🇪🇹አዲስ ዜና ከምንጩ
440
مشترکین
+324 ساعت
+167 روز
+4930 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
በትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ
በድሬዳዋ አሥተዳደር ጀሎ በሊና ቀበሌ ቢርካ አካባቢ ሌሊት 6፡30 ገደማ በደረሰ የትራፊክ አደጋ የ11 ሰዎች ሕይወት አለፈ፡፡
ከሟቾች በተጨማሪም በ10 ሰዎች ላይ የአካል ጉዳት መድረሱን ድሬዳዋ አሥተዳደር ፖሊስ መረጃ አመላክቷል፡፡
አደጋው የደረሰው ከድሬዳዋ ወደ ሐረር ሰው አሳፍሮ ሲጓዝ የነበረ በተለምዶ “ዶልፊን” የሚባለው ሕዝብ ማመላለሻ በተቃራኒ መስመር ይጓዝ ከነበረ በተለምዶ “ሲኖትራክ” ተብሎ ከሚጠራው የደረቅ ጭነት ተሸከርካሪ ጋር በመጋጨታቸው መሆኑ ተገልጿል፡፡
#NationalExam
የተፈጥሮ ሳይንስ የ2016 የ12ኛ ክፍል ብሔራዊ ፈተና ዛሬ መሰጠት ተጀመረ።
ፈተናው ለሶስት ተከታታይ ቀናት ነው በወረቀት እና በኦንላይን የሚሰጠው።
Photo unavailableShow in Telegram
#NATIONAL_EXAM
ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ሀገር አቀፍ መልቀቂያ ፈተና ዛሬ መሰጠት ይጀምራል።
ሁለተኛው ዙር የተፈጥሮ ሳይንስ ተማሪዎች የ12ኛ ክፍል ፈተና ከዛሬ ሐምሌ 9/ 2016 ዓ.ም ጀምሮ ለሦስት ተከታታይ ቀናት በወረቀት እና በኦንላይን እንደሚሰጥ ይታወቃል።
በዛሬው የመጀመሪያ ቀን ፈተና የእንግሊዝኛ እና የሒሳብ ትምህርት ፈተናዎች ይሰጣሉ።
በተመሳሳይ በትግራይ ክልል ሁለተኛው ዙር የ12ኛ ክፍል ፈተና ከዛሬ ሐምሌ 9/2016 ዓ.ም ጀምሮ ለአራት ተከታታይ ቀናት በመቐለ፣ ራያ፣ አዲግራት እና አክሱም ዩኒቨርሲቲዎች ይሰጣል፡፡
የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ለአዲሱ በጀት ዓመት የ230 ነጥብ 39 ቢሊዮን ብር ረቂቅ በጀት ለከተማዋ ምክር ቤት ማቅረቡን ቢቢሲ አማርኛ ዘግቧል።
ረቂቅ በጀቱ፣ የከተማዋ አስተዳደር ተጨማሪውን በጀት ጨምሮ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ከተጠቀመው አጠቃላይ በጀት የ68 ነጥብ 3 ቢሊዮን ብር ጭማሪ እንዳለው ከአስተዳደሩ ፋይናንስ ቢሮ መስማቱን ዘገባው ጠቅሷል።
ከአዲሱ ረቂቅ በጀት 62 በመቶውን ድርሻ የሚይዘው የካፒታል ወጪው እንደኾነና 38 በመቶው ደሞ ለመደበኛ ወጪዎች እንደተመደበ ዜና ምንጩ አመልክቷል።
Photo unavailableShow in Telegram
የግል ተፈታኞች ቅሬታና የትምህርት ሚኒስቴር ምላሽ
ባለፈው ወር የተሰጠውን የመውጫ ፈተና የወሰዱ የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተማሪዎች ከፈተናው ጋር ተያይዞ ያላቸውን ቅሬታ አቅርበዋል።
"የመንግሥት እና የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት እኩል ፈተናውን ወስደው፣ ውጤት ለምን በተለያየ ጊዜ ተገለፀ?" "የመንግሥት ተፈታኞች በብዛት ሲያልፉ በርካታ የግል ተቋማት ተፈታኞች ለምን ወደቁ?" "እያንዳንዳቸው አንድ አንድ ነጥብ ያላቸው መቶ ጥያቄዎች ተፈትን 37.92 አይነት ውጤት እንዴት ተመዘገበ?" የሚሉ ጥያቄዎች በተፈታኞቹ ተነስቷል።
#ቲክቫህ_ዩኒቨርሲቲ በትምህርት ሚኒስቴር የግል ከፍተኛ ትምህርት ተቋማት አገልግሎት ዴስክ ኃላፊ የሆኑትን እዮብ አየነው (ዶ/ር) ጠይቋል።
ከውጤት ነጥብ ጋር በተያያዘ ለተነሳው ጥያቄ ኃላፊው ተከታዩን ብለዋል፦
1. የጤና ትምህርት ዘርፍ ሁለት ፈተና (ጠዋት ከ100 ከሰዓት ከ100 በድምሩ ከ200) ስለሚፈተኑና ለማለፊያ የሁለቱ ፈተናዎች ውጤት ተደምሮ አማካኝ ውጤት ስለሚያዝ ውጤታቸው በነጥብ ሊቀመጥ ይችላል፡፡
2. አንዳንድ የትምህርት ፕሮግራሞች ለምሳሌ ሒሳብ እና ማርኬቲንግ ማኔጅመንት በተለያዩ ምክንያቶች ተማሪዎች የተፈተኑት ጥያቄ ቁጥር ከመቶ ያነሰ ስለነበር ያገኙት ውጤት ወደ መቶ ሲቀየር በነጥብ ሊቀመጥ ይችላል፡፡
"ውጤት ሲገለፅ የጊዜ መቀዳደም ካልሆነ በስተቀር በሲሰተሙ ላይ ምንም አይነት ችግር እንዳልነበረ" ኃላፊው አረጋግጠዋል።
የማለፍ ምጣኔን በተመለከተ "ተፈታኞቹ የተማሩባቸውን ተቋማት እንዲሁም የራሳቸውን ብቃት መመልከት" አለባቸው ብለዋል።
ያስፈተኗቸውን ተማሪዎች 100% ያሳለፉ የግል ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት እንዳሉ ኃላፊው ገልፀዋል።
Photo unavailableShow in Telegram
#DigitalSkill
እንደ ዓለም ባንክ ትንበያ በ2030 እ.አ.አ ከሰሃራ በታች ባሉ የአፍሪካ ሀገራት ከ230 ሚሊዮን በላይ የዲጂታል ሥራዎች ይፈጠራሉ ተብሎ ይጠበቃል። እነዚህ የሥራ ዕድሎች በፍጥነት በማደግ ላይ ባለው የዲጂታል ኢኮኖሚ አማካኝነት የሚፈጠሩ ናቸው።
እነዚህን እድሎች በአግባቡ ለመጠቀም መካከለኛ እንዲሁም የላቀ የዲጂታል ክህሎት መኖር ግድ ይላል። በተጨማሪም መሰረታዊ የፋይናንስ እና የዲጂታል እውቀት በእጅጉ ያስፈልጋል።
አሁን ላይ በአህጉሪቱ ከፍተኛ የዲጂታል ክህሎት ክፍተት ከመኖሩም በተጨማሪ በጾታ መካከል ያለው ልዩነት ሰፊ ነው። የቴክኖሎጂ ልምምድ አናሳ መሆን በተለይ ደግሞ በፐብሊክ ሴክተሩ ያለው ደካማ የዲጂታል ክህሎት በፍጥነት ከሚጓዘው የቴክኖሎጂ እድገት ጋር የማይጣጣም ነው።
የአሁን ላይ ባለው የዲጂታል እድገት የሥራው ዓለም በፍጥነት እየተቀየረ መጥቷል። በዚህም በሚቀጥሉት 10 ዓመታት በዓለም አቀፍ ደረጃ ከ10 ስራዎች 9ኙ የሚሆኑት የዲጂታል ክህሎቶችን እንደሚፈልጉ ይገመታል።
ለዚህ ደግሞ የትምህርት ሥርዓቱን ማሻሻል፤ በምን፣ እንዴት፣ እና በማን የሚሉ ጥያቄዎችን የሚመልስ ግልጽ የፖሊሲ ሥርዓት ያስፈልጋል። በተጨማሪም ህጻናት በትምህርት ቤታቸው እንዲህ አይነቱን ክህሎት እንዲያገኙ ማስቻልና ልዩ ልዩ ንቅናቄዎችን መፍጠር አስፈላጊ ነው።
Photo unavailableShow in Telegram
ለጥንቃቄ‼️
በኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ የዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ ማዕከል ከሚደርሱ የወንጀል ጥቆማዎች መካከል ከፍተኛውን ቁጥር የያዘው አጭበርባሪዎች ከባንክ የተደወለ በማስመሰል ‘'የሞባይል ባንኪንግ አገልግሎትን እናስተካክላለን’' በሚል እና ሌሎች አሳሳች መልዕክቶችን በመጠቀም በባንክ ደንበኞች ሂሳብ ላይ የሚፈፀም ስርቆት መሆኑን ፖሊስ በቅርቡ ሥራ ላይ በዋለው ዘመናዊ ቴክኖሎጂ ማረጋገጡን አስታውቋል፡፡
በባንኮች አሠራር መሰረት ከሞባይል ባንኪንግ አገልግሎት ጋር በተያያዘ ደንበኞች ወደ ባንክ ቅርንጫፍ በአካል ሳይሄዱ በስልክ ተደውሎ የሚሰጥ ምንም ዓይነት አገልግሎትም ሆነ የአሠራር ሂደት እንደለለ ባንኮች ለፖሊስ አሳውቀዋል።
በመሆኑም የባንክ ደንበኞች በስልክ የሚደርሱ ማናቸውንም ዓይነት ጥያቄዎች እንዳያስተናግዱ እና ከአጭበርባሪዎች ገንዘባቸውን እንዲጠብቁ እንዲሁም መሰል የማጭበርበር ድርጊቶች ሲያጋጥሙ የተደወለበትን ስልክ ቁጥር በዜጎች ተሳትፎ መተግበሪያ (EFPApp) የፎቶ፣ የቪዲዮ እና የፅሁፍ መረጃ በመላክ ወይም በ991 ነፃ የስልክ መስመር ላይ በመደወል ጥቆማ እንድትሰጡ የኢትዮጵያ ፌደራል ፖሊስ ጥሪውን አቅርቧል።
Photo unavailableShow in Telegram
የየመን ሀውቲ ታጣቂዎች በኤደን ባህረ ሰላጤ እና በእስራኤል ኢላት ወደብ ጥቃት መክፈታቸውን ገለጹ
ቃል አቀባዩ እንደገለጸው የአሁኑ የሀውቲ ጥቃት እስራኤል በካን ዮኒስ የፈጸመችውን እና ቢያንስ 90 ሰዎች የገደሉበትን ጥቃት ለመበቀል ነው።
ሴቶች ሀብታም ወንድ እንዲያገቡ የምታሰለጥነው ቻይናዊት በአመት 19 ሚሊየን ዶላር እያገኘች ነው
July 15, 2024
አስተምሮዋ የማህበረሰቡን ወግና ባህል ይቃረናል የሚል ተቃውሞ ቢበዛባትም የህይወት መስመራችን አስተካክላለች የሚሉ ደጋፊዎችም አሏት
በቻይና ሴቶች እንዴት ሀብታም ወንዶችን ማግባት እንደሚችሉ የምታሰለጥነው ወጣት ሀብት እያካበተች ነው ተባለ።
“ኩ ኩ” በሚለው የማህበራዊ ገጽ ስሟ የምትታወቀው ለ ቹዋንጉ ባለፈው አመት ነው የማህበራዊ ሚዲያውን የተቆጣጠረችው።
አወዛጋቢዋ የኢንተርኔት ተጽዕኖ ፈጣሪ በአጭር ጊዜ በርካታ ተከታዮችን ያፈራች ሲሆን፥ የምታነሳቸው ሃሳቦች ግን እንደ ዌይቦ ካሉ የማህበራዊ ትስስር ገጾች እንድትታገድ አድርጓታል።
“ኩ ኩ” የፍቅር ግንኙነትም ሆነ ትዳር ገንዘብ የሚገኝበት “ማህበረሰባዊ መሰላል ነው” ብላ ታምናለች።
የመጀመሪያ የፍቅር ቀጠሮ ዕለት መክፈል ያለበት ማን ነው?
የአሜሪካውን ግዙፍ አማካሪ ተቋም ስያሜ ተውሳም “የፍቅር ግንኙነት ማኬንሲ” ነኝ ብላ ራሷን የምትጠራው ለ ቹዋንጉ፥ በምትለቃቸው ቪዲዮዎች ሁሉም የፍቅር ግንኙነቶች ጥቅም(ገንዘብ) ሊያስገኙ ይገባል እያለች ስትሞግት ትደመጣለች።
“የትኛውም የፍቅር ግንኙነት ጥቅሜን የሚያሳድግና ቀጣይ ህይወቴን የሚያቀና መሆን አለበት” ስትልም ትገልጻለች።
የቀድሞዋ ዘፋኝ የአሁኑ የፍቅር አጋሯን እንዴት እንደመረጠችው ስትገልጽም 4 ሚሊየን ዩዋን (550 ሺህ በላይ ዶላር) ጥሎሽ እንደሚሰጣት እንደነገራት ታወሳለች።
አድናቂዋ እና የትዳር አጋሩ እንድትሆን የጠየቃት በ15 አመት የሚበልጣት ሰውም በየወሩ 4 ሺህ ዶላር ሊሰጣትና 2 ነጥብ 8 ሚሊየን ዶላር የሚያወጣ ቤት በሻንጋይ ሊገዛላት ቃል ገብቶ እንደነበር ነው የገለጸችው።
ይሁን እንጂ ከገንዘቡ ይልቅ የወደፊት ህልሙ ያሳመነኝ የአሁኑ ፍቅረኛየ በመሆኑ ከእርሱ ጋር መቀጠልን መርጫለሁ ብላለች።
በአንድ በኩል ገንዘብን አሳዱ እያለች እየመከረች ለራሷ ሲሆን ግን ፍቅርን አስቀድማለች የሚሉ ትችቶች ቢሰነዘሩባትም “ፍቅረኛየ ነገ የምፈልገውን እንደሚያሳካልኝ ስላመንኩ ነው” የሚል አጭር ምላሽ ትሰጣለች።
“ኩ ኩ” በኦንላይን ለሚከተሏት ሰዎች ነቀፌታ የበዛበትን አስተምሮዋን ለማስተላለፍ “ገንዘብ” እና “እርግዝና” ለሚሉ ቃላት የራሷን አዳዲስ ቃላት የፈጠረች ሲሆን፥ የማህበራዊ ትስስር ገጿን ከመዘጋት ለመታደግ ሰው ሰራሽ አስተውሎትንም ትጠቀማለች።
የፍቅር ግንኙነትም ሆነ ትዳር ጥቅም የሚጋራበት ነው ብላ የምታምነው በግል እና በተለያዩ መድረኮች እየተገኘች የማማከር ስራ እየሰራች ነው ብሏል ሳውዝ ቻይና ሞርኒንግ ፖስት በዘገባው።
በአመት 142 ሚሊየን ዩዋን (19 ሚሊየን ዶላር በላይ) እያገኘች ነው የሚለው ዘገባው በቀጥታ ስርጭቷ ምክር ለማግኘት 155 ዶላር እንደምታስከፍል ያነሳል።
“ውጤታማ ግንኙነት” ለሚለው ታዋቂ ስልጠናዋ ደግሞ 480 ዶላር ታስከፍላለች።
በግል ወጣቷን አግኝቶ ለማነጋገር በየወሩ ቢያንስ 1400 ዶላር መክፈል ይጠበቅበታል የሚለው ዘገባው፥ የቹዋንጉ ጉዳይ ቻይናውያንን ለሁለት መክፈሉን ይጠቅሳል።
አስተምሮዋ የማህበረሰቡን ወግና ባህል ይቃረናል የሚል ተቃውሞ የሚያነሱባት እንዳሉ ሁሉ የህይወት መስመራችን አስተካክላለች የሚሉ ደጋፊዎቿ ቁጥርም ቀላል የሚባል አይደለም።
ከምታማክራቸው ሰዎች የምታገኘው ገንዘብም የተከታዮቿን መበራከት ያሳያል ነው የሚለው።
ሴቶች ሀብታም ወንድ እንዲያገቡ የምታሰለጥነው ቻይናዊት በአመት 19 ሚሊየን ዶላር እያገኘች ነው
የቀድሞዋ ዘፋኝ “ገንዘብን አሳዱ” እያለች ከምትመክራቸው ሰዎች ጠቀም ያለ ገንዘብ እያገኘች ነው ተብሏል።
یک طرح متفاوت انتخاب کنید
طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.