fa
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

کانال بسته
1 145
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
photo content

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 16/2016ዓ.ም በምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ ተካሄደ። የልምድ ልውውጡን ያካሄደው የኮሌጁ ሠራተኞች ማህበር አባላት ሲሆኑ ዋና ዓላማው የከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው
+1
ዕለተ ሰኞ መጋቢት  16/2016ዓ.ም       በምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ                     ልውውጥ ተካሄደ። የልምድ ልውውጡን ያካሄደው የኮሌጁ ሠራተኞች ማህበር አባላት ሲሆኑ ዋና ዓላማው የከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የኮሌጁን ማህበረሰብ በሌማት ትሩፍት ተጠቃሚ ለማድረግ የተለያዩ ስራዎችን መተግበር የተጀመረ ሲሆን ይህንን አጠናክሮ ለማስኬድ ቀደም ብለው ወደ ትግበራ ከገቡት ኮሌጆች ልምድ ለመጋራት የምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሰራተኛ ማህበር አመሰራረትና አደረጃጀት፣ ማህሩ ወደ ስራ የገባበት መንገድና ያጋጠማቸው ተግዳሮትና የፈቱበትን አግባብ በማጤን በኮሌጃችን ወደ ስራ እየገባ ያለው የሰራተኞች ማህበር የሚያገኘውን  ተሞክሮ  እና አልሞ የተነሳውን ዓላማ  በማዋደድ ወደ ስራ እንደሚገባ ለማወቅ ተችሏል።  ማህበሩ ምን ምን ተግባራትን እያከናወነ እንዳለ የማህበሩ አባላት በዝርዝር ማብራሪያ ሰጥተወበታል ለተደረገልን. ማብራሪያም ምስጋናችን የላቀ ነው ።                                 ኮምንኬሽን ክፍል

ዕለተ ዓርብ መጋቢት 13/2016 ዓ.ም በኮሌጁ የተቋቋመው የISO ትግበራ ቡድን አባላት ውይይት አካሄዱ። የዉይይቱ ዋና ዓላማ "ISO 21001:2018 Educational quality managemen
+2
ዕለተ ዓርብ መጋቢት 13/2016 ዓ.ም በኮሌጁ የተቋቋመው የISO ትግበራ ቡድን አባላት ውይይት አካሄዱ። የዉይይቱ ዋና ዓላማ "ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና ለማግኘትና ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል ትግበራ መጀመሩ ይታወሳል። በመሆኑም ይህ መርሃ ግብር በተያዘለት አቅጣጫ እውን እንዲሆን የኮሌጁ ማህበረሰብ በቁርጠኝነት እና በእኔነት ስሜት መሳተፍና መተግበር  እንዲያስችለው ፕሮግራሙን እና የአፈጻጸም አቅጣጫውን የጋራ ለማድረግ የሚያስችል አቅምን ለመፍጠር ለኮሌጁ ማህበረሰብ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና መስጠት አስፈላጊ ሆኗል። በመሆኑም ስልጠናውን ለመስጠትና ስልጠናውን በምን መልኩ ብናስኬድ ውጤታማ መሆን ይችላል? በሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች ላይ ውይይት ተካሂዷል።                                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

ዕለተ ዓርብ መጋቢት 13/2016 ዓ.ም የፅዳት ዘመቻ ንቅናቄ መርሀ-ግብር ተካሄደ ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በጉለሌ ክ/ከተማ የወረዳ ሁለት ፅዳት አስተዳደር ጽ/ቤት ጋር በመተባበር "ፅዱና ውብ ት/ቤት ለተማሪዎችና ለአስተዳደር ሰራተኞች" በሚል መሪ ቃል የኮሌጁን ማህበረሰብና ሰልጣኞኝን ባሳተፈ መልኩ የፅዳት ዘመቻ የንቅናቄ መርሀ-ግብር ተካሄደ። በመርሀ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክቻቸውን አስተላልፈው የመማሪያና የመስርያ ቦታችንን ምቹና ማራኪ በማድረግ ቆሻሻን የሚጠየፍ ትውልድ ማፍራት እንደሚገባና ይህን ተግባር ለመከወን ከኮሌጁ ማህበረሰብ ባሻገር የሰልጣኞች ሚና የጎላ መሆኑን ገልፀዋል። አክለውም ወር በገባ የመጀመርያው ዓርብ ከሚካሄው የፅዳት ዘመቻ በተጨማሪ የዕለት ተዕለት ተግባራችን ልናደርገው እንደሚገባ አመላክተዋል። በተያያዘም የጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ ሁለት ፅዳት አስተዳደር ጸ/ቤት ሀላፊ ወ/ሮ ሽታ ሀይሉ ቆሻሻን በአግባቡ ከያዝነው ሀብት እንደሆነና ቆሻሻ ከምንጩ እንዲቀንስ አካባቢያችንን አፅድተን በማሳየት መልካም ምሳሌ መሆን እንደሚገባን አመላክተዋል። አክለዉም በያለንበት ስፍራ የፅዳት አንባሳደር በመሆን አካባቢያችንን እናፅዳ በማለት የፅዳት ዘመቻውን በይፍ አሰጀምረዋል። በመጨረሻም የጉለሌ ክ/ከተማ የፅዳት አንባሳደር እማማ ፊሽካ የኮሌጁን ሶስት የፅዳት አንባሳደር በመምረጥ ከስልጠና ሰዓት ውጪ በትርፍ ሰዓታቸው ኮሌጁን እንዲያፀዱ ቃል በማስገባት የበኩላቸውን ተወጥተዋል። ከወረዳ ሁለት የመጡ እንግዶች እና የኮሌጁ ማህበረሰብ በተቀመጠለቸው አቅጣጫ መሠረት ወደ ስራው ተሰማርተው በማፅዳቶ ፕሮግራሙ ተጠናቋል።                                        ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረብዕ መጋቢት 12/2016ዓ.ም የሙከራ ትግበራ ያለ አቅምን አሟጦ በመቀም ማህበረሰብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ማከናወን መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት ያለ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም
+5
ዕለተ ረብዕ መጋቢት 12/2016ዓ.ም                የሙከራ ትግበራ ያለ አቅምን አሟጦ በመቀም ማህበረሰብን ተጠቃሚ የሚያደርጉ ተግባራትን ማከናወን መንግስት ትኩረት ሰጥቶ እየሰራበት ያለ መሆኑ ይታወቃል። በዚህም የከተማ አስተዳደሩ ባስቀመጠው አቅጣጫ መሰረት የኮሌጁን ማህበረሰብ የሌማት ትሩፍት ተጠቃሚ ለማድረግ ብሎም የኮሌጁን የውስጥ ገቢ ለማሳደግ በኮሌጁ የተለያዩ ስልጠና ዘርፎች የሚገኙ ማሽነሪዎችን እና አቅምን በማቀናጀት መስራት ችላ የማይባል ተግባር ነው ። በመሆኑም  ከነኝህ ሐብቶች መካከል አንዱ የሆነው በሆቴልና ቱሪዝም ስልጠና ዘርፍ ለረጅም ዓመታት ያለስራ የተቀመጡ የዳቦ መጋገርያ ማሽኖችን አስጠግኖ ወደስራ ማስገባት የሚያስችል እንቅስቃሴ ተጀምሯል። ለዚህም የመጀመሪያ ዙር የሙከራ ትግበራ ተካሂዷል። የተካሄደውን የሙከራ ትግበራ በቀጣይ ዕውን በማድረግ በተመጣጣኝ ዋጋ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ዳቦ ከማቅረብ ባሻገር በሂደት የአካባቢውን ማህበረሰብ ተጠቃሚ የማድረግ ስራ እንደሚሰራ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ገልፀዋል።                                      ኮሙኒኬሽን ቡድን

ማሳሰቢያ: የ plumbing ሙያ በ13/7/2016 ምዘና በምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተይዞ የነበረው በምዘና ጣቢያ ችግር ምክንያት የተሰረዘ መሆኑን እናሳውቃለን።

photo content
+3

ዕለተ ረብዕ መጋቢት 11/2016 ዓ.ም በመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን በኮሌጁ የነበረውን የኦዲት ስራ የመውጫ ውይይት ተካሄደ። በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የመንግስት ንብረት አስተዳደር ባለስልጣን ከንብረት ኦዲትና ኢኒስፔክሽን ዳሬክቶሬት በመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች የኮሌጁ የ2013 ዓ.ም በጀት ዓመት ኦዲት ስራ ከተጀመረ ወራቶችን የወሰደ መሆኑን ይታወቃል ።  ምንም እንኳን የወሰደው ጊዜ ረዘም ያለ ቢሆንም በያዝነው ሳምንት ተጠናቆ አጠቃላይ ስራውን አስመልክቶና በግኝቶቹ ላይ የመውጫ ውይይት ተካሄዷል ። የውይይቱ ዋና ዓላማ የ2013 በጀት ዓመት በጥቆማ ኦዲት ግኝቶች ላይ መወያየት፣ በኦዲት ወቅት ያልቀረቡ ነገር ግን ሊቀርቡ የሚችሉ ሰነዶች መረጃዎች ካሉ እንዲቀርቡ ማድረግና ለሀላፊዎች በተገኘው የኦዲት ግኝት ላይ ግንዛቤ በመፍጠር እርምጃ እንዲወስዱ ማድረግ ላይ ያለመ ነው። ከዚህ ጋር በተያያዘ ከተቋሙ የመጡ ከፍተኛ ባለሙያዎች ባደረጉት ምልከታ ከአሰራር ስርዓት ጋር ተያይዞ የታዩ ክፍተቶች እንዲታረሙና በቀጣይ ይህንን ለማረጋገጥ የናሙና ኦዲት እንደሚካሄድ አመላክተዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የተሰጡትን ገንቢ አስተያየቶች በመቀበል መከወን ያለባቸውን ማሻሻያዎች ተግባራዊ ማድረግ እንዲሁም ከቀረበው ሪፖርት አንፃር የስራ ክፍሉ ሰራተኞች መረጃዎችን በማደራጀት ምላሽ መስጠት እንደሚገባቸው አሳስበዋል።                                                                                                        ኮምንኬሽን ክፍ

ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ በመጡ ባለሙያዎች ሱፐርቪዥን ተካሄደ። በ2016 ዓ.ም የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም ምዘና ከአዲስ አበባ ከ
+6
ዕለተ ማክሰኞ መጋቢት 10/2016 ዓ.ም ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ በመጡ ባለሙያዎች ሱፐርቪዥን ተካሄደ። በ2016 ዓ.ም የስድስት ወር የስራ አፈፃፀም ምዘና ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ስራና ክህሎት ቢሮ በመጡ ባለሙያዎች የተካሄደ ሲሆን በምዘናው ወቅት የሁለተኛ ሩብ ዓመት የኮሌጁ ማጠቃለያ ሪፖርት፣ ወቅቱንና ጥራቱን የጠበቀ የዕቅድ ሰነድ ስለመዘጋጀት እና የወርክሾፖች አደረጃጀት ምን እንደሚመስል ምልከታ አድርገዋል። በምልከታ ወቅት የታዩ ደካማና ጠንካራ ጎኖች በባለሙያዎቹ የተነሱ ሲሆን ቆይታቸው መልካም እንደነበር፤ የመረጃ አያያዝና የወርክሾፖች አደረጃጀት የላቀ ደረጃ ላይ እንደሆነና ለሌሎች ኮሌጆች አርአያ እንደሚሆን ገልፀው ክፍተት የተስተዋለባቸውን አንዳንድ ተግባራት እንዲሁም ምድረግቢውን ማስዋብ ላይ የተጀመሩ ስራዎች ከግብ ማድረስ እንደሚገባ አመላክተዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ አመራሮች የተሰጧቸው ገንቢ አስተያየቶች እንደ ግብዓት በመጠቀም ክፍተት የተስተዋለባቸውን ተግባራት ለማስተካከል ቃል ገብተዋል።                                         ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒ ኮሌጅ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቋሚ የጽዳት ዘመቻ ቀን መጀመሩ ይታወሳል። ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠል ኮሌጃችንን
+4
ዕለተ ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒ ኮሌጅ የፅዳት ዘመቻ ተካሄደ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቋሚ የጽዳት ዘመቻ ቀን መጀመሩ ይታወሳል። ይህንን አጠናክሮ በማስቀጠል ኮሌጃችንን ውብና ማራኪ እንዲሁም ምቹ የስራ አካባቢን መፍጠር የሁሉም የኮሌጁ ማህበረሰብ ተሳትፎን የሚጠይቅ በመሆኑ በዛሬው ዕለት ለ4ኛ ግዜ የፅዳት ዘመቻ ተካሂዷል። ይህ የፅዳት ዘመቻ ወር በገባ የመጀመርያው ሳምንት ዓርብ የሚካሄድ ሲሆን በዛሬው ዕለት የተካሄደው የፅዳት ዘመቻ  የስልጠና ዘርፎች በስራቸው ያሉትን አሰልጣኞች እና ሰልጣኞችን በማስተባበር እንዲሁም ዳይሬክቶሬቶች በክፍላቸው ካሉ ሰራተኞች ጋር በመሆን በተመደቡበት የፅዳት ስፍራ ላይ በመገኘት ሀላፊነታቸውን ተወጥተዋል።          "ምቹ የስራ አካባቢን በጋራ እንፍጠር"                                  ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም ለሠልጣኞች የስነ-ምግባር ስልጠና ተሰጠ። ከየስልጠና ዘርፍ ለተወጣጡ ሰልጣኞች በስነ-ምግባር ዳሬክቶሬት ለሦስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በዛሬው ዕለት የተጠ
+3
ዕለተ ዓርብ መጋቢት 6/2016 ዓ.ም      ለሠልጣኞች የስነ-ምግባር ስልጠና ተሰጠ። ከየስልጠና ዘርፍ ለተወጣጡ ሰልጣኞች በስነ-ምግባር ዳሬክቶሬት ለሦስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው  ስልጠና በዛሬው ዕለት የተጠናቀቀ ሲሆን የስልጠናው ዓላማ ሠልጣኞች የተሻለ ስነ-ምግባር እንዲያዳብሩ፣ የኮሌጁን ህግና ደንብ በማክበር መብትና ግዴታቸውን እንዲወጡና ስልጠናቸውን በአግባብ እንዲከታተሉ ማስቻል ሲሆን ፤በተያያዘም የስነ-ምግባርና ፀረ -ሙስና ክበብ ማቋቋም ላይ ያለመ ነው ስልጠናውን የሰጡት የሥነ-ምግባር ዳሬክቶሬት ወ/ሮ ዝግጁ ግዛቸው እና የሥነ-ምግባር ባለሙያ አቶ መከታው ሹመት ሲሆኑ ስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች፦ - ስነ-ምግባር ማለት ምን ማለት ነው? - የስነ-ምግባር መርሆዎች፣ - መልካም ባህርያት በህይወታችን እንዲጎለብቱ ምን ማድረግ አለብን ? - የሰልጣኞች መብትና ግዴታ ምን ይመስላል? -የሰልጣኞች የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ክበብ   ማቋቋም አስፈላጊነት - የስነ-ምግባርና ፀረ-ሙስና ክበብ አባላት አደረጃጀት፣   ተግባርና ሀላፊነት የሚሉ ርዕሰ ጉዳዮች በዝርዝር   ተዳሰዋል። ስልጠናው ሁለትዮሽ የአሰለጣጠን ስርዓትን የተከተለ ከመሆኑም ባሻገር ሰልጣኞች ልምዳቸውንና ሃሳባቸውን የሚያንሸራሽሩበት በቡድን የተከፋፈሉ የመወያያ ርዕሶች ላይ ውይይት በማካሄድ፣ በኮሌጅ ውስጥ የሚስተዋሉ ችግርችን በማንሳትና የመፍትሄ ሀሳቦችን ያመላከቱበትም ነበር ። በተያያዘም የክበብ አወቃቀር እና በቀጣይ የሚከናወኑ ተግባራትን አስመልክቶ አቅጣጫ በማስቀመጥ ስልጠናው ተጠናቋል ።                                                              ኮሙኒኬሽን ክፍል

photo content
+2

ዕለተ ዓርብ መጋበት 6/2016 ዓ.ም   የስነ ጥበብ ሰልጣኞች  በኮሚክ የስዕል ስራ   ውድድር  ላይ እንዲሳተፉ ገለጻ ተደረገላቸው ። ፍራንስ ካፍክ የጀርመን ሀገር ደራሲ ሲሆን የተወለደው በጀርመን ፕራግ ውስጥ ነው። በስዕል ስራዎቹና ድርሰቱ የተለየ የአፃፃፍ ስልት የሚጠቀም እና በጀርመን ትምህርት ስርዓት ውስጥ የሚያልፍ ተማሪ ሁሉ የካፍክን ስራዎች ጠንቅቆ እንዲያውቅ የተደረገለት አንጋፋ ሰዓሊና ደራሲ ነው ። ከዚህ ጋር በተያያዘ በያዝነው በፈረንጆቹ ዓመት 2024 የካፍክ ዓመት እየተከበረ በመሆኑ ይህንን ምክንያት በማድረግ የጀርመን ባህል ማዕከል የካፍክ ዓመት መክፈቻ ፕሮግራሙ  ላይ 18 የሚጠጉ የካፍክ መጽሐፍትን በአማርኛ በማስተርጎም አስመርቋል። እንዲሁም ኦስትርያዊ ሰዓሊ ኒኮላስ ማነር በካፍክ የህይወት ታሪክ ላይ የሰራቸውን ኮሚክ የስዕል ስራዎች ማርች 20 /2024 ላይ በፖስተር የሚያቀርብ ሲሆን ከዚህ ጋር በተያያዘ አንድ ወርክ ሾፕ ለኢትዮጵያ ሰዓሊያን በተለይም ለተማሪዎች ካፍክ የፃፍቸውን አጫጭር ታሪኮች ወደ ስዕል እንዲቀይሩ  ዕድል ተመቻችቷል። በመሆኑም የስነ ጥበብ ሰልጣኞችን ተሳታፊ ለማድረግ በጀርመን ባህል ማዕከል የቤተ-መጽሐፍትና የኢንፎርሜሽን ማዕከል ሀላፊ እንዲሁም የ2024 ካፍክ ዓመት ፕሮጀክት አስተባባሪ በአቶ ዮናስ ታረቀኝ አማካኝነት ማብራሪያ የተሰጠ ሲሆን የስነ ጥበብ ዘርፍ ሰልጣኞች እንዲሁም ከሌላ ስዕል ት/ቤት የተውጣጡ ተማሪዎች የስዕል ውድድሩ ላይ  እንደሚሳተፉ የተገለፀ ሲሆን በተቀመጠላቸው የካፍክ ታሪክ ላይ በመመስረት አንድ የኮሚክ ስራን በማቅረብ መወዳደር እንደሚችሉ ተገልጿል ። ለዚህም እንደመነሻ ይሆን ዘንድ አፍሪ ኮሚክስ የተሰኘ ከሁለት ዓመት በፊት የተጀመረ በአፍሪካ ኢትዮጵያን ጨምሮ 14 ሃገራት የተሳተፉበት ጋና በሚገኝ ጎተን ኢንስቲትዩት የሚመራው ፕሮጀክት ላይ የተሳተፉ ሰዓሊያን ቅኝ ግዛት ላይ ትኩረት ያደረገ በጀርመን ሀገር የታተመ ኮሚክ ስዕሎች የተካተቱበት መጻሕፍት እንዲሁም የፍራንክ ካፍክ ድርሰት ለቤተ-መጽሐፍ ተበርክቷል። መጻሕፍቱን በሚገባ በማንበብና የስዕል ስራዎችን በመመልከት የተቀመጠውን መስፈርት ያሟሉ ሰልጣኞች በተመረጡ የስዕል ስራዎች የእግዚቢሽኑ ተሳታፊ መሆን እንደሚችሉም ተጠቁሟል። የዝግጅት ክፍላችንም ለተወዳዳሪዎች መልካም እድልን እንመኛለን።                                   ኮሙኒኬሽን ቡድን

ዕለተ ረቡዕ መጋቢት 4/2016 ዓ.ም ለስራ ፈላጊ ወጣቶች ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክ/ከተማ 7 ወረዳዎች የተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶችከ3-5 ቀናት የሚቆይ ስልጠና በእንጦጦ ፖሊ
+2
ዕለተ ረቡዕ መጋቢት 4/2016 ዓ.ም ለስራ ፈላጊ ወጣቶች ስልጠና ማስጀመሪያ ኦረንቴሽን ተሰጠ። ከጉለሌ ክ/ከተማ 7 ወረዳዎች የተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶችከ3-5 ቀናት የሚቆይ  ስልጠና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በዛሬው ዕለት ተጀምሯል። ስልጠናው ወጣቶቹ ወደ ስራው አለም ለመቀላቀል እሚያስችላቸውን በቢዝነስ ስልጠና የሂሳብ መዝገብ፣ የደንበኛ አያያዝ እንዲሁም የተግባቦት አቅምን ለማሳደግ የሚያስችል ስልጠና በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና በሽሮ ሜዳ ካምፓስ ከ2100 በላይ ሰልጣኞችን ተቀብሎ በሶፍት እስኪል /ልል ክህሎት/ የሚያሠለጥን ሲሆን  በቀጣይ የሙያ ስልጠናው እንደየ ምርጫቸው እንደሚቀጥል ገልፀው በኮሌጁ ባላቸው ቆይታ የግቢውን ህግና ደንብ አክብረው መንቀሳቀስና በአግባቡ መሰልጠን እንዳለባቸው ያሳሰቡት በጉለሌ ክ/ከተማ ምክትል ስራ አስፈጻሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ኃለፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ አሳስበዋል አክለውም ሠልጣኞች በሚወስዱት ስልጠና የሙያ ክህሎታቸውን አዳብረው ወደ ስራ በመግባት እራሳቸውን ብሎም ሀገራቸውን የሚጠቅሙ እንደሚሆኑ ባለሙሉ ተስፋ መሆናቸውን ገልፀው መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል፡፡                                         ኮሙኒኬሽን ክፍል

ዕለተ ረብዕ መጋቢት 4/2016ዓ.ም የ IT የስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። በ IT የስልጠና ዘርፍ በ2015 ዓ.ም በአዲሱ ካሪክለም ሲያሰለጥናቸው የቆዩ በደረጃ ሁለት web developmen
+3
ዕለተ ረብዕ መጋቢት 4/2016ዓ.ም የ IT የስልጠና ዘርፍ የተቋም ምዘና አካሄደ። በ IT የስልጠና ዘርፍ  በ2015 ዓ.ም በአዲሱ ካሪክለም ሲያሰለጥናቸው የቆዩ በደረጃ ሁለት web development and data base administration (WDDBA) የሰለጠኑ 44 ሰልጣኞችን  እንዲሁም Hardware (HMS) በደረጃ ሁለትና በደረጃ አራት ያሰለጠናቸውን አስር ሰልጣኞች በአጠቃላይ 54 ሰልጣኞ ከአንድ ወር የትብብር ስልጠና ቆይታ መልስ የንድፈ ሃሳብ እና የተግባር ምዘና ያጣመረ ፓኬጅ ሲሆን ለሶስት ተከታታይ ቀናት ዘልቆ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል፤ በምዘናው ብቁ የሆኑት ወደሚቀጥለው ደረጃ የሚሸጋገሩ ሲሆን በምዘናው ውጤታማ ያልሆኑ ሠልጣኞችን የማብቃትና እንደገና የመመዘን ስራ እንደሚሰራም የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዋ ወ/ሮ መሰረት ተሾመ ገልፀዋል።                                                             ኮሙኒኬሽን ክፍል

ዕለተ ሰኞ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም ከተለያዩ የስራ ክፍሎች የተወጣጡ የISO ፎካል ፐርሰን አባላት ውይይት አካሄዱ። እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በ"ISO 21001:2
+2
ዕለተ ሰኞ መጋቢት 2/2016 ዓ.ም ከተለያዩ የስራ ክፍሎች የተወጣጡ የISO ፎካል ፐርሰን አባላት ውይይት አካሄዱ። እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል ስምምነት በመፈፀሙ ይህንን እውን ለማድረግ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ ተወካዮች በኢትዬጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዮት አማካኝነት ስልጠና መሰጠቱ ይታወሳል። በመሆኑም ስለ ነበረው የስልጠና ሁኔታ፣ የ ISO ትግበራን ተቋማዊና ሁሉን አካታች ማድረግና ቀጣይ  መከናወን ያለባቸው ተግባራት፣ ለትግበራ በኮሌጅ ውስጥ ያሉ መልካም አጋጣሚዎችና  በስራ ሂደት ውስጥ ሊሚያጥሙ  የሚችሉ ተግዳሮቶች ዙሪያ የጋራ ምክክር ተካሂዷል።                                                  ኮምንኬሽን ክፍል

ዕለተ ቅዳሜ የካቲት 30/2016 ዓ.ም በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰራተኞች የዕውቅና መርሀ-ግብር ተካሄደ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2015 ዓ.ም የሰራተኞች የዕውቅና መርሀ-ግብር የተካሄደ
+9
ዕለተ ቅዳሜ የካቲት 30/2016 ዓ.ም በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሰራተኞች የዕውቅና መርሀ-ግብር ተካሄደ። በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2015 ዓ.ም የሰራተኞች የዕውቅና መርሀ-ግብር የተካሄደ ሲሆን በመርሀ-ግብሩ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን አቶ በላይ ከፍአለ የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው የመርሀ-ግብሩ ዋና ዓላማ 2015 ዓ.ም በጀት ዓመት መልካም የስራ አፈፃፀም ያላቸው የኮሌጁ ሰራተኞች እውቅና መስጠትና በቀጣይ ለተጀመረው ተቋማዊ ሪፎርም ስራ መነሻ የሚሆን ቀን መሆኑን በማብሰር መልካም ግዜ ተመኝተዋል። በተያያዘም የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዬች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ ይህን ቀን ስናከብር ከእውቅና መርሀ-ግብሩ ባሻገር የISO ትግበራን እውን ለማድረግ ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበት እንዲሁም ለ100ኛ ዓመት ክብረ በዓል የቅድመ ዝግጅት ስራ የምንሰራበት መሆኑን በማመላከት ይህ ፕሮግራም የተሳካ እንዲሆን ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በመጨረሻም የላቀ አፈፃፀም ላስመዘገቡና ካይዘን  ትግበራን ዕውን ላደረጉ የኮሌጁ ባልደረቦች ስጦታና የምስክር ወረቀት በማበርከት መርሀ-ግብሩ ተጠናቋል።                                         ኮምንኬሽን ክፍል

ከየስራ ስራ ክፍሉ ለተወጣጡ ተወካዮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በ"ISO 21001:2018 Educational quality mana
+5
ከየስራ ስራ ክፍሉ ለተወጣጡ ተወካዮች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከኢትዩጰያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት በ"ISO 21001:2018 Educational quality management system" በዓለም አቀፍ ደረጃ ዕውቅና በማግኘት ኮሌጁን ተወዳዳሪ ሊያደርግ የሚያስችል የውል ስምምነት መፈፀሙ እና ወደ ስራ መግባቱ ይታወሳል፤ ይህንን እውን ለማድረግ ከተለያዩ የስራ ክፍሎች ለተወጣጡ ተወካዮች በኢትዬጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዮት አማካኝነት ለአምስት ቀናት ሲሰጥ የነበረው ስልጠና ተጠናቀቀ። የስልጠናው ማጠቃለያ መርሀ-ግብር ላይ ንግግር ያደረጉት የኢኒስቲትዩቱ የስልጠና ዋና ዳሬክተር አቶ መንግስቱ ኮሌጁ መቶኛ ዓመቱን በአለማቀፍ ደረጃ ሰርቲፋይ ሆኖ እንዲያከብር በእኔነት ስሜት በጋራ መስራት እንደሚጠበቅና በቀጣይ የኦዲት ስልጠና እንደሚሰጥ ጠቁመዋል። በተያያዘም የኮሌጁ ተቋማት አቅም ግንባታ ም/ዲን አቶ በላይ ከፍአለ ለኢኒስቲትዩቱ ከፍተኛ ባለሙያዎች ምስጋናቸውን አቅርበው ISO ሰርቲፋይ መሆን እንደ ኮሌጅ ብቻ ሳይሆን እንደ ሀገር ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክት ገልፀው ለዚህም ማኔጅመንቱ ለትግበራው ያለው ቁርጠኝነት የላቀ እንደሆነ አመላክተዋል። በመጨረሻም የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ ይህንን ትግበራ በአጭር ግዜ ውስጥ እውን ለማድረግ በርካታ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን በመግለፅ  ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት አበርክተዋል።                                              ኮምንኬሽን ክፍል

photo content