cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ምስራቅ ጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ East Gurage Zone Justice Department

+251904202912

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
538
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+17 روز
+1730 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

ይቅርታ የጥፋተኝነትን ውሳኔ ይሽራልን? አንድ በወንጀል የተከሰሰ ሰው በተከሰሰበት ወንጀል ጥፋተኛ ከተባለ በኃላ በወ/ህ/ቁ 84 መሠረት ከሳሽ ዐ/ህግ የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶችን ካለው እንዲያቀረብ ፍ/ቤቱ የሚጠይቀው ሲሆን በዚህ ድንጋጌ መሠረት ዐ/ህግ ከሚያቀርባቸው የቅጣት ማክበጃ ምክንያቶች መካከል ደግሞ በአንቀፅ 84(1)(ሐ) መሠረት የወንጀለኛው የቀድሞ ጥፋተኝነቱ አንዱ ነው፡፡ ሆኖም አንድ ተከሳሽ(ወንጀለኛ) አስቀድሞ በሌላ ወንጀል የቅጣት ውሳኔ ከተሰጠበት በኃላ ሥልጣን በተሰጠው አካል ቅጣቱ በይቅርታ ቢቀር የቀድሞ ጥፋተኝነቱን ያስቀረዋለልን? የሚለውን ስናይ በወንጀል ህግ አንቀፅ 229(2) ይቅርታ ሲሰጥ በተቀጪው ላይ የተወሰነው ፍርድ ከሚያስከትለው ውጤት ጋር በወንጀለኞች መዝገብ ላይ ተመዝግቦ ይኖራል ሲል ይደነግጋል፡፡የፌ/ጠ/ፍ/ቤት ሰበር ሰሚ ችሎትምበቅፅ 10 በሰ/መ/ቁ 41248 ላይ በይቅርታ ከተፈታው በኃላ እንደሪከርድ ተወስዶ ቅጣቱ ከብዶ መወሰኑ አግባብነት የለውም ሲል የሰበር አመልካች ያቀረበለትን አቤቱታ ተመልከቶ ይቅርታ የጥፋተኝነት ውሳኔ እንዳልነበረ የሚያስቆጥር አይደለም፡፡ለአመልካች የተሰጠው ይቅርታ እንጂ ምህረት ያለመሆኑን ያላገናዘበ በመሆኑ የአመልካች አቤቱታ ተቀባይነት የለውም ሲል ፍርድ ሰጥቷል፡፡ከዚህም መገንዘብ የሚቻለው በወ/ህ/ቁ 230(2) እንደተገለፀው የጥፋተኝነትን ታሪክ(ሪኮርድ) እንዳልነበር የሚያደርገው ምህረት እንጂ ይቅርታ አለመሆኑን ነው፡፡ ከኢትዮጵያ ህግ
نمایش همه...
👍 3
የአካል ጉዳተኞች የሥራ ሥምሪት መብት ጥበቃ በኢትዮጵያ ✍ በማህረሰቡ ዘንድ ስር ሰዶ የቆየ ለአካል ጉዳተኝነት ያለው የተሳሳተ ግንዛቤ በአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መብት ላይ የራሱን አሉታዊ ተጽኖ ያደረሰ መሆኑ የሚታወቅ ነው፡፡ ስለሆነም ኢትዮጵያ አካል ጉዳተኛ የሆኑ ዜጎቿ የሚደርሰባቸው ከሥራ ቅጥር ማግለል ወይም መድሎ ለማስወገድ የአካል ጉዳተኞች የሥራ ስምሪት መብት አዋጅ በ2000 ዓ.ም እንዲወጣ አድርጋለች፡፡ በዚህ ጽሁፍም የአካል ጉዳትተኛን ምንነትና በአዋጁ የተመለከቱ መብቶችን እንመለከታለን፡፡ ✍ አካል ጉዳተኛ የሚባለው ማን ነው? አካል ጉዳተኛ የሚለው ቃል በተለያየ መንገድ የተለያየ ትርጉም ያለው ሲሆን ለዚህ ጽሁፍ አላማ ሲባል ከሥራ ስምሪት ጋር በተገናኘ የተሰጠውን ትርጉም እንመለከታለን፡፡ በአለም አቀፍ ደረጃ አካል ጉዳተኛ የሚለው ቃል ሲተረጎም “በደረሰበት የአካል ወይም የአምሮ ሰላም፣ የስሜት ህዋሳት ጉዳት ምክንያት ፕሮፌሽናል ሥራዎችን ወይም መደበኛ ሥራን ለማስራት የተገደበ ወይም በአካል ጉዳቱ ምክንያት ማህበራዊ ወይም ባህላዊ ተግባራትን ለማከናወን የተገደበ ሰው እንደሆነ ትርጉም የተሰጠው ሲሆን አዋጅ ቁጥር 568/2000 አንቀፅ 2(1) ላይ አካል ጉዳተኛ ማለት የደረሰበትን የአካል፣ የአዕምሮ ወይም የስሜት ህዋሳት ጉዳት ተከትሎ በሚመጣ የኢኮኖሚያዊ፣ የማህበራዊ ወይም የባህላዊ መድሎ ሳቢያ በሥራ ስምሪት የእኩል እድል ተጠቃሚ ያልሆነ ሰው ነው” በማለት ትርጉም ሰጥቶታል፡፡     ✍ የአካል ጉዳተኞች የሥራ ቅጥር ሁኔታ በማስታወቂያ በወጣ ክፍት የሥራ ቅጥር ላይ የተወዳደር አካል ጉዳተኛ የወጣው የሥራ ቅጥር የሥራው ጠባይ ወይም ባህሪ የማይፈቅድ ካልሆነ በቀር አስፈላጊ የችሎታ መመዘኛዎችን ካሟላ እና በውድድሩ ከፍተኛ ነጥብ ካመጣ የመቀጠር መብቱ የተጠበቀ ሲሆን በውድድሩ ያመጣው ነጥብ ከሌሎች ተወዳዳሪዎች ጋር የተቀራረበ ወይም እኩል ነጥብ የሆነ እንደሆነ ቅድሚያ የመቀጠር መብት አለው፡፡ በሌላ በኩል በማንኛውም መስሪያ ቤት ወይም ድርጅት ውስጥ ያለን ክፍት የሥራ ቦታ በዕድገት፣ በድልድል ወይም በዝውውር የመያዝ ወይም በሀገር ውስጥም ሆነ በውጭ አገር በሚሰጥ የስልጠና ፕሮግራም ለመሳተፍ መብት ያለው ሲሆን ከላይ በተዘረዘሩት የቅጥር ሁኔታና ስልጠና አካል ጉዳተኛ የሆነ ሰራተኛ ያመጣው ነጥብ ከሌሎች ጋር የተቀራረበ ወይም እኩል ከሆነ ቅድሚያ የማግኘት መብት አለው፡፡   ✍ የተከለከለ ተግባርና መድሎ የተከለከለ ስለመሆኑ ማንኛውም የሥራ ቅጥር ማስታወቂያ ሲወጣ በማስታወቂያው ላይ የሚዘረዘሩት የመወዳደሪያ መስፈርቶች ለሥራው ባህሪ አስገዳጅ ካልሆነ በስተቀር በተወዳዳሪው ላይ ያለውን ጉዳት የሚመለከት መስፈርት ማውጣት የተከለከል መሆኑ በአዋጁ አንቀፅ 4(3) ተደንግጓል፡፡ የሥራው ጠባይ ወይም ባህሪ ማለት የሚሰራው ሥራ ለአካል ጉዳተኛ የማይሆን የሥራ አይነት ሲሆን ለምሳሌ የውትድርና ማለትም እንደ ፖሊስና መከላከያ ባለ ተቋም ለመቀጠር ምንም አይነት የአካል ጉዳት መኖር እንደሌለበት የሚታወቅ ነው፡፡ በመሆኑም በነዚህ ተቋማት ለመቀጠር አንዱና ዋናው መስፈርት ምንም አይነት የአካል ጉዳት የሌለበት መሆን እንዳለበት ያስገድዳል፡፡ ከዚህ ውጪ የአካል ጉዳተኛን እኩል የሥራ እድል የሚያጣብብ ህግ፣ አሰራር፣ ልምድ፣ ዝንባሌ መፍጠር ህገ ወጥ ሲሆን በቅጥር፣ በእድገት፣ በድልድል፣ በዝውውር ወይም በሌሎች የሥራ ስምሪት ሁኔታዎች ለማወዳደሪያ የሚቀመጡ መስፈርቶች የአካል ጉዳተኞችን የሥራ እድል የሚያጠብ ሆኖ ከተገኘ እንደመድሎ የሚቆጠር ነው፡፡ ✍ የአሰሪ እና የአካል ጉዳተኛ ሰራተኞች ኃላፊነት ለማንኛውም ሰራተኛ የሥራ ቦታ ምቹና ሳቢ መሆን ያለበት ሲሆን በተለየ ሁኔታ ግን አካል ጉዳተኞች በሚሰሩበት ቦታ የመስሪያቤቱ ወይም አሰሪው • የሥራና የስልጠና አካባቢን የማመቻቸትና ተስማሚ የሆኑ የሥራ ወይም የስልጠና መሳሪያወችን የማሟላት፣ • ማንኛውም ረዳት የሚያስፈልገው አካል ጉዳተኛ ሥራውን ለመስራት ወይም ስልጠናውን ለመከታተል እንዲችል ረዳት የመመደብ፣ • ሴት አካል ጉዳተኞች በፆታ እና በአካል ጉዳት ምክንያት ያለባቸውን ተደራራቢ ጫና ያገናዘበ ማስተካከያና የድጋፍ እርምጃዎችን የመውሰድ እንዲሁም በሥራ ቦታ የሚደርስባቸውን ፆታዊ ጥቃት የመከላከልና ተፈፅሞ ሲገኝም በፈፃሚው ላይ ህጋዊ ርምጅ የመውሰድ ወይም እንዲወሰድ የማድረግ ኃላፊነቶች አሉበት፡፡ በሌላ በኩል አካል ጉዳተኛ ሰራተኛ በተመደበበት ሥራ በሙሉ ኃላፊነት የማከናወን ግዴታ ያለበት ሲሆን የሥራውን ኃላፊነት በትክክል ባይወጣ ወይም ጥፋት ቢፈፅም አካል ጉዳቱ ከተጠያቂነት የማያድነው መሆኑን አዋጁ አንቀፅ 8 በግልፅ ደንግጎ ይገኛል፡፡ የአካል ጉዳተኛ ሥራ ስምሪት መብት ሲጣስ ምን አይነት እርምጃ የወሰዳል? ✍ በአዋጅ ቁጥር 568/2000 የተቀመጡትን ድንጋጌዎችና አዋጁን ለማስፈፀም የወጡ ደንብና መመሪያወችን የተላለፍ አሰሪ የወንጀል ተጠያቂነት እንዳለበትና የቅጣቱም መጠን ከብር 2,000 (ሁለት ሺ) የማያንስና ከብር 5,000 (አምስት ሺ) የማይበልጥ መቀጮ እንደሆነ ተቀምጧል፡፡ በወንጀል ህጉ የበለጠ የሚያስቀጣ በሆነ ጊዜ ግን በወንጀል ህጉ የተመለከተው ቅጣት ተፈፃሚ ይሆናል፡፡ ✍ ሌላው በዚህ አዋጅ የተሸፈነው የመብት ጥሰት ሲያጋጥም ክስ በማን ይመሰርታል?  ለሚለው ጥያቄ ምላሽ ሲሆን በዚህም መሰረት በአዋጁ ላይ የተቀመጡ ድንጋጌዎች ወይም አዋጁን ለማስፈፀም የወጡ ደንቦችና መመሪያዎች ባለመከበራቸው መብቱ የተጣሰበት የአካል ጉዳተኛ ወይም አካል ጉዳተኛው አባል የሆነበት የአካል ጉዳተኖች ማህበር ወይም አካል ጉዳተኛው አባል የሆነበት የሰራተኞች ማህበር ወይም አዋጁን የሚያስፈፅም አግባብ ያለው አካል ስልጣን ላለው ፍርድ ቤት ክስ የማቅረብ መብት ያለው መሆኑ በአዋጁ አንቀፅ 10 ተደንግጓል፡፡ ይህን የህግ ክፍል ስንመለከት በህገ መንግስቱ አንቀጽ 37 ላይ የተቀመጠውን ፍትህ የማግኘት መብት አስፍቶ መብት የሰጠ ሲሆን የአካል ጉዳተኛው የሥራ ስምሪት መብት ሲጣስ መብቱ የተጣሰበት ግለሰብ ብቻ ሳይሆን ሌሎች አባል የሆነባቸው ማህበራትም ክስ ማቅረብ አንደሚችሉ የሚያሳይ ነው፡፡ ✍ በዚህ አዋጅ ሌላው የተሸፈነው ጉዳይ ክስ ሲመሰረት የማስረዳት ሸክምን በተመለከተ ሲሆን በነባራዊው ሁኔታ አንድ ሰው ክስ ሲመሰርት ለክሱ መነሻ የሆነውን ምክንያት በተገቢ ሁኔታ ማስረዳት እንዳለበት የተቀመጠ ሲሆን በአካል ጉዳተኛ የስሥራ ስምሪት መብት ግን በአካል ጉዳቱ ምክንያት ብቻ በቅጥር፣ በእድገት፣ በድልድል፣ በዝውውር ወይም በሌሎች የሥራ ሁኔታዎች ላይ መድሎ ተፈፅሟል በሚል ጭብት በማስያዝ ብቻ ክስ መመስረት የሚቻል ሲሆን ክስ የቀረበበት ወገን ድርጊቱ አድሏዊ እንዳልነበረ በማስረጃ ማረጋገጥ አለበት በማለት የማስረዳት ሸክሙን ወደ ተከሳሽ አዙሮታል፡፡   
نمایش همه...
አለሕግ🔵AleHig

Alternative legal enlightenment/ALE አማራጭ የሕግ እውቀት፣ ጠበቃና የሕግ አማካሪ 📞 +251920666595 👉WhatsApp: Telegram👉 @MikiasMelak ነፃ የሕግ ምክርና ድጋፍ፣ የተለያዩ ህጎች፤ አዋጅ፣ ደንብ፣ መመሪያ፣ የሕግ መረጃና መሰረታዊ የሕግ እውቀት ያገኛሉ Website //linktr.ee/alehig ለአስተያየት👉 @LawsocietiesBot

ክስ የተመሰረተባቸዉ ሁለት የፖሊስ አባላት በ13 እና በ8 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነባቸዉ ሆሳዕና ሰኔ 21 ቀን 2016 (ማ.ኢ.ፖ.ኮ) በጉራጌ ዞን ሞህር አክሊል ወረዳ አንዝሬ ቀበሌ ንዑስ ፖሊስ ጣቢያ ተመድበዉ የህዝብን ሰላምና ደህንነት እንዲጠብቁና እንዲያስጠብቁ ሃላፊነት የተሰጣቸዉ የፖሊስ አባላት በተመሰረተባቸዉ ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል እና ጉቦ በመቀበል ወንጀል ጥፋተኛ ሆነዉ በመገኘታቸዉ በ13 እና በ8 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ተወሰነባቸዉ። ተከሳሾች 1ኛ.ኮንስታብል ታሪኩ ሙክታር 2ኛ.ም/ሳጅን እድሪስ አብላ በእስራት የተቀጡት በቀን 25/05/2016 ዓ.ም በምሁር አክሊል ወረዳ አንዝሬ ገበያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የግል ተበዳይ ለሽያጭ ያዘጋጀዉ የከብቶች ማሰሪያ ገመድ ጠፍቶብኛል ገመዱን የወሰደብኝን ተጠርጣሪ እጅ ከፍንጅ እንዲይዙለት ሲጠይቃቸው ብር ካልሰጠኸን አንይዝም በማለት 1000 ሺህ ብር ተቀብለዉ ተጠርጣሪዉን እና ኤግዚቢቱን ከያዙ በኋላ በተጨማሪ 1000 ሺብር እንዲሰጣቸው የጠየቁ በመሆኑ የተጣለባቸውን ኃላፊነት ባለመወጣት ያለምንም ክፍያ አገልግሎት መሰጠት ሲገባቸው በፈጸሙት የማይገባ ጥቅም መቀበል የሙስና ወንጀል የተከሰሱ ሲሆን:- በክስ 2 የግል ተበዳይ የሆነው ግለሰብ ከባለቤቱ ጋር በተፈጠረ አለመግባባት ምክንያት ተከሳሾች በህግ ቁጥጥር ስር አድርገውት በአንዝሬ ንኡስ ፖሊስ ጣቢያ ካሳደሩት በኋላ በቀን 16/05/2016 የተሰጣቸውን ኃላፊነት ያላግባብ በመገልገል ወደ ሀዋሪያት ፖሊስ ጣቢያ ከምንወስድህ 5000 (አምስት ሺህ) ብር ስጠን አለበለዚያ ከእስር አንፈታህም በማለት የግል ተበዳዩን በማስፈራራት 1500(አንድ ሺህ አምስት መቶ) ብር የተቀበሉት በመሆኑ፣ በክስ 3 በአንዝሬ ቀበሌ እለቱ የገበያ ቀን ስለነበረ የበግ ነጋዴ የሆነው የግል ተበዳይ ለንግድ የገዛቸው በጎች እየነዳ ከበጎች መሸጫ በረት ካወጣ በኋላ የዋጋ ግምቱ 1000 (አንድ ሺህ)ብር የሚገመት አንድ ነጭ ግልገል በግ ከበጎች ተነጥላ ስትሮጥ የበጉ ባለንብረት /የግል ተበዳይ/ በጉን አራሩጦ ሲይዘዉ ወንጀል መፈፀሙን ሳያረጋግጥ ወይም የወንጀል አቤቱታ ሳይቀርብላቸዉ አንተ ሌባ ነህ በማለት ተበዳዩን ከእነበጉ በመያዝ ወደ አንዝሬ ንኡስ ፖሊስ ጣቢያ በመውሰድ ሌባ ስለሆንክ በጉን አንሰጥህም ሳምንት መጥተህ ጠይቀን በማለት የግል ተበዳይ በሳምንቱ ንብረቴን ስጡኝ ብሎ ሲጠይቃቸው የተሰጣቸውን ኃላፊነት ተገን በማድረግ ንብረቱን በቁጥጥራቸዉ ስር ካደረጉ በኋላ ለባለንብረቱ ያልመለሱ በመሆኑ፤ በክስ 4 የግል ተበዳይ ለምግብ አገልግሎት የሚውል የተፈጨ በርበሬ እና ሽሮ በገበያ ውስጥ እየሸጠ ባለበት ተከሳሾች ዛሬ የምትሸጠው በርበሬ አፈር የተቀላቀለበት ነው አንተ በምትሸጠው በርበሬ የተሰራ ፍርፍር ፣ፓስታ እና አንቁላል መልኩን ቀይሯል በማለት የሚሸጠውን በርበሬ አሸክመዉ ወደ አንዝሬ ንኡስ ፖሊስ ጣቢያ ከወሰደው በኋላ ከቀኑ ከ5፡00 እስከ 11፡30 ስዓት ድረስ በአንድ ክፍል ውስጥ አስገብተው አስረውት ካቆዩት በኋላ ወደ ወረዳው ፖሊስ ጣቢያ ከምንወስድህ ገንዘብ ስጠን እና ጉዳዩን እዚህ እንሸፍንልሀለን በማለት 3000 (ሶስት ሺህ) ተቀብለውት የግል ተበዳዩን ከሰዎች ጋር ሳትቀላቀል እያየንህ በመኪና ውስጥ ገብተህ ሂድ በማለት የተሰጣቸውን ኃላፊነት በግልጽ ተግባር ያለ አግባብ የተገለገሉበት በመሆኑ በፈጸሙት ስልጣንን ያለአግባብ መገልገል የሙስና ወንጀል የተከሰሱ ሲሆን በክስ 5 አንደኛ ተከሳሽ ላይ ብቻ የሙስና ወንጀሎች አዋጅ ቁጥር 881/07 አንቀጽ 11/1/ ስር የተደነገገውን በመተላለፍ በሞህር አክሊል ወረዳ በመገራን ቀበሌ ልዩ ቦታው ቁጥር1 የዌሬት በሚባል አካባቢ የግል ተበዳዩ የጎረቤት ሰራተኛ ደብድበሀል በማለት ወደ አንዝሬ ንኡስ ጣቢያ ወስዶ ካሰረው በኋላ ጉዳዩን በእርቅ ጨርሰው ከእስር እንዲፈታዉ ሲጠይቀው የኮሚሽን ብር ሳትሰጠኝ አትወጣም በማለት 1400 (አንድ ሺህ አራት መቶ)ብር ከተቀበለ በኋላ ከእስር የለቀቀው በመሆኑ ተከሳሽ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ማድረግ የሚገባውን ለማድረግ ከግለሰብ ጥቅም የተቀበለ በመሆኑ፤ በክስ 6 ላይ የግል ተበዳይን ትፈለጋለህ በማለት ወደ አንዝሬ ንኡስ ጣቢያ ወስዶት ወደ ማረፊያ ቤት ሲያስገባዉ ስልኩን ተቀብሎት ካሰረው በኋላ ጉዳዩን በእርቅ ጨርሰው ከእስር ሲፈታዉ ቀድሞ የተቀበልዉን ስልክ እንዲመልስለት ሲጠይቀዉ ብር ሳትሰጠኝ ስልክህን አልመልስልህም በማለት ተከሳሽ የግል ተበዳይን ሲያስረዉ የተቀበለዉን ስልክ ያለምንም ክፍያ ለባለንብረቱ መመለስ ሲገባዉ 300(ሶስት መቶ) የተቀበለዉ በመሆኑ በተሰጠው ኃላፊነት መሰረት ማድረግ የሚገባውን ለማድረግ ከግለሰብ ጥቅም የተቀበለ በመሆኑ በፈፀመዉ ያልተገባ ጥቅም መቀበል የሙስና ወንጀል የተከሰሰ ሲሆን በክስ 7 ላይ የኢ.ድ.ሪ የወንጀል ህግ አንቀጽ 556 /2/ሀ/ ስር የተደነገገውን በመተላለፍ ተከሳሽ የአካል ጉዳት ሊያደርስ የሚችለ መሳሪያ በመጠቀም አንዝሬ ገበያ እየተባለ በሚጠራው አካባቢ የኮሚሽን ብር /ጉቦ/ ለምን አትሰጠኝም በማለት በያዘው የጎማ ዱላ በክስ 1 ላይ የተገለፀዉን የግል ተበዳይ የግራና የቀኝ በኩል ጭንቅላቱን 2 ጊዜ በመምታቱ ጭንቅላቱ ላይ የመፈንከት ጉዳት ያደረሰ በመሆኑ ተከሳሽ አስቦ በፈጸመው ቀላል የአካል ጉዳት ማድረግ ወንጀል ተከሷል። የጉራጌ ዞን የሙስና ወንጀሎች ዐቃቤ ህግ ከላይ በተገለፁት ዝርዝር ሁኔታዎች በተከሳሾቹ ላይ የሙስና ወንጀል ክሶችን በማዘጋጀት ለጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት አቅርቦ የጉራጌ ዞን ከፍተኛ ፍርድ ቤት የግራ ቀኙን ሲያከራክር ቆይቶ በቀን 20/10/2016 በዋለዉ ችሎት አንደኛ ተከሳሽ በ13 ዓመት ፅኑ እስራት 2ኛ ተከሳሽ በ8 ዓመት ፅኑ እስራት እንዲቀጡ ወስኗል፡፡ "ህዝብን ለማገልገል በመንግስት ተቀጥረዉ ያልተገባ ጥቅም ለማግኘት ማህበረሰቡን ለእንግልት የሚዳርጉ እና ባልተገባ መንገድ ለመበልፀግ ህዝብን የሚበዘብዙ አካላትን በህግ እንዲጠየቁ እና የህግ የበላይነት እንዲረጋገጥ ለማስቻል ማህበረሰቡ ጥቆማ በማቅረብ ከፍትህ ጎን እንዲቆም ጥሪ መቅረቡ ከጉራጌ ዞን ፍትህ መምሪያ የተገኘዉ መረጃ አመላክቷል።
نمایش همه...
የውል ይርጋ 1)የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1810(2) ላይ የተመለከተው የይርጋ ገደብ ተፈፃሚ የሚሆነው ውል በፈቃድ ጉድለት ወይም በችሎታ ማጣት የተነሳ እንዲፈርስ ጥያቄ የቀረበ እንደሆነ ብቻ ስለመሆኑ የፍ/ብ/ህቁ 1810 የሰ/መ/ቁ 48012 ቅፅ 12 2)በውል ግንኑነት ውስጥ የራስን ግዴታ ሳይወጡ ሌላው ወገን ግዴታውን አልተወጣም በሚል የሚቀርብ ክስ ተቀባይነት የሌለው ስለመሆኑ የፍ/ብ/ሕ/ቁ 1757 በሰ/መ/ቁ 39568 በቅፅ 12 3)የማይንቀሳቀስ ንብረት ሻጭ በዉሉ መሠረት የመፈፀም ፍላጎት የሌለው መሆኑን በማያሻማ ሁኔታ ለገዢ ያላሳወቀ እንደሆነ ገዥ ውሉ እንዲፈፀምለት የመጠየቅ መብቱ በ10  ዓመት ይርጋ የሚታገድበት ስለመሆኑ 1845;1789:1731:1732 የሰ/መ/ቁ 38935 ቅፅ 12 4)የፍትሐብሄር ጉዳዮች የ ይርጋ ጊዜ መቆጠር የሚጀምረው ግዴታውን ለመጠየቅ ተገቢ ከሆነው ጊዜ ጀምሮ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ሕ/ቁ 1846 የሰ/መ/ቁ 36756 ቅፅ 12 5)የፀና የውል ግዴታ የገባ ሰው ውሉ በፍርድ እንዲሰረዝ ለመጠየቅ የሚችለው ሌላኛው ተዋዋይ ወገን ግዴታውን በአግባቡ ያልፈፀመ(ያልተወጣ) እንደሆነ ወይም የፈፀመው ፍፁም ባልሆነ አኳኃን ከሆነ ስለመሆኑ በፍ/ብ/ህ/ቁ 1784;1785(2).(1)"የሰ/መ/ቁ 66935 ቅፅ 13 ላይ ሰፍሯል።
نمایش همه...
👍 1
ጭብጥ አጭርና ግልጽ መሆን አለበት ሀ) ጭብጥ ሲመሰረትና ሲጻፍ በአጭሩ መሆን ይኖርበታል። ክርክሩን እንዳለ የሚደግም ወይም የተንዛዛ መሆን የለበትም:: በተቻለ መጠን በጥያቄ መልክ ሊቀመጥ ይገባል:: ውል የተደረገው በማታለል በመሆኑ ሊፈርስ ይገባል በሚል ከሳሽ ለአቀረበው ክስ የክስ ምክንታቱን ሲገልጽ "የንግድ ልምድ የሌለኝ ከገጠር የመጣው መሆነን አውቆ ተከሳሹ የመኪናውን ሞዴል እና የተሰራበትን ጊዜ በሚመለከት በማሳሳት አሮጌ መኪና የሸጠልኝ በመሆኑ የሽያጭ ውሉ ፈርሶ የከፈልኩትን ገንዘብ እንዲመልስልኝ ይወሰንልኝ" በሚል ቢገልጽ ተከሳሽ በሰጠው መልስ "ከሳሹ ከገጠር የመጣ ሳይሆን እዚሁ ከተማ ያደገ ቀደም ሲልም መኪና ገዝቶ የሸጠ በመሆኑና ትክክለኛ መረጃ የተሰጠው በመሆኑ የተፈፀመ ማታለል የለም” በሚል መልስ ቢሰጥ የሚያዘው ጭብጥ “በውሉ አደራረግ ማታለል ተፈጽሞአል ወይስ አልተፈፀመም?" የሚለው እንጂ “ተከሳሹ ከሳሽ ከገጠር የመጣና የንግድ ልምድ የሌለው መሆኑን በማወቅ የመኪናውን ሞዴልና ስሪት በተመለከተ አሳስቶታል ወይስ አላሳሳተውም?” የሚል መሆን የለበትም፡፡ የከሳሽ የንግድ ልማድ አለመኖር ...ወዘተ የመሳሰሉት ሁኔታዎች በጭብጡ ውስጥ የሚካተቱ እንጂ ራሳቸውን ችለው የሚቀመጡ አይደሉም፡፡ ለ) ጭብጡ ግልጽ ሊሆን ይገባል:: ለተከራካሪ ወገኖች በቀላሉ ሊገባቸው የሚችል፣ ውሳኔ ሊሰጥበት የተፈለገውን የህግ ወይም የሥረ ነገር ጉዳይ ምን እንደሆነ አውቀው  የማሰረጃዎቻቸውን አግባብነት አንዲገመግሙ፣ ማስረጃዎቻቸው ጭብጡን ማስረዳት አለማስረዳታቸውን በተመለከተ የበኩላቸውን ግምት እንዲሰጡ በሚያስችል መልኩ መቀመጥ አለበት፡፡   
نمایش همه...
Repost from N/a
   *የስጦታ ምንነት*    በአጭሩ ለማስቀመጥ ስጦታ ማለት ሰጪው ተቀባይ ለተባለ ሌላ ሰው  ከንብረቶቹ አንዱን ያለ ዋጋ የሚለቅበት ወይም ግዴታ የሚገባበት ውል ነው። በመሆኑም ስጦታ በራሱ ውል ነው ማለት ነው።                የስጦታ ልዩ ባህሪያት     በመርህ ደረጃ ስጦት ግላዊ ተግባር ነው ይህም ማለት ስጪው እራሱ የሚያድረገው ተግባር ነው ማለት ነው። ስጦታ የሚደረገው በወኪሉ ሲሆን ደግሞ የሚሰጠው ንብረት አይነት እና ለማን እንደሚሰጥ በግልጽ ሊመለከት ይገባል። ስጦታ የሚደረገው የሰጪው ንብረት በሆነው ለይ ብቻ ነው።ስጦታ አድርጋለሁ ብሎ የተስፋ ቃል መስጠት በህጉ መሠረት ግዴታን አያስከትልም ከዚህም በተጨማሪ ስጦታ ተቀባዩ ስጦታውን እቀበላለሁ በሚል ሀሳቡን መግለፅ ይኖርበታል።ስጦታ እንዲቀነስ ወይም እንዲሻር የሚቀርበው ጥያቄ ስጦታው ከተደረገበት ቀን አንስቶ እስከ ሁለት አመት ለዳኞች ካልቀረበ በቀር ዋጋ አይኖረውም።             የስጦታ ሥርዓት ፎርም*      ስጦታ በማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ላይ  ወይም በሚይንቀሳቀሱ ግዙፍ ንብረቶች ላይ ሊደረግ ይችላል። *1)በማይንቀሳቀስ ንብረቶች ላይ የሚደረግ ስጦታ *     በማይንቀሳቀስ ንብረቶች ላይ የሚደረግ ስጦታ በፍትሐብሔር ህግ አንቀጽ 881 ላይ በተደነገገው መሠረት በግልጽ ኑዛዜ ሥርዓት ፎርም መሠረት የሚፈጸም መሆኑን ህጉ ያስረዳል።በሌላ በኩል በማይንቀሳቀሱ ንብረቶች ለይ የሚደረገው ስጦታ በፍ/ህግ አንቀጽ 1723 መሠረት በጽሁፍ ሆኖ በፍርድ ቤት መዝገብ ወይም ውል ለማዋዋል ስልጣን በተሰጠው አካል ፊት መሆን አለበት።      *2) በሚንቀሳቀሱ ግዙፍ ንብረቶች ለይ የሚደረግ ስጦታ*    በሚንቀሳቀሱ ግዙፍ ንብረቶች ላይ የሚደረግ ስጦታ በሁለት አይነት መልኩ ሊደረግ ይችላል ይህም እጅ በእጅ በሚደረግ ማስተላለፍ ብቻ ወይም ለማይንቀሳቀስ ንብረት ስጦታ በሚደረገው ፎርም ሊሰጥ ይችላሉ።   ስጦታ እንደማድረግ የማይቆጠርባቸው ሁኔታዎች ያሉ ሲሆን እነኚህም ሁኔታዎች። 1)ያለ ዋጋ የሚደረግ የአገልግሎት ሥራ ወይም የራሱን እቃ ያለ ዋጋ ዝግጁ ማድረግ ስጦታ አይባልም የፍ/ህግ አንቀጽ 2430።                2)መንፈሳዊ ተግባርን ለመፈጸም የሚደረገው የገንዘብ መክፈል ስራ ስጦታ አይባልም የፍ/ህ አንቀጽ 2432። 3) አንድ ሰው ለሰጪው ወይም ለቤተሰቡ አገልግሎት በልማድ መሠረት ያደረገው የሥራ ዋጋ መክፈል ስጦታ አይባልም የፍ/ህ አንቀጽ 2433። 4)ወራሽነትን አልፈልግም ብሎ መተው ወይም ኑዛዜ የተደረገለትን ስጦታ አልቀበልም ማለት ስጦታ ነው ተብሎ አይቆጠርም የፍ/ህግ 2431።                  ስጦታ ፈራሽ የሚሆንባቸው ምክንያቶች*    በሚንቀሳቀስ ወይም በማይንቀሳቀስ ንብረቶች ለይ የተደረገው ስጦታ በህጉ በተጠቀሱት  በተለያየ ምክንያቶ ፈራሽ ሊሆን የሚችሉባቸው ምክንያቶች ያሉ ሲሆን እነኚህም:-        1ኛ የሰጪው አዕምሮ ትክክል አለመሆን  ሰጪው ስጦታውን በሚያድርግበት ወቅት በአዕምሮ መታወክ(ህመም ምክንያት) በፍርድ የተከለከለ ሲሆን ያደረገው ስጦታ  ፈራሽ ሊሆን ይችላል ።የፍ/ህ አንቀጽ 2437        2ኛ ግብረ ገብነት የሌለው ወይም ህገ ወጥ ምክንያት ያለበት ስጦታ ፈራሽ ነው። የፍ/ህ አንቀጽ 2438              3)በመንፈስ መጫን ምክንያት የተደረገውን ስጦታ ዳኞች ለመቀነስ ወይም ለመሻር ይችላሉ።የፍ/ህ አንቀጽ 2439       4ኛ በ ፍ/ህ አንቀጽ 2442 ሥር በሚፈቅደው መሠረት ስጦታው የተደረገው በስህተት ወይም በተንኮል የሆነ እንደሆነ ፈራሽ ይሆናል።   5 ስጦታ የተደረገው ክርክር ያለበት ሀብት ላይ ሲሆን ስጦታው ፈራሽ ይሆናል። henoktayelawoffice https://t.me/abouttradelaw21
نمایش همه...
ስለ ኢትዮጵያ ንግድ ሕግ

" ስለ ንግድ ሕግ እና ሌሎች ሕግ ነክ ጉዳዮች ከፈለጉ ይቀላቀሉን" Contact @Advice3087

👍 2
Mobile banking directive.pdf1.09 KB
Nbe Establishment Proclamation.pdf2.99 KB
NBE Supervision variou directives.pdf1.91 MB
New Deliquent list formatBSD-07-2013.pdf3.60 KB
NRNT FCY account.pdf0.97 KB
Operation of Forex.pdf0.31 KB
proclamation_no_731_2012_commercial_registration_and_business_licensing.pdf1.35 KB
proclamation-no-746-2012-insurance-business-proclamation.pdf8.18 KB
proclamation_no_780_2013_money_laundering_and_financing_of_terrorism.pdf30.35 MB
نمایش همه...
አዲሱ የመኖሪያ ቤት ኪራይ ሞዴል ውል.pdf2.62 KB
የፌዴራል መንግሥት ሠራተኞች ረቂቅ አዋጅ ማብራሪያ በጠየቃችሁን መሠረት የተላከ Source: @tikvahethiopia
نمایش همه...
የፌደራል_መንግስት_ሠራተኞች_ረቂቅ_አዋጅ_አጭር_ማብራሪያ_1.pdf4.69 KB
በወንጀል ጉዳዮች የአተረጓጎም ልዩነት ያለባቸው ድንጋጌዎች ላይ ወጥነት ያለው ትርጉም ለማምጣት እንዲቻል የተዘጋጀ የሕግ ማብራሪያ አዘጋጅ፡- ፍትሕ ሚኒስቴር https://t.me/EsubalewAmareLawOffice
نمایش همه...
አከራካሪ_የወንጀል_ሕግ_ድንጋጌዎች_ማብራሪያ_.pdf1.06 MB
የፍትሐብሔር_ሥነ_ሥርዓት_ሕግ_አጭር_ማብራሪያ.pdf1.66 MB
የወንጀል_ቅጣትን_መገደብ_ሕጉና_ተግባሩ.pdf9.16 KB
👍 1
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.