cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

My Poem💁‍♀ For Christ🙏🙏

"ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።" የሉቃስ ወንጌል ምዕ 2÷52

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
474
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ምሳሌ 31 (Proverbs) 8፤ አፍህን ስለ ዲዳው ክፈት፥ ተስፋ ስለሌላቸውም ሁሉ ተፋረድ። 9፤ አፍህን ክፍት፥ በእውነትም ፍረድ፤ ለድሀና ለምስኪን ፍረድ። @poemsforchrist @poemsforchrist
نمایش همه...
"ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።" የሉቃስ ወንጌል ምዕ 2÷52 ግጥሜን ለኢየሱስ 🙏🔥✍ https://t.me/poemsforchrist 👆👆👆👆👆👆👆👆👆👆
نمایش همه...
My Poem💁‍♀ For Christ🙏🙏

"ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።" የሉቃስ ወንጌል ምዕ 2÷52

👉https://t.me/poemsforchrist ✍Reyni Tamiru ካልከበርክ ማልከብር ካልታየ ማልታይ ከሌለ የሌለው ማንነቴ የሆንከው መኖር ሚያኖረኝ ያንተ ምርኮኛ ነኝ። #ኢየሱስ_ማንነቴ_ነህ!!
نمایش همه...
My Poem💁‍♀ For Christ🙏🙏

"ኢየሱስም ደግሞ በጥበብና በቁመት በሞገስም በእግዚአብሔርና በሰው ፊት ያድግ ነበር።" የሉቃስ ወንጌል ምዕ 2÷52

✍#Reyni_Tamiru ማንን ላንሳ ?? ማን አለና ማንን ላንሳ ? ትላንትናን ያስረሳ ከሰው ልጆች ማንን ላውሳ ? ሁሉም አልፎ እንደ ዋዛ ዛሬን ስደርስ በእርሱ እገዛ በድካሜ ረድቶ ከህመሜ የፈወሰኝ ማን አለና ማንን ላንሳ ? ተረኛ አርጎኝ በእርሱ ተራ ፊት ሲሆነኝ ቀኝ ግራ ኃላ ሆኖ ከእኔ ጋራ አሻገረኝ እየመራ ... አንድ አለ ግን የሚነሳ 🙋‍♀ ለዘላለም የሚወሳ ዕድሜ ልኬን የማልከፍለው ለዚ ጌታ የሚገባው ውዬ ባድር ማልጨርሰው ውለታ አለኝ ማልመልሰው። (ኦሪት ዘዳግም ምዕራፍ 32) ---------- 10፤ በምድረ በዳ በጥማት፥ የነፋስ ጩኸትም በሞላበት ውድማ አገኘው፤ ከበበው ተጠነቀቀለትም፤ እንደ ዓይን ብሌን ጠበቀው። . . . 11፤ ንስር ጫጩቶቹን እንደሚያወጣ፥ በእነርሱም ላይ እንደሚሰፍፍ፥ ክንፎቹን ዘርግቶ ወሰዳቸው፥ በክንፎቹም አዘላቸው። . . . 12፤ እግዚአብሔር ብቻውን መራው፤ ከእርሱም ጋር ሌላ አምላክ አልነበረም። በ #2014 የእግዚአብሔርን እጅ ብቻ ነው ያየውት !! 😍🔥🙌 🙋‍♀ @poemsforchrist 🙋‍♀ 🙋‍♀ @poemsforchrist 🙋‍♀ 👆👆👆👆 👆👆
نمایش همه...
ፊቴ የቆመውን ባሕር ያኔ አሳልፎኝ ነበር ዛሬስ ደግሞ ሌላው ቢገጥመኝ በየተራ ቢሰለፍብኝ ዓይኔን ማንከራተቱን ትቼ ልምታ ከበሮዬን አንስቼ የሰልፉ ጌታ ከእኔ ጋር ነው ዛሬም ጠላቴን ሊያዋርደው (፪x) ያሻገረኝ ጌታ ያን የትላንቱን (፫x) አሁንም ይሰራል ያን ሃይሉን ሳምን (፫x) በእውነት ላመልከው ከልቤ ስነሳ (፫x) ሁሉን አሳመረው የይሁዳ አንበሳ (፫x) አዝ ከእንግዲህማ ወስኗል ልቤ ከእንግዲህማ ምንም ላይፈራ ከእንግዲህማ ጌታ ኢየሱስ እያለ ከእኔ ጋራ ከእንግዲህማ ሌላውን አልሰማም ከእንግዲህማ ከንቱ ነውና ከእንግዲህማ እዘምራለው ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ኢየሱስ ጌታ ነውና ኢየሱስ ጌታ ነውና (፪x) ፊቴ የቆመውን ባሕር ያኔ አሳልፎኝ ነበር ዛሬስ ደግሞ ሌላው ቢገጥመኝ በየተራ ቢሰለፍብኝ ዓይኔን ማንከራተቱን ትቼ ልምታ ከበሮዬን አንስቼ የሰልፉ ጌታ ከእኔ ጋር ነው ዛሬም ጠላቴን ሊያዋርደው የቆመው ተራራ ፊቴ ተከምሮ (፪x) አይመስልም ሚታለፍ እንደሚከብድ ሆኖ (፪x) ለእኔ እንጂ ለአምላኬ መቼ አስቸገረው (፪x) በተአምራቱ ሁሉን ሜዳ አደረገው (፪x) አዝ ከእንግዲህማ ወስኗል ልቤ ከእንግዲህማ ምንም ላይፈራ ከእንግዲህማ ጌታ ኢየሱስ እያለ በእኔ ጋራ ከእንግዲህማ ሌላውን አልሰማም ከእንግዲህማ ከንቱ ነውና ከእንግዲህማ እዘምራለው ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ከልቤ ለእርሱ ምሥጋና ኢየሱስ ጌታ ነውና ኢየሱስ ጌታ ነውና (፬x) @poemsforchrist 🙋‍♀ @poemsforchrist 🙋‍♀
نمایش همه...
አስተማማኝ የሆነ የህይወቴ እረኛ ኢየሱስ ክርስቶስ ስላለኝ ነገ ምን እሆን ብዬ በፍፁም አልሰጋም። "በአንተ ታምናለችና በአንተ ለምትደገፍ ነፍስ ፈጽመህ በሰላም ትጠብቃታለህ።" (ትንቢተ ኢሳይያስ 26:3) @poemsforchrist ☺️
نمایش همه...
ቢገባንም ባይገባንም እኛ ብናውቅም ባናውቅም እግዚአብሔር ሁሌም ለእኛ መልካም ነው መልካምነት ማንነቱ ነው 🙏🙏 መልካም የሚለው ቃል መልካም ነህ ብሎሃል .. መልካም የሚለው ቃል መች አንተን ገልፃሃል .. ትበልጣለ ☺️ 👉 እግዚአብሔር መልካም ነው፥ በመከራ ቀንም መሸሸጊያ ነው፤ በእርሱ የሚታመኑትንም ያውቃል። " (ትንቢተ ናሆም 1:7) ያየነውን የሰማነውን እንመሰክራለን ..✝✝✝ እግዚአብሔር ሁሌም ለልጆቹ መልካም ነው። @poemsforchrist @poemsforchrist
نمایش همه...
(መጽሐፈ ዜና መዋዕል ቀዳማዊ ምዕራፍ 17) ---------- 16፤ ንጉሡም ዳዊት ገባ፥ በእግዚአብሔርም ፊት ተቀምጦ እንዲህ አለ። አቤቱ አምላክ ሆይ፥ እስከዚህ ያደረስኸኝ እኔ ማን ነኝ? ቤቴስ ምንድር ነው? 17፤ አምላክ ሆይ ይህ በፊትህ ጥቂት ነበረ፤ አቤቱ አምላክ ሆይ፥ ስለ ባሪያህ ቤት ደግሞ ለሩቅ ዘመን ተናገርህ፤ እንደ አንድ ባለ ማዕርግ ሰው ተመለከትኸኝ። 18፤ አንተ ባሪያህን ታውቀዋለህና ለባሪያህ ስለ ተደረገ ክብር ዳዊት ጨምሮ የሚለው ምንድር ነው? 19፤ አቤቱ፥ ይህን ታላቅ ነገር ሁሉ ታስታውቀው ዘንድ ስለ ባሪያህ እንደ ልብህም ይህን ታአምራት ሁሉ አድርገሃል። 20፤ አቤቱ፥ እንዳንተ ያለ የለም፥ በጆሮአችንም እንደሰማን ሁሉ ከአንተ በቀር አምላክ የለም። @poemsforchrist 🙌
نمایش همه...
" ውኃ ባሕርን እንደሚከድን ምድር የእግዚአብሔርን ክብር በማወቅ ትሞላለችና።" (ትንቢተ ዕንባቆም 2:14) 😭😭🔥🔥😭😭አሜን🔥🔥😭😭🔥🔥 @poemsforchrist🙋‍♀ @poemsforchrist🙋‍♀
نمایش همه...
✍ለነብሴ ነብሷ ነህ አንተ : ካለህበት ወዳንተ : መጠጋት ለነብሴ : ጠቀማት ለሰላሟ : መብዛት እረፍቷ : ሆንክላት ለመዳኗ : ምክንያት ህይወት :የሆንክላት ካንተ : ውጪ : ማየት መስማትም : ያቃታት በፍቅር : ሰንሰለት ጠፍረ : የያዝካት በቤት : መሰንበት መዋል : የሆነላት ለነብሴ : ነብሷ : ነህ ኖረ : ምታኖራት። #Reyni_Tamiru @poemsforchrist🙋‍♀ @poemsforchrist🙋‍♀
نمایش همه...