1 146
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
1 146
+4
ጥቅምት 15 ቀን 2017 ዓ.ም
የ2017 ዓ.ም የትምሀርት ዘመን አዲስ ገቢ ሰልጣኞችን አስመልክቶ ለሚዲያ አካላት መግለጫ ተሰጠ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ ኮሌጅ በዛሬዉ ዕለት ከቴሌቪዥን ፣ ሬዲዮ ፣ ማህበራዊ ሚደያዎች እና የህትመት ሚዲያዎች ለመጡ ጋዜጠኞች በ2017 የት/ት ዘመን በኮሌጁ የሚሰጡ የስልጠና መስኮችን አስተዋወቋል። የመግቢያ ነጥብ ፣ ለመመዝገብ ምን ያስፈልጋል ፣ በኮሌጁ መሰልጠን የሚችለዉ ማነዉ፣ የምዝገባ ጊዜ እና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ማብራሪያ ተሰጥቷል።
በተጨማሪም ይህን ታሪካዊ ኮሌጅ የሚዲያ አካላት እንዲያዉቁት መረጃ የተላለፈ ሲሆን ኮሌጁን ምን ለየት ያደርገዋል ፣ የስልጠና አሰጣጥ ፣ ቴክኖሎጅ ፣ ምርምር እና ስራ ፈጠራ፣ የሚከናወኑ ሁነቶች፣ ፋሲሊቲ ፣ ማህበራዊ ሃላፊነት ፣ የ100ኛ ዓመት ክብረበዓል ዝግጅት ፣ ስለ ኮሌጁ የሚዲያ አካላት መረጃ የሚያገኙባቸዉን አማራጮች (ዌብ ሳይት እና የማህበራዊ ድህረ ገጾች ) እንዲተዋወቁ ተደርጓል።
በመግለጫዉም በ2017 የበጀት ዓመት ኮሌጁ ከ2000 በላይ ሰልጣኞችን ተቀብሎ ለማሰልጠን ዝግጁ መሆኑ ተገልጿል። የመግቢያ መስፈርቱን የሚያሟሉ 12ኛ ክፍል የጨረሱ ተማሪዎችን ከደረጃ 1- 5 በ11 የስልጠና ዘርፎች ከ40በላይ የስልጠና መስኮች ከዛሬ ጀምሮ በመመዝገብ መሰልጠን እንደሚችሉ ተገልጿል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+7
ዕለተ ረቡዕ ጥቅምት 13/2017ዓ.ም
የሙያ ስልጠና አማሪጮችን የማስተዋወቅ ፕሮግራም ተጀመረ።
ሠልጣኞች የወደፊት የስራ መስካቸውን በመረጃ ላይ ተመስርተው እንዲወስኑ ለመርዳት ያለመ የሙያ ስልጠናን አማራጮች የማስተዋወቅ ፕሮግራም መጀመሩንና ከጥቅምት 13 -15/2017ዓ.ም እንደሚዘልቅ የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች አሳውቋል።
በዚህ የሙያ ስልጠናዎችን የማስተዋወቅ ፕሮግራም የስልጠና ዘርፎች ምንነት እና በስራ ገበያው ያላቸው ተፈላጊነት እንደዚሁም የስልጠና ዘርፎቹ ሠልጣኞችን ብቁ አድርገው ለማውጣት ያላቸውን ዝግጅት ለተመዝጋቢዎች ሲያብራሩ ተስተውሏል።
የማስተዋወቅ ፕሮግራሙን ያስጀመሩት የክብር እንግዳ አበራ ብሩ (ዶ/ር ) በቢሮ ኃላፊ ማዕረግ የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ስልጠናና ተቋማት አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ሲሆኑ በማስጀመሪያ ንግግራቸው አንጋፋው ተቋም በዚህ መልክ ሰልጣኞችን ለመቀበል ያደረገውን ዝግጅት አድንቀው አሠልጣኞችንም ምስጋና ችረዋቸዋል።
ስልጠናው ላይ ለመሳተፍ የ2ኛ ደረጃ ትምህርትን/ 12ኛን ክፍል ያጠናቀቁና ለምዝገባ የሚያበቃቸውን የመቁረጫ ነጥብ ያሟሉ መሆን እንደሚጠበቅባቸው ለማወቅ ተችሏል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የ2017 የቴክኒክና ሙያ የመደበኛ ስልጠና ዘመን መቁረጫ ነጥብ ይፋ ሆኗል።
የተፈጥሮ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት !
🟢 የስልጠና ደረጃ 1 እና 2
° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 141 እና ከዚያ በታች፤
° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 137 እና ከዚያ በታች፤
° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 138 እና ከዚያ በታች፤
° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 134 እና ከዚያ በታች፤
° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤
🟡 የስልጠና ደረጀ 3 እና 4 ፦
° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 142 እና ከዚያ በላይ፤
° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 138 እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 እና እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና ከዚያ በላይ፤
° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤
🔴 የስልጠና ደረጀ 5 ፦
° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 179 እና ከዚያ በላይ፤
° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 167 እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 170 እና እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 162 እና ከዚያ በላይ፤
° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 154 እና ከዚያ በላይ፤
⬇️
የማህበራዊ ሳይንስ የመግቢያ ውጤት !
🟢 የስልጠና ደረጃ 1 እና 2
° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 139 ከዚያ በታች፤
° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና ከዚያ በታች፤
° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 134 እና ከዚያ በታች፤
° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤
° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 124 እና ከዚያ በታች፤
🟡 የስልጠና ደረጀ 3 እና 4 ፦
° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 140 ከዚያ በላይ፤
° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 136 እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 135 እና እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤
° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 125 እና ከዚያ በላይ፤
🔴 የስልጠና ደረጀ 5 ፦
° ወንዶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 172 ከዚያ በላይ፤
° ወንዶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 164 እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢን #ሳይጨምር የመቁረጫ ነጥቡ 165 እና እና ከዚያ በላይ፤
° ሴቶች ከታዳጊ ክልሎች እና አርብቶ አደር አካባቢዎች የመቁረጫ ነጥቡ 160 እና ከዚያ በላይ፤
° ለሁሉም የአካል ጉዳተኞ የመቁረጫ ነጥቡ 154 እና ከዚያ በላይ፤
1 146
ጥቅምት 8/2017ዓ.ም
የአመራር ጥበብ ስልጠና ተሰጠ።
ለኮሌጁ ማኔጅመንት፣ አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት፣ ለስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች እና ኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ባለሙያዎች በኰሌጁ ቅጥር ግቢ ዉስጥ ለግማሽ ቀን የቆየ የአመራር ጥበብ ስልጠና ተሰጠ።
የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ይህ ሥልጠና በየደረጃው ያሉትን የአመራር አባላት አቅም የመገንባት ሂደት አካል መሆኑን በማስታወስ ሠልጣኞች ንቁ ተሳታፊ በመሆን. የሚያገኙትን ዕዉቀትና ክህሎት በየሥራ ክፍላቸው ለሚጠበቀው ውጤት አስተዋፅኦ እንደሚኖረው እንደሚያደርጉ እምነታቸው ፅኑ መሆኑንም ጨምረዉ ገልፀዋል።
ስልጠናውን የሰጡት ዶ/ር አሸናፊ አበበ በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የLeader ship and management መምህር ሲሆኑ በመጀመሪያ እንኳን ለ100ኛ ዓመት ክብረ በዓል አደረሳችሁ በማለት መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል። በመቀጠል አመራር ጥበብ ነው የሚሉት አሠልጣኝ ፤በየደረጃው ያለው የአሁኑ የኮሌጅ አመራር እንዴት እየመራው ነው? እሚል ጥያቄ ሰንዝረው ት/ቤቱ እና/ወይም ኰሌጁ በ100 ዓመታት ጉዞው በርካታ አመራሮች እንደተፈራረቁበት አውስተው በዛው ልክ በርካታ አንቱታን ያተረፉ ዘወትር የሚዘከሩ የሃገር ባለውለታዎች ያፈራ መሆኑን በመጠቆም ለፈር ቀዳጆቻችን ምስጋና ይገባቸዋል በማለት ምስጋናቸውን አልነፈጉም።
በዋነኛነት የአመራር ጥበብ ሳይንስ ነው ። የአመራር ጥበብ ማለት ባለሙያዉ (መሪው) በሌሎች ሰዎች (ተመሪዎች) ላይ አወንታዊ ተፅዕኖ በማሳደር እና በማነቃቃት የድርጅታቸውን ወይም የሚሰሩበት መ/ቤት ስኬታማ እንዲሆን አስተዋፅኦ እንዲያደርጉ ማስቻል ነው ይላለሉ። ለጥቀውም አመራር የሰው ሃይልና ሃብትን አስተባብሮ ተቋሙ የተሻለ እንዲሆን መስራት ነው በማለት ሰፊ ማብራሪያ አክለዋል።
- ሰራተኞች በተገቢው መንገድ ስራቸውን የማይሰሩት ለምንድ ነው ? የሚል ጥያቄ ያነሱና ምክንያት ይሆናሉ ያሉዋቸዉን እንደሚከተለው ይዘረዝራሉ።
- ምን መሰራት እንዳለበት
- እንዴት መስራት እንዳለበት እና
- ለምን እንደሚሰራ ስለማያውቁ
- ተሳታፊ እንዲሆኑ ስለማናስችላቸው
- ምቹ የስራ አካባቢ ካለመኖሩ
- በጥንካሬው ላይ በደንብ ስለማንሰራ
- አለቃውን ካለማመን
- በአደባባይ ማመስገን እና ለብቻ
መውቀስን ስለማናመቻች
- ሃላፊነትን አለመውሰድ ከብዙ በጥቂቱ
መሆናቸዉንም አብራርተዋል ።
አመራሩ ይህን የሚመልስ ምላሽ ተገቢ በሆነ ልክ እና መልክ መስጠት እንዳለበትም አሳስበዋል ።
በተጨማሪም ሰው የሦስት ነገሮች Body,sool, and spritual ጥምር ውጤት ነው በማለት ትንታኔ ሰጥተዋል።
ከኰሌጁ ነባራዊ ሁኔታ ጋር በማያያዝ የተሰጠው
ሥልጠና መሳጭ ሳቢ እና ራስን በራስ ፈትሾ የማስተካከያ እርምጃ ለመዉሰድ የሚረዳ መሆኑን ግንዛቤ መዉሰድ ይቻላል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ሰኞ ጥቅምት 4/2016ዓ.ም
በእ/ፓ/ቴ/ኮሌጅ የምህራን እና ሠራተኞች
አጠቃላይ ስብሰባ ተካሄደ።
የኮሌጁ መምህራንና ሠራተኞች አጠቃላይ ስብሰባ አድርገዋል ። የዚህ ስብሰባ ዋና ዓላማ የመጀመሪያ ሩብ ዓመት ዕቅድ ክንውን ለመገምገምና ቀጣይ አቅጣጫ ለማስቀመጥ ሲሆን በተያያዘ በቀደሙት ግዚያት በተካሄዱት ግምገማዊ ስልጠና የተለዩ ችግሮችን እና የተቀመጡ የመፍትሄ ሃሳቦችን በማብራራት የዕቅድ ክንውን ግምገማውን ለማጎልበትና የመፍትሄ አቅጣጫውን ለማዳበር መሆኑን ግንዛቤ ለመውሰድ ተችሏል።
የዕቅድ ክንውኑን ግምገማ በኮሌጁ ዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ወ/ሪት ፀዳለ አድማሱ በቀረበ ሪፖርት ተጀምሯል። ከዚሁ ጋር በተያያዘ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ በ15ቱም ኮሌጆች የተጠናው ጥናት ግኝቶች እና በኮሌጁ የጥናትና ምርምር ክፍል በተጠናው ጥናት የተገኙ ግኝቶችን በኮሌጁ የስነ-ምግባር ዳይሬክቶሬት ተጠሪ ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው ቀርቧል። በዚህ የጥናት ግኝት በክፍተት መልክ የታዩት በዝርዝር የቀረበ ሲሆን ክፍተቱን ለመሙላት የሚያስችሉ ሃሳቦችም ተካተውበታል።
በክፍተት ወይም በውሱንነት ከተገለጹት ስራዎችና የስራ ክፍሎች ጋር ተያይዞ የሚከተሉት ዋና ዋና ተግባራት ተቀምጠዋል።
- በግዢ አፈጻጸም የመንግስት ህግ፣ደንብና
መመሪያን አለማክበርና አለመጠቀም ፣
- የሰው ሃብትን በአግባቡ ካለመጠቀም ጋር
በተያያዘ የታዩ ጉድለቶች ፣
- በሙያ ስልጠና የምስክር ወረቀት አሰጣጥ ላይ
የታየ ዳተኝነት ፣
- ከመንግስት ንብረት አያያዝና አጠቃቀም ጉድለት
የሚፈጠር ብክነትና ብልሹነት፣
- የኦዲት ስራዎች አግባብነት ባለው መልኩ
አለማካሄድና ግኝቶችንም በግብአትነት
አለመጠቀም፣
- የፕሮጀክት ፈንድአጠቃቀም አግባብነት የተሳነው መሆን የሚሉ ሲሆን ውስንነቶቹ በከተማ ደረጃ ያሉ ኮሌጆች ውስጥ የታዩ ቢሆንም ኮሌጃችን በአንድ ወይም በሌላ መልክ ውስንነቶቹን የሚጋራ መሆኑ በጋራ መግባባት ላይ ተደርሷል። በተጨማሪም የኮሌጃችን ተገልጋዮችም ሆኑ ሌሎች ባለድርሻ አካላት ከአገልግሎት አሰጣጥ ጋር ተያይዞ ቅሬታ የሚሰማባቸው መሆኑ ወይም በአገልግሎታችን አለመርካታቸውን የሚያሳዩ ምልክቶች መኖራቸውን በውይይቱ ተነስቷል።
በዕቅድ ክንውን ውይይቱ በሩብ ዓመቱ መጀመሪያ ወራት በተደረጉ ግምገማዊ ስልጠና የታዩ ችግሮች እና የመፍትሄ ሃሳብ ተብለው የተቀመጡ መካተታቸው የታወቀ ሲሆን ውስንነቶችን ለመቅረፍ የሚያስችል ዕቅድ በቅደም ተከተላቸው በመካከለኛና በአጭር ግዜ የሚፈቱ በሚል ተቀምጦላቸዋል። በዚህ ውይይት ችግሮችን ለመፍታት በሚደረገው ርብርብ መልካም አጋጣሚዎችን መጠቀም የበለጠ ውጤት ለማስመዝገብ እንዲያስችል በአጽንኦት በማሳሰብ ኮሌጁ እያከናወናቸው ያሉትን የ100ኛ ዓመት በዓል እንቅስቃሴና የISO የምስክር ወረቀት የማግኘት ሂደትን የኮሌጁን ገጽታ ለመገንባት ሁሉም ሠራተኛ ያላሰለሠ ጥረት እንዲያደርግ እና በከተማው እየተከናወነ ያለውን የኮሪደር ልማት ድርሻችንን በማበርከት ተጠቃሚ ልንሆን የምንችልበትን ፈጠራ በማከል ስራችንን የምናከናውንበት ዕቅድ በየስራ ክፍላችን አዘጋጅተን ወደ ተግባር እንቀይር የሚል መልእክት በኮሌጁ ዲን ለተሳታፊዎች ተላልፏል።
በአጠቃላይ በመንግስት ሰነድ አጠቃቀም ውሱንነት የተጠቀሱትን ተግባራት የመንግስት ህግ፣ ደንብና መመሪያ በማክበር እንዲፈቱ ማድረግ ፤ ከሠራተኛው ቁርጠኝነትና ተነሳሽነት ጋር የተያያዙት ደግሞ ሠራተኛው ከውይይቱ ግንዛቤ በመውሰድ እንዲያስተካክል ፤ ከግብዓት እጥረት ጋር ያለውን እና ሌሎች የተነሱ ችግሮችን የሚመለከታቸው ክፍሎች በተቀመጠው አግባብ አፋጣኝ ማስተካከያ እንዲያደርጉና የኮሌጁ ማኔጅመንትም በቅርበት በመከታተል ድጋፍ እንዲሰጥ በሚል የጋራ መግባባት ተደርሶ የዕለቱ ውይይት ተጠናቋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+5
ዕለተ ሰኞ ጥቅምት 4/2017ዓ.ም
ሰነድ የመመለስና ናሙና የማስረከብ
ፕሮግራም ተከናወነ ።
በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለ2017 በጀት ዓመት ግብኣት አቅርቦትን ለማሟላት ያስችል ዘንድ በግልጽ ጨረታ ግዢ ለማከናወን መስከረም 19/2017ዓ.ም በወጣው አዲስ ዘመን ጋዜጣ በ17ሎት የተከፋፈለ ፍላጎት የወጣ ሲሆን ናሙና ማቅረብ የሚፈለግባቸውን አቅርቦቶች ናሙና የማቅረብ እና አያይዞም የጨረታ ሳጥኑን የማሸግ ስራው በዛሬው ዕለት ጥቅምት 4/2017ዓ.ም ከጥዋቱ 4:30 ተጠናቆ ከ30 ደቂቃዎች በኋላ ከጥዋቱ 5:00 ሰዓት ላይ አምስቱ የጨረታ ቡድን አባላት፣ የግዢ ዳይሬክቶሬት ተጠሪና ባለሙያዎች ፣ የኮሌጁ የውስጥ ኦዲት ተጠሪና ባለሙያዎች እንዲሁም የጨረታው ተሳታፊ አቅራቢዎች በተገኙበት ከጠዋቱ 5:00 ሰዓት ላይ ተከፍቷል። በመክፈቻው ላይ የተገኙት የግዢ ዳይሬክቶሬት ተጠሪ አቶ ከበደ ሳጥኑን በመክፈት ሂደት በቅደም ተከተል የሚከናወኑ ተግባራትን ሲያብራሩ በመጀመሪያ በቅደም ተከተል በየዘርፉ የተወዳደሩትን መለየት በመቀጠልም ኮፒና ኦሪጅናል ሰነዶችን መለየት አስከትሎም ቴክኒካል መታየት ያለባቸውን በቅደም ተከተል አቅራቢዎቹ ባሉበት እንደሚያዩ የአሰራር ቅደም ተከተል አስቀምጠው ሳጥኑን በመክፈት ወደ ስራ ተገብቷል / ስራው ተጀምሯል።
በአጠቃላይ የጨረታ ስራው የተሳለጠ እንዲሆን እና በተቀመጠለት መርሃ ግብር እንዲጠናቀቅ በኮሚቴው የሚጠየቁ ግብአቶች በወቅቱ እንዲቀርቡ የሚመለከተው አካል በትኩረት እንዲከታተለው እና እንዲያበረታታቸው እየጠየቅን መልካም የስራ ግዜን እንመኛለን ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+3
ዕለተ ሰኞ ጥቅምት 4/2017 ዓ.ም
በእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰንደቅ
ዓላማ ቀን ተከበረ።
ወርሃ ጥቅምት የመጀመርያው ሰኞ ብሄራዊ የሰንደቅ ዓላማ ቀን ሆኖ እንዲከበር የኢፌድሪ ሪፐብሊክ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት በአዋጅ ቁጥር 654/2001 ባፀደቀውና ማሻሻያ በተደረገው መሠረት የሚከበር መሆኑ ይታወቃል።
በዓሉ የሚከበርበት ዋና ዓላማ ሉዓላዊነታችንን በማስከበር ሃገራዊ አንድነታችንንለማጠናከር ታሳቢ ያደረገ ነው ።
በመሆኑም ለ17ኛ ግዜ በሚከበረው የሰንደቅ ዓላማ ቀን የእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኞች የኢትዮጵያ ህዝብ መዝሙርን በመዘመር እና ሰንደቅ ዓላማችንን በማውለብለብ በዓሉን አክብረውታል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
