ፍኖተ መጻሕፍት 📚FinoteBooks1623 ➮አድራሻ አዲስ አበባ ፒያሳ ገነተ ፅጌ ቅዱስ ጊዮርጊስ ቤተክርስቲያን ማኅበረ በኩር ሰንበቴ ፊት ለፊት ለበለጠ መረጃ ፦በ0913083816 ይደውሉ።
رفتن به کانال در Telegram
📚ፍኖተ መጻሕፍት @finoteBooks1623 ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን። [ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?] ይደውሉልን!📞፦0913083816 t.me/FinoteBooks1623
نمایش بیشتر3 310
مشترکین
-324 ساعت
-87 روز
-3530 روز
آرشیو پست ها
Repost from የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
📜ወይቤሉ በበይናቲሆሙ ፥ አኮኑ ይነድደነ ልብነ ፥ ዘከመ ይነግረነ በፍኖት ፥ ወይፌክር ለነ መጻሕፍተ!📖
«እርስ በርሳቸውም፦ “በመንገድ ሲናገረን መጻሕፍትንም ሲከፍትልን ልባችን ይቃጠልብን አልነበረምን?” ተባባሉ»
[ሉቃ ፳፬፥፴፪]
📚#የበርሃ_ምንጮች📚
[ማላንካራውያን]
.....ኢትዮጵያውያን ወላጆችም ልክ እንደ ማላንካራውያን የዛሬ ሕፃናት የነ አባቶች፣ የዛሬ ሕፃናት የነገ ሀገር መሪዎች፣ የዛሬ ሕፃናት የነገ ካህናት ጳጳሳት መሆናቸውን ተረድተን ልጆቻችን እንዲሆኑ የምንመኘውን የምንፈልጋትን ኢትዮጵያ እና ቤተክርስቲያንን ለማየት እንድንችል ዛሬ ላይ ሆነን ነገን በጋራ ለልጆቻችን እንሥራላቸው፡፡ ሥራችንን ከቤታችን እንጀምር። ቢያንስ የወለድናቸውን ልጆች የእግዚአብሔር እንዲሆኑ እናድርጋቸው እኔ ካየሁት እውነት በመነሳት ይህንን የማትጊያ መጽሐፍ ለነገይቱ ቤተክርስቲያን እና ልጆቿ ይጠቅማል ብዬ ሳበረክት እንደመነሻ ይሆን ዘንድ እንጂ ከዚህ የተሻለ ሥራ ይዘው የሚቀርቡ ወንድሞችና እህቶች እንደሚኖሩ ሙሉ እምነት አለኝ፡፡ የተወደዳችሁ አንባብያን መጽሐፉን ስታነቡት የአጻጸፍ ግድፈትም ሆነ ሌላ ክፍተቶችን ካገኛችሁ የእኔ የጸሓፊው ድክመት እንጂ የማንም አለመሆኑን በቅንነት እንድትረዱኝ እጠይቃለሁ ።
[✍️ ጸሐፊው]
➲ማሳሰቢያ የመጽሐፉ ሙሉ ገቢ ለቤተክርስቲያን የተደረገ ሲኾን በኹለት ወገን የምንጠቀምበት መጽሐፍ ነው..!
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚#ኅብረ_ሥርዐት
➥ዘመናችን ሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን እጅጉን ፈተና ላይ የወደቀበት፤ የቤተ ክርስቲያን ሥርዐቷ ባለቤት ያጣበት ጊዜ መሆኑን መናገር ለቀባሪ የማርዳት ያህል ነው። ነገሩ ሲከፋ ደግሞ የቤተ ጉባኤና የቤተ ክርስቲያንን የሥርዐት መጻሕፍት ጠቅሶ ማስተማር የሚያሳፍር የሚመስልበት ደረጃ ላይ ደርሰናል። "ጸሐፊ" እና "ሰባኪ" የሚል ስም ተሸክመው ፍትሐ ነገሥትን የመሰሉ የሥርዐት መጻሕፍትን ለመጥቀስ እንኳ ፍላጎት የሌላቸው "አገልጋዮች" እጅግ ብዙ ናቸው። ይህ ደግሞ ምእመናንን ለእግዚአብሔር ሥርዐት ግዴለሽ እንዲሆኑ አድርጓል። በውጤቱም ክርስትና ከተግባር ቅድስና ይልቅ ስብከትና ጽሑፍ ብቻ እንዲሆን አስገድዷል። ስለዚህም እንደዚህ ያሉ የሥርዐተ ቤተ ክርስቲያን መጻሕፍት በእጅጉ ያስፈልጉናል። ይህ መጽሐፍ ኹሉንም የቤተ ክርስቲያኗን ሥርዐቶች ለማካተት ይዘቱ፣ መጠኑ ባይፈቅድም ወሳኝ የሚባሉትን ነጥቦች በጥያቄና መልስ እያሰናሰለ ይዟል። ትኩረቱን ደግሞ በተለይ የዘመናችን የሥርዐት ክፍተት የሚታይባቸው የቅዳሴ፤ የቤተ ክርስቲያን ዙሪያና መሰል ጉዳዮች ላይ አድርጓል። ጸሐፊው፦ መምህር አብርሃም ከልጅነታቸው ተምረው በዜማ፤ በቅኔና በመጻሕፍተ ትርጓሜ የበሰለ አእምሮ ከጥሩ ብዕር ጋር ያላቸው ናቸውና ለዚህ የመጀመሪያ የጽሑፍ ሥራቸው መርቀናቸዋል። መሰል መጻሕፍትን ከመንፈስ ቅዱስ እርዳታ የተነሣ ከትበው ያበረክቱልናል የሚል ተስፋ አለን፡
[ዲያቆን ዮርዳኖስ ]
◉ስንንጠቁም ለንባብ ስንመርጥ ከምንኮራባቸው መጻሕፍት መካከል አንዱ ነው አዘገጃጀቱም ለአንባቢ የሚገባና ቀላል ነው፤ ጸሐፊውን መርቀናል፥ አንብባችሁ ተጋሩን!
📚ፍኖተ መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
t.me/FinoteBooks1623
📚#ሦስቱ_መጻሕፍተ_መነኰሳት
#በተስፋ_ገብረሥላሴ_ዘብሔረ_ቡልጋ የተዘጋጀ....
...#ታሪክ ፤ የሙሴ ፡ ጸሊም ፡ ጌቶቹ ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ያመልኩ ፡ ነበር ፤ እነዚያ ፡ ሙተው ፡ ለልጆቹ ፡ ይገዛል ልጆቹም ፡ ፀሐይ ፡ ጨረቃ ፡ ያመልካሉ ፡ ከዕለታት አንድ ፡ ቀን ፡ ከባልንጀሮቹ ፡ ጋራ ፡ ሊሠርቁ ፡ ሊቀሙ ፡ በረኃ ፡ ለበረኃ ፡ ሲሄዱ ፡ ዋዕየ ፡ ፀሐይ ጸናባ ቸው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ ሳለ ፡ ቀና ፡ ብሎ ፡ ፀሐይን፡ ስትባክን ፡ አይቶ ፡ አሁን ፡ ይች ፡ ፀሐይ ፡ ምን ፡ ምላክ ፡ ናት ፤ አምላክስ ፡ የኔ ፡ ጌቶች ናቸው ፡ በል ተው ፡ ጠጥተው ፡ ከጥላ ፡ አርፈው ፡ የሚውሉ አላቸው ። እነሱም አሻግረው ፡ አይተው ፡ አምላክ አምላክ ፡ ትላለህ ፡ አምላክማ ፡ ከፈለገህ ፡ ያባ ኤስ ድሮስ ፡ ገዳም ፡ ያውልህ አትሄድምን ፡ አሉት ያው ፡ ተነሥቶ ፡ ሄደ ፤ ከገዳሙ ፡ ቢደርስ ፡ ግብሩን፡ ያውቃሉና ፡ ማኅበሩ ፡ ተሸበሩ ፣ አበ ፡ ምኔቱ ፡ አባ ኤስድሮስ ፡ ነው ፤ ጸጋ ፡ እግዚአብሔር ፡ ጠርታ ፡ አ ምጥታዋለችና ፡ ይልቅ ፡ ተቀበሉት ፡ አላቸው : ተቀብለው ፡ አገቡት ፣ ከዚያ ፡ በኋላ ፡ ልጄ ፡ ምን ፡ አመ ጣህ ፡ አለው ፡ ትመክረኝ ፡ ብዬ ፡ አለ። መከረው አስተማረው ፤ አመነ ፡ ተጠመቀ ፤ ደግ ሰው ሆነ አመንኩሶታል።
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
ጉባኤ ቤታችን [ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ] በኦርቶዶክሳውያን ክርስቲያኖች አማካኝነት ያሠራቸውን የደቀመዛሙርት መኖሪያ ቤቶች አስመረቀ!
─━━━━━⊱✿⊰━━━━━─
በ«ብፁዕ አባታችን አቡነ ቀሌምንጦስ የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ» መልካም ፈቃድ ፣ በክቡር መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ በኩል ገዳሙ ባመቻቸልን ቦታ ፣ በጉባኤ ቤቱ መምህር በሊቀ ሊቃውንት ነቢየ ልዑል አዳሙ አስተባባሪነት፦
፩. በሕፃን ወለተ-ገብርኤል
፪. በኀይለ-ገብርኤል
፫. በወለተ-ብርሃን
፬. በወለተ-አማኑኤል
አማክኝነት ሙሉ ውጪው ተሸፍኖ - ገዳማችን በማቻቸልን ቦታ - የተሠሩ የደቀመዛሙርት ቤቶችን ፥ በሀገረ ስብከታችን ሊቀ ጳጳስ በ«ብፁዕ አባታችን አቡነ ቀሌምንጦስ» ቡራኬ በዛሬው ዕለት አስመርቋል።
በብፁዕ አባታችን መሪነት ሥርዐተ ቅዳሴ በገዳሙ አገልጋይ ካህናት ከተከናወነ በኋላ - የቡራኬ ሥርዐቱ በብፁዕነታቸው ተፈጽሟል።
ለእንግዶች የ«እንኳን ደና መጣችኹ» መልእክት ያሰሙት የጉባኤ ቤቱ መምህር - ጉባኤ ቤቱን በተወሰነ ደረጃ ለእንግዶች የሚያስተዋውቅ ከውጥን ኺደቶች አንሥተው አኹን እስካለበት ኹኔታ አውስተው ፥ ጉባኤ ቤቱ በዚኽ ልክ ሰፍቶ ማየታቸው በብፁዕነታቸው የቅርብ ክትትል መኾኑን በማንሣት ለብፁዕነታቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ከጉባኤ ቤቱ ደቀመዛሙርት መካከል የኔታ ዳዊት (የድጓ መምህር) በያሬዳዊ ዜማ ምሥጢርን ከኩነታዊው ኹኔታ አዋድደው ጥዑም ዜማ ያሰሙ ሲኾን - በመ/ር ኢሳይያስና በመ/ር ዕዝራ የቅኔ ቆይታ ተደርጓል።
ጉባኤ ቤቱ እያደረገ ያለው አካባቢያዊ አገልግሎት ፣ ነባር አገራዊ ታሪኮችን ድጋሚ በአከባቢው በማንበር ትልቅ ሥራ እያከናወነ ያለ መኾኑን ከገዳሙ መነኰሳትና ከአገር ሽማግሌዎች ከተሰጡ አስተያየቶች ተደምጠዋል።
ክቡር የገዳማችን አበምኔታ መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ ከተማ - የተሰጡ ሐሳቦችን አጠናክረው ፥ ከጉባኤ ቤቱ መወጠን አንሥቶ የታሪኩ አካል እንደመኾናቸው መጠን ስለ ጉባኤ ቤቱ አጀማመር ካነሡ በኋላ አኹን ያለበትን ኹኔታ ሲመለከቱ እጅግ የሚገረሙ መኾናቸውን አንሥተው ይኽ ኹሉ የኾነው በእግዚአብሔር አጋዥነት ፣ በብፁዕነታቸው አጋዥነት ፣ በጉባኤ ቤቱ መምህር ትጋት መኽኑን ገልጸዋል።
በመጨረሻ ንግግር እና ቃለ ምዕዳን የሰጡት ብፁዕነታቸው - እያዩት ባለው ነገር ፥ በቦታው ያለው ትጋት ፣ የአገልግሎት ፍቅር ፣ ያለኹበት ኹኔታ ይበቃኛል ባለማለት ዕለት ዕለት በመሻሻል [በኹሉም ዘርፍ ራሱን ለማብቃት የሚያደርጋቸው ጥረቶች] እያሳየ ያለውን ራእይ የቀደመው አገልግሎት ያጀበው እንቅስቃሴውን ከማድነቅ ጋር አበረታትተዋል።
ቤቱንም ለጉባኤ ቤቱ አሠርተው ያስረከቡ፦
◆ሕፃን ወለተ-ገብርኤልን
◆ኀይለ-ገብርኤልን
◆ወለተ-ብርሃንን
◆ወለተ-አማኑኤልን
የሠሩት ቤተክርስቲያን ለአገልግሎት የምትጠብቃቸው አገልጋዮቿ - ተሠርተው በቅተው ነቅተው የሚወጡበት መኾኑን በማስገንዘብ ፤ ከዚኽ የበለጠ መንፈሳዊ ግብርም አለመኖሩን በማንሣት - አባታዊ ቡራኬን ሰጥተዋል።
በመጨረሻም ጉባኤ ቤቱ ፍቅሬን ይገልጽልኛል ብሎ ያዘጋጃቸውን ሥጦታዎች ፥ በብፁዕነታቸው እጅ በሥራው ጉልኽ ድርሻ ለነበራቸው አበርክቷል።
ለብፅዕነታቸው (ይመጥናል ብሎ ሳይኾን የልጅነት ፍቅሩን ለመግለጽ) - በግል በአታቸው ቅዱሳት መጻሕፍትን የሚመለከቱባ ስማቸው የተቀረጸባት አትሮንስ እና የሊቁ ቅዱስ ቄርሎስን ድርሳን ጉባኤ ቤቱ አበርክቷል።
ለክቡር አባታችን መልአከ ሰላም ቆሞስ አባ ወልደ ጊዮርጊስ - የእጅ መስቀል - እንዲኹም ለተራዱን የገዳሙ አገልጋዮች የመጻሕፍት ሽልማትን በብፁዕነታቸው እጅ ሸልሟል።
ቤቱን ላሠሩልን፦
እንደ ሽልማት ሳይኾን ማስታወሻ ይኾናቸዋል ብሎ ያሰባቸውን ስጦታዎች - አበርክቷል።
በመጨረሻም የቊልፍ ርክክ ከተደረገ በኋላ በብፁዕነታቸው መሪነት ጉብኝት ተደርጎ የመርሐ ግብሩ ፍጻሜ ኹኗል።
--------------------------
ጉባኤ ቤቱ "ሰፊ" ከሚባሉ በርካታ ደቀመዛሙርትን ተረክበው ከሚያስተምሩ ቤተ ጉባኤዎች መካከል እየኾነ ያለ ጉባኤ ቤት ነው [በመጽሐፍ ቤት ደረጃ ከ90 በላይ ደቀመዛሙርትን ተቀብሎ ማስተማር መቻል ትልቅ ነገር ነው]።
ይኼ ታላቅ ጅምር ቢኾንም «በእግዚአብሔር ፈቃድ» አኹን የተመረቁ ቤቶችን ያካተተ በርከታ የጥናት እና የምርምር ማዕከላትን ያቀፈ ዐጸደ ጉባኤ እንደሚኖረን ባለ - ሙሉ ተስፋ ነን!!
-----------------------
ስለኹሉም ነገር የጉባኤ ቤት አምላክ ልዑል እግዚአብሔር እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም “ቅዱስ” ብላ የገለጸችው ስሙ ለዘለዓለሙ የተመሰገነ ይኹን!!
─━━━━━⊱✿⊰━━━━━─
©️ጉባኤ ደብረ ምጥማቅ
13/08/2018 ዓ.ም
📚#በትረ_ሃይማኖት📚
በቀሲስ መዝገቡ ካሣ (ዶ/ር)
"በትረ ሃይማኖት" የተሰኘ ተወዳጅ መጽሐፍ የተዋሕዶ ነገረ መለኮታዊ አስተምህሮና የምዕራባውያን ፍልስፍና በሚንጸባረቅባቸው ክርስቲያናዊ አመለካከቶች ላይ በግልጽ የሚያስረዳ መጽሐፍ ነው።
በእውነቱ ይህ መጽሐፍ ሁሉም ሊያነበው የሚገባ ከዛም አልፎ እንደ ማጣቀሻ ከቤት ሊጠፋ የማይገባው ድንቅ መጽሐፍ ነው።
መሠረታዊውን የኦርቶዶክስ ተዋሕዶ አስተምህሮ ግልጽ በሆነ መልኩ የሚያስቀምጥ፣ ከዘመናዊነት ጋራ አብረው የመጡና የተቀየጡ ፍልስፍናዊ አስተምህሮዎችን አንጥሮና አጉልቶ የሚተነትን የቀናውን ኦርቶዶክሳዊውን የእምነት መንገድ ፍንትው አድርጎ በመጻሕፍት እያጣቀሰ የሚያሳይ ግሩም መጽሐፍ ነው።
[@አንባብያን]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
Repost from የደብረ ምጥማቅ ጻድቃኔ ማርያም ገዳም የ፬ቱ ጉባኤያት ት/ቤት
🏛️ ከዳግማይ ትንሣኤ የምንማራቸው የሕይወት ስንቆች
➟ ዳግማይ ትንሣኤ ለኦርቶዶክሳዊ ሰው የሃይማኖት ማረጋገጫ፥ የጥርጣሬ ማክተሚያና የአዲስ ሕይወት መጀመሪያ ነው።
➟ ከዚኽ ዕለት የምንማራቸው መሠረታዊ ቁምነገሮች እነዚኽ ናቸው፦
➻ የአንድ ነፍስ ክብር [ግላዊ እንክብካቤ]፦ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለኹለተኛ ጊዜ የተገለጠው በተለይ ስለ ቶማስ ተብሎ ነው። ይኽም የሚያስተምረን እግዚአብሔር እኛን በጅምላ ሳይኾን በስማችን የሚያውቀን መኾኑን ነው። አንድ ኦርቶዶክሳዊ ሰው በፈተናና በጥርጣሬ ውስጥ ሲኾን "ጌታ ይተወኛል" ብሎ ሊሰጋ አይገባም። ጌታ ስለ አንዲት ነፍስ ሲል ዝግ በሮችን ሰብሮ እንደሚመጣ ከዳግማይ ትንሣኤ እንማራለን።
➻ ከመስማት ወደ መዳሰስ መሸጋገር፦ ቶማስ ከሌሎቹ ሐዋርያት "ጌታን አየነው" የሚል ቃል ሰምቶ ነበር ። ነገር ግን እርሱ የፈለገው የራሱ የኾነ ግንኙነት ነው። ኦርቶዶክሳዊ ሰውም ስለ ጌታ ከመስማት ባለፈ ፥ በምስጢራተ ቤተክርስቲያን [በተለይ በቅዱስ ቍርባን ] ጌታን የመዳሰስና የመቅመስ ፍላጎት ሊኖረው ይገባል። ምክንያቱም ሃይማኖት በወሬ ሳይኾን በመዳሰስ [በመኖር ]የምትገለጥ መኾኗን እንረዳለን።
➻ የቁስል ምስጢር (የመከራ ትርጉም)፦ ጌታችን የተነሣው ኹሉንም ቁስሉን አጥፍቶ ሳይኾን የችንካሩንና የጦሩን ምልክት ይዞ ነው። ይኽም የሚያስተምረን በሕይወታችን የሚደርሱብን ቁስሎችና መከራዎች በትንሣኤው ብርሃን ወደ "ክብር ምልክትነት" እንደሚቀየሩ ነው። ኦርቶዶክሳዊ ሰው መከራን የሚመለከተው እንደ ውድቀት ሳይኾን እንደ ድል አክሊል መኾኑን ከቶማስ መዳሰስ እንማራለን።
➻ ከማኅበረ ምእመናን አለመለየት፦ ቶማስ በመጀመሪያው ቀን ባለመገኘቱ በጥርጣሬ ውስጥ ቆይቶ ነበር ። በኹለተኛው ሳምንት ግን ከሐዋርያት ጋር በነበረበት ወቅት ጌታ ተገለጠለት። ይኽም የሚያስተምረን ጌታን ለማግኘትና ከጥርጣሬ ለመውጣት ከቤተክርስቲያንና ከቅዱሳን ማኅበር አለመለየት አስፈላጊ መኾኑን ነው። ብቸኝነት ለጥርጣሬ ፥ አንድነት ግን ለእምነት መጽናት ምክንያት ይኾናል።
➻ የልቦና ደጆችን ለሰላም መክፈት፦ ጌታ "ደጆች ተዘግተው ሳለ" ገባ። ይኽ ለኦርቶዶክሳዊ ሰው ትልቅ ትምህርት ነው። ልባችን በኃጢአት፣ በጭንቀትና በዓለማዊ ሐሳብ ተዘግቶ ቢኾን እንኳ፣ ጌታን ከፈቀድንለት በዝግ በራችን ገብቶ "ሰላም ለእናንተ ይኹን" ይለናል። መነሳት ማለት የተዘጉ የሕይወት በሮችን በጌታ ኃይል ከፍቶ ወደ ብርሃን መውጣት ማለት ነው።
➻ ብፅዕናን መናፈቅ (ሳያዩ ማመን)፦ "ሳያዩ የሚያምኑ ብፁዓን ናቸው" የሚለው የጌታ ቃል ለእኛ የተሰጠ ትልቅ ተስፋ ነው። ኦርቶዶክሳዊ ሰው በዓይኑ ያላየውን መንግሥተ ሰማያት፣ ያልዳሰሰውን መለኮታዊ ክብር አምኖ የሚኖር የብፅዕና ተካፋይ ነው። ይኽ ዕለት ከሥጋዊ እይታ ወጥተን በመንፈሳዊ ዓይን እንድንመለከት ያግዘናል።
➻ ፍጹም ምስክርነት፦ ቶማስ "ጌታዬና አምላኬ!" ብሎ ሲጮኽ፣ በፊቱ ያለውን "ሰው" ብቻ ሳይኾን "አምላክነቱንም" በአንድነት መሰከረ። ኦርቶዶክሳዊ ሰውም በክርስቶስ ፍጹም ሰውነትና ፍጹም አምላክነት ላይ ጥርጣሬ የሌለው ፥ ይኽንንም እውነት እስከ ሕይወት መሥዋዕትነት ድረስ የሚመሰክር ሊኾን ይገባዋል።
⚠️ ማጠቃለያ፦ አንድ ኦርቶዶክሳዊ ሰው ከነዚኽ ነጥቦች ውጭ ከኾነ፣ የሕይወት መሠረቱ ይናወጣል። እነዚኽን ምስጢራት በልቡ አኑሮ በጽናት ካልቆመ ፥ እንደ ሀይላንድ ውኃ በትንሽ የዓለም ንፋስና የክህደት ወሬ ወዲያና ወዲኽ የሚንገዋለል ይኾናል። ዳግማይ ትንሣኤ ግን ከመወዛወዝ አውጥቶ "ጌታዬና አምላኬ!" በሚል ዐለት ላይ ያቆመናል።
✨ በዓሉ የሰላምና የጽናት ይኹንልን! ✨
#ዳግማይ_ትንሣኤ #ኦርቶዶክስ #ተዋሕዶ #ቅዱስ_ቶማስ #ጌታዬና_አምላኬ #እምነት
@ ነቅዐ ጥበብ ገሠሠ የጉባዔ ደብረ ምጥማቅ የብሉይ ኪዳን ደቀ መዝሙር "
📚#ሐዋርያውያነ_አበው
►ፓሊካርፐስም ወደ ሜዳው ሲገባ "ፓሊካርፐስ ሆይ በርታ ፤ ጽኑ ኹን! " የሚል ቃል ከሰማይ መጣ ተናጋሪውን ያየው ማንም የለም ፤ ነገር ግን በዚያ የነበሩት ወንድሞች ድምፁን ሰሙ ።
በመጨረሻም ወደ ፊት ሲያቀርቡት ሀገር ገዢው ፓሊካርፐስ እርሱ መኾኑን ጠየቀው ፤ እርሱም መኾኑን ሲያምን ሃይማኖቱን እንዲክድ ሊያግባባው እየሞከረ እንዲህ አለው "ለሽምግልናህ እዘን ደግሞም እነርሱ እንደሚያደርጉት ኹሉ በቄሳር መልካም እድል ማል ፤ ሐሳብህንም ለውጥና 'አምላክ የሌላቸው ይጥፉ' በል " አለው ። ያንጊዜም ፓሊካርፐስ በመሰብሰቢያው የነበሩትን ዓመፀኞች አረማውያን ኹሉ በእርጋታ ተመለከተ ፤ በእጁም እነርሱን አመለከተ ቃተተም ወደ ሰማይም ቀና ብሎ "አምላክ የሌላቸው ይጥፉ ! " አለ ።
ከዚያም ሀገረ ገዢው እየገፋፋው "ማል ፤ እኔም ነጻ አወጣሃለሁ ፤ ክርስቶስን ስደብ " አለው ። ፓሊካርፐስም "ሰማንያ ስድስት ዓመት አገልግዬዋለሁ ፤ እርሱም ከቶ ምንም አልበደለኝም ። ታዲያ ንጉሤንና መድኃኒቴን እንዴት ልሰድብ እችላለሁ ? " ብሎ መለሰለት ።
[ ከውስጥ ገጽ ]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
►►►ራእይ፡ ሠለስቱ
«ወዐቀቡ፡ ወተልእክዎሙ፡ ለኅሩያኒሁ፡ #ለእግዚአብሔር፡ በንጹሕ፡ ወበየዋሀት።»
በንጽሕ ወበየዋሃት ሲል ነው፤ ንጽሕናን፡ አንድም፡ ሕገጋትን፡ የጠበቁ፡ የእግዚአብሔር፡ ምርጦችንም፡ በንጽሕናና፡ በየዋህነት፡ ያገለገሏቸው፤ አንድም፡ እለ፡ አንጽሑ፡ ርእሶሙ፡ #ለእግዚአብሔር፡ ወዐቀቡ፡ ብለህ፡ ግጠም፤ ራሳቸውን፡ #ለእግዚአብሔር፡ በንጽሕና፡ የጠበቁ፤ ንጽሕናን፡ ገንዘብ፡ ቢያደርጉ፡ የሚጠቀሙበት፡ የሚከብሩበት፡ እነርሱ፡ ራሳቸው፡ አይደሉምን፡ ስለምን፡ #ለእግዚአብሔር፡ _ አለች? ቢሉ፡ #ከእግዚአብሔር፡ ዘንድ፡ ዋጋ፡ እናገኝበታለን፡ ብለው፡ _ ያደርጉታልና፤ አንድም፡ ሕገጋትን፡ መጠበቃቸው፡ #እግዚአብሔርን፡ ከመውደዳቸው: በእርሱም፡ ከመተማመናቸው፡ የተነሣ፡ ነውና፡ “እመሰ፡ ታፈቅሩኒ፡ ዕቀቡ፡ ትእዛዝየ” ፣ “ወኵሉ፡ ዘተወከለ፡ ኪያሁ፡ ያነጽሕ፡ ርእሶ፡ በከመ፡ ውእቱ፡ ንጹሕ”፡ እንዲል። (ዮሐ ፲፭፥፲ ፩ ዮሐ ፫፥፫)
[ከውስጥ ገጽ]
📚#ድሳርነ_ሔርማ_ነቢይ
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
..#ጸሎት፥ ጥንቱንም፥ የሰው ልጅ ሥራ ብቻ አይደለም፡፡ ለራሱ ምቾት፣ ለፍላጎቱ መሟላት ወይም ለጥያቄዎቹ መልስ ለማግኘት ብቻ የሚደረግም አይደለም:: የጸሎት ታላቅነቱ በአጠቃላይ የመንፈሳውያን ፍጥረታት ተግባር በመኾኑ ላይ ነውና፡፡ እርሱም የዚህ ዓለም ሥራ አይደለም፡፡ ለዚህ ዓለም ብቻ የሚኾንም አይደለም፡፡ ስለዚህ ጸሎትን ለሰው ልጅ ፍላጎቶች ማሟያ ወይም በዚህ ሕይወት ውስጥ ለሚገጥሙት ልመናዎች መልስ ማግኛ ብቻ አድርገን የምንገድበው ከኾነ፡ መሠረታዊ ታላቅነቱን ያጣል፡፡ አንድ ሰው የእግዚአብሔርን ስም በመቀደስ፣ ለእርሱ ክብርን በመስጠት፣ በምስጋናና በንጹሕ ውዳሴ እርሱን በማምለክ ወደ መንፈሳዊ ፍጡርነት ይለወጣል፡፡ በዚህም ሰማያውያን ሠራዊት ከሚያከናውኑት ረቂቅ አገልግሎት ጋር ይተባበራል።
[ከውስጥ ገጽ]
📚#ኦርቶዶክሳዊ_የጸሎት_ሕይወት
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
📚#ሐተታ_ዘቅዱስ_አትናቴውስ
ቅዱስ አትናቴዎስ በዚህ መጽሐፍ ከሚመልሳቸው ጥያቄዎች.....
አንትያኮስ፦ ርኩሳን መናፍስት የሆኑ አጋንንት ከቅዱሳት መጻሕፍት የሚፈሩት የጸሎት ዐይነት የቱ ነው?
ጥያቄ ፳፩. በውኑ ለኃጥአን ነፍሳት በዚህ ዓለም ዘመዶቻቸው የመታሰቢያ(ተዝካር) ቍርባን፣ ጸሎትና ምጽዋት ቢያደርጉላቸው በዚያኛው ዓለም ይጠቅማቸዋልን?
ጥያቄ ፳፭. ለሰው እጅ ሥራዎች እንዳንሰግድ እግዚአብሔር በነቢያቱ አዝዞናልና ለምን የሰው እጅ ለሠራው ለቅዱሳን ሥዕልና ለቅዱስ መስቀሉ እንሰግዳለን?
፴. አንትያኮስ፡- ከኃጢአት ሁሉ የሚበልጠው ኃጢአት የቱ ነው?
፵፰. አንትያኮስ፦ ብዙ በደልንና ኃጢአትን የሠራ ሰው ቢኖር ከዚያም በኋላ ንስሓ ቢገባ፤ እንደገና ተመልሶ ኃጢአት ቢሠራ እግዚአብሔር ንስሓውን ይቀበለዋልን ወይስ አይቀበለውም?
(ከውስጥ ገጽ)
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
ሐዋርያውም "ሁሉ በአዳም እንደሚሞቱ እንዲሁ ሁሉ በክርስቶስ ደግሞ ሕያዋን ይሆናሉ።" በማለት በመዋቲው አዳም ምክንያት ሞት የታወጀብን እኛ ሕይወት በሆነው በዳግማይ አዳም ክርስቶስ ትንሳኤ ሕይወት እንደ ታወጀልን መሥክሮልናል ፩ቆሮ.፲፭፥ ፳፪
ስለዚህ የክርስቶስ ትንሣኤ ክርስቶስን ላመኑ ሁሉ ሞት ከነ ምንጩ የደረቀበት የሰው ዘር በዲያብሎስ ላይ ድልን ማሸነፍን የተቀዳጀበት የእምነታችን መልህቅ፣ የደስታችን ምንጭ እና ያለመሞት ቃል ኪዳን ነው።
፮.የትንሳኤ በዓልን እንዴት ማክበር አለብን?
ትንሣኤ ከበዓላት ሁሉ የላቀ የበዓላት ሁሉ በዓል ነው ይህ ቀን እጅግ ልዩና ድንቅ በሆነ በደስታ ጸሎት በደስታ ምስጋና በደስታ አምልኮ ይታሰባል።
በተለይህም ምድራዊት ሰማይ በሆነች በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተክርስቲያን ያለው የትንሣኤ በዓል አከባበሩ እንኳንስ በመናገር ተገኝቶ በማየት እንኳ የመዓዛውንና የጣዕሙን ጥልቀት መረዳት በእጅጉ ኅሊናን የሚፈትን ነው።
በዚህች ሌሊት ምዕመናን ከክርስቶስ ከሕማሙም ከሞቱ ከትሣኤውም ይሳተፉባታል።
ልክ ሐዋርያት የክርስቶስን መነሣት ሲጠባበቁ እንደነበሩት የዛሬዎች የክርስቶስ ተከታዮችም ጥልቀት ባለው ተመስጦ በፍጹም ትጋት ክርስቶስ የተነሣባትን መንፈቀ ሌሊት ይጠባበቃሉ።
ያቺ ሰዓትም ደርሳ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ የሚለውን ሲሰሙ ከሐዋርያት የተወለዱ ምዕመናን ሐዋርያት በክርስቶስ ትንሣኤ እንደ ተደሰቱ ደስ ይሰኛሉ።
ትንሣኤ በአፍኣ በመብል በመጠጥ ብቻ የሚከበር ሳይሆን ምዕመናን በፍጹም መታደስ ሆነው የሚያከብሩት በዓል ነው።
ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ
ሰው ሁሉ ከዚህ የእምነት በዓል ይካፈል ሁሉም መልካምነትንና ባለ ጠግነትን ገንዘብ ያድርግመንግሥተ ክርስቶስ ተገልጣለችና ማንም አይዘን ብሏል።
ይህም በዓለ ፋሲካን ከእርሱ ያገኘነውን በማሰብ በፍጹም ተመስጦ ሁነን ልናከብር እንደሚገባን ያስረዳል።
ማጠቃለያ፦
ትንሣኤ አንድ ጊዜ ተከሥቶ የቀረ ታሪክ አይደለም።
ትንሣኤ ሁል ጊዜ መንፈሳዊ ሕይወታችነን የሚሠራ ልቡናችንን የሚያጸና ተስፋችን ዘወትር የምንቀዳበት ሁል ጊዜ የምናስበው።
ከኅሊናችን የማይርቅ በሰውነታችን የምንመካበት ጥልቅ እምነታችን ነው።
በዕለተ ትንሣኤ ክርስቶስ ከሙታን ተለይቶ ተነሣ በማለት ይህንን እምነታችን ከወትሮው በተለየ አብዝተን እንመሠክራለን።
በመሆኑም የተወደዳችሁ ምዕመናን የክርስቶስን ትንሣኤ በቃል ብቻ ሳይሆን በምግባርም ያለ ፍርኀት የምንመሠክረው እምነታችን ነው።
እንኳን ለብርሃነ ትንሣኤው አደረሰን አደረሳችሁ ፤ መልካም የትንሣኤ በዓል ይሁንላችሁ!!
፩ .ትንሣኤ ምንድን ነው?
ትንሣኤ እንደ አገባቡ እንደ አመጣጡ በብዙ መተርጎሙ እንደ ተጠበቀ ሁኖ ክብር ይግባውና ከአምላካችን ከኢየሱስ ክርስቶስ አንጻር ስናየው ግን በፈቃዱ ቅድስት ነፍሱን ከቅዱስ ሥጋ በዕለተ ዐርብ የለየ አምላክ በዕለተ እሑድ የሞትን ኃይል አጥፍቶ መቃብርን ድል ነሥቶ ቁራኝነትን አስወግዶ ቅዱስ ሥጋውንና ቅድስት ነፍሱን ማገናኘቱን የሚያሳይ ቃል ነው።
፪. የክርስቶስ ሞት ከሌሎች ሰዎች ሞት በምን ይለያል?
ክብር ይግባውና የአምላካችን የኢየሱስ ክርስቶስ ሞቱም ትንሣኤውም የታመነና እውነት ነው።
ክርስቶስ በእውነት እንደ ሞተ እናምናለን ያቺን ሞታችንን ያጠፋ ዘንድ የሞታትን ሞት ዘወትር እናስባለን።
ለዚህ ነው በቅዳሴአችን ንዜኑ ሞተከ እግዚኦ አቤቱ ሞትህን እናስባለን ማለታችን።
ነገርግን ማስተዋል የሚገባን መሠረታዊ ጉዳይ የክርስቶስ ሞት እንደ ሰው ሞት ቢሆንሞ ከሰው ሞት የተለየ እንደሆነም መገንዘብ ይገባናል።
እንደ ቤተክርስቲያን አስተምህሮ የጌታ ሞት ከሰው ሁሉ ፈጽሞ የተለየ እንደሆነ ይታመናል።
የዚህም ምክንያቱ የክርስቶስ አካል መዋቲ ሥጋ ብቻ ስላልሆነ ነው።
ክርስቶስ ኢመዋቲ የሆነ መለኮት ነው። ደግሞ ክርስቶስ መዋቲ ሥጋ ገንዘቡ ነው።
ስለዚህ መዋቲነት ገንዘቡ ከሆነ የኢመዋቲነት ባሕርይ ግን የሌለው የሰው ልጅ ሞትና ፍጹም አምላክ ፍጹም ሰው የሆነ የክርስቶስ ሞት አንድ ሊሆን አይችልም።
በመካከል ታላቅ ልዩነት እንዳለ መገንዘብ ይገባናል።
ከእነዚህም ልዩነቶች መካከል አንዱ ጊዜ ተዋሕዶ የሆነው የመለኮትና የትስብእት ተዋሕዶ ባሕርያዊና የትኛውም ክስተት ሊለየው የማይቻለው መሆኑ ነው።
ነፍስ ከሥጋ በተለየች ጊዜ መለኮት ከነፍስም ከሥጋም አልተለየም።
ሰው ሁሉ በሚሞትበት ጊዜ ሥጋ ነፍስ ስትለየው ይበተናል ይፈርሳል ይበሰብሳል ክብር ይግባውና የክርስቶስ ቅዱስ ሥጋው ግን ይህ ሁሉ አላገኘውም ለምን? ቢባል መለኮት ስላልተለየው።
ደራሲ ሰላም ሰላም ለቅዱስ ሥጋከ እም መለኮቱ ዘኢተፈልጠ ለሰዓት አሐቲ ከመ ቅጽበተ ዐይን ኅዳጠ-
ለቅጽበት ከመለኮቱ ላልተለየ ለቅዱስ ሥጋህ ሰላም እላለሁ ማለቱ ይህንን የሚያስረዳ ነው።
ስለዚህ የክርስቶስ ሞት ከሰው ሁሉ ሞት የሚለይበት ምስጢር፦መለኮት ያልተለየውና የማይለየው ከመሆኑ የተነሳ አራቱ ባሕርያት ባለ መለያየታቸው ባለ መፍረስ ባለ መበስበስ ሞትና መቃብር እርሱን ከማግኘት ሌላ ያልሰለጠኑበት መሆኑ እንደሆነ በአግባቡ መረዳት ይገባል።
፫. የክርስቶስ ትንሣኤ ምሥጢር እንዴት ይገለጣል?
ከላይ በእውነት ተነሥቷል ብለን እንደተናገርነው
የአምላካችን ትንሣኤ በዐይን ምስክሮች፣ በቅዱሳት መጻሕፍት በትንቢተ ነቢያት እና በቅዳሴ መላእክት የተገለጠና የተረጋገጠ መለኮታዊ ምስጢር ነው።
በነቢያትና በራሱ በክርስቶስ እንደተነገረው ክርስቶስ በእውነት በሦስተኛው ቀን ከሙታን ተለይቶ ተነሥቷል ።
ቅዱሱ የእግዚአብሔር መላክ የትንሣኤውን ንጉሥ ከመቃብር ሲፈልጉት ለነበሩት ቅዱሳት አንስት ክርስቶስ በመቃብር እንደሌለ የመቃብሩን ባዶነት የሞትን ድል መነሳት ሲያስረዳ እርሱ በእዚህ በመቃብር የለም እንደተናገረ ተነሥቶአል ኑና የተኛበትን ስፍራ እዩ ብሏል። ማቴ ፳፰፥፮
ይሁን እንጂ ይህ የመቃብር ባዶ መሆን የሞት ድል መነሣት ለሰው እንዲህ በቀላሉ የሚረዳ አልነበረም።
ምክንያቱም "ሞት" ለሰው ልጅ የዘመናት ባለጋራ ሁኖት ድል ሲነሳው ዘመዱን ቤተሰቡን ሁሉ ሲነጥቀው የኖረ ነጣቂ ነበርና።
ክርስቶስም የሞትን ነገር ጎላ አድርጎ ለመግለጥ የፈለገበት መሠረታዊ ምክንያት ይህ ነው።
ከመሞቱ በፊት ክርስቶስ እሞታለሁ ብሎ ሞቱን እነሣለሁ ብሎ ትንሣኤውን ተናግሯል።
ከሙታን ተለይቶ ሲነሣም መቃብሩ እንዲመሠክርለት የተገነዘበት መግነዙ እንዲመሠክርለት መላእክትና ደቂቀ አዳም እንዲመሠክሩለት አድርጓል ግን በዚህ ብቻ ያበቃ አይደለም።
ከትንሣኤው በኋላም ለአርባ ቀን ትንሣኤውን በመገለጥ በመዳሰስ በቃልም በግብርም መስክሯል። ይህ ሁሉ የሞትን ድል መነሣት ማመን እጅግ ከባድ ስለ ነበር ነው።
የክርስቶስ ትንሣኤ ዲያብሎስን ያዋረደ መቃብርን ባዶዉን ያስቀረ ሞትን ድል የነሣ ለሰው ልጅ ሕያውነትን ያደለ በሰው ልጆች ሕይወት ውስጥ ትልቅ ቦታ የሚሰጠው ቃላት የማይገልጡት ኅሊናት የማይመረምሩት ጥልቅነቱ የማይደረስበት ነው።
ይህንን ክስተት ሊቁ ቅዱስ አትናቴዎስ - ሞት በድል ተዋጠ - በማለት የክርስቶስ ትንሣኤ በሞት ላይ የሆነ ድል እንደሆነ አስረድቷል።
ስለዚህ የክርስቶስ ትንሣኤ ላመኑ ምዕመናን ወደረ የማይገኝለትና ከድንቅ ሁሉ በላይ የሆነ ድንቅ ነው።
ቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ
ቅዱስ ኤፍሬም በድርሳኑ ስለ ትንሣኤ በተናገረበት አንቀጽ ላይ ለማያምኑት የትንሣኤ ነገር ያጠራጥራቸዋል ፤ ለሚያምኑ ሐዋርያት ግን የክርስቶስ ትንሣኤ የድንቅ ድንቅ ነው። ብሏል።
ከዚህም ትንሣኤ ድንቅ ብለን ብቻ የምናልፈው ሳይሆን ድንቅ በተባለው ላይ ሁሉ ላይ ድንቅ እንደሆነ እንረዳለን።
፬.ክርስቶስን ያስነሣው ማነው
ክርስቶስን ከሞት ያስነሳው ማን ነው? አብ ነው? መንፈስ ቅዱስ ነው? ወይስ በራሱ ሥልጣን?
መጽሐፍ ቅዱስ ሦስቱንም በተለየ ስማቸው እየጠራ ከማስነሣት ጋ አያይዟቸዋል።
ክርስቶስን አብ እንደ አስነሣው፡-
እግዚአብሔር የሞትን ሕማም አጥፍቶ አስነሣው፥ ሞት ይይዘው ዘንድ አልቻለምና። የሐዋርያት ሥራ ፪ ፳፬:
ወልድም በሥልጣኑ እንደ ተነሣ
"ይህን ቤተ መቅደስ አፍርሱት በሦስት ቀንም አነሣዋለሁ። ዮሐንስ፪ ፡፲፱
መንፈስ ቅዱስ እንደ አስነሣው
"ነገር ግን ኢየሱስን ከሙታን ያስነሣው የእርሱ መንፈስ በእናንተ ዘንድ ቢኖር፥ ክርስቶስን ያስነሣው... በመንፈሱም ለሚሞተው ሰውነታችሁ ሕይወትን ይሰጣል።" ሮሜ ፰ ፲፩
አባቶቻችን ይህንን ይዘው ይተረጉማሉ መጻሕፍት አብ ወልድ መንፈስቅዱስ ብለው አድለው መናገራቸው ሦስቱ በአምላካዊ ግብር እንድ መሆናቸውን ለማመልከት ነው።
ስለዚህ ከሙታን ተለይቶ የተነሣው ወልድ ብቻ ቢሆንም ወልድ የተነሣባት ሥልጣን ግን የሦስቱም ስለሆነች መጻሕፍት ለሶስቱም ሰጥተው ተናግረዋል።
ቅዱስ ቄርሎስ ዘኢየሩሳሌም
የሥላሴ አምላካዊ ግብር ለሦስቱ ሁሉ እንደ ሚነገር ሲያብራራ የአብ የወልድ የመንፈስቅዱስን አሠራር ልንለያይ አይገባንም። የእግዚአብሔር ሥራ ሁሉ ለሦስቱ አካላት የሚነገር ነውና ብሏል።
ስለዚህ ትንሳኤ የቅድስት ሥላሴ የአብ የወልድ እና የመንፈስ ቅዱስ የአንድነት ግብር መሆኑን መረዳት ሃይማኖት ነው።
፭.የክርስቶስ ትንሳኤ ለአማኞች ያለው ጥቅም ምንድን ነው?
ትንሳኤ በሞት ላይ ያለን ድል የሚያሳይ ነው።
ትንሣኤ በኃጢአት የተበላሸውን ሰብዓዊ ተፈጥሮአችንን ያደሰ፣ እና የዘላለም ሕይወትን መንገድ የከፈተ ነው ።
ጌታ በትንሣኤው ሞታችንን ድል አድርጎ አጥፍቶታል
እሙታን ተንሢኦ ሢኦለ ከይዶ በሞቱ ለሞት ደምሰሶ
ከሙታን ተለይቶ ተነሥቶ ሲዖልን ረግጦ በሞቱ ሞትን አጠፋው።
እልመስጦአግያ
ስለዚህ ትንሣኤ ሞታችን ድል የተነሣበት በዓል ነው።
ከዚህም በላይ ግን ጌታ በትንሣኤው ያጠፋልን ሞትን ብቻ ሳይሆን የሞትን መገኛም አጥፍቶልናል
አትናቴዎስ ሐዋርያዊ
አትናቴዎስ ክርስቶስን ሲመሰክር ዝ ውእቱ ዘአጥፍኦ ለሞት ወሠአሮ ለዲያብሎስ ይህ በሞቱ ሞትን የሻረ በትንሣኤው ዲያብሎስን ድል የነሣ ነው በማለት ትንሣኤ ሞት ከእኛ የራቀበት ሕይወት ወደ እኛ የቀረበበት ድንቅ በዓል መሆኑን አስረድቶናል።
✧✧
|❀:✧๑ ✞✞ ๑✧❀|:
✥••┈┈••●◉ ✞ ◉●••┈┈••✥
"ወዮም ፍስሐ ኮነ በሰንበተ ክርስቲያን ፤ እስመ #ተንሥአ_ክርስቶስ_እሙታን ፤ ቀደሳ ወአክበራ እምኩሎን መዋዕል ፤አልዓላ አማን ተንሥአ እምነ ሙታን።
[ሥርአተ ማሕሌት በዓለ ትንሳኤ]
◈ በምህረቱ ጠብቆ በቸርነቱ ታግሶ
እንኳን ለበዓለ ትንሳኤው በሰላም አደረሰን።
በዓሉ የሰላም የጤና የፍቅር ያድርግልን።
መልካም የትንሳኤ በዓል🙏
💧በድጋሚ ታትሟል
📚#ፍኖተ_ቅዱሳን📚
በዲያቆን ያረጋል አበጋዝ የተሰናዳው ይህ መጽሐፍ የቅድስናን መንገድ ከሕይወታዊ ማጣቀሻ ጋር የያዘ ግሩም መጽሐፍ ነው..
ለቅምሻ
ትጋሃ ሌሊት
📜✍ሰው እንደ ሥጋ ለባሽነቱ ዕረፍት ቢያስፈልገውም ሌሊቱን ሁሉ ፈጣሪውን ሳያስታውሱ በእንቅልፍ ማሳለፍ ግን ተገቢ አይደለም። መድኅን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ በፈቃዱ በአይሁድ የሚያዝበት ጊዜ እንደ ደረሰ አውቆ ሦስቱን ደቀ መዛሙርቱን ወስዶ ካዘነና ከተከዘ በኋላ ወደ እነርሱ ሲመጣ ተኝተው ስላገኛቸው “እንዲህ ከእኔ ጋር አንዲት ሰዓት እንኳ ልትተጉ አልቻላችሁምን? ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ጸልዩ አላቸው። ማቴ. 26፡40-41 ሁል ጊዜ በጸሎት ጽሙድ ሆኖና ተግቶ መኖር እንዲገባም “ጌታችሁ በምን ሰዓት እንዲመጣ አታውቁምና እንዲሁ ንቁ ሲል ተናግሯል። ማቴ. 24፡42-44 እንዲሁም በመዐልት ብቻ ሳይሆን በሌሊትም በትጋት እግዚአብሔርን ማዘከር እንዲገባ ሲያስረዳ ክቡር ዳዊት “ - ነገር ግን በእግዚአብሔ ሕግ ደስ ይለዋል፣ ሕጉንም በቀንና በሌሊት ያስባል” ይላል። መዝ. 1፡2 በሌሊትም በጸሎትና በተዘክሮ እግዚአብሔርን ማሰብ እንዲገባም በመዝ. 118፡97 ተጽፏል ቅዱሳንም በመዐልትም ልዩ ፈተናዎች ጋር ይታገላሉ። ትጋሃ ሌሊት ከባድ ተጋድሎን የሚጠይቅ ነው።
ከአበው የትጋሃ ሌሊት ተጋድሎ ለአአብነት እንመልከት፦
#ታላቁ_ቅዱስ_አርሳንዮስ ቅዳሜ ማታ ፊቱን ወደ ምሥራቅ አዙሮ እጁን ሰቅሎ ፀሐይ ጀርባውን ስትመታው ጸሎት የጀመረ በማግስቱ እሑድ ጧት ፀሐይ ግንባሩን እስክትመታው ቆሞ ያድር ነበር።በጸሎት ካደረ በኋላ " አንተ ደካማ ሥጋ ሆይ ያውልህ እረፍ "ብሎ አረፍ ይል ነበር።
📚ፍኖተ መጻሕፍት
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
t.me/FinoteBooks1623
📚#ሕማማት
[በዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ]
ስለ መጽሐፉ👇 ...
‹‹የኦርቶዶክሳዊ ክርስትና ሥርዓተ አምልኮ ዋና ዓላማው ምእመናን የልቡናቸውን በር እንዲከፍቱና ክርስቶስ በእነርሱ ውስጥ እንዲኖር ማስቻል ነው፡፡ የዚህ በሩ ደግሞ የክርስቶስ ሕማምና መከራ ነው፡፡ ሕማሙን አሁን እንደተቀበለና በተሰቀለበት ዕለት ውስጥ እንዳለን ሆነን ሁኔታውን ሁሉ ከእመቤታችንና ከቅዱስ ዮሐንስ ጋር አብረን እያየን ከሕማማቱ ተሳታፊ አድርጎ እስከ እግረ መስቀሉ ማድረስ ነው፡፡ ይህን ለማድረግ ግን ለእኛ ትውልድ ቀላል አይደለም፡፡ የዚህ ዓለም ግሳንግስ ፣ ፊልሙ ፣ ዘፈኑ ፣ ኳሱ ፣ ርካሽ ፖለቲካው የከፋፈሉትን ልብ ሰብስቦ ነገረ ድኅነትን በሕሊና የሚስል ፣ በልቡና የሚያሳድር ፣ በአእምሮ የሚቀርጽና ፍቅርን የሚያመጣ ፣ ይቅርታ አድራጊነትን የሚያሰፍን ረዳት የሚፈልግ ካለ ይህ የዲያቆን ሄኖክ ኃይሌ «ሕማማት» መጽሐፍ በእጅጉ ያስፈልገዋል ብዬ አምናለሁ፡፡
✍️[ዲያቆን ብርሃኑ አድማስ]
📚ፍኖተ መጻሕፍት ለውድ አንባብያን በDHL እና በEMS እንዲኹም የDelivery አገልግሎት በመስጠት መጻሕፍትን ተደራሽ እናደርጋለን።
[ እንደ መጻሕፍት ያለ መንገድ ከወዴት ይገኛል?]
ይደውሉልን!📞፦0913083816
Join us
◉Telegram
t.me/FinoteBooks1623
◉Facebook
facebook.com/FinoteBooks1623
◉Tiiktok
tiktok.com/@finotebooks1623
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
