fa
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

کانال بسته
1 145
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
-1930 روز
آرشیو پست ها
photo content
+1

photo content
+9

ዕለተ ሰኞ የካቲት 11/2016ዓ.ም ከጉለሌ ክ/ከተማ ለተውጣጡ እናቶች ሲሰጥ የነበረው ስልጠና የማጠቃለያ መርሀ-ግብር ተካሄደ። በክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ አማካኝነት በእንጦጦ የተገነባው  የእንጀራ መጋገርያ ፋብሪካ የእናቶችን ተጠቃሚነት ከፍ ለማድረግ ያለመ መሆኑ የተጠቆመ ሲሆን ከጉለሌ ክፍለ ከተማ አራት ወረዳዎች የተውጣጡ እና በዚህ ፕሮጀክት ተጠቃሚ የሚሆኑ ከ400 በላይ እናቶች የሙያ ስልጠና መውሰዳቸው ይታወሳል። በመሆኑም በዛሬው ዕለት ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የማጠቃለያ መረሀ-ግብር የተካሄደ ሲሆን በመረሀ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ የእንኳን ደስ አላችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ያለምንም መንጠባጠብ ስልጠናውን ለወሰዱ እናቶች ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም ሰልጥኖ ዳቦ ከመብላት ባሻገር ለሀገር ኢኮኖሚ ትልቅ አስተዋፅኦ እንደሚያበረክቱ ባለሙሉ ተስፋ መሆናቸውን ገልፀው ጥራት ያለው እንጀራ በመጋገር ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ወደ ኢንተርፕራይዝ በሚሸጋገሩ ግዜ ከኮሌጁ ድጋፍና ክትትል እንደሚደረግላቸው ቃል ገብተዋል። በተየያዘም የጉለሌ ክ/ከተማ ም/ዋና ስራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ጽ/ቤት ሀላፊ አቶ ሰለሞን ታደሰ የእንጀራ ፍብሪካው ለስራ ምቹ እንዲሆንና ከሀገር ውስጥ አቅርቦት ባለፈ በኤክስፖርት እስታንዳርድ አንዲሰራበት ተደርጎ የተገነባ መሆኑን ጠቁመዋል። አክለውም ይህን እድል ላመቻቹት ክብርት ከንቲባ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። የጉለሌ ክ/ከተማ ብልፅግና ጸ/ቤት ሀላፊ አቶ ይከበር ስማቸው እንጀራን መጋገር ለኢትዮጰያ እናቶች ልዩ ጥበብ መሆኑን ገልፀው ይህን ጥበብ በዘመናዊና ሳይንሳዊ መንገድ በመጠቀም እራሳችሁን ብሎም ሀገራችሁን የምትጠቅሙበት ይሁን ሲሉ መልካም ምኞታቸውን ገልፀዋል። በተመሳሳይ የጉለሌ ክ/ከተማ ዋና ስራ አሰፈፃሚ አቶ ወልዴ ሞገስ የዛሬ ዓመት ለክብርት ከንቲባ ከጉለሌ እናቶች ተጠቃሚነት ጋር በተያያዘ በቀረበው ጥያቄ መሰረት ይህ ፕሮጀክት መሰራቱን ገልፀው በዚህም ከ450 በላይ እናቶች የስራ እድል እንደተፈጠረላቸውና ለዚህ ፕሮጀክት መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። በመጨረሻም ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ እናቶች የምስክር ወረቀት የተበረከተ ሲሆን በክብርት ከንቲባ ወ/ሮ አዳነች አበቤ አማካኝነት በእንጦጦ 11,500 ካሬ ሜትር ላይ ያረፈው የእንጀራ መጋገርያ ፋብሪካ ተጎብኝቷዋል።                          ኮምንኬሽን ክፍል

photo content

photo content
+1

photo content
+8

አንጋፍው መምህርና ሰዓሊ ታደሰ መስፍን የህይወትና የስራ ልምዳቸውን ለስነ-ጥበብ ት/ክፍል ሰልጣኞች አካፈሉ። በመረሀ-ግብሩን የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የስነ-ጥበብ ስልጠና ዘርፍ  መምህር ሀይሉ ክፍሌ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው በስነ-ጥበብ የትምህርት ክፍል ከመማር ማስተማር ሂደት ባሻገር በየግዜው መልካም ስምና ዝና ያተረፉ የሙያ ባለቤቶች በመጋበዝ የህይወትና የስራ ተሞክሮአቸውን እንዲያጋሩ በማድረግ በሰልጣኞች ዘንድ መነቃቃትን ለመፍጠር ትልቅ ስራ እየተሰራ መሆኑን አመላክተዋል። አክለውም በኢትዮጰያ የስነ-ጥበብ ታሪክ ውስጥ አንጋፋ መምህርና ሰዓሊ ታደሰ መስፍን ለሰልጣኞች የህይወትና የስራ ልምዳቸውን ሊያካፍሉ በመምጣታቸው የተሰማቸውን ደስታ ገልፀው ለፕሮግራሙ መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በኢትዮጵያ የስነ-ጥበብ ታሪክ ውስጥ አንጋፋዉ መምህርና ሰዓሊ ታደሰ መስፍን  ተጋባዥ እንግዶች፣ የሙያ አጋሮቹና ተማሪዎቹ በተገኙበት የትውልድ  አካባቢያቸው ወልድያን፣ አስተዳደጋቸውን እና የትምህርት ሁኔታቸውን ከልጅነታቸው ጀምሮ የስዕል ፍቅር ያደረባቸው በመሆኑ ያገኙትን ቁሳቁስ በመጠቀም ስዕል ይስሉ እንደ ነበር   እና ወደ አዲስ አበባ የመጡበትን አጋጣሚም እንዲሁ ፤ አዲስ አበባ ላይ የተጀመረው ትምህርት በሲውዲኖች ሚሲዎን ት/ቤት፣ ራስ አበበ አረጋይና በዕደ ማርያም ትምህርት ቤት የተማሩ ሲሆን  በ1960 ዓ.ም ዓርት እስኩል በመግባት የስዕል ትምህርታቸውን ተከታትለዋል  በመጨረሻም  ወደ ሶቪየት ህብረት በማምራት የስዕል ትምህርታቸውን እንደቀጠሉ ያወሳሉ። በሃገር ቤትም ሆነ በውጪ ሃገር የነበራቸውን ቆይታ አስመልክቶ ሰፊ ስዕላዊ መግለጫ /ምስል ከሳች ማብራሪያ በመስጠት ታዳሚው በምናቡ ምስሉን እንዲያይ አስችሎታል። በተያያዘም ወደ ስራ ዓለም የተቀላቀሉበትን አጋጣሚ እና የስራ ሁኔታቸውን አስመልክተው በሰፊው ተንትነዋል።  በኢትዮጵያ የስነ-ጥበብ ታሪክ ውስጥ ትልቅ አሻራ ያሳረፉት መምህርና ሰዓሊ ታደሰ መስፍን ከስእል ስራዎቻቸው ባሻገር በኢትዮጵያ የመገበያያ ሳንቲሞች ላይ ያረፉ ምስሎችን እና የተለያዩ መንግስታዊ ድርጅቶች አርማዎችን ቀርፀው አበርክተዋል። በመቀጠልም የሙያ አጋራቸው አርቲስት ልኡልሰገድ ረታ እና ሌሎች አብረዋቸው የስራ ቆይታ የነበራቸው እና በስራ አጋጣሚ የተዋወቋቸው ባለሙያዎች እና ያስተማሯቸው ተማሪዎች ስለ መምህራቸው ምስክርነታቸውን ሰጥተዋል።  ታዲያ እኝህ አንጋፋ መምህርና ሰዓሊ ለኮሌጁ የስነ-ጥበብ ት/ክፍል ሰልጣኞች የህይወትና የስራ ልምዳቸውን እንዲሁም ሰዓሊ ሊኖረው ስለሚገባ ባህርያት ፣ ሙያዊ ስነምግባር፣ ዘመኑን የዋጀ የአሳሳል ጥበብ እና ኢትዮጵያዊ የአሳሳል ጥበብ መሠረትን ባለቀቀ መልኩ አሻራቸውን አኑረው እንዲያልፉ ምክራቸውን አካፍለዋል። በተያያዘም ከታዳሚዎች ለተነሱላቸው ሃስብ፣ አስተያየት እና ጥያቄዎች እንደየ አጠያየቃቸው ምላሽ ሰጥተዋል። በመጨረሻም በት/ክፍሉ የተዘጋጀውን እና የተሰታፊዎች ፊርማ ያረፈበት ማስታወሻ በስጦታ መልክ ተበርክቶላቸዋል።                              ኮምንኬሽን ክፍል

ዕለተ ረብዕ ታህሳስ 6/2916ዓ.ም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ለሚሰጡ አሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳሬክቶሬት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ አን
+3
ዕለተ ረብዕ ታህሳስ 6/2916ዓ.ም የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ለሚሰጡ አሰልጣኞች ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን እና ቴክኖሎጂ ሽግግር ዳሬክቶሬት በጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ አንድ እስከ ስምንት የሚገኙ ኢንተርፕራይዞች ላይ የተመደቡ አሰልጣኞች በድጋፍ የፈራ ሀብት  አለካክ ላይ ለ10 ቀናት የሚዘልቅ ስልጠና መሰጠት ተጀመረ። በስልጠናው የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኢ/ኤ/ቴ/ሽ/ም/ዲን አቶ ወንድምሲያምረኝ  መኮንን የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክታቸውን አስተላልፈው ስልጠናው የሚሰጠው የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን ድጋፍ ለሚሰጡ አሰልጣኞችና  ለወረዳ ባለሙያዎች መሆኑን ገልፀው የስልጠናው የትኩረት አቅጣጫ የኢ/ኤክስቴንሽን ድጋፍና ክትትል ለሚያደርጉ አሰልጣኞች የፈራ ሀብት ስሌትና አመዘጋገብ ላይ ስልጠና በመስጠት ስለ ድጋፍ ያላቸውን ግንዛቤ ማሳደግ፣ የኢንተርፕራይዞችን ውጤታማ ሊያደርግ የሚችል የሰው ሀይል ስምሪት ለመስጠትና የኢንተርፕራይዞችን ፍላጎት መሰረት ያደረገ ስልጠና ለመስጠት መሆኑን በማመላከት መልካም የስልጠና ግዜን ተመኝተዋል። ስልጠናውን የሰጡት የኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን አስተባባሪ አቶ ብርሀኑ ዘገየ ሲሆኑ ስልጠናው ትኩረት ያደረገባቸው ርዕሰ ጉዳዮች - በድጋፍ የፈራ ሀብት ምዝገባ አስፈላጊነት - የሀብት ቅመራ መርሆች - በቴክኒካል ክህሎት ድጋፍ የተገኘን ሀብት ለመለካት   መከተል የሚገባን ሂደት - በኢንተርፕረነርሺፕ የተገኘን ሀብት ለመለካት   የምንከተለው ሂደት - በቴክኖሎጂ ድጋፍ የተገኘ ሀብት ለመለካት መከተል   ያለበት ሂደት በዝርዝር ተዳሰዋል። በመጨረሻም ከተሳታፊዎች ለተነሱ ጥያቄዎች ፣ ሀሳብና አስተያየቶች በአሰልጣኙ ምላሽ ተሰጥቶባቸው የዕለቱ ስልጠና ማጠቃለያ ሆኗል ።                                  ኮምንኬሽን ክፍል

በኢትዮጵያ ፡ ሥነ - ጥበብ ታሪክ ውስጥ አንጋፋው መምህርና ፡ ሠዓሊ ፡ ታደሰ መስፍን ፡ ኅሙስ ፡ የካቲት 7 , 2016 ዓ ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በሥነ ጥበብ ትምህርት ክፍልን የሕይወትና የሥራ ልም
በኢትዮጵያ ፡ ሥነ - ጥበብ ታሪክ ውስጥ አንጋፋው መምህርና ፡ ሠዓሊ ፡ ታደሰ መስፍን ፡ ኅሙስ ፡ የካቲት 7 , 2016 ዓ ም ከ 4 ሰዓት ጀምሮ በሥነ ጥበብ ትምህርት ክፍልን የሕይወትና የሥራ ልምድ ሊያካፍል ይመጣል ።

ከአፄ ልብነድንግል አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች ኮሌጁን ጎበኙ። ከአፄ ልብነድንግል አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ከ5-8ኛ ክፍል የተውጣጡ 24 ተማሪዎች በኮሌጁ የተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ጉብኝ
+1
ከአፄ ልብነድንግል አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ተማሪዎች ኮሌጁን ጎበኙ። ከአፄ ልብነድንግል አንደኛ ደረጃ ት/ቤት የመጡ ከ5-8ኛ ክፍል የተውጣጡ 24 ተማሪዎች  በኮሌጁ የተለያዩ ስልጠና ዘርፎች ጉብኝት አካሄዱ ። የጉብኝቱ ዓላማ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ትምህርት ዘርፍ ህጻናት መነሳሳት እንዲኖራቸው ለማስቻል አልሞ ነው።  በኮሌጁ ካሉ ስልጠና ዘርፎች ኤስቴቲክስ እና ቴክስታይል ጋርመንት ስልጠና ዘርፎችን በአሰልጣኞች በመታገዝ ተዘዋውረው ጉብኘኘት አድርገዋል።                                        ኮምንኬሽን ክፍል

+4
Addis Lissan HIDAR 15-2016 Entoto1.pdf1.80 KB

photo content

photo content
+9

photo content

photo content
+9

ዕለተ ዓርብ የካቲት 1/2016ዓ.ም ተቋማዊ ሪፎርም ለመፍጠር የሚደረገው እንቅስቃሴ ተጠናክሮ ቀጥሏል። ተቋማዊ ለውጥ ለመፍጠር ያለመው መርሃ-ግብር በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ  ማኔጅመንት እና አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት የጋራ የልምድ ልውውጥ መደረጉ ይታወቃል።ተቋማዊ ሪፎርሙን እውን ለማድረግ ያለ መርሃ ግብር በማኔጅመንቱ ቁርጠኝነት በግቢው ውስጥ የተለያዩ ስራዎች እየተከናወኑ ሲሆን ስልጠና ዘርፎች ሞያቸው በሚፈቅደው ሁሉ ስራዎችን አሃዱ ብለው ጀምረውታል። በትላንትናው ዕለት የተጀመረው እና ዛሬም ቀጥሎ የዋለው ይህ ተግባር የማር ማስተማር ሂደቱን ምቹና ቀልጣፋ ለማድረግ እንዲሁም ለሰራተኛው ሆነ ለተገልጋዮች ምቹ  አከባቢን ከመፍጠር አንፃር  የማፅዳትና የማደራጀት ስራ በመሰራት ላይ ነው። የተቀደሰ ተግባር ከታለመለት ግብ እንዲደርስ የኮሌጁ ማህበረሰብ በሰፊው ይቀላቀለው እንላለን።        "ድር ቢያብር አንበሳ ያስር " አይደል ብሂሉ። በኮሌጁ ያሉትን መልካም አጋጣሚዎች በመጠቀምና ምድረ ግቢውን በማሻሻል ኮሌጁን ወደ ቀደመው ከፍታ ለመመለስ የሚደረገውን ጥረት እንቀላቀል ።                                    ኮምንኬሽን ክፍል

photo content
+6

photo content
+9

ዕለተ ዓርብ ታህሳስ 1/2016ዓ.ም የህይወት ክህሎት ስልጠና የማጠቃለያ መርሀ-ግብር ተካሄደ።         ከጉለሌ ክፍለ ከተማ ወረዳ አራት ለተውጣጡ ከ12ኛ ክፍል በታች ለሆኑና ዕድሜያቸው 18-25 ዓመት ለሆኑ ወጣቶች በጉለሌ ክ/ከተማ ስራና ክህሎት ጽ/ቤት የወጣቶች የስራ ላይ ልምምድ አማካኝነት የህይወት ክህሎት ስልጠና መስጠት መጀመሩ ይታወሳል፡፡ በመሆኑም በዛሬው ዕለት ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የማጠቃለያ መረሀ-ግብር የተካሄደ ሲሆን በመረሀ-ግብሩ ላይ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፍዬ ስልጠናው በተቀመጠለት ግዜና አግባብ እንዲከናወን የጉለሌ ክ/ከተማ እና ኮሌጁ በቅንጅት በጋራ እየተናበቡ እነደተሰጠ ገልፀው በስልጠናው ወቅት ሰልጣኞች ስነ-ምግባር በተላበሰ መልኩ ስልጠናውን በማጠናቀቃቸው ምስጋናቸውን አቅርበዋል። አክለውም በቀጣይ የሚወሰዱትን የ6ወር የስራ ላይ ልምምድ በአግባብ በማጠናቀቅና ወደ ስራ በመሰማራት እራሳቸውን ብሎም ሀገራቸውን የሚጠቅሙ እንደሚሆኑ ባለሙሉ ተስፋ መሆናቸውን ገልፀዋል። በተያያዘም የጉለሌ ክ/ከተማ ወረዳ 4 ም/ሰራ አስፈፃሚና የስራና ክህሎት ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ ታረቀኝ በስልጠና ወቅት በትኩረት እንደተከታተሉት እና ሰልጣኞች በጥሩ ሁኔታ እየሰለጠኑ መሆናቸውን እንደተገነዘቡ ገልፀው ለስልጠናው መሳካት ያላሰለሰ ጥረት ላደረጉ አካላት ምስጋና አቅርበዋል። በመጨረሻም የጉለሌ ክ/ከተማ ፅ/ቤት ሀላፊ አቶ እንዳሻው ምንይችል ይህ ስልጠና ወጣቶች ለስራ ያላቸውን ፍላጎትና ተነሳሽነት የምናስመሰክርበት ፕሮጀክት መሆኑን ጠቁመው የስራ ትስስር ፕሮግራሙን በንቃት በመከታተል ሙያ መልመድና ማዳበር እራሳቸውን መቀየር እንደሚገባቸው ገልፀዋል። አክለውም ለሚገጥማቸው የትኛውም ችግር ቢሮው ከጎናቸው መሆኑን በማመላከት ስልጠናውን በብቃት ላጠናቀቁ ሰልጣኞች የምስክር ወረቀት አበርክተዋል።                                                        ኮምንኬሽን ክፍል

ዕለተ ሀሙስ ጥር 30/2016ዓ.ም ቦሌ ማኒፍክቸሪንግ ኮሌጅ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ አደረጉ። ቦሌ ማኒፍክቸሪንግ ኮሌጅ ከተለያየ የስራ ክፍል የተወጣጡ የኮሌጁ ሰራተኞች ከካይዘን
+9
ዕለተ ሀሙስ ጥር 30/2016ዓ.ም ቦሌ ማኒፍክቸሪንግ ኮሌጅ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የልምድ ልውውጥ አደረጉ። ቦሌ ማኒፍክቸሪንግ ኮሌጅ ከተለያየ የስራ ክፍል የተወጣጡ የኮሌጁ ሰራተኞች ከካይዘን ኢኒስቲትውት በተደረገላቸው ጥቆማ በእንጦጦ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እየተገበረ ያለውን የካይዘን አደረጃጀት የልምድ ልውውጥ ለማድረግ ተገኝተዋል። የጉብኝት ብድኑ በየዘርፉ ያሉ ባለሙያዎች በመታገዝ የተለያዮ የስልጠና ዘርፎችን የካይዘን አተገባበር ተዘዋውረው ተመልክተዋል።                             ኮምንኬሽን ክፍል