Addis Ababa Health Bureau / አዲስ አበባ ጤና ቢሮ / AACAHB /
رفتن به کانال در Telegram
ጤና ለሁሉም !! ይህ ቻናል የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ጤና ቢሮ የቴሌግራም ቻናል ሲሆን በከተማ አስተዳደሩ እስከ ጤና ጣቢያ ድረስ የተከናወኑ እንዲሁም ሀገራዊ ፣ አህጉራዊ እና አለማቀፋዊ የጤና መረጃዎች ተደራሽ የሚደረጉበት ነው፡፡
نمایش بیشتر7 341
مشترکین
+624 ساعت
+437 روز
+22030 روز
آرشیو پست ها
በአዲስ ከተማ ክፍለ ከተማ የዛሬ ሁለት ወር ያስጀመርነው የቅጠል ተራ የቤቶች ግንባታ በአስደናቂ ፍጥነት እየተሰራ ነው።
ዛሬ የቤቶቹን ግንባታ ሂደት በሳይቱ በመገኘት የገመገምን ሲሆን፣ የዛሬ ሁለት ወር የተጀመሩ ህንጻዎች 9ኛ ወለል ላይ መድረሳቸውን ተመልክተናል። ቦታውን ከማጽዳት ጋር በተያያዘ የዛሬ ወር የተጀመሩ ህንጻዎችም 4ኛ እና 5ኛ ወለል ላይ የደረሱ ሲሆን ከሁለት ሳምንት በፊት የግንባታውን ሂደት ተመልክተን የጨመርናቸው ሶስት ህንጻዎችም ጅማሮ በጥሩ ሂደት ላይ ይገኛል።
በፕሮጀክቶቹ የሚገነቡት መኖሪያ ቤቶች ብቻ ሳይሆኑ የንግድ፣ የጸጥታ፣ ትምህርት ቤት እና ጤና ተቋማት፣ የስፖርት ማዘዉተሪያ፣ የህፃናት መጫወቻ እና የመሳሰሉ ማህበራዊ አገልግሎት መስጫዎች እንዲሁም ሌሎች የህዝብ የጋራ መገልገያዎች እኩል ትኩረት ተሰጥቷቸዋል።
በመሆኑም የምንገነባው መኖሪያ ቤት ብቻ ሳይሆን ህጻናት ቦርቀው የሚያድጉበት፣ ወጣቶች የአካል እና የአዕምሮ ብቃታቸውን የሚያዳብሩበት፣ ዜጎቻችን አገልግሎቶችን በቅርበት የሚገኙበት እና ክብራችንን የሚያስጠብቅ ምቹና ፅዱ አካባቢን ነው።
በአጠቃላይ የቅጠል ተራ መኖሪያ መንደርን ትናንት ካስጀመርነው የገዳም ሰፈር እና በመሀሉ ላይ የሚገኘውን የጣልያን ሰፈር ጨምረን አገናኝተን በማልማት አካባቢውን የዘመነ አኗኗርና ሰፊ የስራ እድል የሚፈጥር አካባቢ እናደርገዋለን።
በምርጫ ወቅት ላይ ሆነን የፕሮጀክቶቹ ግንባታ ሳይቀዛቀዝ መቀጠሉ በማንኛውም ሁኔታ ውስጥ ነዋሪዎቻችንን በታማኝነት የማገልገል አቋማችን ፅኑ መሆኑን ያሳያል።
ህንጻዎቹን በጥራት እና በፍጥነት ገንብተው በተያዘላቸው ጊዜ እንዲጠናቀቁ እየሰሩ የሚገኙ አመራሮቻችንን፣ ሰራተኞቻችንን፣ ማህበራትን፣ ተቋራጮችን እና ሁሉንም ባለድርሻ አካላት አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
የመረጠንን ህዝብ የምናመሰግነው በቃላት ብቻ ሳይሆን ችግሩን የሚፈቱ ተጨባጭ ተግባራዊ ምላሽ በመስጠት ነው።
በተጣለብን በህዝብ እምነት ዳግም ኢትዮጵያን ለመምራት ተጨማሪ አምስት ዓመት ለፓርቲያችን ብልፅግና በተሰጠበት ማግስት በክረምት በጎ ፍቃድ አገልግሎት እጅግ የተጎሳቀለውን፥ ለኑሮ ምቹ ያልሆኑ መኖሪያ ቤቶችንና አካባቢውን ወደ ንፁህ ፥ውብ መንደር ለመቀየር ከከንቲባ ፅ/ቤት ጀርባ ላይ “ አራዳ የበጎነት መንደር “ግንባታን ጀምረናል።
በክረምት በጐ ፍቃድ 2500 ቤቶችን ለመገንባት ያቀድን ሲሆን ፣ዛሬ ባስጀመርነዉ የአራዳ የበጎነት መንደር ባለ 9 ወለል 8 ህንፃዎች እና ሁለት በላ 4 ወለል የገበያ ማዕከል ያሉት ሲሆን ፥ የተጎሳቆሉ ቤቶችን እና አካባቢውን በመቀየር ለኑሮ ምቹ የሆኑ ፣ ንጽሕናቸውን የጠበቁ የመኖሪያ ቤቶችና አካባቢዎች፣ የጋራ መገልገያዎችን እና አረንጓዴ ሥፍራዎችን እንዲሁም ህፃናት ቦርቀው የሚጫወቱባቸው የስፓርት ሜዳዎች በጥቅሉ ለሰው ልጆች ምቹና ክብር የሚመጥን ዘመናዊ አኗኗርን የሚፈጥር የከተማዋን ውበት የሚቀይር መንደር ነው።
በክረምት በጎ ፍቃድ የምንገነባው ቤት ብቻ ሳሆን አካባቢን እናፀዳለን፥ የጐርፍ መከላከያዎች እንገነባለን፣ ምንም ገቢ ለሌላቸው ማዕድ እናጋራለን፥ ደም ልገሳ እናካሄዳለን፥ የጀመርነው የአረንጓዴ አሻራ ችግኝ እንተክላለን፣ የማጠናከርያ ትምህርት እንሰጣለን፣ የነፃ ህክምና አገልግሎት ፣ የመንገድ ትራፊክ ማሳለጥ እንዲሁም ከተማችን ውብ ፥ ለኑሮ ምቹ ከተማ የማድረግ ስራችን እጠናክረን እንሰራለን።
የምንገነባው መተማመንን፣ ፅናትን፣ አብሮነትን፣ ወንድማማችነትን/ እህትማማችነትን፣ ክብራችንን በጥቅሉ የኢትዮዽያን የብልፅግና መንገድ ነው።
የከተማችን ባለሃብቶች የህዝባችን አኗኗር ለመቀየር በምንሰራቸው ልማቶች ሁሉ ስንጠራችሁ ቀና እና ፈጣን ምላሽ ስለምትሰጡን እጅግ አድርገን እያመሰገንን፤ ዛሬም ግንባታውን የጀመርነው የአራዳ የበጎነት መንደር አብራችሁ ለመገንባት ቃል የገባችሁ ሜድሮክ ኢንቨስትመንት ግሩፕ፥ የኢትዮዽያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት፣በላይነህ ክንዴ ፥ ያደታ ጁነዲን እያንዳንዳቸው አንድ ባለ 9 ወለል ህንፃ የሚገነቡ ሲሆን እንዲሁም ቲኤንቲ ኮንስትራክሽን፣ ግራንድ ሌጋሲ ሃውስ፥ ኢቲ ኦንላይን ኮሌጅ፣ አብይ ማስረሻ፥ ዴማ ሪልስቴት ፥ ቴምር ሪልስቴት፥ ስናፕ ትሬዲንግ፥ ጊፍት ሪልስቴት፥ መሃመድ አድናን ፥ አሚር በድሩ በጋራ ለመገንባት አብራችሁን ስለሆናችሁ በነዋሪዎች እና በራሴ ስም ከልብ አመሰግናለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያንና ህዝቦቿን ይባርክ
ከንቲባ ከዳነች አቤቤ
በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ብልጽግና ፓርቲ 438 የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት መቀመጫዎችን አሸነፈ
አዲስ አበባ በአረንጓዴ ልማት ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ በሚያደርጋት መስመር ላይ ናት - አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር
በአዲስ አበባ የተከናወኑ የአረንጓዴ ልማት ሥራዎች ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ የሚያደርጋትን መስመር እንድትይዝ አስችለዋል አሉ የፌደሬሽን ምክር ቤት አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የ2018 ዓ.ም አረንጓዴ ዐሻራ የማስጀመሪያ መርሐ ግብር ‘‘ተስፋን እንትከል’’ በሚል መሪ ሀሳብ በዛሬው ዕለት ተካሂዷል፡፡
አፈ ጉባኤ አገኘሁ ተሻገር በዚሁ ወቅት እንዳሉት፥ እንደ ሀገር በአረንጓዴ ዐሻራ መርሐ ግብር የተከናወኑ ሥራዎች ከአካባቢ ጥበቃ ባለፈ ለዘላቂ ልማት አይተኬ ሚና እያበረከቱ ነው፡፡
ሀገራዊ ንቅናቄው በተቋም ደረጃ በተቀናጀ ሁኔታ እየተሰራ መሆኑ ሥራውን ይበልጥ ውጤታማ እንዳደረገው ጠቅሰው፥ በዚህም ዓለም አቀፍ እውቅና መገኘቱን አስታውሰዋል፡፡
በዚሁ የአረንጓዴ ልማትና ውበት ሥራ አማካኝነት አዲስ አበባ በአፍሪካ ደረጃ በምሳሌነት የምትጠቀስ ከተማ እየሆነች መምጣቷን አውስተዋል፡፡
ከተማዋ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪ በሚያደርጋት መስመር እየተጓዘች ነው ያሉት አፈ ጉባኤው፥ በተለይም በአረንጓዴ ልማት የተገኘውን ውጤት አጠናክሮ ለማስቀጠል በላቀ ትኩረት መስራት እንደሚገባ አስገንዝበዋል፡፡
ሁሉም ዜጋ የተጀመረውን የአረንጓዴ አሻራ ንቅናቄ በላቀ ተነሳሽነት በመቀላቀል ለሀገር ዘላቂ ልማት የበኩሉን አስተዋጽኦ እንዲያበረክት ጥሪ አቅርበዋል።
ነገ ሰኔ 15/2018 ዓም በወርቃማው ሰኞ አቶ ዘላለም ይትባረክ የተቋም ግንባታ እና የሰራተኞች ባህሪ /በህይወት እስካለን ለሀገራችን፣ ለራሳችን ምን አስተዋጽኦ ማበርከት አለብን / በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ግንዛቤ ይሰጡናል ። በመሆኑም ጠዋት 2:00 ሰዓት በ5ኛ ፎቅ መሰብሰቢያ አዳራሽ እንድትገኙ እናሳስባለን ።
እንኳን ለ2018 ዓ.ም የጋራ አሻራ ማኖር አደረሳችሁ !!
ተስፋን እንትከል!
በጋራ ሆነን የአረንጓዴ አሻራን በማኖር ስራችን ሀገራችን ዘመን የማይሽረው ታሪክ አስቀምጣለች።
ባለፉ ሰባት ዓመታት እንደሀገር በሁሉም ኢትዮጵያዊ ትብብር 48 ቢሊዮን ችግኝ በመትከል ታሪካዊ እና አስደማሚ አሻራ አኑረናል። በከተማችንም ባለፋት ሰባት ዓመታት 90 ሚሊዮን ችግኞችን በመትከል የአረንጓዴ ሽፋናችንን እጅግ ዝቅተኛ ከነበረበት 2 .8 በመቶ ወደ 24 በመቶ ማድረስ ችለናል።
በአረንጓዴ አሻራ መረሃ ግብራችን የተራቆቱ አካባቢዎች አረንጓዴ ለብሰዋል፤ የነጠፉ ወንዞች እና አካባቢዎች ማንሰራራት ችለዋል። አዲስ አበባችንም ንፁህ፣ ውብ፣ ለመኖር ምቹ እና የቱሪስት ማዕከል መሆን ችላለች።
የምንተክለው ተስፋን፣ ልማትን፣ ልምላሜን፣ ጥላን፣ ምግባችንን ብሎም ብልፅግናን ነው። የምንተክለዉ ለዛሬ ጥቅማችን ብቻ ሳይሆን ለትውልድ እዳን ሳይሆን የልምላሜና የብልፅግና ምንዳን ለማውረስ ነው ።
ዛሬ በከተማችን 6 ሚሊዮን ችግኞችን ለመትከል የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈጉባኤ ክቡር አቶ አገኘሁ ተሻገር በተገኙበት በበሻሌ ወንዝ ዳርቻ የማስጀመሪያ መርሃ ግብር አካሂደናል። ውድ የከተማችን ነዋሪዎች በወንዝ ዳርቻዎች፤ በጤና፣ ትምህርትና በሃይማኖት ተቋማት፤ በግል ሴክተሮች እና በጎዳናዎች ለምግብነት የሚውሉ አትክልት እና ፍራፍሬዎችን፣ የጥላ እና የውበት ዛፎችን በመትከል ከተማችን ውብ፣ ጽዱ ኢረንጓዴና ለኑሮ ምቹ ከተማ ለማድረግ እንደ ከዚህ ቀደሙ ሁሉ ህፃን አዋቂ ሳንል ሁሉም ዜጋ በጋራ በመሆን እንድናሳካው ጥሪዬን አስተላልፋለሁ።
ችግኝ መትከል ብቻ በቂ አይደለም እንክብካቤን ይፈልጋል ። ስለሆነም የተከልናቸውን ችግኞች መከታተል፤ መንከባከብ ይኖርብናል።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
ዛሬ የክረምት በጎ ፈቃድ አገልግሎትን በጽዳት ንቅናቄ አስጀምረናል ።
የአንድ ከተማ ዓለም አቀፍ መለኪያው ፅዳት፣ ውበት እና ኢረንጓዴነት ነው። ለዚህም ነው ውብ፣ ፅዱ እና አረንጓዴ ከተማን ለመፍጠር ህዝባችንን አሳትፈን ባለድርሻ አካላትን በማነቃነቅ ውጤታማ ስራ ሰርተን አዲስ አበባን በአፍሪካ ከ10 ፅዱ ከተሞች እንዷ ለማድረግ የቻልነው።
አዲስ አበባ ከዚህ በፊት የምትወቀስበት ፅዱ እና ውብ አለመሆኗን እና የአረንጓዴ ከተማን ሽፋንዋ እየቀነሰ መሄዱን በሰራናቸው ተከታታይ ስራዎች መቀልበስ ችለናል።
ፅዳት የዘወትር ስራ ነው፤ ፅዳት ባህል መሆን መቻል አለበት። ሁልጊዜ ከህይወታችን እየንዳንዱ እንቅስቃሴ ጋር የተሳሰረ መሆኑን በሁሉም አካባቢ ማረጋገጥ ይኖርብናል።
ጽዳት ከቤት ይጀምራል። በመሆኑም ሁላችንም በየአካባቢያችን፤ በየተቋማችን ባህል አድርገን መያዝ ይገባናል። ይህንን ባህል እስኪሆን ያለእረፍት በትጋት በመስራት፣ ሁሌም ክትትል በማድረግ የፅዳት አምባሳደር እንድንሆን አደራ ማለት እፈልጋለሁ።
ፈጣሪ ኢትዮጵያን እና ህዝቦቿን ይባርክ!
ከንቲባ አዳነች አቤቤ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
