fa
Feedback
እስልምና እና ክርስትና

እስልምና እና ክርስትና

رفتن به کانال در Telegram

t.me//AkeelComparative የእስልምና እና የክርስትና ሐይማኖት ንፅፅሮችን በጥልቀት ይዳስሳል። ቻናሉን #join ሌሎችንም #add ያድርጉ!!

نمایش بیشتر
315
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
የክርስቶስ ተቃዋሚ (ጉራጊኛ) በአላህ ሽም አቸም ተጨር ሩኅሩህ አቸም ተጨር አዛኝ በኸረ ሁት፡፡ 5፥111 የሐዋርያት ህኖሜንየ «ብያም በናሁቸረናምም ኧመሮ » በበሮቶ ባዘዝሁ ግዝየ አስታውስ፡፡ وَإِذْ أَوْحَيْتُ إِلَى الْحَوَارِيِّينَ أَنْ آمِنُوا بِي وَبِرَسُولِي "የክርስቶስ ተቃዋሚ" ወበር "ጸረ ክርስቶስ"antichrist" በሮት ቲኸር በግሪክም ደሞ ኮይኔ "አንቲኽሪስቶስ" ይውሪ። "አንቲኽሪስቶስ" ἀντίχριστος ይᎅን ቃልሁት " #አንቲ " ἀντί ወበር "ተቃራኒ" "ተቃዋሚ" "ሐሳዌ" ቲኸር " #ኽሪስቶስ " Χριστός በሮት ደሞ "መሢሕ" "ቅቡዕ" "ክርስቶስ" ቲብር ሁዌት ቃላት ግዝየ የትዋቀረ ቃር ቲኸር "የክርስቶስ ተቃራኒ" "የክርስቶስ ተቃዋሚ" "ሐሳዌ መሢሕ" ወበርሙ፦ -1ኛ ዮሐንስ 2፥18 " ወረ ደንጞ! "የክርስቶስም ተቃዋሚ" ወተነነታ ስሞታሁም የመጨረሻ ሰዓትዌ ወህረታው ። Παιδία, ἐσχάτη ὥρα ἐστίν, καὶ καθὼς ἠκούσατε ὅτι ἀντίχριστος ἔρχεται, በዝህ አንቀጽ ᎈር በነጠላ "የክርስቶስም ተቃዋሚ" የቧሪ ያነ ዋናታ ሐሳዌ መሢሕ ቲኸር ሁት ተተኖተታ እፍቴ ቸነቦም ታነ ያሳስቶ የኸረቦም ህኖ እራሰታ "የክርስቶስ ተቃዋሚዎች" ቧርዮም፦ - 1ኛ ዮሐንስ 2፥18 " ኧኋ እኳን ብዘሁና "የክርስቶስ ተቃዋሚ የኸሮ ቃር" ተረሠቦም፥ ስለዚ የመጨረሻዌ ሰዓት የኸረ ኸማ ንⷕነ። καὶ νῦν ἀντίχριστοι πολλοὶ γεγόνασιν· ὅθεν γινώσκομεν ὅτι ἐσχάτη ὥρα ἐστίν. በግዕዝዌ "ሐሳውያነ መሢሕ" ይᎅን፥ ሐሳውያነ መሢሕ የኸሮ ህኖ ኢየሱስ ክርስቶስ በበሰር የቸነ ኸማ ኤያምሮ ቃሎ፦ -2ኛ ዮሐንስ 1፥7 "ብዘሁና ያሳስተቦ የኸረቦ ቃር ወደ ዓለም ገፖም የኸሬ ህኖመሁና ኢየሱስ ክርስቶስ በበሰር የቸነ ኸማ ኤያምሮ የኸረቦ ቃሎ፤ ዛታ ያሳስትምም "የክርስቶስም ይትቃወምም የኸረ ቃሩ" ። ὅτι πολλοὶ πλάνοι ἐξῆλθον εἰς τὸν κόσμον, οἱ μὴ ὁμολογοῦντες Ἰησοῦν Χριστὸν ἐρχόμενον ἐν σαρκί· οὗτός ἐστιν ὁ πλάνος καὶ ὁ ἀντίχριστος. ይና ሙሥሊም ግን ኢየሱስ ክርስቶስ በበሰር የቸነ ኸማ፣ ክርስቶስ ታአብ ህኖ በበሰር ወተነታምም፣ ኢየሱስም የዳዊት ዘር ተኸረች ተማርያምም ተጨነምታ ታንበሮትም ወደ ንበሮት እማት የኸረ አምላክ ያቸነን ኸማ ናምነ፦ - ሮሜ 9፥5 " አባቶችም/አብ ህኖም የህኖ ቃሎ የኸሬ፤ "ተህኖም" ክርስቶስ በበሰር ቸነም። καὶ ἐξ ὁ Χριστὸς τὸ κατὰ σάρκα -የሐዋርያት ሥራ 13፥23 "ተዝም የሰብ ዘር አምላክ በተስፋታ ቃል ይእስራኤልም መዳኒት ሁትም ኢየሱስ አቸነም። τούτου ὁ Θεὸς ἀπὸ τοῦ σπέρματος κατ’ ἐπαγγελίαν ἤγαγεν τῷ Ἰσραὴλ Σωτῆρα Ἰησοῦν, ሙሥሊም ይና ግን ኢየሱስ መሢሕ የኸረ ኸማ ናምነ የኸሬ "አል መሢሑ ዒሣ" الْمَسِيحُ عِيسَى ቢብር የማዕረግ ሽም ትንጠራኔ በቁርኣንም ደሞ በብዘ መደር በዝ ሽመታ ተጠቀሰም። 3፥45 4፥171 ኧዥ! በተቃራኒየታ ግን "ኢየሱስ 'ክርስቶስ' አንኸረ" ባረም ይኸዳ ሁት የክርስቶስ ይትቃወም ቃሩ፦ -1ኛ ዮሐንስ 2፥22 "ክርስቶስ አንኸረ" ባረምታ ይእየሱስ ይኸዳ ተኸረ ውጤ ᎅችር ቃር ኦጃማ የኸረ ሟኑ? አብምም ወልድምም ይኸዳታ ዝህ የክርስቶስ ተቃዋሚው። "አብ" ወበር በፍካሬአዊ ቃል "ያትረህብ" "ምንጭ" "ፈጣሪ" በሮት ቲኸር "ወልድ" ወበር ደሞ በፍካሬአዊ ቃል "የትረኸበ/የትረከበ" "ተመንጭ" "ፍጡር" ወበሩ። ኢየሱስ "በአምላክም ኧመሮ" "ብያም ደሞ ኧመሮ" ቲብር ይረህ እማት የኸረ አምላክ እየሱስ ደሞ ይትረህ የኸረ መሢሕ ወህረታ ያትየሽ ቃሩ፦ - ዮሐንስ 14፥1 "በአምላክ ኧመሮ፥ ብእያም ደሞ ኧመሮ። πιστεύετε εἰς τὸν Θεόν, καὶ εἰς ἐμὲ πιστεύετε. "ብእያ" ቢብር ቃል ᎈወር “ም” ይብር ጥገኛ ምዕላድ ሁት በጉራጊናም ተጨማሪ የኸረ ቃር ያተዞት የገፓ ቃር ቲኸር በጉራጊኛ "ምም" በግሪኩ "ካይ" καὶ በሮትም በአማርኛ "እና" ይብር መስተጻምር ያትየሼ የገፓ ቃሩ ፥ ዝህም አምላክም ሁት ናሁቸረነም ሁት ኹዌት የትለያዮ ሃልዎትምም ኑባሬምም የኸሮ ኸማ ቁልጭ አመነም ያትየሽ። በእርግጥም በናሁቸረነ ሁት ኧመሮት በሮት በራሁወን ሁት ወመር ወበር የኸረ ኸማ ምክንያተታ ናሁቸር ሁት ይረህ ሁት ቃሩ ባንኸሬ ይትረህ ሁት ቃር ያንኸረ የኸሬው፦ -ዮሐንስ 12፥44 " ኢየሱስም አኸናምታ፥ ዝካ ባረም፦ ብእያ ያመረ በራሄ ኧመሮተታው ባንኸሬ ብእያ አንኸረ። -ዮሐንስ 14፥24 "ትሠመዊ ቃል የራሄ የአብ ቃሩ ባንኸሬ ይእያ ቃር አንኸረ። ውረሙ! ይማተታ ያነ አምላክ የኸረ ጔታም አብምም መሢሑምዌም ኢየሱስ ይኸዶ የኸሮ ህኖ የክርስቶስ ተቃዋሚሎ፦ -ይሁዳ 1፥4 " ይእማተታ ያነዌ ጔታ አምላክምም ጔታንዳምም ኢየሱስ ክርስቶስ ይኸዶ። καὶ τὸν μόνον δεσπότην θεὸν καὶ κύριον ἡμῶν Ἰησοῦν χριστὸν ἀρνούμενοι. "ዴስፖቴን ቴዎን" δεσπότην θεὸν ይብር ሁት ኮዴክስ ቤዛይ ᎈወር ቲኸር 1611 ድኅረ ልደት በታተመ ቅጂዌ በThe King James Version (KJV) ሁት ልክ የኮዴክስ ቤዛይ ኸማ፦ "ይእማተታ ያነ ጔታ አምላክምም ጔታንዳም ኢየሱስ ክርስቶስም ይኸዶ"and denying the only Lord God, and our Lord Jesus Christ" ባሮም አወነበዊም። አምላካንዳ አሏህ የዒሣ ባᎄን ወሕይ ብእንጂል የሐዋርያት ህኖ፦ " ብእያምም በናሁቸረናምም ኧመሮ" ባረም አዘዘኖም ባነም፦ 5፥111 የሐዋርያ ህኖሜንየም « ብእያም በናሁቸረናምም ኧመሮ» በበሮት ባዘዝሁ ግዝየ አስታውስ፡፡ وَإِذْ أَوْحَيْتُ إِلَى الْحَوَارِيِّينَ أَنْ آمِنُوا بِي وَبِرَسُولِي በዝህ አንቀጽ "ባዘዝኹ" ቢብር የገፓ ቃልዌ "አውሐይት" أَوْحَيْتُ የግሥ መደብ ቲኸር የሽም መደበታ "ወሕይ" وَحْي በሮትም "ግልጠተ መለኮት"revelation" ቃሩ፥ በአሏህ አምላክነት በራሁቸረነታ በኢየሱስ መሢሕነት ኧመሮት የአርካኑል ኢማን ክፍሉ። የትግባፓነ ኸማ ተስፋ አሜ። አሏህ ሂዳያህ ያብሁ! ይናም ጽናተታ ያብንደ! አሚን። ጉራጊኛ ትርጉም በ t.me//AkeelComparative @@@@@@@///@@@@@@ ሌሎችንም #በጉራጊኛ ትርጉም የተሠሩ ንፅፅሮች ለማግኘት 👇👇👇👇👇👇👇 t.me/wahidcomguragiga ለአማርኛ ደግሞ 👇👇👇 https://t.me/wahidcom ✍ከዐቃቢ ኢሥላም ወሒድ ወሠላሙ ዐለይኩም

መልካም ዜና ለሐይማኖት ንፅፅር ፈላጊዎች ይህ @AkeelComparative የተሠኘው የንፅፅር ቻናል ላይ ከአማርኛ በተጨማሪ በተለያዩ የሀገራችን ቋንቋዎች ማለትም በኦሮምኛ፣ በትግርኛ፣ በጉራጊኛ፣ በስልጢኛ፣ በአፋርኛና በሌሎችም ቋንቋዎች የሚዘጋጁ ንፅፅሮችን ለማቅረብ ዝግጅታችን አጠናቀናል። በዚህም ደርሶችን እንድትከታተሉ እንዲሁም share እና add እንድታደርጉ በአሏህ ስም እንጠይቃለን። t.me//AkeelComparative

ከክፍል 19 የቀጠለ 2) የፅንስ ሁኔታውን የሚያውቅ፣ ሠማይ፣ምድር፣ የሠው ልጅ የፈጠረና ሙታንን የሚቀሰቅስ #ሰሚ 13፡ 8 الله يعلم ما تحمل كل أنثى وما تغيض الأرحام وما تزداد ۖ وكل شيء عنده بمقدار አላህ ሴት ሁሉ የምታረግዘውን ያውቃል፡፡ ማሕጸኖችም የሚያጎድሉትን የሚጨምሩትንም (ያውቃል)፡፡ ነገሩም ሁሉ እርሱ ዘንድ በልክ የተወሰነ ነው፡፡ 31፡ 28 ما خلقكم ولا بعثكم إلا كنفس واحدة ۗ إن الله سميع بصير እናንተን መፍጠርና እናንተን መቀስቀስ እንደ አንዲት ነፍስ እንጂ ሌላ አይደለም፡፡ አላህ ሰሚ ተመልካች ነውና፡፡ 42፡11 فاطر السماوات والأرض ۚ جعل لكم من أنفسكم أزواجا ومن الأنعام أزواجا ۖ يذرؤكم فيه ۚ ليس كمثله شيء ۖ وهو #السميع البصير ሰማያትንና ምድርን ፈጣሪ ነው፡፡ከነፍሶቻችሁ ሴቶችን ከቤት እንስሳዎችም ዓይነቶችን (ወንዶችና ሴቶችን) ለእናንተ አደረገላችሁ፡፡ በእርሱ ያበዛችኋል፡፡ የሚመስለው ምንም ነገር የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ 3) አላህ(ሱወ) እውነተኛ ፈራጅና እኛንም በእውነት እንድንፈርድ የሚገስጠን እንዲሁም ደግሞ ለቃላቱ ለዋጭ የሌለው #ሰሚ መሆኑን፦ 4፡ 58 إن الله يأمركم أن تؤدوا الأمانات إلى أهلها وإذا حكمتم بين الناس أن تحكموا بالعدل ۚ إن الله نعما يعظكم به ۗ إن الله كان سميعا بصيرا አላህ አደራዎችን ወደ ባለቤቶቻቸው እንድታደርሱ ያዛችኋል፡፡ በሰዎችም መካከል በፈረዳችሁ ጊዜ በትክክል እንድትፈርዱ (ያዛችኋል)፡፡ አላህ በርሱ የሚገሥጻችሁ ነገር ምን ያምር! አላህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ 40፡ 20 والله يقضي بالحق ۖ والذين يدعون من دونه لا يقضون بشيء ۗ إن الله هو السميع البصير አላህም በእውነት ይፈርዳል፡፡ እነዚያም ከእርሱ ሌላ የሚግገዟቸው በምንም አይፈርዱም፡፡ አላህ እርሱ ሰሚው ተመልካቹ ነው፡፡ 6፡ 115 وتمت كلمت ربك صدقا وعدلا ۚ لا مبدل لكلماته ۚ وهو السميع العليم የጌታህም ቃላት እውነተኛና ትክክለኛ ስትኾን ተፈጸመች፡፡ ለቃላቱ ለዋጭ የለም፡፡ እርሱም ሰሚው ዐዋቂው ነው፡፡ 4) አላህ(ሱወ) ባሮቹን ቀጥተኛው መንገድ ሊመራ መልዕክተኞች ላኪ የሆነ፣ ከሸይጧንም የሚጠብቃቸው እንደዚሁም የሚሳሳቱ ባሮቹንም ወደ ቅን መንገድ የሚመራ #ሰሚ መሆኑ፦ 22፡ 75 الله يصطفي من الملائكة رسلا ومن الناس ۚ إن الله سميع بصير አላህ ከመላእክት ውስጥ መልክተኞችን ይመርጣል፡፡ ከሰዎችም (እንደዚሁ)፤ አላህ ሰሚ ተመልካች ነው፡፡ 7፡ 200 وإما ينزغنك من الشيطان نزغ فاستعذ بالله ۚ إنه سميع عليم ከሰይጣንም (በኩል) ጉትጎታ ቢያገኝህ በአላህ ተጠበቅ፡፡ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነውና፡፡ 34፡ 50 قل إن ضللت فإنما أضل على نفسي ۖ وإن اهتديت فبما يوحي إلي ربي ۚ إنه سميع قريب «ብሳሳት የምሳሳተው በራሴ ላይ ብቻ ነው፡፡ ብመራም ጌታዬ ወደኔ በሚያወርደው ነው፡፡ እርሱ ሰሚ ቅርብ ነውና» በላቸው፡፡ ክፍል -20 ይቀጥላል ይህንን መልዕክት ለሌሎች እንዲደርስ #share እንዲሁም #add ያድርጉ t.me//AkeelComparative

99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክፍል -19 📝 በወንድም አቂል ⓳ አስ-ሰሚዕ ( السميع ) {{ የትኛውንም አይነት እንቅስቃሴ ድምፅ መስማት የሚችል (ሰሚ) }}} አስ-ሰሚዕ ሌላኛው ከአላህ 99 የመልካም ስሞቹ መካከል የሚጠቀስ የመልካም ስም መጠሪያው ሲሆን ትርጉሙንም #ሰሚ ማለት ነው። መቼም #ሰሚ /የሚሰማ ሲባል ለድምፅ መሆኑ ግልፅ ነውና በዚህም ደግሞ አላህ(ሱወ) የድምፅ እንቅስቃሴዎችን የሚሰማ የሆነ ጌታ ነው። ድብቅም ይሁን ስውር የትኛውንም አይነት ድምፅ ከአላህ(ሱወ) የተሠወረ አይደለም፤ ሁለት ወይም ከዚያ በላይ ሆነው የሚከራከሩ ወይም የሚወያዩ ሰዎችን ድምፅ ሳይቀር ይሠማል። 58፡ 1 بسم الله الرحمن الرحيم قد سمع الله قول التي تجادلك في زوجها وتشتكي إلى الله والله يسمع تحاوركما ۚ إن الله سميع بصير አላህ የዚያችን በባሏ (ነገር) የምተከራከርህንና ወደ አላህ የምታሰሙተውን (ሴት) ቃል በእርግጥ ሰማ፡፡ አላህም (በንግግር) መመላለሳችሁን ይሰማል፡፡ አላህ #ሰሚ ተመልካች ነውና፡፡ የሰው ልጅ መስማት የሚችለው የቅርብ ድምፆችን ብቻ ሲሆን ሲያረጅ ደግሞ ጭራሽ ላይሰማም ይችላል። በዚህም የመስማት ችሎታው በጊዜ ፣ በቦታና፣ በሁኔታ የተገደበ ነው። አስ-ሰሚዑ አላህ(ሱወ) ግን ቦታ አይገድበውም የሩቁን ይሰማል ፤ ሁኔታ አይገድበውም ሚስጥር ሁሉ ያውቃል። 6፡ 3 وهو الله في السماوات وفي الأرض ۖ يعلم سركم وجهركم ويعلم ما تكسبون እርሱም ያ በሰማያትና በምድር (ሊግገዙት የሚገባው) አላህ ነው፡፡ ምስጢራችሁን ግልጻችሁንም ያውቃል፡፡ የምትሠሩትንም ሁሉ ያውቃል፡፡ 5፡99 ما على الرسول إلا البلاغ ۗ والله يعلم ما تبدون وما تكتمون <<በመልክተኛው ላይ ማድረስ እንጅ ሌላ የለበትም፡፡ አላህም የምትገልጹትን ነገር የምትደብቁትንም ሁሉ ያውቃል፡፡>> 20፡ 7 وإن تجهر بالقول فإنه يعلم السر وأخفى በንግግር ብትጮህ (አላህ ከጩኸቱ የተብቃቃ ነው)፡፡ እርሱ ምስጢርን በጣም የተደበቀንም ያውቃልና፡፡ 👉 አስ-ሰሚዑ የሆነው አላህ(ሱው) የመስማት ችሎታው በቁርዓን ውስጥ ከምን ከምን ጋር ተያይዞ እንደተገለፀ ከብዙ በጥቂቱ እንመልከት፦ 1) ቀንና ሌሊት ማፈራረቅ የሚችል (ቻይ) ፤ በነዚህ ጊዜያት ውስጥ ያለው ፀጥታና የሀይል ባለቤት #ሰሚ መሆኑ 22፡ 61 ذلك بأن الله يولج الليل في النهار ويولج النهار في الليل وأن الله سميع بصير ይህ አላህ ሌሊትን በቀን ውስጥ የሚያስገባ ቀንንም በሌሊት ውስጥ የሚያስገባ (ቻይ) አላህም ሰሚ ተመልካች በመሆኑ ነው፡፡ 6፡ 13 وله ما سكن في الليل والنهار ۚ وهو السميع العليم በሌሊትና በቀንም ጸጥ ያለው ሁሉ የርሱ ብቻ ነው፡፡ እርሱም ሰሚው ዐዋቂ ነው፡፡» 10፡ 65 ولا يحزنك قولهم ۘ إن العزة لله جميعا ۚ هو السميع العليم ንግግራቸውም አያሳዝንህ፡፡ ኀይል ሁሉ በሙሉ የአላህ ብቻ ነውና፡፡ እርሱ ሰሚው ዐዋቂው ነው፡፡ ... ይቀጥላል

⓲ አል- ወዱድ ( الودود ) {{ ወዳድ ወይም የሚወድ }}} #አል_ወዱድ ሌላው ከአላህ(ሱወ) 99 ስሞች መካከል የሚጠቀስ ሌላ መልካም ስም ሲሆን ትርጉሙም < #ወዳድ > አሊያም < #የሚወድ > ማለት ነው። ✔ አል-ወዱድ በቁርዓን 85፡14 وهو الغفور #الودود እርሱም ምሕረተ ብዙ #ወዳድ ነው፡፡ 11፡90 واستغفروا ربكم ثم توبوا إليه ۚ إن ربي رحيم #ودود «ጌታችሁንም ምሕረትን ለምኑት፡፡ ከዚያም ወደርሱ ተመለሱ፡፡ ጌታዬ አዛኝ #ወዳድ ነውና (አላቸው)፡፡ ስለሆነም አል-ወዱድ ባሮቹን የሚወድ የሆነ አምላክ ነው። ኡለማዎች #አል_ወዱድ ማለት " እጅግ ንፁህ እና ምርጥ የሆነ መውደድ ነው" በማለት የተናገሩ ሲሆን ይህም በውስጡ ምንም ጥላቻ የሌለበት የመውደድ ትልቁ ደረጃ ነው። "የሚወደድ" ማለትም ነው ያሉም አሉ። አንዳንድ ሰዎች እገሌን እወደዋለሁ ሲሉ እንሰማለን እኛም ብንሆን ሰዎችን እንወድ ይሆናል፤ ሆኖም ደግሞ የወደድናቸው ሰዎች በሆነ ምክንያት እንጠላቸዋለን። ይህ ውዴታችን የመውደዳችን ጥግ አያሳይም፤ የአላህ ውዴታ ግን ከዚህ ይለያል። ✔ በ <<አል-ውድ >> እና <<አል-ሑብ >> መካከል ያለው ልዩነት <አል-ወዱድ> ከ<አል-ሑብ> በበለጠ ሁኔታ ጥቅልና ሰፊ ትርጉም ያለው ነው። አል-ሑብ (ውዴታ) ሌሎችን ለመውደድ ውስጣችን የምናስቀምጠው ነገር ነው። አል-ውድ ደግሞ እነኚህን ስሜቶች በተግባር የመግለፅ ሁኔታ ነው። አል-ውድ አል-ሑብን ሁሉ አጠቃሎ የሚይዝ ነው። ከዚህም በመነሳት #ወዱድ ሁሉ #ሙሒብ #ሲሆን #ሙሒብ ሁሉ ግን #ወዱድ #አይደለም ። በሌላ አገላለፅ አፍቃሪ ሁሉ የሚወድ ሲሆን የሚወድ ሁሉ አፍቃሪ ላይሆን ይችላል ማለት ነው። ክፍል -19 ይቀጥላል t.me//AkeelComparative

ከክፍል - 17 የቀጠለ 👉 አላህ(ሱወ) ፍጥረታትን የፈጠረው ለሰው ልጅ ጥቅም ሲሆን ሰውና ጋኔን ግን እርሱን በብቸኝነት ሊገዙ እንደፈጠራቸው በ51፡56 ላይ ተናግሯል። ታድያም ይህ ፈጣረውን ሊገዛ የተፈጠረ የሆነው የሰው ልጅ ኩራት ከራሱ ላይ አንስቶ አምላኩን (አላህን) በብቸኝነት መገዛት እንዳለበትና ኩራተኛም ሰው የተጠላ መሆኑን አል- ሙተከቢር (ኩሩው) የሆነው አላህ(ሱወ) ሲናገር እንዲህ ይላል፦ 4፡36 واعبدوا الله ولا تشركوا به شيئا ۖ وبالوالدين إحسانا وبذي القربى واليتامى والمساكين والجار ذي القربى والجار الجنب والصاحب بالجنب وابن السبيل وما ملكت أيمانكم ۗ إن الله لا يحب من كان مختالا فخورا አላህንም ተገዙ፡፡ በእርሱም ምንንም አታጋሩ፡፡ በወላጆችና በቅርብ ዝምድና ባለቤትም፣ በየቲሞችም፣ በምስኪኖችም፣ በቅርብ ጎረቤትም፣ በሩቅ ጎረቤትም፣ በጎን ባልደረባም፣ በመንገደኛም፣ እጆቻችሁም ንብረት ባደረጓቸው (ባሮች)፣ መልካምን (ሥሩ)፤ አላህ ኩራተኛ ጉረኛ የኾነን ሰው አይወድም፡፡ 57፡23 لكيلا تأسوا على ما فاتكم ولا تفرحوا بما آتاكم ۗ والله لا يحب كل مختال فخور (ይህ ማሳወቃችን) ባመለጣችሁ ጸጋ ላይ እንዳታዝኑ አላህም በሰጣችሁ ነገር (በትዕቢት) እንዳትደሰቱ ነው፡፡ አላህም ኩራተኛን ጉረኛን ሁሉ አይወድም፡፡ 👉 የኩራት መጀመሪያው ጥፋት መጨረሻው ደግሞ እሳት ነው። ለዚህም የፈርዖንን ሁኔታ በቁርዓን መመልከት በቂ ነው። 23፡ 46-48 إلى فرعون وملئه فاستكبروا وكانوا قوما عالين فقالوا أنؤمن لبشرين مثلنا وقومهما لنا عابدون فكذبوهما فكانوا من المهلكين ወደ ፈርዖንና ወደ ጭፍሮቹ (ላክናቸው)፡፡ ኮሩም፡፡ የተንበጣረሩ ሕዝቦችም ነበሩ፡፡ «ብጤያችንም ለኾኑ ሁለት ሰዎች ሕዝቦቻቸው ለእኛ ተገዢዎች ኾነው ሳሉ እናምናለን» አሉ፡፡ አስተባበሉዋቸውም፡፡ ከጠፊዎቹም ኾኑ፡፡ 👉 ስለ ኩራተኛ ሰው ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 7 መጽሐፍ 72 ቁጥር 680 አቡ ሁረይራ ዘግበውታል። ነብዩ (ወይም አቡል ቃሲም) እንዲህ ብለዋል፡- ‹‹አንድ ሰው ሁለት ልብስ ለብሶና ፀጉሩ በደንብ ተላጥጦ እየኮራ ሲሄድ በድንገት አላህ ምድር ውስጥ እንዲሰምጥ አድርጎት ወደ ውስጥ እየሰመጠ ይሄዳል። እስከ ትንሣኤ ቀን ድረስ። ***** ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 7 መጽሐፍ 72 ቁጥር 683 አብደላህ ቢን ዑመር ዘግበውታል። የአላህ መልእክተኛ (ሰ.ዐ.ወ) እንዲህ ብለዋል፡- “ከኩራትና ከኩራት የተነሣ ልብሱን (በምድር ላይ) የሚጎተት አላህ በትንሳኤ ቀን አይመለከተውም። አላህ ከኩራት ይጠብቀን!! ክፍል - 18 ይቀጥላል @@@@@//@@@@@ ይህንና ሌሎች ንፅፅሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ! ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር በማድረግ ከኸይሩ እንቋደስ። t.me//AkeelComparative

99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም 🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋 ክፍል - 17 📝 በወንድም Abu Usman (Akel) ⓱ አል ሙተከቢሩ { المتكبار} [[[[ ኩሩው ]]]]] ፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨፨ - አል-ሙተከቢር ፦ ማለት ትርጉሙ #ኩሩ ማለት ነው። ታድያ ብቸኛው ፣ንጉስ፣ ከጉድለት የጠራው፣ ሃያሉ፣ጥበበኛው... ከሆነው ጌታችን አላህ(ሱወ) የመልካም ስሞች መካከልም ይህ #አል_ሙተከቢር የሚለው ስም ሌላኛው የባህሪያቱ መገለጫውና የመጠሪያው ስሙ በመሆን ይታወቃል። እናም ይህ አል-ሙተከቢር ( ኩሩ) የሆነው ጌታም በቁርዓን ሲናገር እንዲህ ይላል። 59፡ 23 هو الله الذي لا إله إلا هو الملك القدوس السلام المؤمن المهيمن العزيز الجبار #المتكبر ۚ سبحان الله عما يشركون << እርሱ አላህ ነው። ያ ከርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ፤ ንጉሱ፣ ከጉድለት ሁሉ የጠራው፣ የሰላም ባለቤቱ ፣ ፀጥታን ሰጪው፣ ባሮቹን ጠባቂው፣ አሸናፊው፣ ሃያሉ፣ #ኩሩው ነው። አላህ ከሚያጋሩት ሁሉ ጠራ!።" ራሱን ቻይና የተብቃቃ የሆነው ጌታ ኩራት የርሱ ልብሱ ነው። ለዚህም ረሱል(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ በሀዲስ ቁዱስ ላይ አቡ ሁረይራ (ረዐ) እንዳስተላለፉት የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- “ሃያሉ የተከበረው ጌታ እንዲህ ብሏል፦ ኩራት ካባዬ፤ ታላቅነት መታጠቂያዬ ነው። ከእነሱ ከአንደኛው እንኳ ከእኔ ጋር የሚፎካከረውን ወደ ጀሐነም እሳት እወረውረዋለሁ።" በማለት ተናግሯል። ✔ ኩራት የአላህ(ሱወ) ብቻ መገለጫ ሲሆን #አል_ሙተከቢሩ (ኩሩው) የሚለው የአላህ ስም በቁርዓን ውስጥ ሁኔታውን ስንመለከተው አብዛኛውንም ጊዜ ከሀዲዎች ከአላህ ውጪ የሆነን ባዕድ አካል በማምለካቸው እና በዚህም በመኩራታቸውም ምክንያት ከመጨረሻው ዓለም ጋር ያላቸው ቁርኝት ጋር ተያይዞ ምን እንደሚመስል ተጠቅሶ እናገኘዋለን። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 45፡ 36-37 فلله الحمد رب السماوات ورب الأرض رب العالمين وله الكبرياء في السماوات والأرض ۖ وهو العزيز الحكيم ምስጋናም ለአላህ ለሰማያት ጌታ ለምድርም ጌታ ለዓለማት ጌታ የተገባው ነው፡፡ ኩራትም በሰማያትም በምድርም ለእርሱ ብቻ ነው፡፡ እርሱም አሸነፊው ጥበበኛው ነው፡፡ 16፡22-23 إلهكم إله واحد ۚ فالذين لا يؤمنون بالآخرة قلوبهم منكرة وهم مستكبرون لا جرم أن الله يعلم ما يسرون وما يعلنون ۚ إنه لا يحب المستكبرين አምላካችሁ አንድ አምላክ ብቻ ነው፡፡ እነዚያም በመጨረሻይቱ ዓለም የማያምኑት ልቦቻቸው ከሓዲዎች ናቸው፡፡ እነሱም የኮሩ ናቸው፤ (አያምኑም)፡፡ አላህ የሚደብቁትንና የሚገልጹትን ሁሉ የሚያውቅ ለመኾኑ ጥርጣሬ የለበትም፡፡ እርሱ ኩሩዎችን አይወድም፡፡ ይህ ክፍል አላበቃም ይቀጥላል @@@@@@//@@@@@@@@ "ወደ ኸይር ስራ ያመላከተ ሰው ስራው እንደሠራው ነው።" ነብዩ(ሰዐወ) ይህንን ክፍል በተከታታይ ክፍሎች እና ሌሎችንም የሐይማኖት ንፅፅራዊ ደርሶችን ለማግኘት ቻናሉን @AkeelComparative ይቀላቀሉ። ለሌሎችም እንዲደርስ ሼር በማድረግ ከኸይሩ እንቋደስ!! t.me//AkeelComparative

. 99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም 🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋🕋 ክፍል - 16 📝 በወንድም Abu Usman (Akel) ⓰ አል ኻፊዱ ( الخافض ) & አር-ራፊዑ ( الرافع) {{ ዝቅ የሚያደርግ፤ የሚያዋርድና የሚቀጣ & ከፍ የሚያደርግ }}} አል-ኻፊድ እና አር-ራፊዑ ሌሎች ከአላህ 99 የመልካም ስሞች መካከል የሚጠቀሱ ሲሆኑ አማኞችንና ከሐዲያንን በእለተ ትንሳኤ ቀን ደረጃቸው የሚያበላልጥበትና የሚያሳንስ መሆኑን ይገልጻሉ። 56፡ 1-3 إذا وقعت الواقعة ليس لوقعتها كاذبة خافضة رافعة መከራይቱ በወደቀች ጊዜ፡፡ ለመውደቋ አስተባባይ (ነፍስ) የለችም፡፡ ዝቅ አድራጊና ከፍ አድራጊ ናት፡፡ 16፡27 ثم يوم القيامة يخزيهم ويقول أين شركائي الذين كنتم تشاقون فيهم ۚ قال الذين أوتوا العلم إن الخزي اليوم والسوء على الكافرين ከዚያም በትንሣኤ ቀን ያዋርዳቸዋል፡፡ እነዚያም «በእነሱ (ጉዳይ) ትከራከሩኝ የነበራችሁት ተጋሪዎቼ የት ናቸው» ይላቸዋል፡፡ «እነዚያ ዕውቀትን የተሰጡት ዛሬ ሐፍረቱና ቅጣቱ በእርግጥ በከሓዲዎች ላይ ነው» ይላሉ፡፡ አር-ራፊዑ ከእለተ ትንሳኤ በተጨማሪም በዚህ አለም ላይም አማኝ ባሪያዎቹን አንዳቸው ከሌላኛቸው በደረጃ ከፍ የሚያደርግ መሆኑን ይናገራል። 40፡15 رفيع الدرجات ذو العرش يلقي الروح من أمره على من يشاء من عباده لينذر يوم التلاق (እርሱ) ደረጃዎችን ከፍ አድራጊ የዐርሹ ባለቤት ነው፡፡ የመገናኛውን ቀን ያስፈራራ ዘንድ ከባሮቹ በሚሻው ሰው ላይ ከትዕዛዙ መንፈስን (ራእይን) ያወርዳል፡፡ 49፡ 13 يا أيها الناس إنا خلقناكم من ذكر وأنثى وجعلناكم شعوبا وقبائل لتعارفوا ۚ إن أكرمكم عند الله أتقاكم ۚ إن الله عليم خبير እናንተ ሰዎች ሆይ! እኛ ከወንድና ከሴት ፈጠርናችሁ፡፡ እንድትተዋወቁም ጎሳዎችና ነገዶች አደረግናችሁ፡፡ አላህ ዘንድ በላጫችሁ በጣም አላህን ፈሪያችሁ ነው፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነው፡፡ ክፍል - 17 ይቀጥላል... @@@@@//@@@@ ለሌሎችም እንዲደርስ ደርሱን ሼር በማድረግ ቻናሉን እንዲቀላቀሉ ያድርጉ 👇👇👇👇👇👇👇👇 t.me//AkeelComparative

⓮ አል ዐሊም ( العليم ) {{ ሁሉን አዋቂው }} #አል_ዐሊም ሌላኛው የአላህ(ሱወ) መልካም ስም መገለጫው ወይም መጠሪያው ስም ሲሆን ትርጉሙም #ሁሉን #አዋቂው ማለት ነው። #ሁሉን #አዋቂው ሲባል ምን ማለት ነው? አላህ(ሱወ) በሰማያትና በምድር ያሉት ፍጥረታት በሙሉ ሁሉ ነገራቸው ያውቃል።ግልፅም ሆነ ስውር የትኛውንም ነገር ከእርሱ የተሰወረ አይደለም። 2፡ 29 هو الذي خلق لكم ما في الأرض جميعا ثم استوى إلى السماء فسواهن سبع سماوات ۚ وهو بكل شيء عليم እርሱ ያ በምድር ያለውን ሁሉ ለእናንተ የፈጠረ ነው፡፡ ከዚያም ወደ ሰማይ አሰበ፤ ሰባት ሰማያትም አደረጋቸው፡፡ እርሱም በነገሩ ሁሉ ዐዋቂ ነው፡፡ 4፡ 35 وإن خفتم شقاق بينهما فابعثوا حكما من أهله وحكما من أهلها إن يريدا إصلاحا يوفق الله بينهما ۗ إن الله كان عليما خبيرا (እናንተ ዋቢዎች) የመካከላቸውንም ጭቅጭቅ ብታውቁ ከቤተሰቦቹ ሽማግሌን ከቤተሰቦችዋም ሽማግሌን ላኩ፡፡ ማስታረቅን ቢሹ አላህ በመካከላቸው ያስማማል፡፡ አላህ ግልጽን ዐዋቂ ውስጥንም ዐዋቂ ነውና፡፡ ስለእውቀት ስናወራ እውቀት በተፈጥሮ ገደብ ያለው ነገር ነው። ለምሳሌ፦ የሠው ልጅ እውቀት በጊዜ፣ በቦታና በሁኔታ የተገደበ ነው። 1) #በጊዜ ፦ በልጅነት እድሜ ላይ እያለን የምናውቃቸው የሆኑ የተለያዩ እውቀቶች ይኖራሉ ነገር ግን እነዚያ እውቀቶች በምናረጅበት ወቅት ይጠፋሉ። ስለዚህ የሰው ልጅ እውቀት #በጊዜ የተገደበ ነው። 2) በቦታ ፦ ከልጅነት እድሜ ክልል ወጥተን ትንሽ ከፍ ስንል ወደ ትምህርት ቤት አምርተን የአካዳሚ ትምህርት እውቀት ቀስመን የተለያዩ እውቀቶችን እናገኛለን። በዚህም የሰው ልጅ እውቀት #በቦታ የተገደበ ነው። 3) ሁኔታ ፦ እውቀት መማር/ማግኛው መንገድ ሁለት አይነት ናቸው። (formal & informal learnning) ትምህርት ቤት ገብተን እውቀት ለመቅሰም የተለያዩ ሁኔታዎችን እናመቻቻለን። ለምሳሌ መምህራን ለተማሪዎቻቸው እውቀት በመስጠት ሁኔታዎችን ያመቻቻሉ። ስለዚህ የሰው ልጅ እውቀት #በሁኔታ የተገደበ ነው። የአላህ(ሱወ) እውቀት ግን ከዚህ የተለየ ሲሆን እውቀቱ ገደብ የለውም ። የእርሱ እውቀት በጊዜ፣ በቦታና በሁኔታ አይገደብም እስቲ ይህንን የቁርዓን አንቀፅ እንመልከት፦ 6፡ 59 وعنده مفاتح الغيب لا يعلمها إلا هو ۚ ويعلم ما في البر والبحر ۚ وما تسقط من ورقة إلا يعلمها ولا حبة في ظلمات الأرض ولا رطب ولا يابس إلا في كتاب مبين የሩቅ ነገርም መክፈቻዎች እርሱ ዘንድ ናቸው፡፡ ከእርሱ በቀር ማንም አያውቃቸውም፡፡ በየብስና በባሕር ያለውንም ሁሉ ያውቃል፡፡ #ከቅጠልም #አንዲትም #አትረግፍም #የሚያውቃት #ቢኾን #እንጅ፡፡ ከቅንጣትም በመሬት ጨለማዎች ውስጥ የለም ከእርጥብም ከደረቅም አንድም የለም ግልጽ በኾነው መጽሐፍ ውሰጥ (የተመዘገበ) ቢኾን እንጅ፡፡ ሱብሀን አላህ!! በጣም የሚገርም ነው!። የእውቀት ባለቤት የሆነውና ሁሉን አዋቂው #አል_ዐሊሙ ጌታችን አላህ ጥራት ይገባው!! ከእርሱ እውቀት የሚያመልጥ የሆነ አንዳችም ሚስጥር የለም። ሁሉንም የፍጥረታቱ እንቅስቃሴ ጉዳይ በእውቀቱ የተከበበ ነው። ለዚህም ደግሞ #አል_ዐሊሙ አላህ ሲናገር እንዲህ ይላል 20፡ 98 إنما إلهكم الله الذي لا إله إلا هو ۚ وسع كل شيء علما ጌታችሁ ያ ከእርሱ በቀር ሌላ አምላክ የሌለ የኾነው አላህ ብቻ ነው፡፡ እውቀቱ ነገርን ሁሉ አዳረሰ፡፡ 67፡ 14 ألا يعلم من خلق وهو اللطيف الخبير የፈጠረ አምላክ እርሱ ዕውቀት ረቂቁ፣ ውስጥ ዐዋቂው ሲኾን (ምስጢርን ሁሉ) አያውቅምን? 72፡28 ليعلم أن قد أبلغوا رسالات ربهم وأحاط بما لديهم وأحصى كل شيء عددا እነርሱ ዘንድ ባለው ነገር ዕውቀቱ የከበበና ነገሩንም ሁሉ በቁጥር ያጠቃለለ ሲኾን የጌታቸውን መልክቶች ያደረሱ መኾናቸውን ያውቅ ዘንድ (ጠባቂ ያደርጋል)፡፡ @@@@@@@@@@@@@ ክፍል -15 ይቀጥላል የዚህን ሙሉ መረጃና ሌሎችም ንፅፅሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative

⓭ አል ፈትታህ ( الفتاح ) {{ የእዝነት በር ከፋች }}} አል-ፈትታሕ የሚለው የአላህ ስም በቁርዓን ሁለት ቦታ ላይ ተጠቅሷል። "የፍተሑ/ይከፍታል ፤ ፈተሕና/ከፈትን " ፣ ድልን ሰጠን።" ደግሞ በቁርዓን ውስጥ ብዙ ቦታ ላይ ተጠቅሷል። የመጀመሪያው ( አል-አዕራፍ፡89) ላይ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ (ሰበእ፡26) ላይ ነው። #አል_ፈትታሕ ፦ <ታ>ን በማጥበቅ ይነበባል። ከአላህ(ሱወ) መልካም ስሞች መካከል አንዱ ሲሆን ቀጥተኛ ትርጉሙ #ከፋች ማለት ነው። እንደ አገባቡ ድልን አጎናፃፊ፣ በእውነት የሚፈርድ ፣ ለባሪያዎቹ የሲሳይን ካዝና የሚከፍት ፣ አሳዋቂ... ልንለው እንችላለን። #ከፈተ የሚለው ቃል የመዝጋት ተቃራኒ ነው። መክፈት ሲባል ደግሞ አንድ የተዘጋን ነገር መግለጥ ማለት ነው። መጀመሪያ የተከፈተን በር ከፈትኩ ማለት አይቻልም፤ ምክንያቱም ከፈትኩኝ ለማለት መጀመሪያ የተዘጋ መሆን ይኖርበታል። ስለሆነም አላህ(ሱወ) የተዘጋን ነገር ሁሉ ይከፍታል ማለት ነው። ታድያ ይህም ሲባል ደግሞ ከጭንቅ ይገላግላል፣ ሐሳብን ያስወግዳል፣ መከራን ያነሳል፣ ከባዱን ነገር ያገራል። በመሆኑም እንገባቸዋለን ብለን ያሰብናቸው በሮች የተዘጉብን እንደሆነ አለም ዙሪያዋን ከጨለመብን ፣ በሰዎች ዘንድ ተስፋ የለህም/ሽም ከተባልን፣ የርዝቃችን በሩ የተዘጋብን እንደሆነ ነገሮች ወለል አድርጎ ወደሚከፍተው #አል_ፈትታሑ አላህ(ሱወ) ዘንድ በመሔድ ጉዳያችንን ነግረነው እሱ ፊት እንደፋ። ኢንሽ አላህ አል-ፈትታሕ ይከፍትልናል። እሱ እንዲህ ይለናል፦ 35፡ 2 ما يفتح الله للناس من رحمة فلا ممسك لها ۖ وما يمسك فلا مرسل له من بعده ۚ وهو العزيز الحكيم አላህ ለሰዎች ከችሮታ የሚከፍታት ለእርሷ ምንም አጋጅ የላትም፡፡ የሚያግደውም ከእርሱ በኋላ ለእርሱ ምንም ለቃቂ የለውም፡፡ እርሱም አሸናፊው ጥበበኛው ነው፡፡ እስቲ ከዚህ ከአል-ፈትታሕ ጋር በተያያዘ ነብያችን(ሰዐወ) በበድር ጦርነት ወቅት ያደረጉትን እንመልከት። በወቅቱ የሙስሊሞች ቁጥር ሶስት መቶ ፤ ፈረሰኞች ደግሞ ሁለት ብቻ ነበሩ። ከሀዲያን ደግሞ 1000 ሲሆኑ 200 ፈረሰኞች ነበሩአቸው። ስለሆነም ነብዩ(ሰዐወ) የብብታቸው ንጣት እስኪታይና ኩታቸው ከላያቸው ላይ እስኪወድቅ ድረስ እጃቸውን ከፍ በማድረግ << ጌታዬ የገባህልኝኝ ቃል ሙላልኝ>> በማለት አላህን በእጅጉ ለመኑት ፤ ተማፀኑት። በዚህም የአላህን እገዛ ድል የጠየቁት ነቢይ ምላሽ መጣላቸው። የቁርዓን አንቀፅ ወረደ። 8፡ 19 إن تستفتحوا فقد جاءكم الفتح ۖ وإن تنتهوا فهو خير لكم ۖ وإن تعودوا نعد ولن تغني عنكم فئتكم شيئا ولو كثرت وأن الله مع المؤمنين ፍትሕን (ፍርድን) ብትጠይቁ ፍትሑ በእርግጥ መጥቶላችኋል፡፡ (ክህደትንና መዋጋትን) ብትከለከሉም እርሱ ለእናንተ የተሻለ ነው፡፡ (ወደ መጋደል) ብትመለሱም እንመለሳለን፡፡ ሰራዊታችሁም ብትበዛም እንኳ ከናንተ ምንም አትጠቅማችሁም፡፡ አላህም ከምእምናን ጋር ነው፡፡ በዚህን ጊዜ ነብዩ(ሰዐወ) ደስ አላቸውና "አላሁ አክበር ጂብሪል የፈረሱን ልጓም ይዞ 1000 መላዕክት እየመራ በበድር ከናንተ ጋር ሊዋጋ መጥቷልና ደስ ይበላችሁ።" አሉ። በዚህም የአላህ ፈትሕ/ድል መጣና ሙስሊሞች ድል አደረጉ። ክፍል - 14 ይቀጥላል t.me//AkeelComparative

. የአይጥ መርዝ ጠጥቶ በህይወት ስለሚገኘው ወጣት እውነተኛ ክስተት አጃኢብ ነው!!!!!!!!!! ''''''''''''''''''''''''''''''""""""""""""""""""""""""""" ይህ ጉዳይ እውነተኛ ክስተት እንጂ በሰሚ ሰሚ ላይ የሰማሁት እና በበሬ ወለደ ወሬ ላይ የተመሠረተ ታሪክ አይደለም። እናም ነገሩ እንዲህ ነው፦ ከዚህ ከእውነተኛው ክስተት ባለታሪክ ልጅ ጋር የአንድ ሰፈር ልጆችና አብሮ አደጎች እንዲሁም የቅርብ ወዳጆች ነን። ታድያ ይህ ወጣት ልጅ የዛሬ አምስት አመት አካባቢ የአይጥ መርዝ (malatine) ጠጥቶ አሁንም ድረስ በመልካም ጤንነት ላይ ሆኖ በህይወት ይኖራል። ሱብሀን አላህ!!! ይህ አስገራሚ ክስተት እና አስደናቂ የአላህ(ሱወ) ስራ ነው!!። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 63፡ 11 ولن يؤخر الله نفسا إذا جاء أجلها ۚ والله خبير بما تعملون ማንኛይቱም ነፍስ የሞት ጊዜዋ በመጣበት ጊዜ አላህ በፍጹም አያቆያትም፡፡ አላህም በምትሠሩት ሁሉ ውስጠ ዐዋቂ ነው፡፡ ታድያ የከተማ ህይወት አልሞላልህ ሲለው የኑሮ ሁኔታ ቢመረው ገጠር ገብቼ ራሴን አረጋጋለሁ በማለት ወደ ትውልድ ቀዬው ቢመጣም በወላጆቹ ቤት ኑሮ እንዳሰበው ሳይሆንለት ቀረ። በዚህ ሁኔታ የተበሳጨው ይህ ወጣት በአላህ (ሱወ) የተወሰነለትን የመሞቻው ጊዜ ሳይደርስ በህይወት ከመኖር ይልቅ መሞትን በመምረጥ ነፍሱን ማጥፋትን ፈልጎ የአይጥ መርዝ መጠጣት ብቸኛው አማራጩ አድርጎ በማሰብ ገዳይ መርዝ ጠጥቶ ነበር። ነገር ግን ይህ የርሱ የመሞት ውሳኔ ተግባራዊ አልሆነም። ምክንያቱም ደግሞ ለዚህ ነበር። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 3፡ 145 وما كان لنفس أن تموت إلا بإذن الله كتابا مؤجلا ۗ ومن يرد ثواب الدنيا نؤته منها ومن يرد ثواب الآخرة نؤته منها ۚ وسنجزي الشاكرين ለማንኛይቱም ነፍስ በአላህ ፍርድ ቢኾን እንጅ ልትሞት አይገባትም፡፡ (ጊዜውም) ተወስኖ ተጽፏል፡፡ የቅርቢቱንም ምንዳ የሚፈልግ ሰው ከእርስዋ እንሰጠዋለን፡፡ የመጨረሻይቱንም ምንዳ የሚፈልግ ሰው ከእርስዋ እንሰጠዋለን፤ አመስጋኞችንም በእርግጥ እንመነዳለን፡፡ ባለ ታሪኩ በጊዜው የነበረውን ክስተት እንዲህ ሲል ይቀጥላል፦ " መጀመሪያ አዲስ አበባ መሳለሚያ ሳንባ ነቀርሳ አካባቢ ሞቢል አጠገብ እየኖርኩ በግ በመግፈፍና የተለያዩ የቀን ስራዎች እየሠራሁ አሳልፍ ነበር። ቀን ቀን እነዚህና ሌሎችም ያገኘኋቸው ስራዎች እየሠራሁ ማታ ማታ ደግሞ እዛው በረንዳ ላይ እተኛ ነበር። ሆኖም ይህ የበረንዳ ኑሮ እጅግ እየከበደኝ ሲመጣ ከአዲስ አበባ ወደ ገጠር ለመሄድ ወስኜ እናት አባቴ ጋር ወደ ገጠር አመራሁ። በወላጆቼ ቤትም ለአራት ወራት ያህል ከቆየሁ በኋላ አባቴ ጠጪ ስለሆነ ከአባቴ ጋር መግባባት አልቻልንምና ያበሳጨኝም ቤትም እንዳልገባ ከቤትም ያባረኝ ጀመር። ከቤትም ተባርሬ ከቤት ደጅ ላይ በሚገኝ አንድ የእቃ ማስቀመጫ እልፍኝ ውስጥ ለብቻዬ ማደር ጀመርኩ። ጭራሽ ይባስ ብሎ ምግብም እንዳይሰጠኝ አደረገ። ይህ የአባቴ ሁኔታ ቀን በቀን እየተባባሰብኝ ሲሄድ ራሴን ለማጥፋት ወሰንኩኝ። ከእለታት አንድ ቀንም ከአንድ ሱቅ ላይ የአይጥ መርዝ ገዝቼ ወደ ማደሪያዬ አመራሁ። በቡና ሲኒ ላይ ውሃ አድርጌ የአይጥ መርዙ እዛው ላይ ጨምሬ ከመጠጣቴ በፊት መረጃ ለማጥፋት አስቤ ሲኒውን ለመቅበር ትንሽዬ ጉድጓድ ቆፈርኩኝ። ከዚያም መርዙን እንደተጎነጨሁት አፌ ላይ በመያዝ ሲኒውን ቀብሬው የተጎነጨሁትን መርዝ ጠጣሁት። ከዚያም ሚለበስ ለብሼ ለጥ ብዬ ተኛሁ። የሆነ ሰዓት ምሽት ላይ ሆዴ እንደ መቁረጥ አድርጎኝ እየተገላበጥኩ ነበር ነገር ግን ከተወሰነ ደቂቃ በኋላ እንቅልፍ ወሰደኝ። ጠዋት ብንን ብዬ ስነቃ ግን በህይወት መኖሬን አረጋገጥኩ። ደንግጬ ወዲያውኑ ተነስቼ ቁጭ አልኩኝ ቤቱ ግን በመርዙ ሽታ ታወዶ ነበር። እናም ይኸው እስከዛሬ ድረስ በህይወት አለሁ።" በማለት ሁኔታውን እንዲህ አጫውቶኛል። ሱብሐን አላህ!! እጅግ የሚገርም ነገር ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ ነብዩ(ሰዐወ) ስለ እያንዳንዳችን ነፍስ ጉዳይ እንዲህ በማለት ይናገራሉ። ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 9፣ መጽሐፍ 93፣ ቁጥር 546 & Sahaih Muslim Divin Decree book 46, hadith 1 የአላህ መልእክተኛ ﷺ እንዲህ ብለዋል፡- " የእያንዳንዳችሁ መሠረት አካል በእናታችሁ ሆድ ውስጥ (ፅንስ ከተፀነሰ በኋላ) ለ40 ቀናት የዘር ፈሳሽ ሆኖ ይሰበሰባል ፣ ለተመሣሣይ 40 ቀናት የረጋ ደም ይሆናል ፣ ለተመሣሣይ 40 ቀናትም የታኘከ የሚመስል ቁራጭ ስጋ ይሆናል። ከዚያ በኋላ ወደርሱ መልዓክ ይላክና ሩህ(ነፍስ) ይነፋበታል። መልዓኩም #4 ነገሮችን እንዲፅፍ ይታዘዛል። ሲሳዩን ፣ #የመሞቻ #ጊዜውን ፣ ስራውን እና እድለ ቢስ(የእሳት) እርጉም አሊያም እድለኛ (የጀነት) ብሩክ መሆኑን።" በሌላም ሐዲሳቸው ላይ ነብዩ(ሰዐወ) <ሩህ አልቁዱስ (ጅብሪል) በውስጤ አንዲት ነፍስ #ሲሳዩዋን #ሳታጠናቅቅ #እንደማትሞት #አሳውቆኛል።>> ብለዋል የዚህም ወጣት ልጅ ሲሳይ ስላልተጠናቀቀ ነው በጊዜው ጠጥቶት ከነበረው የአይጥ መርዝ ያመለጠው!!

⓬ አር- ረዛቅ ( الرزاق ) እና አል-ወህሃቡ ( الوخابو ) {{{ ሲበዛ ለጋስ እና ሲሳይን ሰጭ }}} አር-ረዛቅ እና አል-ወህሃብ ከ99 ሌሎች የአላህ መልካም ስሞች መካከል የሚጠቀሱ ስሞቹ ናቸው። - #አር_ረዛቅ ማለት አብዝቶ የሚለግስ ማለት ነው። ያለ ስስት ይለግሳል። ለእንስሳትም ሆነ ለእፅዋት ፣ ለሠው ልጅም ሆነ ለሌላ ፍጡር፣ በርሱ ላመኑትም ሆነ ለካዱት ሁሉ ይለግሳል፤ ሲሳይ ይሰጣቸዋል። በዚህም አር-ረዛቅ ሲሳይ ሰጪ የሆነ ማለት ነው። 51፡ 58 إن الله هو الرزاق ذو القوة المتين አላህ እርሱ ሲሳይን ሰጪ የብርቱ ኀይል ባለቤት ነው፡፡ ሪዝቅ(ሲሳይ) ስንል በቋንቋ ደረጃ <ድርሻ> አሊያም <ክፍፍል> ማለት ነው። አር-ረዛቅ ደግሞ ሲሳይን የፈጠረ ነው። ✔ አር-ራዚቅ እና አር-ረዛቅ መካከል ያለው ልዩነት አር-ራዚቅ የሚለው ቃል በቁርዓን ውስጥ አንድም ቦታ ላይ አልተጠቀሰም። ነገር ግን #አር_ረዛቅ የሚለው የአላህ ስም ግን ተጠቅሷል። በቋንቋ ደረጃ ሁለቱንም ተመሳሳይ ትርጉም ያላቸው ናቸው። ልዩነታቸው #አር_ራዚቅ ለከፊሎች የሚሰጥ ወይም ለከፊሎች የሚከለክል ማለት ሲሆን #አር_ረዛቅ ግን እጅግ ለጋስና በሲሳዩም ሁሉን የሚያካልል ለሁሉም የሚያዳርስ ማለት ነው። 👉 አር-ረዛቅ ሲሳይን ሲያከፋፍል ለአማኝ ለከሀዲ፣ ለሙስሊም ለክርስቲያን ለቡድሀ፣ በአጠቃላይ ለሁሉም ፍጥረታቱ የሚለግስ ማለት ነው። አር-ረዛቁ አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 11፡ 6 وما من دابة في الأرض إلا على الله رزقها ويعلم مستقرها ومستودعها ۚ كل في كتاب مبين በምድርም ላይ ምንም ተንቀሳቃሽ የለችም ምግቧ በአላህ ላይ ያለ ቢኾን እንጂ፡፡ ማረፊያዋንም መርጊያዋንም ያውቃል፡፡ ሁሉም ግልጽ በሆነው መጽሐፍ ውስጥ ነው፡፡ ታድያ የእያንዳንዳችን ሪዝቅ (ሲሳይ) በአላህ(ሱወ) እጅ ላይ ከመፈጠራችን በፊት ቀድሞ ተወስኖልን የተፃፈ ውሳኔ ሲሆን ከዚህ ውጪ የሚሆን ነገር የለም። ይህንን ከተረዳን ደግሞ ሐራም ለመብላት ከመጣጣር እንታቀባለን። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 30፡ 40 الله الذي خلقكم ثم رزقكم ثم يميتكم ثم يحييكم ۖ هل من شركائكم من يفعل من ذلكم من شيء ۚ سبحانه وتعالى عما يشركون አላህ ያ #የፈጠራችሁ፣ #ከዚያም #ሲሳይን #የሰጣችሁ፣ ከዚያም የሚገድላችሁ ከዚያም ሕያው የሚያደርጋችሁ ነው፡፡ ከምታጋሯቸው (ጣዖታት) ውስጥ ከዚህ ነገር አንዳችን የሚሠራ አለን ለአላህ ጥራት ይገባው፡፡ (በእርሱ) ከሚያጋሩትም ሁሉ ላቀ፡፡ አላህ(ሱወ) <<ሲሳይን የሠጣችሁ>> ሲል ባለፈ ክስተት ነው የተናገረው። ይሕም ማለት ከላይ እንደተጠቀሰው ቀድሞውኑ የተወሰነና የተመጠነ መሆኑን ያመላክታል። የአላህ መልዕክተኛ(ሰዐወ) እንዲህ ብለዋል፦ Sahih Bukhari Vol 9, Book 93 , numeber 546 and Sahih Muslim Divin Decree Book 46, Hadith 1 " የእያንዳንዳችሁ መሠረት አካል በእናታችሁ ሆድ ውስጥ (ፅንስ ከተፀነሰ በኋላ) ለ40 ቀናት የዘር ፈሳሽ ሆኖ ይሰበሰባል ፣ ለተመሣሣይ 40 ቀናት የረጋ ደም ይሆናል ፣ ለተመሣሣይ 40 ቀናትም የታኘከ የሚመስል ቁራጭ ስጋ ይሆናል። ከዚያ በኋላ ወደርሱ መልዓክ ይላክና ሩህ(ነፍስ) ይነፋበታል። መልዓኩም 4 ነገሮችን እንዲፅፍ ይታዘዛል። #ሲሳዩን ፣ የመሞቻ ጊዜውን ፣ ስራውን እና እድለ ቢስ(የእሳት) እርጉም አሊያም እድለኛ (የጀነት) ብሩክ መሆኑን።" ነብዩ(ሰዐወ) በሌላ ሐዲሳቸው <ሩህ አልቁዱስ (ጅብሪል) በውስጤ አንዲት ነፍስ ሲሳዩዋን ሳታጠናቅቅ እንደማትሞት አሳውቆኛል።>> ብለዋል ታድያ ከተጻፈልን ውጪ የሚሆን የለምና ብዙ ጊዜ ቸኩለን ከሐራም በማምጣት በራሳችን ላይ ጣጣ እናበዛለን እንጂ አላህ(ሱወ) የፃፈልንን ሲሳይ ያለጥርጥር በእጃችን መግባቱ አይቀርም። ሆኖም ከሐራም ያመጣነው እንደሆነም መጨረሻችን እሳት ነው። ነገር ግን ተረጋግተን ሲሳይን በሀላል ፈልገን እንደሆነ ምንዳችን ጀነት ነው። እናም ሲሳያችን የተጻፈ ማወቅ ይኖርብናል። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 51፡ 22-23 وفي السماء رزقكم وما توعدون فورب السماء والأرض إنه لحق مثل ما أنكم تنطقون ሲሳያችሁም የምትቀጠሩትም (ፍዳና ምንዳ) በሰማይ ውስጥ ነው፡፡ በሰማይና በምድር ጌታም እምላለሁ፡፡ እርሱ እናንተ እንደምትናገሩት ብጤ እርግጠኛ ነው፡፡ ይህን እና ሌሎችንም ሐይማኖታዊ ንፅፅሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ t.me//AkeelComparative

ጥርስ የሌለው አንበሳ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ በጋዛ ያለው ጦርነት በአስቸኳ እንዲቆምና አፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ በሚል በዓረብ ሃገራት ጥምረት የተዘጋጀውን ረቂቅ የመፍትሄ
ጥርስ የሌለው አንበሳ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባዔ በጋዛ ያለው ጦርነት በአስቸኳ እንዲቆምና አፋጣኝ ሰብዓዊ እርዳታ እንዲገባ በሚል በዓረብ ሃገራት ጥምረት የተዘጋጀውን ረቂቅ የመፍትሄ ሃሳብ በ120 አብላጫ ድምፅ አፅድቋል። እስኪ አላህ ለኸይር ያድርገው! ምናልባትም እስራኤል በሰማይ፣ በምድር፣ በባህር ዛሬ እሳት ማዝነቧ ሳያስቆሙኝ በፊት የልቤን ላድርስ ብላ ይሆናል። አላህ ከነ አገሮቿ መውደቂያዋን ያቅርበው። ባለ አረንጓዴው ጦርነት ይቁም፣ እርዳታ ይግባ ያሉ ናቸው። ባለ ቢጫዎቹ ድምፀ ተዓቅቦ ያደረጉ ናቸው። ባለ ቀዩ ጦርነቱ ይቀጥል፣ እርዳታም አይገባም፣ ፈለስጢናውያን ይጨፍጨፉ ባይዎች ናቸው። የኛዋ ቆማጣ ግን ድምፀ ተዐቅቦ ማድረጓ ጦርነቱ ይቀጥል፣ በረሃብ ይለቁ ማለቷ ነው እንደ? ሐቂቃ የሚመለከተው አካል መጠየቅ አለበት። ቆሻሻ ነገር!

⓫ አል- ቀህሃር ( القهار ) {{{ ሁሉን አሸናፊው }}} #አል_ቀህሃር ሌላኛው የአላህ መልካም ስም ሲሆን ትርጉሙም #ሁሉን #አሸናፊው ማለት ነው። ይህ ስም በቁርዓን ውስጥ 6 ጊዜ ያክል የተጠቀሰ ሲሆን በሁሉም ቦታ የእርሱን ታላቅነት የሚመሰክርና ከእርሱ ውጪ ከእርሱ ጋር የሚስተካከል የሆነ ሌላ አምላክ የሌለ መሆኑን በሚናገር መልኩ ተጠቅሷል፦ ለምሳሌ 1 ፦ ከአላህ ጋር የሚስተካከል ሌላ የሌለ መሆኑን ሲናገር 13፡16 قل من رب السماوات والأرض قل الله ۚ قل أفاتخذتم من دونه أولياء لا يملكون لأنفسهم نفعا ولا ضرا ۚ قل هل يستوي الأعمى والبصير أم هل تستوي الظلمات والنور ۗ أم جعلوا لله شركاء خلقوا كخلقه فتشابه الخلق عليهم ۚ قل الله خالق كل شيء وهو الواحد القهار «የሰማያትና የምድር ጌታ ማን ነው» በላቸው፡፡ «አላህ ነው» በል፡፡ «ለነፍሶቻቸው ጥቅምንም ጉዳትንም የማይችሉን ረዳቶች ከርሱ ሌላ ያዛችሁን» በላቸው፡፡ «ዕውርና የሚያይ ይስተካከላሉን ወይስ ጨለማዎችና ብርሃን ይስተካከላሉን ወይስ ለአላህ እንደርሱ አፈጣጠር የፈጠሩን ተጋሪዎች አደረጉለትና ፍጥረቱ በእነሱ ላይ ተመሳሰለባቸውን>> በል፤ << አላህ ሁለመናው ፈጣሪ ነው። እርሱም አንዱ አሸናፊው ነው>> በል። 12፡39 يا صاحبي السجن أأرباب متفرقون خير أم الله الواحد القهار «የእስር ቤት ጓደኞቼ ሆይ! የተለያዩ አምላኮች ይሻላሉን ወይስ አሸናፊው አንዱ አላህ 38፡65 قل إنما أنا منذر ۖ وما من إله إلا الله الواحد القهار «እኔ አስፈራሪ ብቻ ነኝ፡፡ ኀያል አንድ ከኾነው አላህ በቀር ምንም አምላክ የለም» በላቸው፡፡ ምሳሌ 2፦ አላህ ልጅ የሌለውና እርሱም አሸናፊው አንድ አላህ መሆኑን ሲናገር እንዲህ ይላል 39፡ 4 لو أراد الله أن يتخذ ولدا لاصطفى مما يخلق ما يشاء ۚ سبحانه ۖ هو الله الواحد القهار አላህ ልጅን መያዝ በፈለገ ኖሮ ከሚፈጥረው ውስጥ የሚሻውን ይመርጥ ነበር፡፡ ጥራት ተገባው፡፡ እርሱ አሸናፊው አንዱ አላህ ነው፡፡ ምሳሌ 3 ፦ የመጨረሻው ቀን ባለቤት እርሱ አሸናፊው አላህ ብቻ ስለመሆኑ ሲናገርም እንዲህ ይላል፦ 14፡ 48 يوم تبدل الأرض غير الأرض والسماوات ۖ وبرزوا لله الواحد القهار ምድር በሌላ ምድር የምትለወጥበትን ሰማያትም (እንደዚሁ) አንድ አሸናፊ ለኾነው አላህም (ፍጡራን ሁሉ) የሚገለጹበት ቀን (አስታውሱ)፡፡ 40፡ 16 يوم هم بارزون ۖ لا يخفى على الله منهم شيء ۚ لمن الملك اليوم ۖ لله الواحد القهار እነርሱ (ከመቃብር) በሚወጡበት ቀን በአላህ ላይ ከእነርሱ ምንም ነገር አይደበቅም፡፡ «ንግሥናው ዛሬ ለማን ነው?» (ይባላል፤)፡፡ «ለአሸናፊው ለአንዱ አላህ ብቻ ነው» (ይባላል)፡፡ *///* ክፍል - 12 ይቀጥላል ሌሎች ንፅፅሮችን ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችን t.me//AkeelComparative ይቀላቀሉ

35፡ 32 ثم أورثنا الكتاب الذين اصطفينا من عبادنا ۖ فمنهم ظالم لنفسه ومنهم مقتصد ومنهم سابق بالخيرات بإذن الله ۚ ذلك هو الفضل الكبير ከዚያም እነዚያን ከባሮቻችን የመረጥናቸውን መጽሐፉን አወረስናቸው፡፡ #ከእነርሱም #ነፍሱን #በዳይ #አልለ፡፡ ከእነርሱም መካከለኛ አልለ፡፡ ከእነሱም በአላህ ፈቃድ በበጎ ሥራዎች ቀዳሚ አልለ፡፡ ያ (ማውረስ)፤ እርሱ ታላቅ ችሮታ ነው፡፡ 33፡ 72 إنا عرضنا الأمانة على السماوات والأرض والجبال فأبين أن يحملنها وأشفقن منها وحملها الإنسان ۖ إنه كان ظلوما جهولا እኛ አደራን በሰማያትና በምድር፣ በተራራዎችም ላይ አቀረብናት፡፡ መሸከሟንም እንቢ አሉ፡፡ ከእርሷም ፈሩ፡፡ ሰውም ተሸከማት፡፡ እርሱ #በጣም #በደለኛ ተሳሳች ነውና፡፡ 39፡ 53 قل يا عبادي الذين أسرفوا على أنفسهم لا تقنطوا من رحمة الله ۚ إن الله يغفر الذنوب جميعا ۚ إنه هو الغفور الرحيم በላቸው «እናንተ #በነፍሶቻችሁ ላይ #ድንበር #ያለፋችሁ #ባሮቼ ሆይ! ከአላህ እዝነት ተስፋ አትቁረጡ፡፡ አላህ ኃጢኣቶችን በመላ ይምራልና፡፡ እነሆ እርሱ መሐሪው አዛኙ ነውና።>> ታድያ አል-ገፋር ፣ አል-ገፍፋር የሆነው አላህ(ሱወ) ምህረት ድንበር የሌለው ስለመሆኑ ምሳሌዎችን እንመልከት። ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ ይላሉ፦ ሶሒሕ ቡኻሪ ቅፅ 3 መጽሐፍ 41 ቁጥር 573 በአቡ ዳር ዘግበውታል። አንድ ጊዜ ከነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ጋር እያለሁ... ነብዩ(ሰዐወ) እንዲህ አሉ፦ ጂብሪልም መጣና እንዲህ አለኝ፡- ‹‹ከተከታዮችህ ከአላህ ጋር አንድንም ሳይገዙ የሞተ ሰው ጀነት ይገባል›› አለኝ። " አልኩትም "እንዲህ ያሉ እና የመሳሰሉትን ነገሮች ቢያደርግም? (ማለትም ቢሰርቅም ወይም ህገወጥ የግብረ ሥጋ ግንኙነት ቢፈጽምም መጠጥ ቢጠጣም? )" "አዎ" ህዝብህን አብስር አለኝ። ።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክፍል - 11 ይቀጥላል ይህን ርዕስ በተከታታይ ክፍሎች ለማግኘት የቴሌግራም ቻናላችንን ይቀላቀሉ ለሌሎችም #ሼር ያድርጉ t.me//AkeelComparative ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።

99ኝ የአላህ መልካም ስሞች ትርጉም ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። ክፍል -10 ⓾ አል-ገፍፋር ( الغفار ) እና አል-ገፉር ( الغفور ) {{{ የሰፊ ምህረት ባለቤት እና መሐሪ }}} #አል_ገፍፋር እና #አል_ገፉር ሁለቱንም ከአላህ 99ኙ የመልካም ስሞች መካከል የሚጠቀሱ ስሞች ሲሆኑ ሁለቱንም ስሞች ከምህረቱ ጋር ተያይዘው ይጠቀሳሉ። < መግፊራ፣ ጉፍራን ፣ አስተግፊሩላህ...> የሚሉ ቃላት ትርጉም ✔ << ገፈረ >> የሚለው ቃል ሸፈነ፣ደበቀ፣ ጠበቀ... እንደማለት ነው። ይህም አንድን ነገር እንዳይጎዳ አድርጎ ያዘ፣ ጠበቀ፣ ሸፈነ፣ሸሸገ ማለት ነው በዐረቢኛ ቋንቋ። - #ገፉር (መሐሪ) የሚለው ቃል ትርጉሙም ለአላህ(ሱወ) የሚባል ሲሆን ይህም በዚህም ሆነ በመጨረሻው ዓለም ይሸፍንሀል፣ በትንሳኤ ቀን ደግሞ ከእሳት ይጠብቅሀል ማለት ነው። - #መግፊራ ፣ #ጉፍራን ምህረት ማለት ሲሆን #አስተግፊሩላህ ማለት ደግሞ ከአላህ ምህረትን እለምናለሁ ማለት ነው። - #ገፈረ ማለት ማረ፣ ምህረት ሰጠ እንደማለት ነው። 👉 ገፉር ፣ ገፍፋር እና ጋፊር መካከል ያለው ልዩነት - #ገፉር የሚለው የአላህ ስም በቁርዓን ውስጥ 91 ጊዜ ተጠቅሷል - #አል_ገፍፋር ድሞ 5 ጊዜ የተጠቀሰ ሲሆን #ጋፊር ደግሞ 1 ጊዜ ነው የተጠቀሰው። በዚህም መሠረት #ገፉር የሚለው ስም በብዛት ተጠቅሷል ማለት ነው። ለምሳሌ፦ 28፡16 قال رب إني ظلمت نفسي فاغفر لي فغفر له ۚ إنه هو الغفور الرحيم «ጌታዬ ሆይ! እኔ ነፍሴን በደልኩ፡፡ ለእኔም ማር አለ፡፡» ለእርሱም ምሕረት አደረገለት እርሱ #መሓሪ አዛኝ ነውና። - #ገፍፋር የሚለው ስም ደግሞ 71፡ 10 فقلت استغفروا ربكم إنه كان غفارا «አልኳቸውም፡- ጌታችሁን ምሕረትን ለምኑት፡፡ እርሱ በጣም መሐሪ ነውና፡፡ - #ጋፊር ደግሞ በጋፊር ምዕራፍ ቁጥር 3 ላይ የተጠቀሰው ነው። አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 40፡ 3 غافر الذنب وقابل التوب شديد العقاب ذي الطول ۖ لا إله إلا هو ۖ إليه المصير ኀጢአትን መሓሪ፣ ጸጸትንም ተቀባይ፣ ቅጣተ ብርቱ፣ የልግስና ባለቤት ከኾነው (አላህ የወረደ ነው)፡፡ ከእርሱ በቀር አምላክ የለም፡፡ መመለሻው ወደርሱ ብቻ ነው። ኡለማዎች በሶስቱ ስሞች ትርጉም ዙሪያ ያሉት አለ። ይኸውም፦ ✔ #ጋፊር ማለት አንድ ወንጀል (ሐጢአት) የሚምር ማለት ነው። ✔ #ገፉር ማለት የቱን ያህል ቢበዙም ብዙ ወንጀሎችን (ሐጢአቶችን) ሁሉ የሚምር ማለት ነው ያሉ ሲሆን ✔ #ገፍፋር ማለት ደግሞ እጅግ የከፉና ከበባድ የሆኑ ወንጀሎችን የሚምር ማለት ነው ብለዋል። ታድያ ሰዎች ከወንጀሎቻቸው አንጻር በሶስት ይከፈላሉ። እነርሱም በዳይ ፣ በጣም በደለኛ እና በበደል ውስጥ ድንበር ያለፈ። አላህ(ሱወ) በተለያዩ የቁርዓን አንቀፆች ውስጥ እንዲህ ብሏል፦

በመሠረቱ በሐይማኖት ላይ አዲስ ነገርን መፍጠር/ የሐይማኖት ፈጠራ ይህም ቢዳአ/ጥመት/ኑፋቄ የሚሉት ነገር ከጥንትም ጀምሮ የነበረ ጉዳይ ነው። ለምሳሌ፦ እንደ መፅሐፍ ቅዱስ ከሄድን ጳውሎስ እንዲህ ይላል፦ - #የሐዋርያት ስራ 24፥14 " ነገር ግን ይህን እመሠክራለሁ። በህጉ ያለውን በነቢያት የተፃፉትን ሁሉ አምኜ የአባቶቼን አምላክ እነርሱ #ኑፋቄ ብለው እንደሚጠሩት መንገድ አመልካለሁ።" በማለት ይናገራል። - #2ኛ የጴጥሮስ መልዕክት 2፥1-2 " ሀሰተኞች አስተማሪዎች በህዝቡ መሀል ነበሩ፥ እንዲሁም ሀሰተኞች አስተማሪዎችም ይሆናሉ። እነርሱም የዋጃቸውን አምላክ እንኳን ክደው የሚፈጥን ጥፋት በራሳቸው እየሳቡ ፈጥኖ የሚያጠፋ የሆነን #ኑፋቄ አሹልከው ያገባሉ።በእነርሱም ጠንቅ የእውነት መንገድ ይሰደባል።" ይላል ✅ በቡኻሪ በ3ኛ መፅሐፍ ላይ 2652 ነብዩ (ሰ.ዓ.ወ) ምርጡ ትውልድ የኔው ትውልድ ነው፤ ከዛም የሚቀጥለው ከዛም የሚቀጥለው ብለዋል። ℹ ነብዩ ምርጡ ትውልድ የሶሐቦች ትውልድ ነው ከዛም የታኣቢዎች ከዛም የታኣቢ ተከታዮች ናቸው በማለት ተናግረዋል። በክርስትናው እምነት ዘንድ ፓትርያርክ...ቄስ ብለን መሪዎቹን እንዳየነው ሁሉ በእስልምናውም ዘንድ ሙፍቲህ፣ ኢማም.. ብለን እንጠራለን። ታድያ እነዚህ ኢማሞችን መከተል ደግሞ ተቅሊድ ይባላልና ሐኒፍ ወይም በአሁን ሰዓት ሐነፊይ ተብሎ እየተጠራ የሚታወቀው እምነትም እነዚያን የጥንት ኢማሞች/ ሼህኦች ከመከተል አንፃር ጋር የመጣ አዲስ የማስተካከያ ፈጠራ ነው። @AkeelComparative አላህ በቁርዓን ራሳችሁን ሙስሊም ተብላችሁ ተጠሩ እንጂ ሐነፊይ ፣ ሐኒፍ፣ ኸኒፋ ብላችሁ ጥሩ አላለም። ወይም ደግሞ ስለዚህ የመጠሪያ ስም ጉዳይን በተመለከተ በዚህ ስም ተጠሩ የሚል ሶሒሕ ሐዲስ ካለ ጠቁሙንና እንከተላችሁ። እውነቱ ግን ይህ ነው ሙስሊም መባል ብቻ!!! አላህም እንዲህ በማለት ይናገራል፦ አላህ ሱወ እንዲህ በማለት ይናገራል፦ 22፡78 وجاهدوا في الله حق جهاده ۚ هو اجتباكم وما جعل عليكم في الدين من حرج ۚ ملة أبيكم إبراهيم ۚ هو سماكم المسلمين من قبل وفي هذا ليكون الرسول شهيدا عليكم وتكونوا شهداء على الناس ۚ فأقيموا الصلاة وآتوا الزكاة واعتصموا بالله هو مولاكم ۖ فنعم المولى ونعم النصير <<... የአባታችሁ የኢብራሂምን ሀይማኖት ተከተሉ። እርሱ ከዚህ በፊት ሙስሊሞች ብሎ ሰይሞአችኋል፤ በዚህም ቁርዓን መልክተኛው በናንተ ላይ መስካሪ እንዲሆን እናንተም በሰዎች ላይ መስካሪዎች እንድትሆኑ ሙስሊሞች ብሎ ሰይሞአችኋል።>> አበቃ!! ሌላ ተጨማሪ መጠሪያ ስም አያስፈልገንም። ምክንያቱም አላህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦ 30፥32 << ከእነዚያ ሐይማኖታቸውን ከለያዩትና ክፍፍሎችም ከሆኑት አትሁኑ። ህዝብ ሁሉ እነሱ ዘንድ ባለው ነገር ተደሳቾች ናቸው።>> በማለት ይናገራል። ታድያም የኡማቸውን ሁኔታ የሚያስጨንቃቸውንም ነብይ ነብዩ ሙሀመድ (ሰ.ዓ.ወ) እንዲህ ይላሉ፦ ✅ በሱና አቡዳውድ ሐዲስ 4579 እና 4580 ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) አይሁዶች ለ71 እና ለ72 እንዲሁም ክርስቲያኖች ለ71 እና ለ72 ቦታ እንደተከፈሉት ሁሉ ሙስሊሞችም ለ73 ይከፈላሉ ብለዋል። ✅ ተርሚዚ 131 እና 2643 ላይ እንደተጠቀሰው ረሱል(ሰ.ዓ.ወ) የእስራኤል ልጆች፣ አይሁዶችና ክርስቲያኖች ለ72 መንገድ ተከፍለዋል የኔንም ኡማ ለ73 መንገድ ይከፈላል። አንዱ ሲቀር ሁሉም የእሳት ናቸው።ብለዋል ሶሃቦችም እነማናቸው የሚተርፉት ብለው ጠየቋቸው። ረሱልም (ሰ.ዓ.ወ) እኔና ሶሀቦችን የተከተሉ። በማለት መልሰውላቸዋል። በመጨረሻም ሶሒሕ ቡኻሪ ጥራዝ 3 ተ.ቁ 4565 " የሙስሊሙን ኡማ የሚከፋፍል ሰው ካለ በሰይፍ ምቱት እምቢ ብሎም ከድርጊቱ አልቆጠብም ካለ ግደሉት" ብለዋል። ።።።።።።።።///።።።።።።። ክፍል -3 በሌላ ግሩፕ ይቀጥላል t.me//AkeelComparative

የሐኒፍ እምነት ከነብዩ(ሰዐወ) በፊት በጃሂሊያ ዘመን በዚህ መልኩ የአብረሀም እምነት ነው ተብሎ ይታመን ነበር። ታድያ ለመሆኑ አብረሐም ክርስቲያን ነበረ ወይስ አይሁድ? አላህ(ሱወ) እንዲህ ይላል፦ 3፡ 67 ما كان إبراهيم يهوديا ولا نصرانيا ولكن كان حنيفا مسلما وما كان من المشركين << ኢብራሂም ይሁዳዊም ክርስቲያንም አልነበረም። ግን ወደ ቀጥተኛው ሀይማኖት የተዘነበለ ሙስሊም ነበረ። ከአጋሪዎችም አልነበረም።>> በመፅሐፍ ቅዱስ ውስጥ የትኛውንም ነብይ ሐይማኖቱ ክርስቲያን ወይም አይሁድ ነበር የሚል አንድ ነጥብ እንኳን የለም። በተመሳሳይ መልኩ የአብረሐምንም ሐይማኖት #ክርስትና ወይም አይሁድ ነበር የሚል ማስረጃ ከመፅሐፍ ቅዱስ ማግኘት አንችልም። ቁርዓን ግን ኢብራሂም (ዐ.ሰ) ሙስሊም እንደነበሩ ይነግረናል። ታድያም ሐነፊይ ማለት ከእስልምና በፊት በነበረ የጃሂሊያ ዘመን ይታይ የነበረ እምነት መሆኑንንም ከተገነዘብን ሐኒፍ {"حنيف } < remonized > (እንደገና ማስተካከል) እና ሐኒፋ { حنيفاء} " renunciate" (መክዳት) የሚሉትን በጥቂቱ እንመልከታለን፦ በቁርዓን ውስጥ {حنيفا } " haneefan "የሚለው ቃል 9 ጊዜ ተጠቅሷል። እነዚህም፦ 2፡135፣ 3፡67 ፣ 3፡95፣ 4፡125፣ 6፡79፣ 10፡105፣ 16፡120፣ 16፡123 & 30፡30 ለምሳሌ፦ 2፡ 135 وقالوا كونوا هودا أو نصارى تهتدوا ۗ قل بل ملة إبراهيم #حنيفا ۖ وما كان من المشركين << አይሁድን ወይም ክርስቲያን ሁኑ ፤ (ቅኑን መንገድ ትመራላችሁና>> አሉም። <<አይደለም የኢብራሂምን ሐይማኖት ቀጥተኛ ሲሆን እንከተላለን፤ ከአጋሪዎችም አልነበረም>> በላቸው። ይላል!! እንደ የአረብኛ ቋንቋ ህግ መሠረት በአንድ ቃል ላይ አንድ ፊደል በጨመረ ቁጥር የቃሉ ትርጉም እንደ ጭማሪው ይለያያል። በቁርዓን ውስጥ حنيفا የሚለው ቃል "ቀጥተኛ" ለማለት የሚያገለግል ሲሆን ይህም ኢብራሂም ቀጥተኛ ሙስሊም እንደነበሩ ይገልፃል። በWikipedia ላይ { حنيفاء} ተብሎ የተጠቀሰው ቃል "መክዳት" የሚል ትርጉም ሲሰጠው حنيف የተሰኘው ቃል ደግሞ remonized "ማስተካከል" ተብሎ ተጠቅሷል። ይህም ማለት ደግሞ አንድን አምላክና ቀጥተኛውን መንገድ በመካድ ሌላ መንገድ መከተል/ማሻሸል ማለት ነው። ኢብራሂም ግን፦ 4፡ 125 ومن أحسن دينا ممن أسلم وجهه لله وهو محسن واتبع ملة إبراهيم #حنيفا ۗ واتخذ الله إبراهيم خليلا << እርሱ ከመልካም ሰሪ ሆኖ ፊቱን ለአላህ ከሠጠና የኢብራሂምን መንገድ ቀጥተኛ ሲሆን ከተከተለ ሰው ይበልጥ ያማረ ማነው? አላህም ኢብራሂምን ፍፁም ወዳጅ አድርጎ ያዘው።>> ይላል። እዚጋ أسلم " አስለም "የተባለው ለአላህ የታዘዘ ለማለት ነው ይህም "ኢስላም "إسلم ከሚል ቃል derive የተደረገ ነው። ኢስላም ማለት የታዘዘ/ታዛዥ ማለት ነው። ኢብራሂም ግን ከአጋሪዎች ክርስቲያን/አይሁድ በኩል ሳይሆኑ ለአላህ የታዘዙ ኢስላም/ ቀጥተኛ حنيفا /ሙስሊም ነበሩ። Wikipedia ላይ patriarch Abraham በማለት የገለፀው ደግሞ እነርሱ /የክርስትና ሐይማኖት የእምነቱ ከፍተኛ ደረጃ ላይ የተቀመጡ መሪዎች የሚጠቀሙበት መጠሪያ ስም ሲሆን የስም ጀረጃውም ፓትሪያርክ፣... ቄስ.. እያለ ይቀጥላል። በዚህ እምነት ውስጥ ሁለት አይነት አስተሳሰቦች አሉ፦ እነርሱም ሚስጥረ ስላሴን የማመንና ያለማመን ሲሆኑ በዚህም ምክንያት የመጣ ክርስትና ለብዙ ጎራዎች ተከፋፍለዋል። ይህ ማለት ደግሞ በቀደምት ሐነፊዮች ዘንድ የተከሰተው ክስተት ማለት ነው። ታድያ ነብዩ (ሰዐወ) ከመጡ በኋላ ክርስቲያን / አይሁድ ሆነው ሐኒፊ ይባሉ ከነበሩት ሰዎች ጥቂቶቹ እስልምናን ተቀብለው ነበር። ከእነዚህ ሰዎችም መካከል እነ Warakeh ibnu Newfal እና ሌሎችንም የመሳሰሉትን ይገኙ ነበር። ሌሎች ኸኒፋ የሚባሉት ክርስቲያኖች ግን አንድ "አምላክን በመካድ" henotheismን በመመስረት different godsን በማምለክ (Godን renunciate) በማድረግ ስላሴን በማምለክ ሲቀጥሉ ከረሱል(ሰዐወ) ህልፈት በኋላና ከሶሐቦች ዘመን መጨረሻ አካባቢም አንዳንድ ታቢዎች(ሶሐቦችን ያዩ) ደግሞ ሙስሊምም ሆነው አንድ አምላክን እያመለኩ ቢሆን ነገር ግን ሐይማኖቱን እንደገና ማስተካከል በሚል (ሐኒፍ ፤ remonized) ብዳአን ተግባራዊ ማድረግ ጀመሩ።

- monotheism is distinguished from henotheism, religious system. beliver worships d/t gods with equal validity. ይህ ማለት ደግሞ የስላሴ ፅንሰ ሀሳብ ማለት ነው። እሺ የዚህ monotheism ፅንሰ ሀሳብ እንደዚህ ከሆነ Patriarch Abraham የተባለውን ጉዳይ ሁኔታ እንመልከተው፦ - patriarch is the highest ranking bishops in estern Orthodox, Oriental Orthodox, the Catholic church, independent catholic churches(are termed patriarchs in certain cases also Popes(ቀሳውስት). Such as, Rome pope, Alexanderia pope) በማለት ይተረጉመዋል። አሁን ወደ ራሳችን ሙግት እንመለስ! በመጀመሪያ ደረጃ ስለዚህ እምነት ሐነፊይ (ሐኒፍ) በሐዲስ ውስጥ እንደዚህ ተጠቅሶ እናገኘዋለን፦ ሶሒሕ አል ቡሓሪ ቅፅ 5፣ መጽሐፍ 58፣ ቁጥር 169 አብደላህ ቢን ዑመር ዘግበውታል። ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) ወደ ነብዩ (ሶ.ዐ.ወ) መለኮታዊ ተመስጦ ከመምጣቱ በፊት በለዳህ (ሸለቆው ሸለቆ) ግርጌ ላይ የዚድ ቢን ዐምር ቢን ኑፈይልን አገኙት። ለነብዩ (ሰ.ዐ.ወ) (ከዚያም ለዛይድ ቀረበ)፡- “በድንጋይ ጣዖቶቻችሁ ስም የምታርዱትን አልበላም። በእርድ ጊዜ የአላህ ስም የተጠራባቸውን ነገሮች እንጂ ሌላ አልበላም። የዚድ ብን ዐምር ቁረይሾች ከብቶቻቸውን የሚታረዱበትን መንገድ በመተቸት “አላህ በጎችን ፈጠረ ውሃውንም ከሰማይ ላከላቸው፣ ከምድርም ሣር አበቀለላት። አንተ ግን ከአላህ ስም ሌላ ታርደዋለህ፡ ይለው ነበር፡ ድርጊቱን ውድቅ አድርጎ እንደ አጸያፊ ነገር ቆጥሮታል፡ ኢብኑ ዑመር እንደተረከው፡- ዘይድ ቢን ዐምር ቢን ኑፈይል ስለ እውነት ጠየቀ ወደ ሻም ሄደ። ሃይማኖትን መከተል ያለበት አንድ የአይሁድ ሊቅ አግኝቶ ስለ ሃይማኖታቸው ጠየቀው እርሱም ‹ሃይማኖታችሁን ልቀበል አስባለሁና ስለሱ አንድ ነገር ንገረኝ› አለው አይሁዳዊውም ‹‹አንተ ካልሆነ በቀር ሃይማኖታችንን አትቀበልም›› አለው። የአላህን ቁጣ ድርሻህን ተቀበል» አለው ዘይድ፡ "እኔ ከአላህ ቁጣ በቀር አልሮጥም፤ እሱን የማስወገድ አቅም ካለኝም ትንሽ እንኳ አልሸከምም። ስለ ሌላ ሀይማኖት ንገረኝ?” ሲላቸው፡ “ #ከሐኒፍ በስተቀር ሌላ ሃይማኖት አላውቅም።” ዘይድ፡ “ሀኒፍ ምንድን ነው?” ሲል ጠየቀ፡- “#ሐኒፍ (የነቢዩ) የኢብራሂም ሃይማኖት ነው። አይሁዳዊም ክርስቲያንም አልነበረም አላህንም (ብቻውን) ብቻ አያመልክም ነበር" ከዛ ዘይድ ወጥቶ አንድ የሃይማኖት ሊቅ አገኘና እንደ ቀድሞው ነገረው። ክርስቲያኑም "አንተ ሃይማኖታችንን አትቀበልም በቀር የአላህን እርግማን ድርሻ ታገኛለህ።” ዛይድም እንዲህ ሲል መለሰ፡- “ከአላህ እርግማን በስተቀር አልሮጥም፤ የአላህን እርግማንና ቁጣንም ከነሱ የመራቅ አቅም ካገኘሁ ምንም አልሸከምም። ስለ ሌላ ሀይማኖት ንገረኝ?" እርሱም መልሶ "ከሐኒፍ በቀር ሌላ ሃይማኖት አላውቅም" ዛይድም " #ሐኒፍ #ምንድን ነው?" ሲል ጠየቀው እርሱም መልሶ "#ሐኒፍ #የአብርሃም (የነቢዩ) #ሀይማኖት #ነው እሱም ሁለቱም ያልሆኑ አይሁዳዊም ክርስቲያንም አላህን እንጂ ሌላን አይገዛም ነበር" ዘይድ ስለ ኢብራሂም (ሃይማኖት) ንግግራቸውን በሰማ ጊዜ ከዚያ ቦታ ወጣና በወጣም ጊዜ እጆቹን ወደ ላይ አውጥቶ እንዲህ አለ። አላህ ሆይ እኔ በአብርሃም ሀይማኖት ላይ መሆኔን ምስክር አደርግሃለሁ። አስማ ቢንት አቢ በክር እንደተረከው፡- የዚድ ቢን አምር ቢን ኑፈይልን በካዕባ ላይ በጀርባው ቆሞ እንዲህ ሲል አየሁ፡- "የቁረይሽ ሰዎች ሆይ! የትንንሽ ሴት ልጆችን ሕይወት ይጠብቅ ነበር፡ አንድ ሰው ሴት ልጁን ሊገድላት ከፈለገ “በአንተ ፈንታ አበላታለሁና አትግደላት” ይለው ነበር። ስለዚህ ይወስዳት ነበር፣ እሷም በመልካም ስታድግ ለአባቷ “አሁን ከፈለግሽ እሰጥሀለሁ፣ ከፈለግሽ ደግሞ እኔ በአንተ ስም እመግባታለሁ” ይለዋል።

የኡማውን አንድነት የሚከፋፍል ሰው #ይገደል!!! ።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።።። 📝 በወንድም @Akel1941 ክፍል -⓶ #ሐነፊይ ምን አይነት መንገድ ነው? ወድ የዚህ ግሩፕ አባላት በሙሉ አል- ሀዲ የሆነውን አሏህ(ሱ.ወ) ቀጥተኛውን መንገድ ይምራን። የዚህ ርዕስ አላማው በእስልምና ውስጥ የተከፋፈሉ የሆኑት ቡድኖችን ጉዳይን በተመለከተ አላማቸው፣ አመጣጣቸውና አመሠራረታቸው ምን እንደሚመስል በተከታታይ ክፍሎች የሚዳስስ ፕሮግራም ነው። ታድያም እንደሚታወቀው በአለማችን ላይ ብዙ ተከታይ ካሏቸው ሀይማኖቶች መካከል እስልምና ቁጥር አንድ ሀይማኖት ቢሆንም ይህ ቅዱስ ሐይማኖት ለ73 መንገድ እንደሚከፈልም ነብዩ(ሰዐወ) ተናግረዋል። ከዚህ አንጻር በአሁን ሰዓት ይህ የክፍፍል ክስተት በሰፊው ይስተዋላል። ከነዚህም ክፍፍል ግሩፖች መካከልም ሐነፊይ፣ ሰለፍይ፣ ሱንይ፣ አህለል ሀዲስ፣ ወህሃብይ፣ አህለል ሱና፣ ቁጡቢይ፣ መድኸሊይ፣ ሱሩሪይ፣ ጉርቢያተል አህለል ሀዲስ፣ ኢህዋንይ፣ ጃሚአተል አህለል ሀዲስ፣ ማሊኪይ፣ ሻፊእይ፣ ... በመባል ተከፋፍለዋል። እናም እነዚህ ግሩፖች ከየት መጡ? እንዴት ተመሠረቱ? በቁርዓንና በሶሒሕ ሐዲስ ውስጥ ይታወቃሉ ወይ? አሏህ(ሱ.ወ) እንዲህ ይላል፦ 30፡ 32 من الذين فرقوا دينهم وكانوا شيعا ۖ كل حزب بما لديهم فرحون << ከእነዚያ ሀይማኖታቸውን ከለያዩትና ክፍፍሎችም ከሆኑት (አትሁኑ)። ህዝብ ሁሉ እነሱ ዘንድ ባለው ነገር ተደሳቾች ናቸው።>> #ሐነፊይ ከዚህ በፊት በክፍል 1 በነበረው ትምህርታችን ላይ #የሰለፊይ (selefism) እምነት አመጣጥና አስተሳሰብ ምን ይመስል እንደነበር ለማየት ችለን ነበር። ቀጥሎም በዚህ ክፍል ሁለት ደግሞ በአላህ ፈቃድ #የሐነፊይ እምነት ጉዳይ ምን ይመስላል የሚለውን ትምህርት እንቃኛለን። - ሐነፊይ ማለት ምን ማለት ነው? ሐነፊይ ማለት ነብዩ ሙሐመድ(ሰ.ዐ.ወ) ከመምጣታቸው በፊት(በጃሂሊያ ዘመን) የአብረሐም ሐይማኖት ነው በማለት ያምኑና ይከተሉት የነበረ እምነት ነው። እንደ Wikipedia አገላለፅ መሠረት ሐኒፋ ማለት a "hanif" ( حنيف), remonized ; Plural : " hanifa" ( حنيفاء ) meaning : #renunciate. ታድያ " remonized" የሚለው ቃል " እንደገና መስተካከል(ማስተካከል) " የሚል የአማርኛ ትርጉም ሲኖረው " #renunciate " የሚለው ደግሞ" መክዳት " የሚል ትርጉም ይይዛል። በበዚህም Wikipedia ላይ - #renunciate is some one who maintaince the pure monotheism of #patriarch Abraham. ይለዋል። እስቲ ይህንን ማብራሪያ ቃል በቃል እንተርጉመው - monotheism ; is the belif that there is only one deity, an all- supreme being. that is universally referred to as God. በማለት ሲጠቅሰው ከዚህም በማስከተልም በነዚህ የmonotheism አራማጆች መካከል ልዩነት ተፈጠረና በሁለት ተከፈሉ። እነርሱም አንድ አምላክ የማምለክና ከአንድ በላይ አምላክ የማመን እሳቤ ነው ብሎ ይጠቅሳቸዋል።