fa
Feedback
በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

በወላይታ አከባቢ ዘኦርቶዶክስ ተዋህዶ ልጆች ማህበር

رفتن به کانال در Telegram

እውነተኛ የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ድምፅ!! በዚህ የቴሌግራም ቻናል የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ዶግማን፡ቀኖናን እና ትውፍትን የጠበቁ ስርዓተ አምልኮ ትምህቶች እና ዝማሬዎች ይቀርቡበታል!!!

نمایش بیشتر
326
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" የሉቃስ ወንጌል 2:11 እንደተባለው ተወለደ! የ2016ተኛ ዓ/ም የክርስቶስ ልደት በዓል በወላይታ ሶዶ ደብረ መንክራት አ
+2
"ዛሬ በዳዊት ከተማ መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋልና።" የሉቃስ ወንጌል 2:11 እንደተባለው ተወለደ! የ2016ተኛ ዓ/ም የክርስቶስ ልደት በዓል በወላይታ ሶዶ ደብረ መንክራት አቡነ ተክለሐይማኖት ገዳም ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ የወላይታ ሀ/ስብከት ሊቀ ጳጳስ እና ሊቃውተ ቤ/ያን በተገኙበት በድምቀት ተከብሯል!! እንኳን በሠላም በጤና በፍቅር በደስታ አደረሰን አደረሳችሁ ! መልካም በዓል🙏🙏🙏

#ብፁዕ_አባታችን_በአበላ አባያ ወረዳ በአባያ ጉሩቾ ቀበሌ በብላቴ ለሰማዕቷ ቅድስት አርሴማ ቤ/ያን 100 ቆርቆሮና 10 ባኮ ሚስማር አበረከቱ!! በኢትኢዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን በወላይታ ሀገረ ስብከት በአበላ አባያ ወረዳ በአባያ ጉሩቾ ቀበሌ በብላቴ ወንዝ በጎርፍ አደጋ ለተፈናቀሉ ሕዝበ ምእመናን አዲስ እየተሐነፀ ላለው ቤተክርስቲያን በታኅሣሥ 24 /04/2016 ዓ.ም ብፁዕ አቡነ ይስሐቅ በታላቁ ገዳማችን በክብረ በዓሉ 100 ቆርቆሮ እና 10 ባኮ ሚስማር በማበርከት በመላው ዓለም ያላችሁ ልጆቼ ከጎኔ ቁሙልኝ ለተፈናቀሉ ወገኖቻችን እንድረስላቸው በማለት አባታዊ ጥሪ አስተላልፈዋል። ስለሆነም ሁላችሁም ከአንድ ቆርቆሮና ከአንድ ባኮ ሚስማር ጀምራችሁ እንዲትሳተፉ ቤተክርስቲያንቷ ጥሪዋን ታስተላልፋለች!! የሰማዕቷ የቅድስት አርሴማ ወለታዋ ያለበት ዝም ብሎ አያልፍምና!!! የቤተክርስቲያንቷ አካውንት እነሆ 👉1000598723757 150 ቆርቆሮ ጎሎባታልና ተረባርበን እንሙላ ለሰማዕቷ #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

እንመልስ፡፡ በመጨረሻም በአሁኑ ጊዜ በሀገራችን በተከሠተው የድርቅና የሰው ሰራሽ ምክንያት በችግር ላይ የወደቁ ወገኖች በርካታ ናቸው በመሆኑም የወገን ደራሽ ወገን ነውና ሁሉም ካለው ብቻ ሳይሆን የቀን ቍርሱን ለተቸገሩ ወገኖች እንዲለግስና በመተጋገዝ ረኃቡን እንድንከላከለው ጥሪያችንን በእግዚአብሔር ስም እናስተላልፋለን፡፡ መልካም የልደት በዓል ያድርግልን እግዚአብሔር አምላክ ኢትዮጵያንና ሕዝቦችዋን ይባርክ!! ወስብሐት ለእግዚአብሔር!!! አሜን። አባ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአኵስም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት አዲስ አበባ - ኢትዮጵያ

"ሰበብ አስባብ እየተፈለገ በሆነውም ባልሆነውም ከመተላለቅ ለምን ኢትዮጵያ የሁላችን ናት ብለን በእኩልነትና በስምምነት መኖር አቃተን?" ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ታኅሣሥ 26 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) ++++ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ በዓለ ልደትን አስመልክቶ ለመላው የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻቸው መልእክት አስተላልፈዋል። የቅዱስነታቸው ቃለ በረከት ከዚህ እንደሚከተለው ቀርቧል። በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን ! በሀገራችን በኢትዮጵያ በገጠርና በከተማ የምትኖሩ፣ ከሀገር ውጭ በተለያዩ አህጉር የምትገኙ፣ የሀገራችንን ዳር ድንበር ለመጠበቅና ለማስከበር በየጠረፉ የቆማችሁ በሕመም ምክንያት በየፀበሉና በየሆስፒታሉ ያላችሁ፤ እንዲሁም የሕግ ታራሚዎች ሆናችሁ በየማረሚያ ቤቱ የምትገኙ ኢትዮጵያውያንና ኢትዮጵያውያት ሁሉ፡ በፍጹም ፍቅሩ እኛን ወደ ሰላም ለማምጣት በእኛ ሰውነት በዚህ ዓለም የተወለደው ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እንኳን ለብርሃነ ልደቱ በደኅና አደረሳችሁ! “ትእምርተ ሰላምነ ወልድ ተወልደ ለነ፡ የሰላማችን ሰንደቅ ዓላማ የሆነው ወልድ ወይም ወልደ እግዚአብሔር ኢየሱስ ክርስቶስ ለኛ ተወለደልን'' (ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ) ዓለም ሁሉ በተለይም የክርስቲያኑ ዓለም በትክክል እንደሚያውቀው ቅዱስ መጽሐፍ በሰዎች የቋንቋ ዘይቤ የተጻፈ የእግዚአብሔር ቃል ነው፤ በመንፈሳዊም ሆነ በዓለማዊ ርእዮት ቋንቋ የመልእክት ማስተላለፊያና መግባቢ መሳሪያ እንደሆነ ይታወቃል፤ እግዚአብሔርም ከጥንት ጀምሮ መልእክቱን በዚህ መንገድ ለሰዎች ሲያስተላል ኖሮአል፤ የሚያስተላልፈውም መልእክት እንዲሁ ተሰምቶ እንዲቀር ሳይሆን እንዲታወቅ፣ እንዲታመን እንዲተገበርና ሰዎች እንዲጠቀሙበት ነው፤ ከሚፈለገው ጥቅም ለመድረስም ሰዎች መልእክቱን በሚገባ መረዳት የግድ ይሆናል፤ ሰዎች እንዲረዱት ደግሞ በቋንቋቸውና በባህላቸው ዘይቤ ሊነገራቸው ይገባል፤ በመሆኑም እግዚአብሔር ቃሉን በሰዎች ቋንቋ ባህላዊ ዘይቤ መልእክቱን ለዓለም ሲያስተላልፍ ኖሮአል ቤተክርስቲያንም ይህንን መሠረት አድርጋ የእግዚአብሔርን ቃል በሰው ቋንቋ ዘይቤ ታስተምራለች፤ ከዚህ አንጻር በሰው ልማዳዊ የዘይቤ ቋንቋ ለጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስም "የሰላም ሰንደቅ ዓላማ" የሚል ቅፅል ተሰጥቶታል፡ ምክንያቱም ንጉሥም ወታደርም ተራው ሕዝብም የሀገሩ ነጻነትና ክብር፤ አንድነትና ሉዓላዊነት ምልክት የሆነውን ሰንደቅ ዓላማ ተከትሎ ስራ ይሰራል ክብሩንም ይገልፃልና ነው፤ ተከተል አለቃህን ተመልከት ዓላማህን የሚለው ብሂልም ይህንን ያንፀባርቃል፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! ጌታችን በመድኅንነቱ የሁላችን የሰላም ሰንደቅ ዓላማ በመሆኑ መምህራችን ቅዱስ ያሬድ የሰላማችን ሰንደቅ ዓላማ የሆነ ልጅ ተወለደልን ብሎ ይገልፀዋል፤ ጌታችን በዛሬው ዕለት በቤተልሔም ሰውነታችንን ሰውነት አድርጎ መወለዱ ራሱ የሰላም ማሳያ ምልክት ነው፤ ምክንያቱም ሳይወደን አይቀርበንም፤ አይዋሐደንምና ነው፤ በልደቱ ዕለት "ለዕጓለ እመሕያው ሠምሮ የሰው ልጅን ወደደው" ተብሎ በቅዱሳን መላእክት የተዘመረበትም ምክንያት ይኸው ነው፤ እንደ እውነቱ ከሆነ ጌታችን የተዋሐደው ሰውነት የወዳጁ አልነበረም የጠላቱ እንጂ፤ ቅዱስ መጽሐፍ ይህንን ሲገልፅ "ጠላቶቹ ሳለን እግዚአብሔር በልጁ ሞት ታረቀን" ይላልና ነው፡ በዚህ ዓለም የኖረውም ከሚያሳድዱት፣ ከሚከሱት፤ ስሙን ከሚያጠፉና ሊገዱሉት ከሚከጅሉ ጋር እንጂ ከወዳጆቹ ጋር ብቻ አልነበረም፤ እሱ ግን ሁሉንም በፍቅር ይቀበል ነበረ፤ ይፈውስና ያድን ነበረ፤ ያስተምርም ነበረ፤ ለሁሉም ስርየተ ኃጢአትን ሰጠ ለጠላቶቹም ጸለየ፤ ጌታችን በዚህ ሁሉ ለኛ አርእያና የተግባር መምህር በመሆኑ የሰላም ሰንደቅ ዓላማችን ነው፡ ምእመናንና ምእመናት ዓለም በጌታችን ዕለተ ልደት የተዘመረውን ሰማያዊውን የሰላም መዝሙር መዘመር ከጀመረች እነሆ ዛሬ ድፍን ሁለት ሺሕ ዐሥራ ስድስት ዓመት ሆነ፤ የሰላሙ መዝሙር ዛሬም በመላው ዓለም በሚገኙ ክርስቲያኖች ይዘመራል፤ ይሁን እንጂ በዚህ ዓለም ሰላም ሰፍኖ እየታየ አይደለም፤ ይህ ለምን ሆነ ቢባል ደምበኛ መልስ ሊሆን የሚችለው እግዚአብሔርን አለማመንና አለመፍራት ያመጣው ችግር ነው የሚል ነው፤ ምክንያቱም ሃይማኖትና ፈሪሐ እግዚአብሔር ከሌለ ፍትሕ ይጐድላል፣ ፍትሕ ከጐደለ ብሶት ይፈጠራል፣ ብሶት ካለ ሰላም ሊኖር አይችልም፤ በሁሉም የዓለማችን ክፍል ሃይማኖትና ፈሪሐ እግዚብሔር እየተዘነጋ በመሄዱ ቀውሱ ተባብሶ ይታያል፤ የሰው ልጅ ኑሮ በየትም ይሁን በየት በስጋት የተሞላ ሆኖአል፤ የሚወራው ሁሉ ስለ ግጭት ስለአየር ብክለት ስለ ረኃብና እልቂት ሆኖአል፤ ዓለም የጉልበተኞችና የባለ ሀብቶች ብቻ እንድትሆን የተፈጠረች እስክትመስል ድረስ ከባድ የፍትሕ መዛባት አጋጥሞአታል፤ የዝቅተኛው ማኅበረሰብ ሰብአዊ መብት ተዘንግቶአል፣ ከዚህ አኳያ ዓለም በዚህ እስከ ቀጠለች ድረስ ሰላም የማግኘቷ ዕድል በጣም አጠራጣሪ ነው፡ የክርስቶስ ልደት ያስተማረን ግን እንደዚህ አልነበረም፤ ጌታችን የተወለደው በተዋበና ምቹ በሆነ የሀብታም ቤት ሳይሆን በከብቶች በረት ነበረ፤ የተገለጠውም ለባለሥልጣኖች ሳይሆን ዝቅተኞች ለሚባሉ እረኞች ነበረ፤ ልዑላኑ ሰማያውያንና ትሑታኑ ምድራውያን በአንድነት አገናኝቶ ስለ ሰላም በጋራ እንዲዘምሩ አደረገ፤ አሳዳጅ ሳይሆን ተሳዳጅ ሆኖ በግብጽ አገር በመንከራተት አደገ፤ ይህን ሁሉ ያደረገው እኛ እሱን እያየን እንደ ሰንደቅ ዓላማ እንድንከተለው ነበር፤ ጌታችን ከባለሥልጣናቱና ከባለሀብቶቹ ይልቅ በድሆቹ ደረጃ የተወለደው ለድሆቹና ለዝቅተኞቹ ትኩረት እንድንሰጥ ለማስተማር ነው፤ የእኛ ድርጊት ግን ግልባጩ ሆኖ እየተስተዋለ ነው፡፡ እጅግ የሚያሳዝነው ደግሞ ክርስቲያን ነኝ ብሎ፤ በስመ እግዚአብሔር ተሰይሞ፤ መስቀልን በአንገቱ ተሸክሞ የእሱ መሰል በሆነው ወይም መስቀል በተሸከመው ወንድሙ እና እኅቱ እንዲሁም በመሰል ፍጡር ላይ ያለ ርኅራኄ ሲጨክን መታየቱ ነው፡ እንዲህ እየሆነ እንዴት ሰላም ይምጣ? እግዚአብሔርስ እንዴት በረከቱ ይሰጣል? ይህ እጅግ በጣም ሊታሰብበት የሚገባ ጉዳይ ነው፡፡ የተወደዳችሁ የመንፈስ ቅዱስ ልጆቻችን ምእመናንና ምእመናት! እኛ ኢትዮጵያውያን ከእንዲህ ዓይነቱ የሃይማኖትና የሞራል ዝቅጠት በአስቸኳይ መውጣት አለብን፤ ጠቡ፤ መለያየቱ፣ መጨካከኑ፤ ለኔ ለኔ መባባሉ ከረምንበት፤ ሆኖም ያመጣልን ነገር ቢኖር ሁለንተናዊ ውድመት ብቻ ነው፡ ያስገኘልን ትርፍ ይህ መሆኑ እያወቅን በዚሁ ልንቀጥል አይገባም፡ ሰው ችግሩን በልቡ እያወቀ በዓይኑ እያየ እንዴት ገደል ውስጥ ይገባል? ዕርቅና ይቅርታ ማንን ጐዳ? ሰላምና አንድነት ማንን አከሰረ? ሰበብ አስባብ እየተፈለገ በሆነውም ባልሆነውም ከመተላለቅ ለምን ኢትዮጵያ የሁላችን ናት ብለን በእኩልነትና በስምምነት መኖር አቃተን? ሦስት ሺሕ ዘመናት አብረው የኖሩ ሕዝቦች እንዴት ችግራቸውን በጠባይና በብልሐት ማስወገድ አቃታቸው? ይህ ከቶ ሊሆን አይገባም፤ ሁላችንም ሰክን ብለን እናስብ፤ ለሁሉም የማሰቢያና የመመካከሪያ ጊዜ ፈጥረን ችግሩን በስፍሐ አእምሮ እንፍታው፡ ችግርን በምክክርና በይቅርታ መፍታት አማራጭ የሌለው ጥበብ ነው፤ የሃይማኖት መሪዎች፤ የሀገር ሽማግሌዎች፤ ምሁራንና ልኂቃን በዚህ ተግተን ልንሰራ ይገባል፤ መንግሥትና የፓለቲካ ፓርቲዎችም ለዚህ የበኩላቸውን ድጋፍ ያድርጉ፤ በዚህም ሰላማችንን

በወንድማማችነት መካከል ጠብን ከሚዘሩ ጥላቻንና መራራቅን ከሚያሰፉ ንግግሮችና ድርጊቶች በመቆጠብ ሁሉም የማኅበረሰብ ክፍል እግዚአብሔር ለሀገራችን ፍጹም ሰላምን ይሰጣት ዘንድ በጸሎት እንዲተጋ ቋሚ ሲኖዶስ አሳሰበ ! ታኅሣሥ 26 ቀን 2016 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ)የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ በዛሬው ዕለት ያወጣው መግለጫ ከዚህ እንደሚከተለው ይቀርባል ! መንፈሰ ሰላም ማዕከለ ኢየሱስ ክርስቶስ ወማዕከለ ቤተ ክርስቲያን… ውእቱ… የሰላም መንፈስ በኢየሱስ ክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል ነው:፡ (መጽሐፈ ምሥጢር) ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ የተሰጠ መግለጫ በዚህ የሕይወት ቃል አማካኝነት የሰላም መንፈስ በኢየሱስ ክርስቶስና በቤተ ክርስቲያን መካከል በየዘመናቱ ያለና የሚኖር መሆኑን እንመለከታለን፡፡ የዚህም መንፈሰ ኃይል በቤተ ክርስቲያን መኖር ሕማመ ነፍስ በሌለበት ምግባረ ሃይማኖት በፍቅር እንድንኖር ለምንሻው ሁሉ እግዚአብሔር በምልዓት በሚከብርበት ቤተ መቅደስ በኩል የሚሰማው የሰላም ጥሪ በማያቋርጠው የመንፈሳዊ ኑሮ ሂደት ለመንፈስ አንድነት፣ ለአካላዊ ሕብረት የሚጠቅም የሕይወት ምሰሶ ነው፡፡ በመሆኑም ‹‹ወብነ ክሂል ከመ ንቅትል ኅሊና ሰይጣናዌ …ሰላምን የሚያሳጣ ክፉ ሓሳብን በቤተ ክርስቲያናችን መካከል ባለው ሰላም ከእኛ የማራቅ ችሎታ አለን›› ተብሎ እንደተጻፈው ፍጥረተ ሰብእ ሕይወቱን ለበጎ በሚቀርጸው ሥርዓተ ሃይማኖት በመመራት፣ የሰላምን አስፈላጊነት በትምህርት በድርጊት በመግለጽ ባልተዛነፈ ሰብእና በተሟላ ሰላም መኖር የሚችልበት ክሂል ያለው ፍጡር መሆኑ አያጠራጥርም፡፡ (ዜና አበው) የሰላም መንፈስ በመካከሏ ሆኖ ከስሕተት የሚጠብቃት ቅድስት ቤተ ክርስቲያናችንም አመለካከቱ ስሕተት ንግግሩ ሐሰት በሆነው ዓለም የጽድቅና የሰላም ባሕርይ መገለጫ ነው፡፡ ልጆቿ በሰላም በፍቅር በታነጸ ዕለታዊ ሕይወት እንዲኖሩ በማድረግ ሰላም የደግነት ሁሉ አክሊል የመንፈሳዊ ምግባራት ዘውድ መሆኑን ስታውጅ መኖሯን የታሪክ መዛግብት፣ ዕውነትን ለመግለጥ የሚተጉ ጸሐፍት ከመቅድም እስከ ህዳግ ይመሰክሩላታል። መሪዋና አጽናኟ ከሆነው መንፈስ ቅዱስ በተገኘው የሰላም እሴት በእምነታቸው ጸንተው በምግባር በትሩፋት አጊጠው የሚኖሩት ማኅበረ ካህናትና ማኅበረ ምእመናንም የረጅም ዘመናት የቅድስና ታሪክ ጉዞዋ ማሳያዎች ናቸው። የእውነትና የሰላም አምድ እንደመሆኗም በሀገራችን እየተከሰቱ ያሉ አለመግባባቶችንና የእርስ በእርስ ደም መፋሰሶች እንዲቆሙ የሰላም ጥሪ ከማድረግ ጀምሮ ምህላ፣ ጾምና ጸሎት በማወጅ እግዚአብሔር ለሀገራችንና ለሕዝባችን ሰላምን እንዲሰጥ ስትማጸን ቆይታለች። የየዕለት አገልግሎቷም ይህንኑ መሠረት ያደረገ ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን የሰላም መንፈስ በመካከሏ እንዲሆን አድርጎ ወኃቤ ሰላም መድኃኔ ዓለም ክርስቶስ በደሙ የመሠረታት ስለሆነ በዓለም ሁሉ ሰላም እንዲሰፍን ማድረግ የክብር ስፍራውን ይዞ የሚቀጥል ቀዳሚና ዐቢይ ተልእኮዋ መሆኑን ማስገንዘብ እንወዳለን ። በመጨረሻም ሰላም የሚጸናው ማንኛውም ማኅበረሰብ እርስ በእርሱ በመተሳሰብና በፍቅር በእውነተኛ መግባባትና በፍትሕ በርኅራሄና በመከባበር አብሮ መኖር ሲቻል ነውና በወንድማማችነት መካከል ጠብን ከሚዘሩ ጥላቻንና መራራቅን ከሚያሰፉ ንግግሮችና ድርጊቶች በመቆጠብ ሁሉም የማኅበረ ሰብእ ክፍል እግዚአብሔር ለሀገራችን ፍጹም ሰላምን ይሰጣት ዘንድ በጸሎት እንዲተጋ ቋሚ ሲኖዶስ ያሳስባል፡፡ ከምን ጊዜውም በላይ ሰላምና ፍቅር በሀገራችን እንዲሰፍን በአንድነት ሆነን የምንሠራበት ወቅት ላይ በመሆናችን በመጪዎቹ ዐበይት በዓላት፣ በዘወትሩ መንፈሳዊ አገልግሎት ሁሉም በየደረጃው ያላችሁ የቤተ ክርስቲያናችን አባቶችና አገልጋዮች "ወፍሬሃኒ ዘጽድቅ በሰላም ይዘራዕ ለእለ ይገብርዋ ለሰላም ... የጽድቅም ፍሬ ሰላምን ለሚያደርጉ ሰዎች በሰላም ይዘራል" በሚለው ሐዋርያዊ ቃል መሠረት በየዐውደ ምሕረቱ ሰላምንና እርቅን በመስበክ በሀገራችን ኢትዮጵያ ያለው ችግር እንዲወገድ፣ ማኅበራዊ ሰላም እውን እንዲሆን የበኩላችሁን ጥረት እንድታደርጉ ቋሚ ሲኖዶስ ጥሪውን ያስተላልፋል። ያዕ 3÷18 እግዚአብሔር ለሀገራችን ሰላምን ጽድቅን፣ፍቅርንና ፍትሕን ይስጥልን :: የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ቋሚ ሲኖዶስ

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ አሜን። ታኅሣሥ ሃያ ዐራት በዚህች ዕለት የተመሰገነ እና የከበረ አዲስ ሐዋርያ አባታችን ተክለሃይማኖት ተወለደ በጸሎቱ የምትገኝ በረከቱ ከእኛ ጋር ትኑር🙏 ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።

"ወደ ተራራው ውጡ፥ እንጨትንም አምጡ፥ ቤቱንም ሥሩ፤ እኔም በእርሱ ደስ ይለኛል፥ እኔም እመሰገናለሁ።"ይላል እግዚአብሔር።                              ትንቢተ ሐጌ 1 : 8 በዳውሮ ሀ/ስብከት በኢሠራ ወረዳ ቤተክህነት ስር የሚገኘው የሀገሊ  የሰማዕቱ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ያን እየታነፀ አቅም በማጠሩ ምክንያት ቆሟል😢😢 ስለ ሁሉም ነገር እግዝአብሔር ይመስገን እያልኩኝ በዝህ ስፈራ የምኖረው ህዝበ ክሪስቲያኖች በምደርስባቸው የእአማንያን ተፅዕኖ እና የቤተክርስቲያን አለመኖር የአግልጋይ ካህናት ማጣት ልጆቻቸውን ለማቁረብ ስፈልጉ የተሟላ አግልግሎት ባለማግኘታቸው እንዲሁም በማህበራዊ  ኑሮ በሚድርስባቸው ተፅዕኖ ከኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኞች ጋር አብረን በደቦ፣በለቅሶና በተለያዩ በማህበራዊ ጉዳይ አንደራርስም በማለት ከአንድ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማኝ ልጁ ሞቶበት አትቀብሩም አናስቀብርም በማለት አስክሪኑን እስከ አራት ቀን እስከማቆየት ድረስ አደማ በመደረግ  ለብዙ ዘመናት ስበደሉ የኖሩ  አይዞአችሁ የሚል ባለመኖሩ ምክነያት  የተነሳ ሀይማኖታቸውን ስቀይሩ ወደ ክህደት ጎዳና ስጓዙ ቆይተዋሉ። የአገሊ 02 ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት የተዋህዶ ልጆች ያለቤተክርስትያን አገልገሎት ለቡዙ ዘመናት ኑሮዋል። ይሁን እንጂ በቁጥር 15 የምሆኑ  እኛ አግዚአብሔርን ይዘን አንፈራም በማለት እልህ አስጨራሽ ፈተናዎችን በማለፍ  የሰማዕቱ የቅ/ጊዮርጊስ ቤ/ያን ለማነፅ በ2012 ዓ.ም ከተለያዩ አጥብያ ቤ/ያን ከካህናት አባቶች፣ ከዲያቆናት፣ ከሰ/ት/ቤት ዘማሪያንና ከህዝብ ምዕመናን ጋር  በመሆን ህንፃ ቤ/ያንን ለማነፅ መሠረተ ድንጋይ ተጥሎ ስራው  እንደተጀመረ  ጠላት አይተኛምና በድጋሚ በጣም በምያሳዝን መልኩ በዚህ ስፍራ ኢ-አማንያን የበዙበት ቦታ ስለሆነ አይታነፅም አይሰራም ተብሎ ከብዙ ውጣውረድ በሃላ በእግዚአብሔር ሀይል ቤ/ያኑ ማነፅ  ተጀምሮ ይህ በታች በፎቶ በሚትመለከቱት ደረጃ ላይ አድርሰውታል።   እንግዲህ የእግዚአብሔር ቤተሰቦች እነዚህን ምዕመናን በቁጥር (15 ) አስራ አምስት ናቸው  ስለዚህ አቅም አጣን እርዱን   እያሉ  እጃቸውን ወደ እግዝአብሔር እና ወደ ህዝብ ክርስቲያኑ እየዘረጉ  ይገኛሉ ።   የተዋህዶ ልጆች   እንደምታዩት በጣም ከአቅማቸው በላይ ስለሆነና አሁን እየታነፀ እጅ አጥሯቸው ቆሞ ይገኛል።  ስለሆነም ለእነዛ (ለኢ-አማንያን) መሳለቂያ እንዳይ ሆኑ ልናግዛቸው ይገባልና  በሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ስም እንረባረብ!! ስለዚህ ይህን ጽሑፍ ለማንበብ የታደላችሁ በሙሉ  እነዚህ ክርስቲያን ወገኖቻችን ቤተክርስቲያን ለመስራት ስነሱ በእጃቸው ብር ይዘው ሳይሆን እግዚአብሔርን እና ክርሰቲያን እህት ወንድሞችን ተሰፋ በማድረግ ነው። ብዙ ንዋዬ ቅድሳት፣ታቦተ ሕግ፣የተለያዩ ነገሮች ስላልተሟላ እባካችሁ ውድ የሰመዕቱ ወዳጆችና የተዋህዶ ልጆች በልዑል እግዝአብሔር ስም እንማፀናለን!!! #ስለዚህ ይህንን ቤተክርስቲያን ለመርዳት ከስር ባለው ህጋዊ የቤተክርስትያኗ የባንክ ህሳብ ቁጥር ይቀሙ!! የሀገሊ 02 የሰማዕት ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ያን  CBE ' ንግድ ባንክ AC 👉1000333008231 #Share በማድረግ ለብዙዎች ለልቤ ቅን ሰወች አድርሱልንን!! ለቁጥጥር  አመቺ እንዲሆን ቃል የሚትገቡ እና ብር የሚትልኩ ሰዎች በኮሜን መስጫ ላይ እስክን ሹት አድርጎ ያስቀምጡልን🙏 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

የሊቀመላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በድምቀት ከሚከበሩ ቦታዎች አንዱ ነው የደልቦ ገብርኤል! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን በወላይታ ሀ/ስብከት ታርካዊውና ጥንታዊው የደልቦ ደብረ ኃይል ቅዱስ
+1
የሊቀመላእክት ቅዱስ ገብርኤል በዓል በድምቀት ከሚከበሩ ቦታዎች አንዱ ነው የደልቦ ገብርኤል! በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤ/ያን በወላይታ ሀ/ስብከት ታርካዊውና ጥንታዊው የደልቦ ደብረ ኃይል ቅዱስ ገብርኤል ቤ/ያን ለገናናው ሊቀመላእክት ቅዱስ ገብርኤል ዓመታዊ በዓል በድምቀት ለማክበር ዝግጅቱን ጨርሶ እንግዶችን በመጠባበቅ ላይ ነው። መቅረት የለለበት!!! እንኳን አደረሳችሁ የተዋህዶ ልጆች🙏🙏🙏 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

ስለ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ 👉ተጀምሮ ከመንገድ ላይ የቀረ የመጥምቀ መለኮት ዮሐንስ ህንፃ ቤተክርስቲያን በወላይታ ሀ/ስብከት በኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ያንዳ ጬራቼ /አርቤ/ የምትገኘው የቅዱስ ዮሐንስ ቤተመቅደስ ስራ ጥሪ!! #share በማድረግ ለብዙዎች እንዲታደርሱ በመጥምቁ ዮሐንስ ስም ብለናል። በወላይታ ሀ/ስብከት ኪንዶ ኮይሻ ወረዳ ቤተክህነት ጬራቼ ያንዳ /አርቤ/ መጥመቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ህንፃ ቤተክርስቲያን ከተጀመረ ረጅም ጊዜ በመቆየቱ ኦርቶዶክሳውያን ተሰፋ በመቁረጥ ከሃይማኖታቸው እየወጡ ይገኛሉና የተጀመረችውን ቤተመቅደስ አጠናቅቁልን እያሉ ይማጸናሉ!!!🙏 ለህፃው የቆመው እንጨት በዝናብና በፀሀይ መፈራረቅ እንዳይወድቅ በማለት አንድ ወንድማችን በብድር ሙሉ ቆርቆሮ ከአንድ ነጋዴ በመውሰድ ጣሪያ አልብሷል በብድር! ስለሆነም ከ50 ብር ጀምሮ አቅማችሁ የቻለውን ያላችሁን በመስጠት ቤተክርስቲያን ከተተከለችበት ስፍራ እንዳትፈርስ እንረባረብ!!! አሁን ቀሪ ሐቤተክርስቲያን ግንባታ የሚያስፈልገውን 👇 👉 የቆርቆሮ ገንዘብ ብድር ለመክፈል 👐 👉 በርና መስኮት በር 4ት መስኮት 3ት 👉 የቆርቆሮ ሻሽ 👉 የጭቃ ስራዎች 👉 ጭድ 👉 ባለሞያ ለልጥፍና ለልስን ስራ 👉 ለውሃ 👉 የኮርነስ ስራዎች 👉 ሞራሌ ሸሬራ ጨርቅ 👉 የባለሙያ የእጅ 👉 የቀለም ስራዎች 👉 ለቀለም ግዢ 👉 ለባለሙያ የእጅ ክፍያ 👉 በጠቅላላ እስከ 250 ሺህ ብር በላይ ያስፈልጋል!!! ☝ እነዚህ ከላይ የተጠቀሱ ያስፈልጉናልና ስለመጥምቁ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ብላችሁ ከታች በተጠቀሰው ህጋዊ አካውንት የአቅሞን ያድርጉ ዘንድ የአካባቢው አባቶችና እናቶች ይማጸናሉ😢😢 እነሆ የቤተክርስትያኗ ሕጋዊ የሂሳብ ቁጥር የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ...ጬራቼ ያንዳ አርቤ መጥምቀ መለኮት ቅዱስ ዮሐንስ ቤተክርስቲያን Account No  1000574184235 #ሼር_በማድረግ_ለሁሉም_አጋሩ🙏 👉የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ፈጣንና ወቅታዊ የቤ/ያን መረጃዎችን ያግኙ👉 https://t.me/httplif 👉ልንኩን በመጫን የፈስ ቡክ ፔጃችንን ቤተሰብ ይሁኑ https://www.facebook.com/teka132 #followlikecommentandshare

ለእግዚአብሔር ታቦቱ መቅደሱ ቀርበናል በአንቺ ወደ ንጉሡ✝️ የክብራችን ጌጥ ሽልማት እንወድሻለን ኪዳነምህረት ።።።።።።።።።።።።።።።።። እንኳን አደረሳችሁ🙏🙏🙏
ለእግዚአብሔር ታቦቱ መቅደሱ ቀርበናል በአንቺ ወደ ንጉሡ✝️ የክብራችን ጌጥ ሽልማት እንወድሻለን ኪዳነምህረት ።።።።።።።።።።።።።።።።። እንኳን አደረሳችሁ🙏🙏🙏

“ጻድቃን ሆይ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤ ለቅኖች ምስጋና ይገባል።” (መዝሙር 33፥1) ሰናይ ሰንበተ ክርስትያን ቅድስት💕🙏💕 #followlikecommentandshare
“ጻድቃን ሆይ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ፤ ለቅኖች ምስጋና ይገባል።” (መዝሙር 33፥1) ሰናይ ሰንበተ ክርስትያን ቅድስት💕🙏💕 #followlikecommentandshare