1 146
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
1 146
የእንጦጦ ፖ /ቴ/ኮሌጅ የማኔጅመንት እና አካዳሚክ የስራ ክፍሎች የ4ኛዉ ሩብ አመት አቅድ አፈጻጸም ሪፖርት እና እቅድ ግምግማ ቀረበ።
ሰኔ 24 ቀን 2016 ዓ.ም
የአመቱ የመጨረሻዉ ሩብ አመት የእቅድ አፈጻጸም ሪፖርት በእንጦጦ ፖ /ቴ/ኮሌጅ የማኔጅመንት እና አካዳሚክ የስራ ክፍል ሃላፊዎች በዛሬዉ እለት ቀርቦ ተገምግሟል ።
በሪፖርቱም የኮሌጁ አቅም ግንባታ ፣ ፀረ ሙስና፣ ግዥ አስተዳደር ዳይሬክቶሬቶች እንዲሁም የኮንስትራክሽን ት /ክፍል እና ሌሎችም የስራ ክፍሎች 100 % የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡ ሲሆን በሌላ በኩል 100% አፈጻጸም ያላስመዘገቡ የስራ ክፍሎች ያጋጠመቸዉን ተግዳሮት ገልጸዉ የተሻለ አፈጻጸም ለማስመዝገብ እንደሚጥሩ ገልጸዋል።
ሪፖርት እና ግምገማዉን በቪዲዮ ኮንፈረንስ የመሩት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በማጠቃለያ መልእክታቸዉ እያንዳንዱ የስራ ክፍል በ BSC እቅድ መመራቱ እንዲሁም አዲሱን የ ISO አሰራር ተከትሎ ሪፖርት መቅረቡን አድንቀዉ በቀጣይ ስራዎች በእቅዳቸዉ መሰረት ሙሉ በሙሉ መከናወን እንዳለባቸው ፣ ኮሌጃችንን የበለጠ ዉብና ማራኪ ማድረግ እንደሚገባ እንዱሁም ለ100ኛ አመት የኮሌጃችን ምስረታ ታላቅ በአል ሁለም የኮሌጁ ማህበረሰብ በንቃት እንዲሳተፍ አሳስበዋል ።
መረጃዉን የሰጡን የኮሌጃችን የእቅድና በጀት ዝግጅት ፣ ክትትልና ግምገማ ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር ወ/ት ፀዳለ አድማሱ ናቸዉ።
የኮሌጁ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ በሶስት ክፍት የስራ መደቦች ስራ ፈላጊዎችን አወዳድሮ ቀጠረ።
የኮሌጁ የሰዉ ሃይል አስተዳደር አወጥቶት በነበረዉ 3 ክፍት የስራ መደቦች ማለትም የጥበቃ ሰራተኛ ፣ ፅዳትና ተላላኪ እንዲሁም የእንስሳት ተንከባካቢ መደቦች በአጠቃላይ 114 ሰዎች ለስራ እድሉ ተመዝገበዉ የነበረ ሲሆን ከእነዚህ መካከልም 17 አመልካቾች ለስራዉ ብቁ ሆነዉ ሲያልፉ 17 አመልካቾች ደግሞ በተጠባባቂነት ተይዘዋል። በዚሁም መሰረት በጥበቃ ሰራተኛ መደብ 7፣ በፅዳትና ተላላኪ 7 እና በእንስሳት ተንከባካቢ 3 አመልካቾች ቅጥር ይፈፅማሉ ተብሎ ይጠበቃል።
የስራ ቅጥር ዉድድሩ ለሶስቱም መደቦች ከሰኔ 13 ቀን 2016- ሰኔ 19 ቀን 2016 ዓ.ም ድረስ ባሉት የተለያዪ ቀናት ዉስጥ የተከናወነ ሲሆን የተግባር እና የፅሁፍ ፈተናዎች እንዲሁም ቃለ ምልልስ ለዉድድሩ መመዘኛ መዋሉን እና በግልጸኝነት እና ብቃትን መሰረት ባደረገ መልኩ ምዘናዉ መከናወኑን መረጃዉን የሰጡን የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የሰዉ ሃብት አስ/ዳይሬክተር ወ/ሮ መለሱ ዘላለም ገልጸዋል ።
የእንጦጦ ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
14ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በተሳካ ሁኔታ ተጠናቀቀ።
-የእንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በፋሽን ሾዉ ዉደድር 2ኛ በመዉጣት ተሸለመ።
ሰኔ 20 ቀን 2016 ዓ.ም
በየአመቱ የሚካሄደው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ኤግዚቢሽን ዘንድሮ ለ14ኛ ጊዜ ''ቴክኒክና ሙያ ለዘላቂ ልማት" በሚል መሪ ቃል ከሰኔ 15 እስከ ሰኔ 20 በተለያዩ ሁነቶች (ምርት እና ማምረቻ ኤግዚቢሽን ፣ ፓናል ዉይይት ፣ ዉድድሮች ፣ ልምድ ልዉዉጥ ፣ ጉብኝት ወዘተ) ሲካሄድ ቆይቶ በዛሬው ዕለት ተጠናቋል።
በኤግዚቢሽን ሳምንቱ ሽልማት እና እዉቅና የሚያስገኙ የጥናትና ምርምር ፣የክህሎት ፣የቴክኖሎጂ፣ስፓርታዊ እና የፋሽን ሾው ውድድሮች ተካሂደዋል።
በዝግጅቱ ማጠቃለያ ላይ ተገኝተው መልዕክት ያስተላለፉት
በቢሮ ኃላፊ ደረጃ የኢንተርፕራይዝና ቴክኖሎጂ ልማት ዘርፍ ኃላፊ አቶ መክብብ ወልደ ሐና የቴክኒክና ሙያ ሳምንቱ ማህበረሰቡ በዘርፉ ያለውን ግንዛቤ እንዲያሳድግ ማስቻሉን በመግለፅ በቀጣይም በኤግዚቢሽኑ የቀረቡ ቴክኖሎጂ የኢንተርፕራይዞችን ምርትና ምርታማነት ለማሳደግ ለኢንተርፕራይዞች እንደሚሸጋገሩ ተናግረዋል።
በማጠቃለያ መርሀ ግብሩ በየዘርፉ ከአንደኛ እስከ ሶስተኛ ደረጃ ለወጡ ሰልጣኞች አሰልጣኞች እና ኮሌጆች የዋንጫ፣የሰርተፍኬት እና የገንዘብ ሽልማት ተበርክቶላቸዋል።
በኤግዚቢሽኑ ማጠቃለያ ከተካሄዱት ሁነቶች መካከል በቴክኖሎጂ ውድድር የ ተግባረ-ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በአንደኝነት ሲያጠናቅቅ ፣ጄኔራል ዊንጌት ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለተኛ እንዲሁም አቃቂ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሶስተኛ ደረጃን በመያዝ አጠናቀዋል ።
በሌላ በኩል በፋሽን ሾው ውድድር ምስራቅ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንደኛ ሆኖ ሲያጠናቅቅ እንጦጦ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ተግባረ ዕድ ፓሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሁለተኛ እና ሶስተኛ ሆነው አጠናቀዋል ።
14ኛዉ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት በአጠቃላይ በርካታ ሰዎች የጎበኙት ፣ ሚዲያዎች የዘገቡት ፣ የቴክኖሎጅ እና ልምድ ልዉዉጥ የተከናወነበት ፣ የቴ /ሙ ተቋማት ያሉበትን ደረጃ ያሳየ እና ለህብረተሰቡ ግንዛቤ የፈጠረ ሆኖ በስኬት ተጠናቋል ።
የእንጦጦ ኮሙኒኬሽን ቡድን
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
