ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
رفتن به کانال در Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
نمایش بیشتر3 303
مشترکین
-224 ساعت
-107 روز
-3830 روز
آرشیو پست ها
+1
# አቡሻክርና ፍካሬ ፊደል #
እንደ ዳይኖሰር ሊጠፉ
የተቃረቡ የቤ/ክርስቲያኗ ሀብቶች ናቸው።
መምህራችን መምህር ዘለዐለም ሐዲስ ፤
የ፬ጉባኤያት ምክትል መምህርና የደብሩ ስብከተ ወንጌል ኀላፊ ዳይኖሰራችን ከጥፋት ስለታደጉት ከልብ እናመሰግነዎታለን ።.........................።
በተመሳሳይ
ፋኖ አቋቋም ፤ ቤተ ማርያም አቋቋም ፤ ሰደድ ኲላ ቅዳሴ፤ አጫብር አቋቋም ፤ ተጉለቴ ፤ ቆሜ ድጓ ፤ ተክሌ አቋቋቋምን የመሳሰሉ ፤ ከቅኔ ወገን ደግሞ፤ ያ የቀደሙሞው ብሉይና ሐዲስን የሚያገናኘው ፣ የነ አድማሱ ጀምበሬ የድማዎቹ፤ የነ የኔታ ወልደ ሰንበት የወሎዎቹ፤ የነ የኔታ ክፍለ ዮሐንስ የጎንደሮቹ፤ የነ የኔታ ናሁ ሠናይ የመቀሌዎቹ፤ የነ የኔታ አካለ ወልድ የቦሩዎቹ፤ የነ እሜቴ ገላነሽ የጎጃሞቹ ቅኔ እየጠፋ በላ ጠጣ ፤ ሄደ መጣ ፤ አየሩ በረረ ፣ መኪናው ተሰበረ ወዘተ የሚል ቅኔ የምንቀኝ ኾነናል ። ይህም እየቀነሰ መሄዱ ነው።
ታድያ ይህ አቡሻክርም እንደ ዳይኖሰር ሊጠፋ ትንሽ ሊቀረው ሲል መኖሪያውንና አኗኗሩን በሚገባ ጠቁመው አሳይተዋልና በእጅጉ እናመሰግነዎታለን። ከአኹን በኋላ ጫካውን ካሳዩን አድኖ መያዝማ የኛ ድርሻ ነው። በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
#አሐቲ_ድንግል!
መርሐ ግብሩን ዲ/ን ሄኖክ ኃይሌ ይመራዋል!
ቀሲስ ግርማ ባቱ እና ዶ/ር አባ ኃይለገብርኤል ዳሰሳውን ያቀርባሉ።
የኔታ ሊቀ ሊቃውንት ዕዝራ ያስተምራሉ።
የኔታ ርእሰ ሊቃውንት አባ ገብረ ኪዳንም ....!
ይታደሙ!
ዮሐንስ አፈ ወርቅ ተወዳጅ ሥራ የኾነው የማቴዎስ ወንጌል ቅጽ ፪ መጽሐፍ በቀጣይ ሳምንት ይወጣል!
መምህር ዘለዓለም ሐዲስ (የጎንደር መንበረ መንግሥት መድኃኔ ዓለም የአራቱ ጉባኤያት ምክትል መምህርና የደብሩ ስብከተ ወንጌል ኃላፊ) ያሳተሙት መጽሐፈ አቡሻክር በገበያ ላይ ዋለ።
የመጽሐፍ ምርቃት መርሐ ግብር ላይ ይሳተፉ።
-የአባ ገብረ ኪዳን ግርማ "አሐቲ ድንግል" የተሰኘ መጽሐፍ ቅዳሜ ጥቅምት 2 በቦሌ መድኃኔ ዓለም ቤተክርስቲያን ይመረቃል። ስለዚህ የመጽሐፍ ምርቃት መርሐ ግብር ላይ ይሳተፉ።
-ሰዓት 7:30
+1
"ዮም መስቀል ተሰብሐ፤ ዛሬ መስቀል ተመሠገነ፤" ቅዱስ ያሬድ
***
እንኳን ለብርሃነ መስቀሉ አደረሰን!
Repost from ማራናታ
✍️በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ
" ቅዱሳት መጻሕፍት የአእምሮ ምግብ ናቸው። ሆድን አጥግቦ አእምሮን ባዶ ማድረግ የመንፈስ ረሀብ ያመጣል። ሆድ ሲራብ አእምሮ ሆድ ይሆናልና ውስጣቸው እየሞተ ያሉ ሰዎች ማሳያው ማንበብ ማቆማቸው ነው። መጻሕፍት ስትገዛ የምትከፍለው ገንዘብ ለወረቀቱ እንጂ ለአሳቡ አይደለም። በምድር እጅግ ደግ የሚባሉት እውቀታቸውን ሳይሰስቱ የሚሰጡ ጸሐፍት ናቸው። የኪስ ምጽዋት የሚሰጡትን እያከበርህ የነፍስ ምጽዋት የሚሰጡትን ደራስያን አትናቅ። ጌጥ ለመግዛት የማይከራከር መጽሐፍ ለመግዛት የሚከራከር ደካማ ትውልድ ነው። ከሳንሱር ሕጎች በላይ የሚያሳዝነው የማይጽፉ ሰዎች የሚጽፉትን መተቸታቸው ነው። የሐሳብ ክብር በሌለበት የሀገር ዕድገት አይታሰብም። የራስህንና የሰዎችን ዋጋ የሚያሳውቁህ ደገኛ መጻሕፍት ናቸው።"
+1
እነዚህ በድጋሚ የታተሙ
ጽዋዔ እና
ምዕላደ ጥበብ ቁጥር አንድ
በግዮን መጻሕፍት መደብር በልዩ ቅናሽ ታገኙታላችሁ።
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት
ጽዋዔን በመደብራችን በልዩ ቅናሽ
በግዮን መጻሕፍት መደብር የተለያዩ
መጻሕፍቶችን ዘወትር በልዩ ታገኛላችሁ
መጽሐፍ ቅዱስ፣ ድርሳናት ፣ ገድላት፣
መዝሙረ ዳዊት፣ መዝገበ ጸሎት፣
በአጠቃላይ የታሪክና መንፈሳዊ
ነባር ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍቶችን ያገኛሉ
አድራሻ ፦መናገሻ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ
በምዕራብ በር ማኅበረ በኵር ሰንበቴ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።
+1
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት
ለረጅም ጊዜ ከገበያ ጠፍቶ የነበረውና ተወዳጁ ምዕላደ ጥበብ ቅጽ ፩ መጽሐፍ ድጋሚ ታትሞ ወቷል።እንዲሁም ቁጥር ፪ በመጻሕፍት መደብራችን እየተሸጠ ይገኛል።
በግዮን መጻሕፍት መደብር የተለያዩ
መጻሕፍቶችን በልዩ ቅናሽ ታገኛላችሁ።
ይጎብኙን - ደርዛቸውን የጠበቁ አዳዲስና
ነባር ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍቶችን ያገኛሉ!
ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።
"ቀኑ እስኪነፍስ ጥላውም እስኪያልፍ ድረስ፥ ወደ ከርቤው ተራራ ወደ ዕጣኑም ኮረብታ እሄዳለሁ" መኃ. 4:6
በየዓመቱ የእኛን ሕይወት ስታድስ የኖረችዋ የግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ጥንታዊ ሕንፃ በዘመን ብዛት እድሳት ሊደረግላት ነው:: ይህንን አስመልክቶ ነገ ነሐሴ 26 ከቀኑ 7:00 ጀምሮ የመጀመሪያው እርከን ፕሮጀክት ይፋ የሚደረግበት ልዩ ጉባኤ ይካሔዳል:: የግሸን ውለታም መንፈሳዊ ትውስታም ፍቅርም ያለበት ሁሉ ጊዜው አሁን ነው::
|••••••••••••••••••••••••••••••••|
*ቤትሽን እንድንሠራ ፍቀጅልን!*
|••••••••••••••••••••••••••••••••|
ነሐሴ 26/2016ዓ/ም
•ከቀኑ 7 ሰዓት ጀምሮ
•ቦታ:- በአ/አ ደብረ አሚን አቡነ ተክለ ሃይማኖት ቤተክርስቲያን ስብከተ ወንጌል አዳራሽ፤
ስለ ግሸን ደብረ ከርቤ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን እንድንነጋገር "ልዩ መንፈሳዊ የኪነ-ጥበብ ዝግጅት" ተዘጋጅቷል።
•የመግቢያ ዋጋ *በነጻ*
#ዜና_መጽሐፍ
የአቡነ ሺኖዳ መጻሕፍት ለኢትዮጵያ ያስተዋወቀ
መምህር አያሌው ዘኢየሱስ ያለመታከት በውብ ቋንቋ እና ቀለል ባለ የቃላት አጠቃቀም መንፈሳዊ ስብከቶችን በመጻሕፍት መልክ ተርጉመው ለገበያ አቅርበውልናል ከዚህ በፊት 44 መጻሕፍት ተርጉመው አቅርበውልናል እነዚህ ሁለት መጻሕፍት በተጨማሪ ለገበያ ቀርበዋል ታነቧቸው ዘንድ ግብዣችን ነው።
**ስለክርስቶስ ልደት
**እንዴት ልወስን እችላለሁ?
እነዚህን ሁለት መጽሐፍቶችን
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
+1
#ዜና_ድጋሚ_ኅትመት
ለረጅም ግዜ ከገቢያ ጠፍቶ የነበረ
ቀደም ሲል በተስፋ ገብረ ሥላሴ ዘብሔረ ቡልጋ ታትሞ የነበረ ገድለ ተክለሃይማኖት ተአምረ ተክለሃይማኖት መልክአ ተክለሃይማኖት በግዕዝና በአማርኛ።
በግዮን መጻሕፍት መደብር የተለያዩ
ደርዛቸውን የጠበቁ አዳዲስና ነባር ኦርቶዶክሳዊ መጻሕፍትን ያገኛሉ!
ለበለጠ መረጃ በ0913083816 ይደውሉ።
t.me/GhionBooksGhionBookStore1623
#ቅምሻ
"በዚህ ዓለም ገዢ የኾኑ ስዎች የማሰር ሥልጣን አላቸው፤ ማሰር የሚችሉት ግን ሥጋን ብቻ ነው፡፡ የካህናት የማስር ሥልጣን ግን ነፍስን ጨምሮ ሰማያትንም ዘልቆ የሚገባ ነው፡፡ ካህናት እዚህ ታች የሚያደርጉትን እግዚአብሔርም በላይ ያጸድቀዋልና፤ የአገልጋዮቹን ውሳኔ ጌታቸውም ያጸናዋልና፡፡ “ለእለ ኀደግሙ ኃጢአተ ይትኀደግ ሎሙ ወለእለሰ ኢጎደግሙ ኢይትኀደግ ሎሙ - ኃጢአታቸውን ይቅር ያላችኋቸው ኹሉ ይቀርላቸዋል፤ የያዛችሁባቸውም ተይዞባቸዋል" በማለት ኹሉንም ሰማያዊ ሥልጣን ሰጥቷቸዋልና (ዮሐ.20፡23)። ታዲያ ከዚህ የሚበልጥ ምን ሥልጣን ይኖራል? “አብ ፍርድን ኹሉ ለወልድ ሰጥቶታል" (ዮሐ.5፡22)፡፡ እዚህ ላይ ግን ወልድ ፍርድ ኹሉ ለካህናት ስጥቷቸው እናያለን፡፡ ልክ ወደ ሰማየ ሰማያት እንደ ወጡ፣ የሰዋዊ ባሕርይ ወሰንም አልፈው እንደ ኼዱ፤ እኛንም ከሚማርከን የሥጋ አምሮት አርነት እንደ ወጡ ኾነው ወደዚህ ክብር ተጠርተዋልና፡፡"
ቅዱስ ዮሐንስ አፈ ወርቅ፥ በእንተ ክህነት፥ ድርሳን ፫ ቁጥር ፭
___
ግዮን መጻሕፍት መደብር!
አድራሻችን፦ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ በምዕራብ በር
+2
#ድጋሚ_የታተሙ_ገድላት
፩. ገድለ አቡነ ዘርዐ ቡሩክ
፪. ገድለ አቡነ አረጋዊ ወአቡነ ጰንጤሌዎን
፫. ገድለ አባ ሳሙኤል ዘዋልድባ
በግዮን መጻሕፍት መደብር ዘወትር በልዩ መጽሐፍቶችን እናቀርባለን።
📚 #ከማራኪ_መጽሐፍ_ገፆች📚
🔥‹‹በዕለት ከዕለት ኑሯችን ውስጥ የሚደርስብንን ሁሉ ነገር መቆጣጠር አንችልም፤ ነገር ግን ለደረሰብን ጉዳይ ምላሽ የምንሰጥበትን መንገድ መቆጣጠር እንችላለን። አንዳንዴ ሕይወት የቤታችን በር በውስጥ በኩል ትቆልፍና ውጭ ላይ ገልብጣ ታሰጣናለች። ዝናብና ፀሐይ፣ ውርጭና ብርድ፣ ችግርና መከራ እንዲፈራረቁብንም ታደርጋለች። መሰል ሁኔታዎች ሲፈጠሩ የምናሸንፈው ተስፋን ስንቅ፣ ፅናትን ምርኩዝ፣ እምነትን መሰላል እንዲሁም ትዕግሥትን ጋሻ ጦር በማድረግ ነው።
🔥በሕይወታችን ውስጥ ግጭቶች በጠነከሩ ቁጥር የምናገኘው ድል ይበልጥ ክብር ያለው ይሆናል። ብዙ ጊዜ እንደ እንቅፋትና መሰናክል የምንመለከታቸው ነገሮች ታላቅ የለውጥ እድል የሚፈጥሩልን መሸጋገሪያ ድልድዮች ናቸው። ተግዳሮቶች አዲስ የስበት ማዕከል እንድንፈልግ የሚያስገድዱን ስጦታዎች ናቸው። ሁሌም ራሳችን ከትናንት የተሻልን ለማድረግ ስንጥር በዙሪያችን ያለው ነገር ሁሉ የተሻለ እየሆነ ይመጣል።
🔥ለስኬታማ ሕይወት ትልቁ ሚስጥር ተሰጥኦን መርምሮ ማወቅና በእርሱ ጥላ ስር ፈተናዎችን ተቋቁሞ መሽከርከር ነው። ስለዚህ በቅድሚያ ማን እንደሆን ራሳችን መዝነን አውቀን ያን ሰው በትክክል ልንሆን ይገባል። ነፍሳችን በዚህ ፕላኔት ላይ ያስቀመጠችው ያን እንድንሆን ነው። ያንን እውነት እናግኝ፣ ያንን እውነት በጥልቀት እንረዳ፣ ያንን እውነት በተግባር እንኑር፣ ካለንበት እንጀምር፣ ያለንን እንጠቀም፣ የምንችለውን ሁሉ እናድርግ። ቀስ በቀስ ሁሉም ነገር ወደ እኛ ይመጣል››
#ኅብር
ከደራሲ መምህር በረደድ ገዳሙ
የደራሲ መምህር በረደድ ገዳሙ አራት መጻሕፍት በገበያ ላይ
#ኅብር
#ሉባር 5ተኛ ዕትም
#ስሙር 2ተኛ ዕትም
ዘወትር በልዩ ቅናሽ በግዮን መጻሕፍት
+2
#በገበያ_ላይ_ዋለ!
ከሳይንስ ጋር የተገናኙ ፍልስፍናዊ ጉዳዮች ለክርስቲያኖች ያን ያህልም አስፈላጊነት የሌላቸው መስለው የሚታዩዋቸው ወገኖች ይኖሩ ይሆናል። ሳይንስ የሚመለከተው ይህን ዐለም ነው፡ ይህ ዐለም ደግሞ ጊዜያዊና ኃላፊ ነው፤ ታዲያ ክርስቲያኖች ኃላፊና ጠፊ ስለሆነው ስለዚህ ዐለም ምን ያስጨንቃቸዋል? የሚሉ ይኖሩ ይሆናል። ሳይንስ ለመንፈሳውያን ሰዎች ምን ያደርግላቸዋል? ሳይንስንስ ከሃይማኖት ጋር ምን ያገናኘዋል? የሚሉ ወገኖች አይታጡ ይሆናል።
እውነታው ግን ከዚህ የተለየ ነው። ተወደደም ተጠላም የምንኖርበትን ዐለም ለመምራት የሚሻኮቱት እሳቤዎች የየራሳቸው ፍልስፍናዊ መነሻ ያላቸው ናቸው። በአዎንታም ይሁን በአሉታ ልዩ ልዩ አቋሞቻችንና አመለካከቶቻችን የሚቀረጹት ከሳይንሳዊ ቲዎሪዎችና እሳቤዎች አንጻር የሚሆንባቸው ብዙ ሁኔታዎች አሉ = በሳይንስና በፍልስፍና ስም የሚናኙ ዘርፈ-ብዙ የሆኑ ርእዮተ ዐለሞች በየጊዜው ይሰበካሉ፣ እነዚህ የተለያዩ ፍልስፍናዊ አቋሞችም ዐለምን ወደየራሳቸው አመለካከት ለማስገባት ይራኮታሉ።.....
(ከመጽሐፉ መቅድም የተቀነጨበ)
____
መጽሐፉ በመደብራችን እየተሸጠ ይገኛል!
አድራሻችን፦ ገነተ ጽጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ በምዕራብ በር ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት
ለበለጠ መረጃ 0913083816 ላይ ይደውሉ
የምንኖርበትን ሳይንሳዊ ዓለም በክርስትና ዓይን የሚመረምር እና ትክክለኛ ሚዛናዊ እይታን የሚሰጥ ድንቅ መጽሐፍ ነው። የታላቁ መ/ር ያረጋል አበጋዝ
አዲስ መጽሐፍ በገቢያ ላይ
በግዮን መጻሕፍት መደብር ታገኙታላችሁ።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
