fa
Feedback
አውደ ከዋክብት

አውደ ከዋክብት

رفتن به کانال در Telegram

የኮከብ አቆጣጠር

نمایش بیشتر
369
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

کانال‌های مشابه
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
ابر برچسب‌ها
هیچ داده‌ای
مشکلی وجود دارد؟ لطفاً صفحه را تازه کنید یا با مدیر پشتیبانی ما تماس بگیرید.
اشارات ورودی و خروجی
---
---
---
---
---
---
جذب مشترکین
دسامبر '24
دسامبر '24
+29
در 0 کانال‌ها
نوامبر '24
+110
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '24
+223
در 0 کانال‌ها
Get PRO
سپتامبر '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اوت '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئیه '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژوئن '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مه '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
آوریل '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
مارس '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
فوریه '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
ژانویه '240
در 0 کانال‌ها
Get PRO
دسامبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
نوامبر '230
در 0 کانال‌ها
Get PRO
اکتبر '23
+385
در 0 کانال‌ها
تاریخ
رشد مشترکین
اشارات
کانال‌ها
09 دسامبر+4
08 دسامبر+2
07 دسامبر+2
06 دسامبر+4
05 دسامبر+5
04 دسامبر+5
03 دسامبر+2
02 دسامبر+4
01 دسامبر+1
پست‌های کانال
ሰላም ሰላም ውድ የቻናሌ ቤተሰቦች ስለጠፋሁ ይቅርታ እያልኩ ነገር ግን ይህ የሆነው በሀገራችን ወቅታዊ ሁኔታ ምክንያት ኢንተርኔት በመዘጋቱ ነው። ይህንንም መልእክት የማስተላልፍላችሁ ሌላ ክልል በመሆን ለእናንተ መልእክቱን ለማስተላለፍ ነው። ሁላችሁም እኔን ማናገር የምትፈልጉ ሰዎች በቀጥታ የስልክ ቁጥር +251935455504 ( 0935455504) ብቻ መሆኑን ልነግራችሁ እወዳለሁ በቻልኩት አቅም ሁላችሁም እንደዚህ መልእክቶችን አደርሳችኋለሁ። በተረፈ በዮቲዩብ ላይም አንዳንድ ቪዲዮዎችን ኢንተርኔት ሲከፈት ለመልቀቅ አሁን እያዘጋጀሁ መሆኑን በደስታ እገልጻለሁ። ኮከብ ማስቆጠር የምትፈልጉም በስልክ በመደወል ማሳየት ትችላላችሁ ልብ በሉ እኔን ለማግኘት ይህንን ስልክ ቁጥር ብቻ ተጠቀሙ 0935455504 አውደ ከዋክብት

2
ዩቲዩብ ላይ 3000 ደርሰናል በጣም አመሰግናለሁ
ዩቲዩብ ላይ 3000 ደርሰናል በጣም አመሰግናለሁ
442
3
እንኳን አደረሳችሁ
እንኳን አደረሳችሁ
523
4
ቪዲዮው ተለቋል እየገባችሁ ተመልከቱት። https://youtu.be/oAitnp6_Nos
536
5
አቃቤ ርዕስ የሚለው ስለበለጠ እሱን እሰራላችኋለሁ።
580
6
እስካሁን 19 ሰው አቃቤ ርዕስ 18 ሰው ግርማ ሞገስ 6 ሰው የሠውር መሬት ኮከብ ገለፃ ይሁን ብለዋል። ያልመረጣችሁ እስከ ነገ ጠዋት ምረጡ
581
7
የትኛው ቪዲዮ ይቅደም?
582
8
بدون متن...
601
9
ቅዱስ ጳውሎስ ቅዱስ ጳውሎስ ለአገልግሎት ከመጠራቱ በፊት ‹ሳውል› ይባል ነበር፡፡ ከኦሪቱ ምሁር ከገማልያል ሕገ ኦሪትንና መጻሕፍተ ነቢያትን ተምሯል፡፡ ለሕገ ኦሪት ቀናኢ ከመኾኑ የተነሣም የክርስቶስ ተከታዮችን ዅሉ ያሳድድ ነበር፡፡ ቅዱስ እስጢፋኖስ በድንጋይ ተደብድቦ በሰማዕትነት በሞተ ጊዜ ቅዱስ ጳውሎስ የገዳዮቹ ልብስ ጠባቂ ነበር (ሐዋ. ፯፥፶፰፤ ፳፪፥፳)፡፡ ክርስቲያኖችን ለማሳደድ ወደ ደማስቆ ሲሔድ ከመንገድ ላይ ለሐዋርያነት ተጠርቷል (ሐዋ. ፱፥፩-፴፩፤ ፳፪፥፩-፳፩)፡፡ ለሐዋርያነት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮም በመላው ዓለም እየተዘዋወረ ወንጌልን በመስበክ ብዙዎችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አሳምኗል፡፡ ሲሰብክም ጣዖት አምላኪ፣ ሕመምተኛ፣ ችግረኛ፣ አረማዊና አይሁዳዊ እየመሰለ ብዙዎችን አስተምሮ ለእግዚአብሔር መንግሥት አዘጋጅቷል (፩ኛ ቆሮ. ፱፥፲፱-፳፫)፡፡ ዐረብ፣ አንጾኪያ፣ እልዋሪቆን፣ ሊቃኦንያ፣ ሦርያ፣ ግሪክና ልስጥራን ካስተማረባቸው አገሮች ጥቂቶቹ ናቸው፡፡ ወንጌልን በመስበኩ ምክንያትም ከአይሁድና ከአረማውያን ዘንድ ብዙ መከራና ስቃይ ደርሶበታል፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ከእግዚአብሔር በተሰጠው ጸጋ ብዙ ድንቆችንና ተአምራትን አድርጓል፡፡ በልብሱ ቅዳጅም ሕሙማን ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፲፱፥፲፩)፡፡ ሐዋርያው በቃል ካስተማረው ሌላ በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ የተመዘገቡ ፲፬ መልእክታት አሉት፡፡ አገልግሎቱን ሊፈጽም ሲልም የሮም ንጉሥ ኔሮን ቄሣር የክርስቲያኖች ቍጥር እየጨመረ የመጣው በቅዱስ ጳውሎስ ትምህርት በመማረካቸው ምክንያት መኾኑን ተረድቶ፤ ይልቁንም የቤተ መንግሥቱ ሰዎች ሳይቀር በቅዱስ ጳውሎስ በመማረካቸው ተቈጥቶ ቅዱስ ጳውሎስን ወደ ፍርድ ሸንጎው አስቀረበው፡፡ ቅዱስ ጳውሎስም በቀኝ እጁ ከሰንሰለቱ ጋር መስቀሉን ይዞ ንጉሡንና ወታደሮችን ሳይፈራ የኢየሱስ ክርስቶስን የእግዚአብሔር ልጅነትና አምላካዊ ሥልጣን ይመሰክር ነበር፡፡ ንጉሡም በቍጣ ይሙት በቃ ፈረደበት፡፡ ከላይ እንደ ተገለጸው ሮማውያን የሞት ፍርድ ሲፈርዱ የሚቀጣው ሰው የሌላ አገር ዜጋ ከኾነ ከፍርዱ ውጪ ተጨማሪ ቅጣት ይቀጡትና ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጳውሎስ ግን የሮም ዜግነት ስለ ነበረው ሳይገርፉ በአንድ ቅጣት ብቻ በሰይፍ እንዲገደል ወስነውበታል፡፡ ወደሚገደልበት ስፍራ ሲወስዱትም በንግግሩና በአስተያየቱ ዅሉ ምንም ፍርኀት አይታይበትም ነበር፡፡ እንዳውም በጦርነት ድል አድርጎና ማርኮ እንደ ተመለሰ ወታደር ይደሰት ነበር እንጂ፡፡ ለሚገድሉትም ይቅርታን ይለምን ነበር፡፡ በገዳዮቹና በተከታዮቹ ፊትም የክርስትና ሽልማቱ የእግዚአብሔር መንግሥት መኾኑን የሚያስገነዝብ ቃል እያስተማረ እግዚአብሔር የሚሰጠውን የጽድቅ አክሊል ለመቀበል ይቻኮል ነበር (፪ኛ ቆሮ. ፬፥፮-፲፰)፡፡ ወታደሮች ሊገድሉት ሲወስዱትም ከንጉሥ ኔሮን ወገን የኾነችውን የአንዲት ብላቴና መጐናጸፊያ ‹‹ዛሬ እመልስልሻለሁ›› ብሎ ከተቀበላት በኋላ ‹‹መልካሙን ገድል ተጋድያለሁ፤ ሩጫዬን ጨርሻለሁ፡፡ ሃይማኖቴን ጠብቄአለሁ፤ ወደፊትም የጽድቅ አክሊል ተዘጋጅቶልኛል፤›› በማለት ራሱ በመልእክቱ እንደ ተናገረው (፪ኛ ጢሞ. ፬፥፯-፰)፣ ፊቱን በብላቴናዋ መጐናጸፊያ ተሸፍኖ አንገቱን በሰይፍ ተቀልቶ አገልግሎቱን በሰማዕትነት ፈጽሟል፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ራሱን ከአንገቱ ጋር ቢያደርጉት እንደ ቀድሞው ደኅና ኾኖላቸው በክብር ገንዘው ቀብረውታል፡፡ ሰያፊው ቅዱስ ጳውሎስን እንደ ገደለው ለመናገር ወደ ንጉሡ ሲመለስም ያቺ መጐናጸፊያዋን የሰጠችው ብላቴና ‹‹ጳውሎስ ወዴት አለ?›› አለችው፡፡ እርሱም ‹‹ራሱን ተቈርጦ በመጐናጸፊያሽ ተሸፍኖ ወድቋል›› ሲላት ‹‹ዋሽተሃል፤ እነሆ ጴጥሮስና ጳውሎስ በእኔ በኩል አልፈው ሔዱ፡፡ እነርሱም የመንግሥት ልብስ ለብሰዋል፡፡ በራሳቸውም በዕንቍ ያጌጡ አክሊላትን አድርገዋል፡፡ መጐናጸፊያዬንም ሰጡኝ፡፡ ይህችውም እነኋት፤ ተመልከታት›› ብላ ሰጠቸው፡፡ ከእርሱ ጋር ለነበሩትም አሳየቻቸው፡፡ አይተውም አደነቁ፤ ስለዚህም በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ አመኑ፡፡ ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ በስብከተ ወንጌል አገልግሎታቸው ጨለማውን ዓለም በማድመቃቸው ‹ብርሃናተ ዓለም› ተብለው ይጠራሉ፡፡ የቅዱሳኑ አገልግሎት፣ ገድላቸው እና ተአምራቸው በመጽሐፈ ስንክሳር፣ በዜና ሐዋርያት እና በገድለ ሐዋርያት በሰፊው ተጽፎ ይገኛል፡፡ እኛም በዓለ ዕረፍታቸውን ለማስታወስ ያህል ታሪካቸውን በአጭሩ አቀረብን፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ያቆዩልንን የቤተ ክርስቲያን አስተምህሮ ጠብቀን፣ በክርስቲያናዊ ምግባር ጸንተን እንድንኖር፤ በመጨረሻም የእግዚአብሔርን መንግሥት ለመውረስ እንድንበቃ የቅዱሳኑ ጸሎት ይርዳን፡፡ ምንጭ:- https://eotcnor.no/2020/07/11/%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5-%E1%8C%B4%E1%8C%A5%E1%88%AE%E1%88%B5-%E1%89%85%E1%8B%B1%E1%88%B5-%E1%8C%B3%E1%8B%8D%E1%88%8E%E1%88%B5/
552
10
በየዓመቱ ሐምሌ ፭ ቀን በአንድ በኩል የጾመ ሐዋርያት ፋሲካ የሚከበርበት ዕለት ሲኾን፣ በሌላ በኩል ደግሞ የብርሃናተ ዓለም ቅዱሳን ጴጥሮስ እና ጳውሎስ በዓለ ዕረፍትም በዚሁ ዕለት ይዘከራል። ቅዱስ ጴጥሮስ ቅዱስ ጴጥሮስ በአባቱ የሮቤል፣ በእናቱ የስምዖን ነገድ ሲኾን፣ የተወለደውም በገሊላ አውራጃ በቤተ ሳይዳ ነው፡፡ ወላጆቹ ያወጡለት ስም ‹ስምዖን› ነበር፡፡ ጌታችን አምላካችንና መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ‹ጴጥሮስ› ብሎ ጠርቶታል፡፡ ትርጕሙም በግሪክ ቋንቋ ዓለት (መሠረት) ማለት ነው፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ የሚተዳደረው በዓሣ አጥማጅነት የነበረ ሲኾን፣ ሰዎችን በወንጌል መረብ እያጠመደ ወደ ክርስትና ሕይወት ይመልስ ዘንድ ጌታችን ለሐዋርያነት ጠርቶታል (ሉቃ. ፭፥፲፤ ማር. ፩፥፲፮)፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ በመንፈሳዊ ቅንዓቱና ለጌታችን በነበረው ፍቅር የሐዋርያት አለቃ ኾኖ ተሹሟል፡፡ ለአገልግሎት ከተጠራበት ጊዜ ጀምሮም በእስያ፣ በሮም፣ በሰማርያ፣ በልዳ፣ በኢዮጴ፣ በአንጾኪያ፣ በገላትያና በሌሎችም አገሮች እየተዘዋወረ ወንጌልን ሰብኳል፡፡ በስብከቱ ምክንያትም ልዩ ልዩ መከራን ተቀብሏል፡፡ በክርስቶስ ኀይል አጋዥነት ብዙ ድንቆችንና ተአምራትን አድርጓል፡፡ ከተሰጠው ጸጋ ብዛት የተነሣ በጥላው ሕሙማን ይፈወሱ ነበር (ሐዋ. ፭፥፲፭)፡፡ ሐዋርያው በቃል ካስተማረው ትምህርት በተጨማሪ በመጽሐፍ ቅዱስ በስሙ የተመዘገቡ ሁለት መልእክታትን ጽፏል (፩ኛ እና ፪ኛ ጴጥሮስ)፡፡ የቅዱስ ጴጥሮስ ምድራዊ የአገልግሎት ዘመኑ ሊፈጸም ሲቃረብም እንዲህ ኾነ፤ በዘመኑ የክርስቲያኖች ጠላት የነበረው የሮም ንጉሥ ወደ አካይያ ዘምቶ ድል አድርጎ በደስታ ወደ ሮሜ ሲመለስ መኳንንቱን ለማስደሰት፤ ጣዖታቱንም ለማክበር ሲል በቅዱስ ጴጥሮስና በሌሎችም ክርስቲያኖች ላይ የሞት ፍርድ ዐወጀ፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስም በሮም ሲያስተምር ቆይቶ የሮም መኳንንት እንዳይገድሉት ትጥቁን ለውጦ ከሮም ሲወጣ ጌታችን መስቀል ተሸክሞ ተገለጸለት፡፡ በዚህ ጊዜ ‹‹አቤቱ ጌታ ሆይ ወዴት ትሔዳለህ?›› ሲል ቢጠይቀው ጌታችንም ‹‹ልሰቀል ወደ ሮም እሔዳለሁ›› አለው፡፡ ‹‹ዳግመኛ ትሰቀላለህን?›› ባለው ጊዜም ‹‹አንተ ስትፈራ ጊዜ ነው እንጂ›› ሲል መለሰለት፡፡ ያን ጊዜም ‹‹ጐልማሳ ሳለህ ወገብህን ታጥቀህ ወደ ወደድኸው ትሔድ ነበር፡፡ ስትሸመግል ግን እጅህን ታነሣና ሌላ ሰው ያስታጥቅሃል፤ ወደማትወደውም ይወስድሃል፤›› (ዮሐ. ፳፩፥፲፰) በማለት ጌታችን የነገረው ቃል አሟሟቱን የሚያመለክት መኾኑን አስታውሶ ወደ ሮም ተመልሶ ስብከቱን ቀጠለ፡፡ በሮማውያን ሕግ ቅጣት የተፈረደበት ወንጀለኛ የሮም አገር ተወላጅ ከኾነ የወንጀሉ ክብደትና ቅለት እየታየ ግርፋት ወይም ሞት ይፈረድበታል እንጂ በአንድ ወንጀል ሁለት ቅጣት አይቀጣም ነበር፡፡ ወንጀለኛው የውጪ አገር ዜጋ (ከሮም ውጪ) ከኾነ ግን ለምሳሌ ቅጣቱ ግርፋት ከኾነ ከተገረፈ በኋላ እስራት ይጨመርበታል፤ ቅጣቱ ሞት ከኾነም ከገረፉት በኋላ በመስቀል ወይም በሌላ መሣርያ ይገድሉት ነበር፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ ዜግነቱ ሮማዊ አልነበረምና በግርፋትም፣ በእስራትም በሞትም እንዲቀጣ ተፈረደበት፡፡ እንደ ሥርዓታቸውም ቅዱስ ጴጥሮስን ከገረፉት በኋላ ሊሰቅሉት ሲሉ ወታደሮቹን ‹‹እንደ ክብር ንጉሥ እንደ ጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስ አቁማችሁ ሳይኾን፣ ዘቅዝቃችሁ ስቀሉኝ›› አላቸው፡፡ እነርሱም እንዳላቸው አድርገው ሐምሌ ፭ ቀን ዘቅዝቀው ሰቅለውታል፡፡ በመስቀል ላይ ሳለም ተከታዮቹን በሃይማኖታቸው እንዲጸኑ ካዘዛቸው በኋላ ነፍሱን ለእግዚአብሔር ሰጠ፡፡ ሥጋውንም መርቄሎስ የሚባለው ደቀ መዝሙሩ ሽቱ ቀብቶ፣ በነጭ ሐር ገንዞ ዛሬ ቫቲካን በምትባለዋ ስፍራ በክብር ቀብሮታል፡፡
465
11
ለዜማ ለቅኔ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ ጸሎት በእንተ ቅኔ ወዜማ ፊጦር አላጦር ወአብዳጦር ፫ተ ቃላተ ከመ አጽንዕ ዘኢያጽናዕኩ ዘአጽናፈ ፋጦርጨርህ ሊተ ለገብርከ እገሌ___ ገቢሩ:- በሰባት ዘቢብ ወይም በንጹሕ ማር ፊትህን ወደ ምሥራቅ አድርገህ በትክል ድንጋይ ላይ ፳፩ ጊዜ ደግመህ ብላ
595
12
eid-mubarak-moon-mosque-beautiful-background_1017-24886.webp
624
13
ውርሻ በራሳችን እንዋረሳለን ለምትሉ ሁሉ መጀመሪያውኑ ደና ደና ደረቅ ጥበብ ብትይዙ ይሻላል ከአጋንንት ጋር ስምምነት መጨረሻው አያምርም። እባካችሁ 🙏🙏 እራሳችሁ ለመዋረስ አትሞክሩ ትበላሻላችሁ በረቂቅ አይምሯችሁን ነው ሚያሳጧችሁ በጣም ጥንቃቄ ያስፈልገዋል። በተጨማሪ ደግሞ ሌላ ውርሻ ያለው ሰው ያስፈልጋል ቃል ሚያስገባላችሁ ያለበለዚያ ባጭር እንዳትቀሩ። ቃል ነው እና ሰማይን እና ምድርን ያረጋ ያቆመ ቃል ሳይገባ ውርሻ የለም።
695
14
~~ለሙግት~ የእሁድ አልሐምዱሊላሂ፡ ረቢ፡ ለዓለሚን፡ ያሐዩ፡ ያቀዩም፡ አጵብ፡ ያረውቀያኤል፡ ለሚዓን፡ ሙጢአን፡ ቢሐቂል፡ ረቢ፡ ለዓለሚን፡ እልሐይ፡ አልቀዩም፡ ወቢሐቂ፡ አልመከ፡ አልመወክል፡ ቢቃይመቂል፡ አርሾ፡ አብጰዊ፡ እሁድ ዕለት ፀሐይ ሳትወጣ 11 ጊዜ ድገምና ወደ ምስራቅ በሚፈስ ውሃ መላ ሰውነትህን ተቀባ ጠላትህን ድል ታደርጋለህ። የሰኞ ኢያከ፡ ናዕቡዱ፡ ወኢያካ፡ ነስተኢን፡ ያጀባር፡ ያሰሪዕ፡ ያቀሪብ፡ ያጅብ፡ ያጅብራኤል፡ ስሚጸዓን፡ ሙጢዳን፡ ቢሐቂ፡ አልማዕቡድ፡ አልሙስተኢን፡ አሰሪዕ፡ አልቀሪብ፡ ወቢልቂ፡ አልመወከል፡ ቢቃይመቲል፡ አርመንሰዒን የማክሰኞ ቀይሪል፡ መቅዱቢ፡ አለይሂብ፡ ወዕዱዋሊን፡ አላሁ፡ አልሻሂድ፡ አልቃሂር ፡ አልአዚዝ፡ ወቢሐቂ፡ አልመለክ፡ አልመወከል፡ ቢቃይመቲል፡ አርሽ፡ ዘሱፈሊ። የረቡዕ መሊኪ፡ የውሚዲን፡ የሙቀሊበል፡ ቁሉብ፡ አጵብ፡ ያሚካኤል፡ ሰሚዓን፡ ሙጡአን፡ ወቢሐቂ፡ አልመለክ፡ አልመወከል፡ ቢቃይመቲል፡ አርሸ፡ ጠይከል።   የሐሙስ ጢራጠሲዚና፡ አንአምታ፡ አለይሂም፡ ያሐኪም፡ ያዓሊም፡ አጅብ፡ ያሰርፍያኤል፡ ለሚዓን፡ ሙጢአን፡ ወቢሐቂል፡ ሐኪም፡ አልዓሊም፡ ወቢሐቂል፡ ሐኪም፡ አልዓሊም፡ ወቢሐቂል፡ አልመለክ፡ አልወከል፡ ቢቃይመቲል፡ አርሽ፡ ሽተለኺሂን። ዘአርብ አራኅመኒ፡ ረኂም፡ አረዑፍ፡ ኦስጢፍ፡ አልመለክ፡ አልመወከል፡ ቢቃይመቲል፡ አልዓረሺ፡ አንያኤል፡ ወቢሐቂል፡ አረዑፍ፡ እሰጢፍ፡ ወቢሐቂል፡ መልአክ፡ አርሸ ። የቅዳሜው አኅዲነ፡ ሊራጠ፡ አልሙስቀቂም፡ ያዘኪዩ፡ ያቀዲሩ፡ ያሙቅተዲሩ፡ ወቢሐቂ ፡ አልመለክ ፡ አልመወከል ፡ ቢቃይመቲል ፡ ያይዝራኤል ፡ አሕደኒ ፡ ሲራጠ ፡ አልሙተለቂም፡ አልቃዲር ፡ አርሽ ፡ ፈቀር። የሁሉም ገቢር ልክ እንደ ዕለተ እሁድ ነው የቀኑን ድጋም መቀያየር ብቻ ነው የሚያስፈልገው።
772
15
ህገ ጠብቅ ማለት ባል ወደሌላ ሴት እንዳይማግጥ ሚስትም እንዲሁ ከባለቤት ውጪ እንዳይገናኙ የሚያደርግ ድንቅ ጥበብ ነው። ህገ ጠብቅ ከዘረደሸት አስማት መጽሐፈ ዘረደሸት መቅዶንያ እልፉዢፌም መበበጀ ርጅርምያከ መርጅሐር ቆያከሸ ክርድያል ቆሐኪም ጂደል ኤል ሕመል ቀውስ መልተሐኪም ኅቡዕ ተኀበዕ ቀሆጡኝ ቆሆሔኝኆኞ ኞቆሆጤ ሸዐ ሮናምቅ ሸኖጅ ናፎንጅ ሮናምቅ ሸኖጅ ናፎንጅ በዝንቱ አስማት ከመ ኢታሀብ ሕልፃሃ ወሕምስሃ ወኢታፍቅር በልቡናሃ ትጽላዕ ወትጽርፎ ለባዕድ እንበለ ብእሲሃ ወታፈቅሮ ወተሐልዮ በኩሉ ጊዜ  በቀይ ሀር 9 ጊዜ ደግመህ በረግረጋማ ስፍራ ቅበር፡፡
678
16
بدون متن...
709
17
ሎጎው እንዴት ነው አሪፍ ነው? በአንድ ወንድማችን የተሰራ ነው። በዚህ አጋጣሚ ወንድሜን ማመስገን እፈልጋለሁ።
631
18
በቃሌ መሰረት ስማቸውን በውስጥ የነገሩኝን ሰዎች ኮከባቸውን ቆጥሬ አሳውቂያለሁ
722
19
بدون متن...
805
20
መልካም በዓለ ሀምሳ ( ጰራቅሊጦስ )
736