1 146
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
1 146
+4
ዕለተ ማክሰኞ ታህሳስ 15/2017 ዓ.ም
ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ ስራ ፈላጊ ወጣቶች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና በCOC ምዘና ተጠናቀቀ።
ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተወጣጡ ለ469 ስራ ፈላጊ ወጣቶች የተሠጠ የንግድ ስራ ስልጠና ማጠቃለያ የCOC ምዘና ተመዘኑ።
ስልጠናው የተግባቦት አቅምን በማሳደግ የሙያ ክህሎታቸውን የሚያዳብሩበት እንዲሁም በዕለት ተዕለት እንቅስቃሴያቸው ውስጥ ስራቸውን በአግባቡ ለመከወን ትልቅ ሚና ያለውና ህልማቸውን ለማሳካት በር ከፋች መሆኑ ተገለፀ። በአጠቃላይ ለምዘና ከተቀመጡት 469 ወጣቶች መካከል 436ቱ በምዘናው ብቁ መሆናቸውን አስተባባሪው አቶ ይስሃቅ አበራ ገልፀዋል።
ኮምንኬሽን ቡድን
1 146
ዕለተ ዓርብ ታህሳስ 2017ዓ.ም
በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ ሠልጣኞች የተቀናጀ ህብራዊ የሙዚቃ ፣ የሥነ-ስዕልና የስነ-ጽሁፍ ምሽት ተዘጋጅቷል።
የቀድሞ የተፈሪ መኮንን የአሁኑ እንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ የሙዚቃ፣የቲያትርና የሥነ-ስዕል ትምህርት ክፍል ያዘጋጁት የሙዚቃና የስነ-ጽሁፍ ምሽት በዛሬው ዕለት ከቀኑ 10:00 ጀምሮ በትንሹ አዳራሽ ተካሂዷል።
ፕሮግራሙን ያዘጋጁት የ3ኛ ዓመት የሙዚቃ ትምህርት ክፍል ሠልጣኞች ሲሆኑ ዓላማው መደበኛና የማታ ክፍለ ግዜ ሠልጣኞች በአንድ መድረክ የሚያገናኙበት፣ እርስ በእርስ የሚተዋወቁበት እንዲሁም በሙያቸው መደጋገፍ የሚያስችላቸውን ልምድ የሚያካብቱበት፣ መድረክን ለመለማመድ የሚያግዛቸው ፣ ከአሠልጣኞቻቸው አስተያየትን በመውሰድ የቀጣይ መንገዳቸውን መደላደል ለመጣል ታልሞ የተዘጋጀ ነው ያሉን የፕሮግራሙ አዘጋጅ ሠልጣኝ አቤሴሎም ብርሃኑ ናቸው።
በፕሮግራሙ መክፈቻ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር ሙሐመድ መድረኩ ሠልጣኞች በራስ መተማመናቸውን የሚያጎለብቱበትና ልምድ የሚለዋወጡበት በመሆኑ በቀጣይ የውጭ ባለሙያዎችን በመጋበዝ ሰፊ ስራ ሊሰራ እንደሚገባና ስራውን በማስተሳሰር ለውጤታማነቱ በጋራ እንደሚሠሩም ጠቁመዋል ።
በተመሳሳይ የስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ፕሮግራሙ ካለው አስፈላጊነት አንጻር ተጠናክሮ መቀጠል ያለበትና በየወሩ የውስጥና የውጭ እንግዶችን በመጋበዝ ተጠናክሮ መቀጠል ያለበት መሆኑንም አሳስበዋል።
በአጠቃላይ ዘወትር በተለያዩ መድረኮች ላይ በመቅረብ ኮሌጃችንን በማስተዋወቅ የሚታወቀው የኤስቴቲክስ ስልጠና ዘርፍ በቀጣይም የበለጠ ተጠናክሮ እንደምናገኘው እምነታችን የፀና ነው ። በርቱ ተበራቱ እንላለለን።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+8
ዕለተ ዓርብ ታህሳስ 11/2017ዓ.ም
ተግባራዊ ጥናትና ምርምር የሚሠራባቸው
6 ርዕሶች ፕሮፖዛል ተገመገመ።
በጥናት ምርምር እና ፐብልኬሽን የስራ ክፍል
በዛሬው ዕለት የተገመገመው ተግባራዊ ጥናትና ምርምር ሊሰራባቸው በቀረቡ 6 የጥናት ርዕሶች ላይ የተዘጋጀ ፕሮፖዛል የተገመገመ ሲሆን ርዕሶቹም:-
1.Improvement of trainers
engagment&motivation in ict development
2.Improving staff caffe service at entoto
poly technic college
3.Enhancing the implementation of
cooperative training programs at
eptc:constraction sector
4. Enhancing skills &competencies of
manufacturing department trainers for
operating surface &universal grinding
machines
5.Minimizing dropout of auto mechanics
level 4 trainees
6.Improving performance of
automechanics level 3 trainees
performance in the automotive
department
መሆናቸውን ከቀረበው ሰነድ ለማወቅ ተችሏል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
+8
በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ የጽዳት ዘመቻ ተከናወነ ።
ታህሳስ 11ቀን 2017 ዓ.ም
ቴክኒክና ሙያን ጽዱ ውብ እና አረንጓዴ ፣ ለስራ ምቹ ፣ ሳቢና ማራኪ ከማድረግ አኳያ ዛሬ በኮሌጃችን ታላቅ የጽዳት ዘመቻ ተከናውኗል ።
የኮሌጁ የተቋማት አቅም ግንባታ እና ህንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት የጽዳት ዘመቻውን ያስተባበሩ ሲሆን የኮሌጁ አሰልጣኞች ፣ ሰልጣኞች እና የአስተዳደር ሰራተኞች በንቃት ተሳትፈዉበታል።
የጽዳት ዘመቻው ባለድርሻ አካላትን ያሳተፈ ሲሆን
ኦሩዝ፣ እዮብና ጓደኞቻቸዉ የኮምፖስት አምራች ህ/ሽ/ማህበር በኮሌጁ ቅጥር ግቢ የኮምፖስት ማምረቻ ቦታ ተሰጥቷቸው በማምረት ላይ ያሉ መሆናቸውን የገለጹት የማህበሩ ሰብሳቢ አቶ ኦሩዝ በኮሌጁ በሚኖሩ ማንኛውም እንቅስቃሴ ላይ ተሳታፊ መሆናቸውን በመግለጽ በቀጣይም ኮሌጁ በሚጋብዘን ወይም እኛን ሊያሳትፍ በሚችል ተግባራት ሁሉ ከኮሌጁ ጎን እንገኛለል ብለዋል ። በተመሳሳይ ከጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 02 አስተዳደር በጽዳት ዘመቻው ተሳታፊ የሆኑት ፈቀደ ፣ ሃብታሙ እና ጓደኞቻቸው የደረቆ ቆሻሻ ማንሳትና ማስወገድ ማህበር በጽዳት ዘመቻዉ ተሳትፈዋል ።
በዛሬው ዕለት የተከናወነው የጽዳት መርሃ-ግብር ሰራተኞችን ለአንድ ዓላማ ያስተሳሰረና የተሳካ ፕሮግራም ነበር ሲሉ የህንጻ አስተዳደር ጽ/ቤት ሃላፊ አቶ አላዬ ጉችዬ ለክፍላችን ገልጸዋል ። አያይዘውም መቆራረጥ ይታይበት የነበረዉ ወርሃዊ የጽዳት ፕሮግራም በቀጣይ በተከታታይ መደበኛ ቀን ተወስኖለት እንደሚከናወን አሳስበው በዘመቻዉ ለተሳተፉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
በISO 210001 :2018 ዙሪያ ለኮሌጁ አመራሮች ስልጠና ተሰጠ።
ታህሳስ 10 ቀን 2017 ዓ.ም
በሁሉም ተቋማት ምርት እና አገልግሎት ላይ አለምአቀፍ የጥራት ደረጃ ስታንዳርድ የሚቀመጥ ሲሆን አለም አቀፉ የትምህርት ተቋም አስተዳደር ጥራት መለኪያ ISO 210001 :2018 ይባላል። አላማዉም የትምህርት እና የስልጠና ተቋማት የተሻለ አሰራር በመዘርጋት ለሃገራዊ ብሎም ለአለም አቀፉ ኢኮኖሚ እና ማሕበራዊ ፋይዳ ዉጤት ማስመዝገብ ነዉ። ይህም ግብአት ሂደት እና ዉጤት ከደንበኞች ፍላጎት እስከ የደንበኞች እርካታ መሰረት አድርጎ አለም አቀፉን የአሰራር መርህ ተከትሎ ሲሰራ ነዉ።
ስልጠናዉ ለኮሌጁ አመራሮች ፣ ዳይሬክተሮች ፣ የስራ ክፍል ሃላፊዎች እና የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች የተሰጠ ሲሆን ስልጠናዉን የሰጡት ከኢትዮጰያ የጥራት ደረጃዎች አቶ ተስፋዬ እሸቱ ናቸዉ።
አቶ ተስፋዬ በስልጠናዉ ወቅት እንዳብራሩት የትምህርት ተቋም አስተዳደር ጥራት ሂደት (EOMS) ወጭን ይቆጥባል ፣ የተሻለ የግንኙነት አዉታር ይፈጥራል ፣ የትምህርት ጥራትን ያሻሽላል ፣ የባለድርሻ አካላት መተማመንን ይጨምራል ፣ የአስተዳደር ሃላፊነት እና ተጠያቂነት ይጨምራል ያሉ ሲሆን በሌላ በኩል ከመተግበር አንጻር የግንዛቤ እጥረት ፣ ለለዉጥ አለመነሳሳት ፣ ቢሮክራሲ ፣ የግንኙነት ማነስ ፣ ለሰራተኞች እዉቅና እና ሽልማት መንፈግ ፣ በስልጣን ተወረድ ዉሰጥ ተሳትፎ አለማድረግ እና የዉሳኔ ሰጭነት ሚና አለመኖር እንቅፋት ሊሆኑ እንደሚችሉም አንስተዋል።
የተቋሙን ራዕይ እና ተልእኮ ለማሳካት የትምህርት ተቋም አስተዳደር ጥራት ሂደት (EOMS) ወሳኝ በመሆኑ ስልጠናዉን የተካፈሉ አካላት በየክፍሎቻቸዉ ላሉ ባልደረቦቻቸው ግንዛቤ በመፍጠር ኮሌጁ ለሰርትፍኬሽን ለሚያደርገዉ ጉዞ የበኩላቸዉን እንዲወጡ በኮሌጁ አመራሮች በኩል አጽንዖት ተሰጥቶ መልእክት ተላልፏል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የመምህራን ማህበር
አዳዲስ ስራ አስፈጻሚዎችን አስመረጠ።
ታህሳስ 07 ቀን 2017 ዓ.ም
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የመምህራን ማህበር በአዲስ አበባ የመምህራን ማህበር ስር ከተቋቋሙ ማህበሮች አንዱ ሲሆን ለኮሌጁ መምህራን ጥቅማ ጥቅም ማለትም የመምህራን ደመወዝ ፣ መምህራን ቤት እንዲያገኙ ፣ ነጻ የትራንስፖርት አገልግሎት ፣ የደረጃ እድገት ፣ የጤና ፣ የወሊድ ፣ የጡረታ ፣ ልዩ ልዩ ፍቃዶች ፣ የተመቻቸ የስራ ቦታ ወዘተ ጉዳዮች ላይ በብርታት ሲሰራ የነበረ ለመምህራን አለኝታ የሆነ ማህበር ነዉ።
ይህን ብዙ ሃላፊነት የተሸከመ አንጋፋ ማህበር በኮሌጃችን ላለፉት አራት አመታት በትጋት ሲመሩ የነበሩ አመራሮች በአዳዲስ የተተኩ ሲሆን በዚህም መሰረት ዛሬ በተካሄደ ምርጫ :-
1. አቶ ዘላለም ሲሳይ - የማህበሩ ሰብሳቢ
2. አቶ ሙሉጌታ ጋሻዉ - ፀሀፊ
3. ወ/ሮ ፌናን መርሻ - ገንዘብ ያዥ ፣
4. አቶ አለማየሁ ፈንታ - ሂሳብ ሹም እና
5. ሐይማኖት ግርማ ደግሞ ስርአተ ጾታ
በመሆን በኮሌጁ መምህራን የተመረጡ ሲሆን ከባለፉት አመራሮች የስራ ርክክብ ተቀብለዉ ማህበሩን ለመምራት በዛሬዉ እለት በአባላቱ ተመርጠዋል ።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የስነ ጥበብ ት/ክፍል
ተመራቂዎች ኤግዚቢሽን አቀረቡ።
ታህሳስ 09 ቀን 2017 ዓ.ም
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ ከሚሰጣቸው የስልጠና ዘርፎች መካከል አንዱ በሆነዉ በኤስቴቲክስ ትምህርት ዘርፍ የስነ ጥበብ ት/ክፍል የ2016 ዓ.ም ተመራቂ ተማሪዎች የጥበብ ስራቸዉን በኮሌጁ የኤግዚቢሽን ማሳያ ማእከል ባሳለፍነዉ ሳምንት ታህሳስ 04 ቀን 2017 ዓ.ም አቅርበዋል ።
የመመረቂያ ስራዎቻቸዉን ያቀረቡት የኮሌጁ የቀለም ቅብ ፣ የቅርጻቅርጽ እና ግራፊክስ ተመራቂ ተማሪዎች ሲሆኑ በመርሃ ግብሩ የኮሌጃችን ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሀመድ እና ሌሎች ሃላፊዎች የተገኙ ሲሆን የኢትዮጵያ ቀራጺያን እና ሰአሊያን ፕሬዚዳንት ሰአሊ አክሊሉ መንግስቱ በተጋባዥ እንግድነት እንዲሁም የኮሌጁ ተማሪዎች ፣ ሰራተኞች ፣ የጥበብ አድናቂዎች እና የተማሪዎች ቤተሰቦች ተገኝተዋል ።
በመርሃ ግብሩ ለቀድሞዉ የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ከእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የስነ ጥበብ ት/ክፍል ለክፍሉ ላደረጉት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የምስጋና ስጦታ ተበርክቶላቸዋል ።
በየአመቱ የሚደረገዉ በተመራቂዎች የሚቀርበዉ ኤግዚቢሽን ዘንድሮ በመደበኛ ሰልጣኞች ለ16ኛ ጊዜ እንዲሁም በማታ ሰልጣኞች ለ10ኛ ጊዜ የቀረበ ሲሆን ሰልጣኞች በኮሌጅ ቆይታቸዉ የቀሰሙትን እዉቀት እና ክህሎት ያካፈሉበት እና ከባለሙያዎች እና የጥበብ አድናቂዎች ከፍተኛ ሙገሳ ያገኙበት ደማቅ ዝግጅት እንደነበር የቲያትር እና ስነ-ስእል ት/ክፍል ባልደረቦች የሆኑት አቶ ትጉህ መሃሪ እና አቶ ሀይሉ ክፍሌ ለክፍላችን ገልጸዋል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 146
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ አዳዲስ አመራሮችን አስተዋወቀ።
- የ5 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀረበ።
ታህሳስ ፣ 2017 ዓ.ም
ወደ እንጦጦ ፖ/ቴ/ኮሌጅ የተመደቡ አዳዲስ የስራ ሃላፊዎች ባሳለፍነዉ ሳምንት ከኮሌጁ ማህበረሰብ ጋር ትዉዉቅ አድርገዋል ። በዚህም መሰረት ፡-
1. አቶ አብዱልበር መሀመድ - የኮሌጅ ዋና ዲን
2. ዶ/ር ከበደ ባዬቻ - የአቅም ግንባታ አስ/ም/ዲን
3. አቶ ተስፋጽዮን አይናለም - የሽሮሜዳ ካምፓስ ም/ዲን
በመሆን የተመደቡ ሲሆን የተጣለባቸውን ሃላፊነት በመወጣት ለኮሌጁ እድገት እንደሚሰሩ ቃል ገብተዋል።
በተያያዘም የ 5 ወራት የስራ አፈጻጸም ሪፖርት የቀረበ ሲሆን
በቴክኖሎጅ እና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን እና የሰልጣኞች ጉዳይ እና የአካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲኖች ቀርበዋል።
የቴክኖሎጅና ኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ም/ዲን አቶ ወንድምሲያምረኝ በሪፖርታቸዉ የቴክኖሎጂ ፍላጎት ዳሰሳ ጥናት፣ የራስ ማብቃት እቅድ ፣ ወርሃዊ ሪፖርት ፣ የተገልጋዮች የአርካታ ትንተና ፣ ደረጃውን የጠበቀ የኢንዱስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ላይ ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን ከዚህ በታች የተዘረዘሩ ቴክኖሎጂዎች መለየታቸዉን ገልጸዋል ።
- በኤሌክትሪክ የሚሰራ የመንገድ ዳር ቆሻሻ መሰብሰቢያ ቴክኖሎጂ
- የወተት ማርጊያ እና መናጫ ማሽን
- የኮምፖስት ግብአት መቆራረጫ ማሽን
- የእንስሳት መኖ ማቀነባበሪያ ማሽን
የሰልጣኞች ጉዳይ እና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ደግሞ በሪፖርታቸው የእቅድ ሪፖርት ዝግጅት ፣ የፀረ ሙስና ትግል ማጎልበት ፣ የትብብር ስልጠና ከ70 በመቶ ወደ 80 በመቶ ማደጉን ፣አጫጭር ስልጠና ከ80 ወደ 90 በመቶ ማደጉን ፣ ሴቶች እና አካል ጉዳተኞችን ተጠቃሚ ማድረግ ላይ እየተሰራ መሆኑን ፣ የአሰልጣኞች ምዘና ፣ ዜጎችን የአንድ ሙያ ባለቤት በማድረግ ሂደት 50 የኮሌጁን ሰራተኛ ለማሰልጠን ታቅዶ ፍላጎቱ በ 8 ሙያዎች 279 ሰራተኞች ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ፣ ከተቋማት ጋር ተባብሮ ከመስራት አንጻር የአዲስአበባ ዩኒቨርስቲ የኢንጂነሪንግ የቀንና የማታ ተማሪዎች በእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ የተግባር ስልጠና መዉሰዳቸወን: የጉለሌ ክ/ከተማ ኢኖቬሽን ፅ/ቤት ጋር በጋራ ለሰለጣኞች የኮዲንግ ስልጠና መሰጠቱ ፤ ከእሳቤዎች አኳይ እየተሰራበት ያለበትን በ8ቱ ዘረመል በማስረጃ እና በፎቶ የተደገፈ ገለፃ መደረጉ እንዲሁም ISOን መሰረት ያደረገ ስራ በኮሌጁ እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።
በአጠቃላይ ተቋሙን ለመለወጥ ምቹ የስራ አካባቢ ለመፍጠር ፣ የኮሌጁን 100 ኛ አመት ክብረበአል አስመልክቶ ሁሉም የኮሌጁ ማሕበረሰብ የበኩሉን እንዲወጣ ማሳሰቢያ የተሰጠ ሲሆን ተከታታይ ክትትል እና ድጋፍ በማድረግ ፣ የመረጃ ልዉዉጥን በማጠናከር በዋነኝነትም ISO 21001: 2018 ላይ ትኩረት ተደርጎ መሰራት እንዳለበት የተገለጸ እና በቀጣይም ከአመራሩ ጀምሮ እስከ ሰራተኛው እጅ ለእጅ በመያያዝ ቃል የመግባት መርዓ ግብር ተካሂዷል ።
በመጨረሻም ከተሳታፊዎች የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱ ሲሆን የቀጣይ አቅጣጫዎች እና ምላሾችም በመድረኩ ተሰጥተዋል።
የእንጦጦ ፖ/ቴ/ኮ
ኮሙኒኬሽን ቡድን
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
