fa
Feedback
The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus - EECMY

رفتن به کانال در Telegram

The Ethiopian Evangelical Church Mekane Yesus (EECMY) is a national Lutheran church with more than 10 million members.

نمایش بیشتر
3 497
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+157 روز
+11030 روز
آرشیو پست ها
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 5ኛው ዓመት ብሔራዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት ክብረ በዓል በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን ከሰኔ 8-14/ 2108 ዓ.ም በተለያዩ መር
የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ 5ኛው ዓመት ብሔራዊ የመጽሐፍ ቅዱስ ሳምንት ክብረ በዓል በሁሉም የቤተ ክርስቲያኒቱ ማኀበራነ ምዕመናን ከሰኔ 8-14/ 2108 ዓ.ም በተለያዩ መርሃግብሮች ይከበራል። የዘንድሮው ዓመት ክብረ በዓል "የእግዚአብሔር ቃል በሁሉም ቤተሰብ፥ በየዕለቱ" በሚል መሪ ቃል የሚከበር ሲሆን ስለ ቤተ ክርስቲያኒቱ የትርጉም አገልግሎት ይፀለያል፤ የቤተ ክርስቲያኒቱ መራሁት የመጽሐፍ ቅዱስ ንባብ(Lexical Bible Reading Calendar) አጠቃቀም ግንዛቤ ይሰጣል፤ እንዲሁም ለትርጉም አገልግሎቱ ሥጦታ የማሰባሰብ ሥራዎች ይሰራሉ። #National_Bible_Week_2026 #Lexical_Bible_Reading_Calendar

የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘደዎች አገልግሎት የየዕለቱ ጥቅሶች ከ1/10/2018 - 30/10/2018 ዘመነ የማርቆስ ወንጌላዊ 👉 Telegram:- https://t.me/YDRadio 👉 Our You
+1
የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘደዎች አገልግሎት የየዕለቱ ጥቅሶች ከ1/10/2018 - 30/10/2018 ዘመነ የማርቆስ ወንጌላዊ 👉 Telegram:- https://t.me/YDRadio 👉 Our You tube :- https://www.youtube.com/@Yemisrachdimtsradio/videos

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴዎች አገልግሎት የስብሐት ለአምላክ 1ኛ የመዝሙር መጽሐፍት አዳዲስ መዝሙሮች ታክለውበት ተሻሽሎና ታርሞ ተዘጋጅቶ ለስርጭት መብቃቱ ተገልጿል፡፡ የመዝሙር መጽሐፍቶቹም በኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ የምሥራች ድምፅ የመገናኛ ዘዴ አገልግሎት በመካኒሳ፣ በአድዋ ድል መታሰቢያ ሙዚየም፣ በመገናኛ፣ በቦሌ፣ በቢሾፍቱ እና በአዳማ የንዋየ ቅዱሳት ማከፋፈያዎች ማግኘት እንደሚቻልም አገልግሎቱ አስታውቋል፡፡ ለተጨማሪ መረጃና በብዛት በሲኖዶስ፣ በሰበካ እና በማኀበራነ ምዕመናን ለማዘዝ ከዚህ በታች የሚገኙትን አድራሻዎች መጠቀም ይቻላል። info@yemsrachdimth.org 0911454202 0911144165

Ibsi bal'aan haala yeroo irratti geggeessitoota Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaatiin Afaan Oromoo
+1
Ibsi bal'aan haala yeroo irratti geggeessitoota Waldaa Kiristaanaa Warra Wangeelaa Makaana Yesuus Itoophiyaatiin Afaan Oromootiin kenname guyyaa boruu irraa kaasee isiniif dhiyaachuu jalqaba. Ibsa kanarratti kaayyoon, qabiyyeenii fi barbaachisummaan xalayaa eegumsa amantootaa (Pastoral letter) karaa pirezidaantii waldattiitiin darbe murtoo waldattii bu'uura taasifachuudhaan haala ifa ta'een irratti mar'atameera. Dabalataan Sirna Waaqeffannaa guyyaa Dilbataa (Sanbata Guddaa) fi kan biroos ilaalchisee dhimmootni gaaffilee uuman garagaraa ka'anii mariin bal'aan hubannaa amantootaaf gargaaru taasifameera. Karaa toora YouTube WKWWMYI argachuu dandeessu. Ayyaannii fi Nagaan Gooftaa keenya Yesuus Kiristoos Isiniif Haa Baay'atu. Horaa Bulaa! https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=qZYcSIBJjzEyxQgo

#ሙሉውን_ማብራሪያ_ነገ_በቤተ_ክርስቲያኒቱ_ዩትዩብ ወቅታዊ ጉዳዮችን በተመለከተ የቤተ ክርስቲያን መሪዎች የሰጡት በሶስት ክፍል የተዘጋጀ ሰፊ ማብራሪያ ነገ ቅዳሜ ግንቦት 22 ቀን 2018 ዓ.ም ከማለዳው 4:00 ሰዓት ጀምሮ በቤተ ክርስቲያቱ የዩትዩብ(YouTube) አካውንት እንድከታተሉ ተጋብዛችኋል። ሰብስክራይ እያደረጋችሁ ጠብቁን :- https://youtube.com/@mekaneyesusofficial?si=mywds9KJe_tAx42i

የኢትዮጵያ ወንጌላዊት ቤተ ክርስቲያን መካነ ኢየሱስ ማዕከላዊ ሲኖዶስ 31ኛ ጉባኤውን በስኬት አካሂዷል። መቀመጫውን በምስራቅ ወለጋ ነቀም ከተማ ያደረገው የማዕከላዊ ሲኖዶስ 31ኛ መደበኛ ጉባኤውን ከሚያዝያ 14-16 ቀን 2018 ዓ.ም አካሂዷል። ጉባኤው "... ፀንታችሁ ቁሙ..." 2ኛ ተሰ 2፥15 በሚል መሪ ቃል ለሶስት ተከታታይ ቀናት የተካሄደ ሲሆን መደበኛ ተግባራቶቹን አካሂዷል። በጉባኤውም የሲኖዶሱን የዓራት አመታት ጉዞን አስመልክቶ በመሪዎች መርኀ ንግግር እና ሪፖርቶች ቀርበዋል። ውሳኔ እና የትኩረት አቅጣጫ በሚፈልጉ ጉዳዮችም ላይ ውጤታማ ውይይቶች ተካሂደዋል። ጉባኤውም ትኩረት ካደረገባቸው ጉዳዮች መካከል የሲኖዶሱ የወንጌል ማዳረስ ቅድሚ የተሰጠው ሲሆን በሰላም አስፈላጊነትና የምዕመናን አስተዋጽኦ ጉዳይ በስፋት ተመክሯል። ለሲኖዶሱ የቃሉ እና ቅዱሳት ሚጥራት አገልግሎት እንዲያግዝ ለ34 አገልጋዮች የቅስና ሀላፊነት በቤተ ክርስቲያኒቱ ፕሬዝዳንት ቄስ ዶ/ር ዮናስ ይገዙ የቅስና ሀላፊነት በጉባኤው ማጠቃለያ ተሰጥቷል። ለመጪ ዓራት ዓመታት ሲኖዶሱን በተለያዩ ሀላፊነቶች የሚመሩ መሪዎችን ጉባኤው መርጧል። በዚህም መሠረት፦ 1. ቄስ ገመቹ አብዲሳ የሲኖዶስ ፕሬዚዳንት 2. ቄስ አብዲ ፍቃዱ ምክትል ፕሬዚዳንት እና 3. አቶ ተመስገን ኤጀታ አቃቤ ንዋይ ሆነው ተመርጠዋል። በጉባኤውም ከፍተኛ የመንግሥት ተወካዮች፣ የአጎራባች ሲኖዶስ ፕሬዚዳንቶች እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል። 📷 የሲኖዶሱ ሚድያ