ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
رفتن به کانال در Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
نمایش بیشتر3 301
مشترکین
-324 ساعت
-107 روز
-4130 روز
آرشیو پست ها
#ጥር_18_ለምን_ይከበራል?
በመናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤ/ክ ቅዳሜ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ ዓመታዊ በዓል በጋራ እናክብር
#ቅምሻ
"እማሆይ ወ/ሚካኤል የተኛች መስላ ሁኔታውን ስትከታተል ነበርና እንዳልሰማች እንቅልፍ እንደ ያዘው ሰው ዝም አለች። ሰሚ ያጣችው እማሆይ [ማየ ገነት] ያለ' ኃይሏን አጠራቅማ ቀና ብላ 'ወለቴ ኧረ ወለቴ' አለች በጩኸት። 'እ... ጠራሽኝ?' በማለት ቀና ብላ አየቻት። 'ኧረ መሞቴ ነው፥ እምነት ስጪኝ' ብላ መኝታዋ ላይ ተዘረረች። እማሆይ ወ/ሚካኤል ፈጠን ብላ ከቤቷ ይዛ የመጣችውን ዘንቢል ከፍታ የሆነ የተጠቀለለ ነገር አውጥታ ቆንጥራ ብርጭቆ ውስጥ ጨምራ በጥብጣ 'ከቤት ያመጣሁት እምነት ነው ጠጪው' አለቻት። እማሆይ ማየ ገነት የምትናገረውን ሁሉ ባይኗ ትከታተላት ነበርና 'እቤት ውስጥ ያለው እምነት እያለ ለምን ሌላ?' ብላ የሆነ ነገር ጠረጠረች። ግን ውጋቱ ፋታ ስለ ነሳት 'እምነት እምነት ነው' ብላ የግዷን ተቀበለቻትና ቀመስ ስታደርገው መረራት። የያዘችውን ብርጭቆ ወረወረችውና የቀመሰችው ካፏ ተፍታው መልሳ መኝታዋ ላይ ድፍት አለች።
"ምን መሆንሽ ነው የምታፈሺው? ግዴታ መጠጣት አለብሽ እኮ። ይሄ የማይገኝ እምነት ነው። የአባቴ ጓደኞች ከትልቅ ዘግተው ከሚኖሩ አባት ያመጡለት ነው'ኮ። ሰው 'በየት ባገኘነው?' ይላል። አንቺ ትደፊዋለሽ እንዴ? ወይስ ፀላኤ ያዘሽ? አባቴ ሲነግረኝ 'ሰይጣን ያለበት እንኳን ሊጠጣት እሱ የገባበት ቤት አይገባም' ብሎኛል። ስለዚህ በሽታሽን ንቅል እንዲያደርገው በግድ መጠጣት አለብሽ' ብላ ድጋሚ በጥብጣ በግድ ልታጠጣት ስትሞክር ከውጪ ቤቶች ክፈቱ የሚል ድምፅና በር መንኳኳት ተሰማ። ቶሎ ብላ ወደ አልጋው ውስጥ አስገባችውና 'ማነው? ይግቡ' ብላ በሩን ከፈተች።
ገድለ ምንኩስና፣ እውነተኛ ታሪክ፣ ገገ. 170-171
https://t.me/EagleBooksandStationery1223/224
#ቅምሻ
"እማሆይ ወ/ሚካኤል የተኛች መስላ ሁኔታውን ስትከታተል ነበርና እንዳልሰማች እንቅልፍ እንደ ያዘው ሰው ዝም አለች። ሰሚ ያጣችው እማሆይ [ማየ ገነት] ያለ' ኃይሏን አጠራቅማ ቀና ብላ 'ወለቴ ኧረ ወለቴ' አለች በጩኸት። 'እ... ጠራሽኝ?' በማለት ቀና ብላ አየቻት። 'ኧረ መሞቴ ነው፥ እምነት ስጪኝ' ብላ መኝታዋ ላይ ተዘረረች። እማሆይ ወ/ሚካኤል ፈጠን ብላ ከቤቷ ይዛ የመጣችውን ዘንቢል ከፍታ የሆነ የተጠቀለለ ነገር አውጥታ ቆንጥራ ብርጭቆ ውስጥ ጨምራ በጥብጣ 'ከቤት ያመጣሁት እምነት ነው ጠጪው' አለቻት። እማሆይ ማየ ገነት የምትናገረውን ሁሉ ባይኗ ትከታተላት ነበርና 'እቤት ውስጥ ያለው እምነት እያለ ለምን ሌላ?' ብላ የሆነ ነገር ጠረጠረች። ግን ውጋቱ ፋታ ስለ ነሳት 'እምነት እምነት ነው' ብላ የግዷን ተቀበለቻትና ቀመስ ስታደርገው መረራት። የያዘችውን ብርጭቆ ወረወረችውና የቀመሰችው ካፏ ተፍታው መልሳ መኝታዋ ላይ ድፍት አለች።
"ምን መሆንሽ ነው የምታፈሺው? ግዴታ መጠጣት አለብሽ እኮ። ይሄ የማይገኝ እምነት ነው። የአባቴ ጓደኞች ከትልቅ ዘግተው ከሚኖሩ አባት ያመጡለት ነው'ኮ። ሰው 'በየት ባገኘነው?' ይላል። አንቺ ትደፊዋለሽ እንዴ? ወይስ ፀላኤ ያዘሽ? አባቴ ሲነግረኝ 'ሰይጣን ያለበት እንኳን ሊጠጣት እሱ የገባበት ቤት አይገባም' ብሎኛል። ስለዚህ በሽታሽን ንቅል እንዲያደርገው በግድ መጠጣት አለብሽ' ብላ ድጋሚ በጥብጣ በግድ ልታጠጣት ስትሞክር ከውጪ ቤቶች ክፈቱ የሚል ድምፅና በር መንኳኳት ተሰማ። ቶሎ ብላ ወደ አልጋው ውስጥ አስገባችውና 'ማነው? ይግቡ' ብላ በሩን ከፈተች።
ገድለ ምንኩስና፣ እውነተኛ ታሪክ፣ ገገ. 170-171
https://t.me/EagleBooksandStationery1223
"ሰው ወደሚበዛበትና የዚህን ዓለም ፍርድ ወደሚሰጡ ቦታዎች አለመኼድ ስለማልችል፣ የምመራው ትልቅ የንግድ ድርጅት ስላለኝ፣ ሥራዬ ጥበበ እድ ስለሆነ፣ ጊዜ ስለሌለኝ፣ ትዳር ስላለኝ፣ ልጆችን ስለማሳድግ፣ የቤተሰብ አስተዳዳሪ ስለሆንኩ፣ እኔ የዓለም ሰው ስለሆንኩ መጻሕፍትን ማንበብ አይጠቅመኝም፤ "መጻሕፍትን ማንበብ በገዳም ለሚኖሩ መነኮሳት ነው" ብለህ አትንገረኝ። "አንተ ሰው! ምን ማለትህ ነው?" "ብዙ የዚህ ዓለም አሳብ ስላለብኝ መጻሕፍት ማንበብ ለእኔ አይደለም" ትለኛለህን? እንዲያውም ልንገርህ! አንተም ስማኝ! ከእነዚያ መነኮሳት ይልቅ ማንበብ ያለብህ አንተ ነህ:: መጻሕፍትን በብዛት ማንበብ የሚገባቸው ብዙ የዓለም አሳብ ያላቸው ሰዎች እንጂ በምግባር በትሩፉት የተጠመዱ መነኮሳት አይደሉምና።
~ የክርስቲያን መከራ
https://t.me/EagleBooksandStationery1223/223
"እንደ ኦርቶዶክሳውያን ወላጆች፥ ዓላማችን ፍጹማን ወላጆች መኾን አይደለም። ይህ የማይቻል ነውና። ... ልጆች የሚፈልጉት [እና የሚያስፈልጋቸው] እንደ እነርሱ የሚሳሳቱና [ከስሕተታቸው እየተማሩ] የሚያድጉ ወላጆችን ነው።"
#ትንሿ_ቤተክርስቲያን፥ ገጽ 447
#ቅምሻ
"ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ጉዞ ሦስት ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በአንድ ጊዜ ተከናውነውለት የሚጀመር ሲኾን፥ እነርሱም፡-
፩) ምሥጢረ ተክሊል፣
፪) ምሥጢረ ሜሮንና
፫) ምሥጢረ ቁርባን ናቸው፡፡
ጉዞው ከእነዚህ ምሥጢራት ውጪ ሊታሰብ አይችልም - ትዳራችንን ትንሿ ቤተ ክርስቲያን የሚያሰኘውም ይህ ነው፡፡ ...
በቅብዓ ሜሮን ስንታተም፡-
🔸 አንደኛ፥ ይህን ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት እንዴት መኖር እንዳለብን የሚያሳስብ፣ እርሱን ስንኖር ኃይል ጽንዕ የሚኾነንን ጸጋ መቀበላችን ነው፡፡
🔸ኹለተኛ፥ በትንሿ ቤተ ክርስቲያን ለምንፈጽማቸው የድኅነት አገልግሎቶች ካህናት ኾነን ስንሾም ነው፡፡ በትንሿ ቤተ ክርስቲያን የምናገለግል ትናንሽ ካህናት እንድንኾን ነው፡፡
በንሥር መጻሕፍትና የጽሕፈት መሣሪያ ታገኙታላችሁ።
#ቅምሻ
"ኦርቶዶክሳዊ የትዳር ጉዞ ሦስት ምሥጢራተ ቤተ ክርስቲያን በአንድ ጊዜ ተከናውነውለት የሚጀመር ሲኾን፥ እነርሱም፡-
፩) ምሥጢረ ተክሊል፣
፪) ምሥጢረ ሜሮንና
፫) ምሥጢረ ቁርባን ናቸው፡፡
ጉዞው ከእነዚህ ምሥጢራት ውጪ ሊታሰብ አይችልም - ትዳራችንን ትንሿ ቤተ ክርስቲያን የሚያሰኘውም ይህ ነው፡፡ ...
በቅብዓ ሜሮን ስንታተም፡-
🔸 አንደኛ፥ ይህን ኦርቶዶክሳዊ ሕይወት እንዴት መኖር እንዳለብን የሚያሳስብ፣ እርሱን ስንኖር ኃይል ጽንዕ የሚኾነንን ጸጋ መቀበላችን ነው፡፡
🔸ኹለተኛ፥ በትንሿ ቤተ ክርስቲያን ለምንፈጽማቸው የድኅነት አገልግሎቶች ካህናት ኾነን ስንሾም ነው፡፡ በትንሿ ቤተ ክርስቲያን የምናገለግል ትናንሽ ካህናት እንድንኾን ነው፡፡
https://t.me/EagleBooksandStationery1223/218
#"ጾመ ድጓ ዘቅዱስ ያሬድ" መጽሐፍ
****
የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ታላቁ ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ለቤተ ክርስቲያናችን ካበረከታቸው መጻሕፍት መካከል ጾመ ድጓ አንዱ ነው።
በንሥር መጻሕፍትና የጽሕፈት መሣሪያ ታገኙታላችሁ።
አልተዘዋወረችም 2ተኛ እትም በንሥር መጻሕፍት ቤት ታገኙታላችሁ።
♦ እንኳን ለቃና ዘገሊላ በዓል አደረሳችሁ አደረሰን 🤲🙏
💚💛❤️
የአመት ሰው ይበለን ፤ ሃገራችንን ሰላሟን ያብዛልን !
እነሆም ከዋነኞቹ አለቆች አንዱ #ሚካኤል ሊረዳኝ መጣ ፣ ት. ዳ. ፲ ፥ ፲፫
የቅዱስ ሚካኤል ረድኤት በረከት ይደረብን ፣ ጥበቃው ያብዛልን 🤲🙏
እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሰን፤ በዓሉ ምሥጢረ ሥላሴ የተገለጠበት፥ዳግመኛ ከውሃ የተወለድንበት፥የዕዳ ደብዳቤያችን የተደመሰሰበት ዐቢይ በዓል ነውና፤ እግዚአብሔር ለሀገራችን ኢትዮጵያ ሰላምን ለሕዝባችን አንድነትን ይላክልን መልካም በዓል ይሁንልን።
የሦስቱ ታላላቅ ቅዱሳን የአቡነ አባለ ክርስቶስ፤ የአቡነ ዐቢየ እግዚእ እና የአቡነ ሰይፈ ሚካኤል (3ቱም በ19 ታስበው ይውላሉ) ገድላቸው በጋራ ታትሞ ለደብረ መድኀኒት ዓዲ አልሓትያ አቡነ አባለ ክርስቶስ ገዳም የተሰጠ ሲሆን መጻሕፍቱን በንሥር መጻሕፍት ቤት ያገኙታል።
ጎንደር : ደብረ - ብርሐን ቅድስት ሥላሴ ቤተ - ክርስትያን
#Ethiopia | ይህ ቤተ - ክርስትያን ጎንደር ደብረ - ብርሐን ቅድስት ሥላሴ ይባላል። በውስጡ በያዛቸው የስዕል ጥበባት በምድሪቱ ላይ ከሚገኙ ታላላቅ ቅርሶች አንዱ ነው። ደብረብርሐን ስላሴ በ17ኛው እና በ18ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ኢትዮጵያ ውስጥ ታላላቅ ነገስታት በነበሩት አባት እና ልጅ አማካይነት በቅብብሎሽ እየጎመራ የመጣ ነው። አፄ ዳዊት እና አዲያም ሰገድ ኢያሱ ዘመናቸውን ያበለፀጉበት ኪነ ሕንጳ ነው።
በደብረ ብርሃን ሥላሴ ውስጥ ጣሪያው እና ግድግዳው በሙሉ ስዕሎች ናቸው። አፍሪካዊ ኢትዮጵያዊ ስዕሎች። ኢየሱስ ክርስቶስን ኢትዮጵያዊ መልክ ሰጥተውት ስለውታል። እናቱ ማርያም ኢትዮጵያዊ ንቅሳት አላት። ፈትልም ትፈትላለች። መላዕክት ጭንቅላት እና ክንፍ ተሰርቶላቸው ይታያሉ። መላዕክት ጦር ጎራዴ ታጥው ኢትዮጵያን ይጠብቃሉ። ስዕሎቹ ዘላለም እንዳበሩ እንዳብረቀረቁ ዛሬም አሉ። ቀለማቱ የተላቆጡት በነጭ ሽንኩርት እና በዕንቁላል በነጩ ፈሳሽ ነው። እናም ያበራሉ።
የሥነ-ስዕል ተመራማሪዎች First Gonderian Art እና Second Gonderian Art እያሉ በአለም የስነ ጥበባት ትምህርት ቤቶች ውስጥ ያስተምሩባቸዋል።
ታሪካቸው ተወስቶ አያልቅም። በሐገሬ ታሪክ በእጅጉ እንድንኮራ ከሚያደርጉኝ የሰው ልጅ የአዕምሮ እና የመንፈስ ግኝቶች መካከል ዋነኛው ደብረብርሐን ሥላሴ - ጎንደር ነው።
መልካም በዓል!!
“ቃልኪዳን በነገረ ድኅነት” (በዲ/ን ያረጋል አበጋዝ)
ቆየት ካሉ ነገር ግን እንደ መጽሐፉ ብስለት ብዙዎች እጅ ካልገቡ፣ በጥልቅ ትንታኔ ከተዘጋጁ መጻሕፍት አንዱ የዲ/ን ያረጋል አበጋዝ “ቃል ኪዳን በነገረ ድኅነት” በሚል ርእስ የተዘጋጀው መጽሐፍ ነው፡፡ ይህን መጽሐፍ ያነበቡ አንባቢያን ትልቅ መንፈሳዊ መረዳትን ስለሚጠይቀው ስለ ቃል ኪዳንና ነገረ ድኀነት በቂ ግንዛቤ አግኝተውበት እምነታቸውን በማጽናት ከክርስቶስና ከቅዱሳን ጋር ተጣብቀው በምድር ሰማያውያንን መላእክትን መስለው ተዋሕዶዊ አኗኗርን ገንዘብ አድርገው ተመላልሰውበታል፡፡ ይህ መጽሐፍ ቅዱሳን ከአምላካቸው ጋር ያደረጉትን ቃልኪዳንና በተሰጣቸው ቃል ኪዳን እኛ እንዴት መጠቀም እንዳለብን የሚተነትን ብቻ ሳይሆን፣ ነገረ ድኅነትን ተተርሰው ለሚነሡ ጥያቄዎች መልስ የሚሰጥ፣ ተግባራዊ ምልልሳችን በክርስትና ሕይወታችን ውስጥ ያለውን ፋይዳ፣ ስለንስሐና ሒደቶቹም በቂ ግንዛቤ እንዲኖረን ያበቃናል፡፡ መጽሐፉ በሰባት ምዕራፎች የተከፈለና በ188 ገጾች ተሰንዶ ለአንባቢያን በሚመች መልኩ የተዘጋጀ ግሩም መጽሐፍ ነው፡፡ ገዝታችሁ አንብቡት ትጠቀሙበታላችሁ፡፡
መጽሐፉን:- በንሥር መጻሕፍት ቤት ያገኙታል።
አጋዕዝት አለም ቅድስት ሥላሴ ምህረትና ቸርነት አይለየን።
የዲያቆን ያረጋል አበጋዝ መጽሐፍት ድጋሜ ሕትመት ይዞላችሁ ቀርቧል።
፩_ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱና ትምህርቱ እና
፪_ የቅዱስ አትናቲዎስ ሐዋርያ ትምህርቱና ሕይወቱ
በንሥር መጻሕፈት ቤት ያገኙታል።
የዲያቆን ያረጋል አበጋዝ መጽሐፍት ድጋሜ ሕትመት ይዞላችሁ ቀርቧል።
፩_ቅዱስ ዩሐንስ አፈወርቅ ሕይወቱና ትምህርቱ እና
፪_ የቅዱስ አትናቲዎስ ሐዋርያ ትምህርቱና ሕይወቱ
በንሥር መጻሕፍት ቤት ያገኙታል።
ግዜው የርአምሞ ነው መጻሕፍቶችን እናንብ ስናንብ እራሳችንን ዕናያለን ስናነብ ሙሉ ሰው እንሆናለን።
በንሥር መጻሕፍትና የጽሕፈት መሣሪያ ያገኙታል (Eagle Books and Stationery) ፦ስልክ 0913083816 / 0931144330 ምኒልክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጀርባ ማይክሮሊንክ ዩንቨርስቲ ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ማኅበር ፊት ለፊት
ልጄ እያለችህ የድንግልና ወተት ታጠባሃለች። በዕቅፏ ያለኸውን አንተን በክንዶቿ ሳለህ በባሕርይ አባትህ ዕቅፍ ታይሃለች። ያን ጊዜም አምላኬ እያለች ትሰግድልሃለች። ወተት የምታጠባህን ታመሰግንሃለች። የምትልክህን ትሰግድልሃለች። እናቴ ትላታለህ፤ ፈጣሪዬ ትልሃለች።
እንደ ድንግል ያንተን ባሕርይ ያወቀ ማን ነው? እናት ልጇን ስታመሰግን የማያውቁ ቅዱሳን መላእክት ተደነቁ። እርሱን በባሕርይው ማመስገናችንን ሳናስቀር እኛ እና እነርሱ ደግሞ አንቺን እናመሰግንሻለን።
የራበንን የምንበላውን እንጀራ ወልደሽልናልና። የጠማንን የሕይወት መጠጥ አፍልቀሽልናልና። ድንግል ሆይ አለን ምስጋና!
መልካም በዓለ ልደተ እግዚእ ይኹንላችሁ !!!
አልተዘዋወረችም
አዲስ መጻሕፍት በገቢያ ላይ ካሁን በፊት በነ ደክተር አሸብር ዙበይዳ ከለታት ግማሽ ቀን የምናውቀው አሌክስ አበርሃም አሁን ደግሞ አልተዘዋወረችም በሚል ይዞልን መቷል።
በንሥር መጻሕፍትና የጽሕፈት መሣሪያ (Eagle Books and Stationery) ፦ስልክ 0913083816 / 0931144330 ምኒልክ አደባባይ መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ጀርባ ማይክሮሊንክ ዩንቨርስቲ ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ማኅበር ፊት ለፊት
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
