fa
Feedback
Ebenezer prayer ministry የአቤንኤዘር የፀሎት ሚኒስትሪ

Ebenezer prayer ministry የአቤንኤዘር የፀሎት ሚኒስትሪ

رفتن به کانال در Telegram

+251944081068 "አቤንኤዘር" "ወደ ፈተና እንዳትገቡ ትጉና ፀልዪ"

نمایش بیشتر
771
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
+2230 روز
آرشیو پست ها
73 ኃይል ያለው በጉልበት ላይ ነው ዘማሪ ተፈራ ወ/ማርያም ኃይል ያለው በጉልበት ላይ ነው /2*/ መንበርከክ መፀለይ ካለ ሁሉም ነገር በእጃችን አለ 1.ሙሴ በኮሬብ ተራራ እግዚአብሄርን ያናገረው በደመና ውስጥ ተከብቦ ክብሩን ማየት የቻለው አርባ ቀንና አርባ ሌሊት በመፆም በመፀለይ ነው -- ኃይል ያለው -- 2.ሐና ለረጅም ዓመታት በምላስ ዱላ ተመትታ ጣውንቷ ስታስጨንቃት ሁል ጊዜ ጧትና ማታ ለአምላኳ ነግራ አልቅሳ ሳሙኤልን ሰጣት ጌታ -- ኃይል ያለው -- 3. ኤልያስ ሦስት ዓመት ሙሉ ዝናብ እንዳይወርድ የዘጋው በእምነት በፀሎት ኃይል ነው አመፀኛውን ሕዝብ የቀጣው ለነገሥታትና ለአህዛብ የአምላኩን ክንድ የገለጸው -- ኃይል ያለው -- 4.በአንበሳ ጉድጓድ ውስጥ አድሮ ዳርዮስ ጠርቶ የጠየቀው ዳንኤል አሳደረህ ወይ አምላክህ የምታመልከው አዎን ድኜ አድሬአለሁ አምላኬን አከብረዋለሁ -- ኃይል ያለው --

23 ዓይኖቼን ምራ ዘማሪ ኢያሱ ረጋሳ ዓይኖቼን ምራ ኢየሱስ አምላኬ መስቀልህ ጋ በስባሹን ሥጋ እያየሁ እንዳልጥል የአንተን ፀጋ በሐዘኔም በደስታ ልማጸነው ደጅህን ባንተው ቀን እስከማየው መልካሙን ፈቃድህን 1. የታረድከው በግ የሱስ የእኔ ልዩ ፍቅረኛ ሲጨንቀኝ የማዋይህ ማታዳላ እረኛ ዘወትር ስትሰጠኝ ሳለ የሚያስፈልገኝን በቅጽበት አነሳሁኝ ከመስቀልህ ዓይኖቼን -- ዓይኖቼን ምራ -- 2. በሰው ልጅ ከመታን በእግዚአብሔር መታመን እጅግም ደስ ያሰኛል ይመልሳል ልብን በስባሹን ሥጋ ማየት ያመጣል ትዕቢትን ትዕቢትም ትቀድማለች ሳይታወቅ ውድቀትን -- ዓይኖቼን ምራ -- 3. ዳግም ማረኝ እላለሁ ጌታ ሆይ ጥፋቴን ሟችና ጠፊውን ገላ አትኩሬ ማየቴን ወደ ሞት እንዳይነዳኝ ጠላት መረቡን ጥሎ አንተን ማየት አይሳነኝ ሰው መስቀልህን ከልሎ -- ዓይኖቼን ምራ -- 4. ለካስ ሰው ሁሉ ሰው ነው እንደ እኔ ኃጢአተኛ ሚዛኑ የሚያዳላ ፊት አይቶ ፈራጅ ዳኛ ከአንተ እንዳይለየኝ የሱስ ዓይኔ ሰዎችን ለምዶ መስቀልህን ያለማምደኝ መንፈስ ቅዱስህ ወርዶ -- ዓይኖቼን ምራ --

ሊነጋጋ ሲል ኢየሱስ በማለዳ ተነስቶ ወጣ ለመጸለይም ወደ አንድ ገለልተኛ ቦታ ሄደ ሌሊቱ ሲነጋ ጐህ ሲቀድ አእዋፍ ሲንጫጩ በአንድነት በዜማ ፈጣሪን ለማምለክ ሲወጡ ሁሉም ከያሉበት እኔ ግን መኝታዬ ሞቀኝ ዝምብለሽ ተኚ ተኚ ቢለኝ መኝታዬን ወዲያ ገፍፌ ለጸሎት ነቃሁኝ ከእንቅልፌ ለጸሎት መንፈሴ ሲነቃ ሥጋዬ ባይደሰት ቢከፋ ሳይወድ በግዱ ያብርና መጸለዬ ይቀጥላል ገና ስሙን ስጠራው የጌታዬን ያድሰዋል ደካማው ጐኔን ቅባቱ መፍሰስ ይጀምራል ለጸሎት ጉልበቴን ያድሳል አዝ፦ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ መች አፍሬ አውቃለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ ድልን አግኝቻለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ መልስን አግኝቻለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ እንደሚሰማ አምናለሁ አንዳንዴ ውስጤ ጸልይ ሲለኝ ስጋዬ ግን ሲያታልለኝ ቆይ ትጸልያለህ በኋላ እያለ ጊዜዬን ሊበላ ግን ዳንኤልን ጉድጓድ ያስጣለው አትጸልይ የሚል ህግ ነው ቢያስመርጡት ከምንም ነገር ጸሎት ነው ለእርሱ ትልቅ ነገር ይህንን ሳስታውስ እነቃለሁ ስጋዬን ተወኝ እለዋለሁ ስታዘዝ ለነቃው መንፈሴ ለጸሎት ተጋልኝ ጉልበቴ ጸሎት ትልቅ መሳሪያዬ ነው ሰይጣንም ይሄ ስለገባው እንዳልጸልይ ቢታገለኝም ምክኒያትን ለሥጋዬ አልሰጥም አዝ፦ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ መች አፍሬ አውቃለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ ድልን አግኝቻለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ መልስን አግኝቻለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ እንደሚሰማ አምናለሁ አንተ ግን ስትጸልይ ወደ እልፍኝህ ግባ መዝጊያህንም ዘግተህ በስውር ላልው አባትህ ጸልይ በስውር የሚያይ አባትህም በግልጥ ይከፍልሃል ግራ ሲገባኝ በሕይወቴ መምበርከክ ሲያቅተው ጉልበቴ ተስፋ በመቁረጥ ውስጥ ስሞላ መፍትሄ መልስን ሳጣ መላ ከመጸለይ ይልቅ በፊቱ ሳወራ ላገኘሁት ሁሉ ይባባስብኛል ችግሬ ያጐብጠኛል ያ ጠብቆ ቀምበሬ ግን በሬን ዘግቼ ስገባ የውስጤን ሁሉ ወደ ሚረዳ በጸሎት ዙፋኑ ስር ስወድቅ ይታደሳል ውስጤ በድንገት ያልወጣሁት ችግር ጸልዬ ፍፁም የለምና በሕይወቴ ባልጸልይ እራሴን እጐዳለሁ ይህንን በተግባር አውቃለሁ አዝ፦ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ መች አፍሬ አውቃለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ ድልን አግኝቻለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ መልስን አግኝቻለሁ እጸልያለሁ (፫x) በፊቱ ወድቄ ለምኜ እንደሚሰማ አምናለሁ

እጅግ በጣም ጥልቅ የእምነትና የተስፋ ፀሎት ነው። ምስጋናዬ ነው > "እግዚአብሔር ሆይ፤ ፈውሰኝ፤ እፈወሳለሁ፤ አድነኝ እኔም እድናለሁ፤ አንተ ምስጋናዬ ነህና።" — ኤርምያስ 17፥14 1. እውነተኛ ፈውስ ከእግዚአብሔር ይመጣል ኤርምያስ "ፈውሰኝ" ሲል ወደ ሰው አልተመለከተም፤ ወደ እግዚአብሔር ተመለከተ። የልብ፣ የአእምሮ፣ የመንፈስ እና የአካል ፈውስ ምንጩ እግዚአብሔር ነው። 2. የእግዚአብሔር ፈውስ ፍጹም ነው "ፈውሰኝ፤ እፈወሳለሁ" የሚለው ቃል ሙሉ እምነትን ያሳያል። እግዚአብሔር ሲፈውስ ፈውሱ እውነተኛና ዘላቂ ነው። የሰው መፍትሔ ጊዜያዊ ሊሆን ይችላል፤ የእግዚአብሔር ግን ሥር የሰደደውን ችግር ይፈውሳል። 3. ድነት የሚገኘው በእርሱ ብቻ ነው "አድነኝ እኔም እድናለሁ" የሚለው ቃል ከኃጢአት፣ ከፍርሃት፣ ከጠላት እና ከዘላለማዊ ጥፋት መዳን በእግዚአብሔር ብቻ እንደሚገኝ ያሳያል። 4. ምስጋና የተስፋ ውጤት ነው "አንተ ምስጋናዬ ነህና" የሚለው ኤርምያስ እግዚአብሔርን ለሚያደርገው ብቻ ሳይሆን ስለማንነቱ እንደሚያመሰግነው ያሳያል። እውነተኛ ምስጋና ከእምነት ይመነጫል። ለስብከት 3 ነጥብ ርዕስ፦ "ፈውሰኝ እፈወሳለሁ" 1. የፈውስ ምንጭ – እግዚአብሔር 2. የድነት ዋስትና – እግዚአብሔር 3. የምስጋና ምክንያት – እግዚአብሔር መደምደሚያ፦ ሰው ሊረዳ ይችላል፣ ግን ሊፈውስ አይችልም፤ ሰው ሊያበረታ ይችላል፣ ግን ሊያድን አይችልም። ኤርምያስ እንዳለው፣ ፈውስና ድነት ከእግዚአብሔር ሲመጡ ፍጹም ናቸው። ስለዚህ በሁሉም ሁኔታ ወደ እርሱ እንጮኽ፦ "እግዚአብሔር ሆይ፣ ፈውሰኝ፤ እፈወሳለሁ፤ አድነኝ፤ እድናለሁ።" አሜን።

አዲስ አበባ አቀፍ የወጣቶች ካምፕ ኮንፈረንስ 📍ቦታ፡ አቃቂ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ት/ቤት ⌚️ቆይታ፡ ለ10 ቀናት 📅ቀን፡ ከሐምሌ 8 እስከ 19፣ 2018 ዓ.ም. ይህ የወጣቶች ካምፕ ኮንፍረንስ
አዲስ አበባ አቀፍ የወጣቶች ካምፕ ኮንፈረንስ 📍ቦታ፡ አቃቂ ሰባተኛ ቀን አድቬንቲስት ት/ቤት ⌚️ቆይታ፡ ለ10 ቀናት 📅ቀን፡ ከሐምሌ 8 እስከ 19፣ 2018 ዓ.ም. ይህ የወጣቶች ካምፕ ኮንፍረንስ ለዚሁ ስልጠና ✈️ ከአሜሪካ የሚመጣው ወንድማችን አንድሬ ዋለርን ጨምሮ ከምንወዳቸው 🤗 አስተማሪዎች ዘውዱ ሰብለወርቅ፣ ጥበበሥላሴ መንግሥቱ፣ ገለቶ ገመቹ እና አቤኔዘር ወርቁ ጋር ለአስር ተከታታይ ቀናት ልዩ የደቀመዝሙርነት ስልጠና የሚሰጥበት ፕሮግራም ነው፡፡ ⚠️ያለን ቦታ እጅግ ውስን ስለሆነ ቀድመው ለሚመዘገቡ ወጣቶች ቅድሚያ እንሰጣለን፡፡⚠️ 📝ለመመዝገብ ይህንን ፎርም👆🏽 ይሙሉ እና የሚጠየቁትን ጥያቄዎች ሁሉ በአግባቡ ይመልሱ፡፡

🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏 01320430028002  AB 1000571918033 CBE lulseged kifle &/ Wakoye terfasa ለፀሎት ኮንፈራንስ የገንዘብ ድጋፍ 🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏

🙏 የአቤንኤዘር የፀሎት ሚኒስትሪ 👉 በየዕለቱ የፀሎት ጥያቄዎች እና ወደ ፀሎት ሊመራን የሚችል ለ30 ደቂቃ የሚነበብ የእግዚአብሔር ቃል ወይም ከ“ትንቢት መንፈስ” መጽሐፍ ፕሮግራም ዝርዝር ❤️ ቋሚ የፀሎት ርዕስ 👉 ስለ መንፈስ ቅዱስ መሞላት ━━━━━━━━━━━━━━━ ❤️ እሁድ – የውይይት ቀን (ጠቅላላ ጉባኤ) ❤️ ሰኞ – ቤትና ቤተሰብ 📖 የዳግም ምፃት ተጠባባቂ መጽሐፍ (Adventist Home) ❤️ ማክሰኞ – የወንጌል ሥራ 👉 በኢትዮጵያ ያለው የወንጌል ሥራ 👉 የአጠቃላይ ቤተክርስቲያን የወንጌል ሥርጭትና ግንባታ 👉 የቦርድ አባላትና ምዕመናን በሙሉ 📖 የክርስቶስ ምሳሌያዊ አስተምሮ ❤️ ረቡዕ – መንፈስ ቅዱስ 📖 ስለ መንፈስ ቅዱስ ሙላትና ሥራ 📖 የፈውስ አገልግሎት መጽሐፍ ❤️ ሐሙስ – ስለመንፈሳዊ መሪዎች 👉 የቤተክርስቲያን መሪዎችና ቤተሰቦቻቸው 📖 የበጎ አድራጎት መጽሐፍ ❤️ አርብ – የፀሎት ጥያቄ 👉 በቃልና በፀሎት እንድንታመን 👉 ት/ቤቶች፣ ተማሪዎችና ተቋማት 📖 ታላቁ ተጋድሎ ❤️ ቅዳሜ – የምስጋና ቀን 🙏 ለእግዚአብሔር ምስጋና እና ምስክርነት ━━━━━━━━━━━━━━━ 🔥 በግል፣ በቤታችን፣ በቤተክርስቲያን እና በሕይወት ዘመናችን ሁሉ በፀሎት መንፈስ እንዲበረታ እንጸልይ! 🙏 “መንፈስ ቅዱስ ሙላት የሕይወታችን መሠረት ይሁን!”