1 148
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-27 روز
-1930 روز
آرشیو پست ها
1 148
ሐምሌ 25/2017ዓ.ም
እንኳን ደስ ያለን ሲጠበቅ የነበረው የጥረታችን ውጤት በእጃችን ገብቷል።
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የISO 21001:2018 Educational Organization Management System /የአሰራረ ስርዓትን ለመተግበር ታህሳስ 9 ቀን 2016ዓ.ም ከኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢንስቲትዩት ጋር ስምምነት ተፈራርሞ ወደ ስራውን ጀምሯል ፤ ከግንቦት 29/ቀን 2016 ጀምሮ ደግሞ ይፋዊ ትግበራውን መጀመሩ ይታወቃል።
በመቀጠልም እልህ አስጨራሽ የትግበራና የግምገማ ሂደትን በመሻገር ኮሌጁ 21001:2018 Educational Organization Management System ሰርተፍኬቱን በዛሬው ዕለት ከኢትዮጵያ ተስማሚነነት ምዘና ድርጅት ኃላፊ ኢንጂነር መዓዛ አበራ እጅ ተረክቧል። በርክክቡ ወቅት ክብርት ኃላፊዋ ISO 21001:2018 Educational Organization Management System ን ተግባራዊ ያደረጉ ኮሌጆች በኢትዮጵያ 3 ብቻ ሲሆኑ እንደ ከተማ ደግሞ ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ 2ኛው ኮሌጅ መሆኑን ጠቅሰው በዚህ የዕውቅና ሰርተፊኬት ኮሌጁ በተለያዩ ደረጃዎች የመወዳደር ፣ እራሱን የመሸጥ እና ማስተዋወቅ የሚችልበት ሁኔታ የሚፈጥርለት በመሆኑን አመላክተው በድጋሚ እንኳን ደስ ያላችሁ መልእክታቸውን አስተላልፈዋል።
በሰርተፊኬት ርክክቡ ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ድርጅቱ ከቅድመ ዳሰሳ ጥናት ጀምሮ በሰነድ ዝግጅትና ክትትል እንዲሁም በምዘና ሂደቱ ለነበረው ቁርጠኝነት ምስጋናቸውን አቅርበው በቀጣይ ድርጅቱ ከሚሰጣቸው በርካታ አገልግሎቶች አንጻር በጋራ የምንሰራቸው ስራዎች እንደሚኖሩ ጠቁመው በሁሉም ደረጃዎች ለኮሌጁ የተመደቡ ባለሙያዎች በመልካም ስነ-ምግባራቸው ከልብ የሚከታተሉን እና የሚደግፉን ነበሩ ለዚህም በግላቸው እና በኮሌጁ ስም ላቅ ያለ ምስጋናቸውን አቅርበዋል። በዚህ አጋጣሚ በዚህ ስራ ላይ ለተሳተፉና ለኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በድጋሚ እንኳን ደስ አላችሁ ደስ ያለን ብለዋል።
በተመሳሳይ የኮሌጁ የበላይ አመራሮች እና አስተባባሪው አቶ ሚካኤል ጎኣ ኮሌጁ ያለውን አቅም በመግለጽ ከድርጅቱ ጋር ለነበረው ቆይታ ምስጋናቸውን አቅርበዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+8
ሐምሌ 24/2017ዓ.ም
7ኛ ዙር ሃገራዊ የአንድ ጀምበር ችግኝ ተከላ መርሃ ግብር ከ10,000 በላይ ችግኞችን በመትከል ተከናውኗል። "በመትከል ማንሰራራት" በሚል መሪ ቃል ሃገራዊ ተልዕኮን በማንገብ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ኮር አመራሮች፣የማኔጅመንት አባላት፣አካዳሚክ ኮሚሽን አባላት፣ የቡድን መሪዎች እና አስተባባሪዎች የተሳተፉበት የችግኝ ተከላ መርሃ ግብር በለሚኩራ ክ/ከተማ ወረዳ 13 ካራ መድኅኒዓለም ቤ/ክርስቲያን አካባቢ በተዘጋጀው ስፍራ ተከናውኗል።
በችግኝ ተከላው መርሃ ግብር ላይ የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ባስተላለፉት መልእክት በዚህ የችግኝ ተከላ መርሃግብር ላይ በመሳተፍ ምህዳርን ለማስጠበቅ አሻራችንን ለማኖር በመቻላችን ኩራት ይሰማናል፤ ለቀጣዩ ትውልድ የምናወርሰው አንዱ ስጦታችን መሆን አለበት በማለት ይህ እውን እንዲሆን እንደከዚህ ቀደሙ ሁሉ አሁን ላይ የተከልነውን ችግኝ ተመልሰን በመጎብኘትና በመንከባከብ ልንከታተለው ይገባልም ብለዋል።
የዝግጅት ክፍላችንም ይህን ሃሳብ በመጋራት በክትትሉ እና በእንክብካቤው ስራ ዳግም ያገናኘን ብለናል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+7
ሐምሌ 22/2017ዓ.ም
የስልጠና ዘመኑ ተመራቂዎች አሠልጣኞቻቸውን አመሠገኑ።
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የማርኬቲንግ የስልጠና መስክ ተመራቂዎች የእናመሠግናለን ፕሮግራም አዘጋጅተው አሠልጣኞቻቸውን ሲያመሠግኑ የዝግጅት ክፍላችን በቦታው ተገኝቶ ነበር።
በተለያዩ ዝግጅቶች የደመቀው የእናመሠግናለን ፕሮግራም ለዚህ ደረጃ እንዲበቁ አስተዋጽኦ ያደረጉ አሠልጣኞች ተሸልመውበታል፣ የግጥም ውዳሴ አግኝተውበታል ። በፕሮግራሙ ላይ የተገኙት የስልጠናና አካዳሚክ ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ሠልጣኞቹ ስላደረጉት ነገር አመስግነው ሠልጣኞች ከምርቃታቸው በፊት በቀጣይ የስልጠና ማጠናቀቂያ ምዘናቸውን በአግባቡ እንዲዘጋጁና እና እንዲወጡ መልእክት አስተላልፈው ሠልጣኞች ያዘጋጁትን ስጦታ ለአሠልጣኞቹ አበርክተዋል።
በተመሳሳይ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪው አቶ አለማየሁ ተስፋዬ እና አሠልጣኞቹ ለተበረከተላቸው ስጦታ ምስጋናቸውን አቅርበው ሰልጣኞች ለምዘና በሚኖራቸው ዝግጅት የበኩላቸውን በማበርከት ለውጤት እንዲበቁ እንሰራለን በማለት ቃል ገብተዋል። አያይዞም ከስራ ጋር የማስተሳሰሩን ስራ አጠንክረው እንደሚሰሩ አቶ አለማየሁ ተስፋዬ ተናግረዋል ።
ይህ የእናመሠግናለን ፕሮግራም በማርኬቲንግ ሠልጣኞች ሲደረግ ለመጀመሪያ ግዜ ሳይሆን ቢያንስ ባለፈው ዓመት ተመሳሳይ ዝግጅት እንደነበር እናስታውሳለን፤ለአሠልጣኞቹ የሞራል ስንቅ ስለሚሆን ተበራተው እንዲሰሩ የበኩሉን አስተዋጽኦ ይኖረዋል የሚል እምነት አለን።
እኛም መልካም የሽግግር ጊዜ ለሠልጣኞች ተመኘን።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+6
ሐምሌ 22/2017ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የበጀት ዓመቱ የዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ ተከናወነ።
ከአዲስ አበባ ስራና ክህሎት ቢሮ የተላከው የባለሙያዎች ቡድን በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ተገኝተው የ2017ዓ.ም ዕቅድ አፈጻጸም ግምገማ አካሂደዋል ። በግምገማው የእቅድ ዝግጅትና ክትትል ዳይሬክቶሬት በዋነኛነት በኮሌጁ ከታቀዱት ተግባራት አንጻር ያለውን አፈጻጸም ምን ይመስላል?? ሌሎች በየዘርፋቸው ባስቀመጡት ዕቅድ መነሻነት ክንውኑ እና ሂደቱ ምን ይመስላል? እሚለው እና በሰነድ የታገዘ መሆን አለመሆኑን የተፈተሸ ሲሆን አስፈላጊ ሆኖ ሲገኝ ማብራሪያ በመስጠት ተሳትፎ አድርገዋል።
በግምገማው አብዛኛው የኮሌጁ ዕቅድ መሆን በሚገባው ልክ የተፈፀመ ቢሆንም አንዳንድ ከመረጃ አያያዝ ጋር የተያያዙ ክፍተቶች መታየቱን ተከትሎ የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ክፍተቱን ለመሙላት በትኩረት መስራት እንደሚያስፈልግ ለገምጋሚ ቡድኑ አስረድተው በግምገማው ለነበራቸው ቆይታ ባለሙያዎቹን አመስግነዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
ሐምሌ 2017 ዓ.ም
የተፈሪ መኮንን ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ከአካዳሚ ኮሚሽን አባላት ጋር ውይይት አካሄደ፡፡
በውይይቱ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች እና ሌሎች የሚመለከታቸው አካላት የተሳተፉበት ሲሆን ለውይይት የቀረቡት አጀንዳዎች ትኩረት እና የተሰጡ የመፍትሄ ሃሳቦች፤ መግባባት የተደረሰባቸው ጉዳዮች የ2017 ተመራቂ ሰልጣኞች የሀገር አቀፍ ምዘና ያለበትን ደረጃ የተመለከተ ሲሆን እያንዳንዱ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪ በየስልጠና ዘርፉ በስልጠና ዘመኑ የተመራቂ ሰልጣኞች ቁጥር፤ የትብብር ስልጠናቸውን ጨምሮ ስልጠናውን ስለማጠናቀቃቸው እና ተቋማዊ ምዘና ወስደው ለሃገር አቀፉ ምዘና ዝግጁነታቸውን በተመለከተ ሪፖርት ቀርቧል፡፡ በተደረገው ውይይት የአውቶሞቲቭ እና የኢንፎርሜሽን ስልጠና ዘርፍ ብቻ ስልጠና እና የተቋም ምዘና እንዲሁም ምዴል ምዘና አስመዝነው ለሀገር አቀፍ ምዘና የሰልጣኞች ዝርዝር የላኩ ሲሆን ሌሎች ስልጠና ዘርፎች በዚህ አግባብ ያላጠናቀቁ መሆኑን በጥብቅ ከተገመገመ በኃላ ቀሪ ስራዎችን እሰከ ነሐሴ አጋማሽ እንዲያጠናቅቁ የጋራ መግባባት ላይ ተደርሰዋል፡፡
በመቀጠልም ተመራቂ ሰልጣኞች የስራ ትስስርን በተመለከተ በትኩረት የተነሳ ሲሆን ሰልጣኞች ስልጠናቸውን አጠናቀው በምዘና ብቃታቸው ከተረጋገጠ በኋላ ከስራ ጋር እንዲተሳሰሩ ስራዎች ይሰራሉ፡፡ ምንም እንኳን የስልጠና ዘመኑ ተመራቂዎች የሃገር አቀፉን ምዘና የጀመሩት ውስን ቢሆኑም አንዳንድ ስልጠና ዘርፍ ተመራቂዎች ቀድመው ከስራ ጋር መተሳሰራቸው የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ገልጸው ያልተሳሰሩት ሠልጣኞች ደግሞ ስልጠናቸውን እና ምዘናውን እንዳጠናቀቁ ከስራ ጋር እንዲተሳሰሩ የተመቻቸ እነደሆነ እነዚህ የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ለተሰብሳቢዎች አስረድተዋል፡፡
በተጨማሪም Ethio coder ስልጠና በሰልጣኝ በአሰልጣኝ ያለበት ደረጃ የተገመገመ ሲሆን
አሰልጣኞች እና ሰልጣኞች የEthio coder ስልጠና በመውሰድ ላይ መሆናቸው በውይይቱ የተገለጸ ሲሆን፤ አወሳሰዱም በተሰጠው አቅጣጫ መሰረት በፍላጎት ላይ የተመሰረተ ሆኖ አንዳንዶች አራቱንም የስልጠና ፓኬጆች ያጠናቀቁ ሲሆን አንዳንዶች ደግሞ አንድም፤ ሁለትም ሶስትም መውሰዳቸውንና ሌሎች ደግሞ ስልጠናውን አየተከታተሉ መሆኑ ታውቋል፡፡
በውይይቱ መጨረሻም የስልጠናው አስፈላጊነት ከተገለጸ በኋላ ሁሉም የኮሌጁ ማህበርሰብ አባላት ሀላፊነታቸውን እንዲወጡ ተሰምሮበታል፡፡
በመጨረሻም የE-School አተገባበር ያለበት ደረጃ የተዳሰሰ ሲሆን የሰልጣኞች መረጃ፤ የሚወስዱዋቸው ስልጠናዎች እና ያስመዘገቡት ውጤት በመረጃ ቋት ሰፍሮ የሚገኝ ቢሆንም በጥቂት የስለጠና ዘርፎች የተሟላ አለመሆኑ ግንዛቤ ተይዞ አስቸኳይ የእርምት እርመጃ እንዲወሰድ ከመግባባት ተደርሷል፡፡
የስልጠና ዘርፍ ተጠሪዎች ይህንን ስራ በማስፈጸም ስራውን እንዲከታተሉ ለተወከሉት አካላት እንዲያሳውቁ አቅጣጫ ተቀምጧል፡፡
ኮሙኒኬሽን ቡድንቀ
1 148
+8
ሐምሌ 17/2017ዓ.ም
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2017በጀት ዓመት ዕቅድ አፈጻጸም ለኮሌጁ ማህበረሰብ ቀረበ።
አፈጻጸሙ በሁለት አካላት የቀረበ ሲሆን አቅራቢዎችም የኮሌጁ ስነ-ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት እና የኮሌጁ ዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት ናቸው ።
በመጀመሪያ የቀረበው የስነ-ምግባር መከታተያ ዳይሬክቶሬት በበጀት ዓመቱ ያቀዳቸውና ያከናወናቸውን ተግባራት አፈጻጸም ሲሆን በተመሳሳይ በዕቅድና በጀት ዳይሬክቶሬት የበጀት ዓመቱን ዕቅድ እና ክንውን የዓበይትእና ቁልፍ ተግባራት ክንውን በዝርዝር ቀርቧል።
በቀረቡት ሪፖርቶች ላይ ተሳታፊዎቹ የታዩ ጠንካራ ጎኖችን በማስቀደም መስተካከል አለባቸው ፣ በትኩረት ሊሰራበት የሚገባቸውን ፣ በሪፖርቱ ያልተካተቱና በሚገባ ያልተዳሰሱ ያሏቸውን ሃሳብ አስተያየት አቅርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በመጨረሻም የኮሌጁ ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ በቀረበው ሪፖርት ላይ እና በተነሱ ሃሳብ አስተያየቶች በቀጥታ ሊወሰዱ ይገባል ያሏቸውን እንደ ግብአት ተወስደው መስተካከል አለባቸው ያሉትንም ደግሞ አቅጣጫ በመስጠት ስብሰባው ተጠቃሏል ።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
1 148
+5
ሐምሌ /2017ዓ.ም
በተፈሪ መኮነን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የንብረት ቆጠራ እየተካሄደ ነው።
የ2017ዓ.ም በጀት ዓመት መጠናቀቅን ተከትሎ የኦዲት ስራውን ለማከናወን እንዲቻል የቆጠራ ኮሚቴ ተዋቅሮ ሐምሌ 1/2017ዓ.ም የፋይናንስ ካዝናዎች ፣ የንብረት ክፍሎችና ሰነዶች መታሸጋቸው ይታወቃል።
ኮሚቴው በሁለት ቡድን ተከፍሎ የታሸጉ የንብረት ክፍሎችን በመክፈት ቆጠራውን እያከናወነ መሆኑን ተመልክተናል።
የቆጠራ አስተባባሪው አቶ እድሜአለም ሳልል በዚህ ሥራ ሲሳተፉ ለ2ኛ ግዜ መሆኑን ጠቅሰው የቆጠራ ሥራው በጥሩ ሁኔታ እየተከናወነ እንደሆነ ይናገራሉ። ባለፈው ዓመት በንብረት ክፍሉ የነበሩ ንብረቶች ለማስቀመጥም ሆነ ለመቁጠር በጣም አስቸጋሪ እና ለረጅም ዓመታት እየተንከባለሉ የቆዩ መሆናቸውን ጠቁመው በአሁን ላይ ያለውን ግን አንጻራዊ በሆነ እይታ የተከማቹ ንብረቶች ወደ ስልጠና ዘርፎች የወጡና የተወገዱ በመሆናቸው ስራው ቀለል እንዲል አስችሎታል ይላሉ። በንብረት አያያዝ/አቀማመጥ፣ ሥርጭትና አጠቃቀም ብሎም አወጋገድ ላይ የበለጠ መስራትና ማስተካከል እንደሚያስፈፈልግም ያሳስባሉ።
1 148
ሰላም እንዴት አረፈዳቹ የስራ ባልደረባችን የሆነችው ሙሉ እመቤት አበባው እናት ስላረፉ የቀብር ስነ-ስርዓት ነገ እሁድ 13/11/17 ዓ.ም ከ4:00-5:00 ፈረንሳ ጉራራ ጊዮርጊስ ስለሆነ ከግቢ 4:00 ላይ እንነሳለን።
1 148
ሐምሌ 11/2017ዓ.ም
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከባለድርሻ አካላቱ ጋር ዕቅድን መሠረት ያደረገ ውይይት አካሄደ።
ኮሌጁ ከአጠቃላይ ትምህርት፣ ከከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት፣ ከምዘና ማዕከል ከተውጣጡ ባለድርሻ አካላት ጋር ያደረገው ውይይት በበጀት ዓመቱ የኮሌጁን የስራ አፈጻጸም በተመለከተ ሲሆን ትኩረት የተደረገበት ደግሞ በአቅራቢያው ካሉ የመደበኛ ትምህርት ቤቶች ጋር መግባባት በተደርሶባቸውና ስለተሰሩ ስራዎች እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል። በቀጣይ መሠራት ስላለባቸው ስራዎችም በውይይቱ የተካተቱ እንደነበርም እንደዚሁ።
በውይይቱ ላይ የተገኙት ዋና ዲን አቶ አብዱልበር መሐመድ ለእንግዶቹ የእንኳን ደህና መጣችሁ መልዕክት አስተላልፈው ከዚህ በፊት በተፈጠሩት መድረኮች እርስ በርስ የመተዋወቅና ኮሌጁ ባለው አቅም በአዲሱ ካሪኩለም ለተጀመረው የሞያ ስልጠና አጋዥ የሆኑ ቁሳቁሶችን ማጋራታቸውን አስታውሰው አሁን ደግሞ በታቀደና በተጠናከረ መልኩ መስራት በጋራ ተጠቃሚ እንሚያደርግ ጠቁመዋል ።
በትስስር ስራዎችን ለመስራት በቅድሚያ በእቅዳችን ላይ አካተን የምናዘጋጃቸውና ለተግባራዊነቱም ያላሰለሰ ጥረት የምናደርግባቸው ሊሆኑ እንደሚገባም በመልዕክታቸው አካተዋል።
በተያያዘም ዲኑ ኮሌጁ ይህንን ፕሮግራም በተሻለና አጠናክሮ እንደሚሰራበትም አሳስበው በ2017ዓ.ም ከኮሌጁ ጋር በነበራቸው የትስስር ስራ አንጻር ከት/ቤቶችና ምዘና ማዕከላት ጋር የነበረውን ግንኙነት በደረጃ ማስቀመጣቸውንም ጠቁመዋል ። በዚህ ደረጃ መሠረትም ኮሌጁ እውቅና በመሥጠት የባለድርሻዎችን ተሳትፎ እንደሚያበረታታ ጨምረው ገልፀዋል።
የዕቅድ አፈጻጸሙን ሪፖርትና ለቀጣዩ የሥራ ዘመን የዕቅድ መነሻ ሃሳቡን ለውይይት ያቀረቡት የኮሌጁ ስልጠናና አካዳሚክ ጉዳዮች ም/ዲን አቶ ደመላሽ ተስፋዬ ናቸው ።
በውይይቱ በአዎንታ ከተነሱት ነጥቦች ውስጥ አንዱና ዋነኛው የሰልጣኞች ቅበላ መጨመር የጋራ ጥረት ውጤት መሆኑ ሲሆን በአሉታ ከተነሱት እና የበለጠ ትኩረት ተሰጥቶት እንዲስተካከል የተጠየቀው የምዘና ጉዳይ ይገኝበታል።
በመቀጠልም ኮሌጁ ፈቃድ ያገኘባቸውን ኢንተርፕራይዞች እና ለተጠቃሚዎች የሚያቀርቡትን ምርትና አገልግሎት ለባለድርሻ አካላቱ በማስተዋወቅ ባለድርሻ አካላቱ የሚመሯቸው የመንግስት መስሪያቤቶች የነዚህ ምርትና አገልግሎቶች ተጠቃሚ እንዲሆኑ ተጠይቋል። ኮሌጁም ተወዳዳሪ የሆኑ ምርትና አገልግሎት በተቀመጠለት የጥራት ደረጃና ጊዜ ማስረከብ የሚችል መሆኑን ተሳታፊዎች እንዲያውቁ መረጃ ተላልፏል ።
በመጨረሻም በቀረበው ሪፖርት መነሻነት ከእንጦጦ አምባ፣ ከድል በርና ከከፍተኛ ትምህርት ጥራትና አግባብነት ሐሳብ አስተያየት ቀርቦ በቀጣይ ሰልጣኝ ቅበላ ላይ እና በሙያ ትምህርት ስልጠና አሰጣጥ ላይ ተጠናክሮ ለመስራት የሁሉም ባለድርሻ አካላት ጥረትና ትብብር ሊኖር እንደሚገባ ተጠቁሟል። ለአጠቃላይ ስራውም እንዲረዳ በግልና በጋራ በሚወስዷቸው ሃላፊነቶች ላይ ባለድርሻ አካላቱ የመግባቢያ ሰነድ ተፈራርመዋል።
ኮሙኒኬሽን ቡድን
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
