፍ በተቋማዊ አቅም ግንባታ፣ በክህሎት ልማት፣ ከቴክኖሎጂ ልማት እና የኢንዱስትሪ ግንኙነት ላይ የተቀመጡ ግቦች እንዲሳኩ መደላድል ለመፍጠር የሚያስችል የክዋኔ ኦዲት ማድረግ መሆኑን ልኡክ ቡድኑ አስታውቋል:: የኮሌጁ ኮምኒኬሽን ግንቦት 22/2016 ዓ.ም

የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በቤተል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ለተማሪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ አካሄደ::  የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ትኩረት አድርጎ እየሰራባቸው ከሚገኙ ዋና ዋና ተግባራት መካከል አንዱ የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች ትምህርታቸውን አጠናቀው ወደ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ከመግባታቸው አስቀድሞ ከት/ቤቶች ጋር በመተባበር ለተማሪዎቹ የግንዛቤ ማስጨበጫ መድረኮችን በማዘጋጀት ስለ ቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ተገቢውን ግንዛቤ እንዲያገኙ የማድረግ ስራ ሲሆን በዛሬው እለትም በቤተል አንደኛና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመገኘት ለተማሪዎች ግንዛቤ ማስጨበጫ መድረክ ማካሄድ ተችሏል::  በመድረኩ ተገኝተው የግንዛቤ ማስጭበጫውን ያካሄዱት የኮሌጃችን ዲኖች ሲሆኑ በመድረኩም ለተማሪዎቹ በቴክኒክና ሞያ ዘርፍ ያሉ ምቹ አጋጣሚዎችን በዝርዝር በማስቀመጥ የሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን አጠናቀው ሲጨርሱ በዘርፉ ሊያገኙ የሚችሉትን ወርቃማ እድል ከወዲሁ ተረድተውት ትክክለኛውን ውሳኔ እንዲወስኑ የሚረዳቸውን መረጃና ግንዛቤ ለተማሪዎች ማስጨበጥ ተችሏል:: ይህን መሰል መድረኮች ቀጣይነት የሚኖራቸው ሲሆን የሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎቹን ግንዛቤ ከማስጨበት ባሻገር ወደ ኮሌጃችን በመጋበዝ የተለያዩ ስልጠናዎችን እንዲሰለጥኑና ለቀጣይ ምዕራፋቸው መሰረት እዲጥሉ የማድረግ ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም የኮሌጁ ዲን አቶ ታደለ አሰፋ ገልፀዋል:: የኢትዮ-ጣሊያን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮሚኒኬሽን ግንቦት 19/2016 ዓ.ም

Repost from N/a
photo content
+5

Repost from N/a
photo content
+9

በአስተዳደሩ የሚገኙ አገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶች ዙሪያ እየተደረገ ያለው ጥናት የደረሰበት ደረጃ ተገመገመ፤ በድሬዳዋ አስተዳደር የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ የቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ኤጀንሲ የኢንዱሰትሪ ኤክስቴንሽንና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዳይሬክቶሬት አስተባባሪነት በድሬዳዋ አስተዳደር ደረጃ ጠቃሚ አገር በቀል እውቀቶችና ክህሎቶች ዙሪያ በመጋቢት ወር 2016 ዓ.ም ጥናት መጀመሩ ይታወሳል፤ በዚህም ጥናት በተለይ  በበጀት አመቱ በባህላዊ ህክምና (መድሀኒት) እና እደ ጥበብ ላይ  እየሰሩ  የሚገኙ ባለሙያዎች  ቦታቸው  ድረስ በመሄድ እና ቃለመጠይቅ በማድረግ ለጥናቱ አስፈላጊ የሆኑ መረጃዎችን መሰብሰብ ተችሏል፤ ስለሆነም ጥናቱ ምን ደረጃ ላይ እንደ ደረሰ  በዛሬው ዕለት የተገመገመ ሲሆን በቀጣይ ጥናቱ ሲጠናቀቅ በቴክኒክና ሙያ ትምህርትና ስልጠና ማለትም በመደበኛም ሆነ በአጫጭር  ስልጠና  ውስጥ እንዲካተት በማድረግ የስራ ዕድል ፈጠራውን በማገዙ ረገድ የሚኖረው አስተዋጽኦ የጎላ እንደሚሆን የቴክኒካል ክህሎት አቅም ግንባታ ቡድን መሪ ወ/ሮ አለምፀሃይ ጌታቸው ገልጸዋል፡፡ የሥራ ክህሎትና ቴክኖሎጂ ልማት ቢሮ ህዝብ ግንኙነት ግንቦት 19/2016 ዓ.ም ድሬዳዋ