fa
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

رفتن به کانال در Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

نمایش بیشتر
3 291
مشترکین
+224 ساعت
+127 روز
+10030 روز
آرشیو پست ها
የጉዲና ቱምሳ ሁለገብ የስልጠና ማዕከል አስተዳደርና ሰራተኞች የጌታችን እና የመዳኒታችን ኢየሱስ ክስትቶስ የልደት መታሰቢያ በዓል በታላቅ ድምቀት አከበሩ። በአከባበሩም የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ፣ የኢትዮጵያዊ ወንጌል አማኞች አብያተ ክርስቲያናት ካውንስል ጠቅላይ ፀሀፊ ቄስ ዶ/ር ደረጀ ጀምበሩ እና የቤተ ክርስቲያኒቱ የክብር ፕሬዚዳንት ቄስ ኢተፋ ጎበና ተገኝተው መልካም ምኞታቸውን አስተላልፈዋል። የበዓሉ አከባበር አያይዘው የቤተ ክርስቲያኒቱ መሪዎች እና አባቶች በታላቅ ትህትና እና መሰጠት ቤተ ክርስቲያናችንን እና መላውን ወንጌል አማኞችን በተቋሙ ከእሁድ እስከ እሁድ እያስተናገዱ የሚገኙ የተቋሙ ሰራተኞችን እንዲባርኩ በማሰብ መሆኑን የማዕከሉ የአስተዳደር ሀላፊ የሆኑት ቄስ ሀረገወይን ገልጸዋል። የማዕከሉም የሰራተኞች ኳየር በዕለቱ ያገለገለ ሲሆን የማዕከሉን የላይብረሪ አገልግሎት ለማጠናከር የቤተ ክርስቲያኒቱ የልጆችና ወጣቶች መምሪያ የመንፈሳዊ መጽሐፍት ድጋፍ አድርጓል።

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የዋናው ጽሕፈት ቤት ሰራተኞች የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል ዋዜማን በጋራ አክብረዋል። ታህሳስ 28/2018 ዓ.ም ፎቶ - ህሊና ታደሰ

Ayyaana Yaadannoo Dhaloota Gooftaa Keenya Yesuus Kiristoos kan bara 2018 ilaalchisee Ergaa Uummata biyyattii maraaf darbe Waldaa Kiristiyaanaa Warra Wangeelaa Makane Yesus Itiyophiyaa Luba Dr. Yonas Yigazu Pirezedaantii Waldaa WWMI Muddee 27/2018

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የ2018 ዓ.ም የጌታችንና የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ልደት መታሰቢያ በዓል የመልካም ምኞት መልዕክት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዚዳንት ታህሳስ 27 / 2018

ሁለንተናዊ የልጆችና ወጣቶች አገልግሎት ስልጠና በማዕከላዊ ሰሜን ኢትዮጵያ ሲኖዶስ ተሰጠ። 'ሁለንተናዊ ዕድገት ለልጆች እና ወጣቶቻችን' በሚል ርዕስ የተዘጋጀው ስልጠና በማዕከላዊ ሰሜን ኢትዮጵያ ሲኖዶስ በሲኖዶሱ ማዕከል ደሴ ከተማ ተሰጥቷል። ስልጠናው የተሰጠው ከሲኖዶሱ ጋር በመተባበር በዋናው ጽ/ቤት የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ በኩል ሲሆን ከሲኖዶሱ ሁሉም ማ/ምዕመናናት የተወጣጡ መሪዎች እና የልጆችና ወጣቶች አገልጋዮች ተሳትፈዋል:: ከስልጠናው ጎን ለጎን ለልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት የሚጠቅሙ ታቅዶ እየተሰራበት ላለው ቤተመጻህፍትን በእያንዳንዱ ማህበረ ምዕመናን የማስጀመር ራዕይ የሚረዱ የልጆች መጽሐፍ ቅዱሶች፣ የወጣቶች ማስተማርያ መጽሐፍቶች፣ ለአገልጋዮች እና ምዕመናን፣ ለደቀመዛሙርትነት እና ለሌሎች ለቤተክርስቲያን ስነ መለኮታዊ አስተምህሮ የሚረዱ የተለያዩ መጽሐፍቶች በመምሪያው በኩል በድጋፍ መልክ ተሰጥቷቸዋል:: የቤተክርስቲያኒቱ የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎት መምሪያ ዳይሬክተር ቄስ ወንድማገኝ ኡዴሣ የተለያዩ መንፈሳዊ መጽሐፍትን ለቤተክርስቲያኒቱ ድጋፍ ያደረጉትን ተቋማት ' Rafiki Foundation' እና ' Lutheran Heritage Foundation ' እና ሌሎችንም በማመስገን : መጽሐፍቶቹን ለቤተክርስቲያኒቱ ማ/ምዕመናናት፣ ሴሚናሪዎች፣ መጽሐፍ ቅዱስ ኮሌጆች እና ት/ቤቶች ከተባባሪ ድርጅቶች ጋር በመሆን ድጋፍ የማድረጉ ስራ እንደሚቀጥል ገልጸዋል። በስልጠናው የተሳተፉ የሲኖዶሱ መሪዎችም ስልጠናው የልጆች እና ወጣቶች አገልግሎትን ጊዜው በሚፈልግ መልኩ ለማሳደግ አስፈላጊ እና ወቅቱን ያገናዘበ መሆኑን ገልጸው ሰልጣኞች በወሰዱት ስልጠና መሰረት ወደ ተግባር መቀየር እንዳለባቸው አጽንኦት ሰጥተው መልዕክት አስተላልፈዋል:: ከስልጠናው በኃላ በደሴ መካነ ኢየሱስ ሁሉንም ምዕመናን ያሳተፈ በቤተሰብ፣ ልጆች እና ወጣቶች ላይ ትኩረት ያደረገ ትምህርታዊ ኮንፈረንስ ተካሂዷል። በተቀሩት የቤተክርስቲያኒቱ ሲኖዶሶችም ተመሳሳይ ስልጠና ከሲኖዶሶች ጋር በመተባበር የሚቀጥል ይሆናል:: 📷 : Nahom, Dessie Congregation 🙏! EECMY Youth Ministry EECMY Children Ministry - MY Sunday School