fa
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

کانال بسته
1 149
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-37 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
photo content
+3

photo content
+1

ጥር 25/2018 ዓ.ም በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት የስራ አፈጻጸም ምዘና ተከናወነ፡፡ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና ኮሚሽን በመጡ የምዘና ቡድን ባለሙያዎች በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥነ ምግባርና ፀረ-ሙስና መከታተያ ዳይሬክቶሬት ተገኝተው የክፍሉን የ2018 በጀት ዓመት የመጀመሪያ 6 ወራት የዕቅድ አፈጻጸም ምዘና አከናውነዋል፡፡ የምዘና ሰነዱ በተመዛኙ ፊት  በምዘና ቡድኑ መሪ በወ/ሮ አገሪቱ ፈንታው ተከፍቶ የምዘናውን ሂደት በማብራራት ምዘናውን አከናውነዋል፡፡ ምዘናው በክፍሉ ከታቀዱ ተግባት አንፃር ያለው አፈጻጸም ምን ይመስላል?የሚለውን ያከተተ ነው፡፡

photo content

ለ2018 ዓ.ም አዲስ ገቢ ሰልጣኞች የETHIOCODERS ስልጠና ተሰጠ! 🇪🇹ጥር 22/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጂ እንደ ሀገር አቀፍ የ500 ሚሊየን የethiocoders ስልጠና ለስልጣኞች በዋናነት የክህሎት፣የስራ ዕድል ፈጠራ፣ የስራ ፈጠራ ፣ የማህበረሰብ አቀፍ አገልግሎት መስጠት ፣ ቴክኖሎጂን ለትምህርት መጠቀም እና የገጠሙ ችግሮችን ለመፍታት ይጠቅማል ። በመሆኑም ለሰልጣኞች የethiocoders ስልጠና መውሰዳቸው ስልጠናቸውን ለማጠናከርና የስራ ዕድሎችን ለማስፋት እንደሚጠቅም አውቀው በአግባቡ ሰልጥናውን መውሰድ ይገባቸውል። ሰልጣኞች ስልጠናዉን መውሰዳቸው ውጤታማ ፣ ተወዳዳሪና ስራ ፈጣሪ ዜጎችን ለማፍራት ጉልህ ድርሻ አለው። በአጠቃላይ ለ350 ሰልጣኞች የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና በአቶ ሙሉነህ ተሾመ የኢንፎርሜሽን ቴክኖሎጂ አስልጣኝ ተሰቷል። በመጨርሻም ሰልጣኞች ስልጠናውን እንዴት እንደሚወስዱና የድጋፍና ክትትል ስራ እንደሚኖር ጪምር በማስገንዘብ ስልጠናው ተጠናቋል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+2

ለስፖርት አፍቃሪ በሙሉ
ለስፖርት አፍቃሪ በሙሉ

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ። 🇪🇹 ጥር18/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ለሀያ ሁለተኛ ሳምንት ተካሄደ። በእለቱ ተሞክሮአቸውን ያካፈሉት አሰልጣኝ አቶ ነገሰ ተፈረደኝ "የሰራተኞች ሀላፊነት " በሚል ርዕሰ ጉዳይ ላይ ለኮሌጅ ማህበረሰብ ግንዛቤ ፈጥረዋል ። የሀላፊነት ስንል ተጠያቂነትንና ግዴታን በውስጡ የያዘ ሲሆን የተሰጠንን ስራ የማከናወን ግዴታ አለብን ሰርተን ካልተገኘን ተጠያቂ እንሆናለን ። እንደኮሌጅ የእኛ የሰራተኞች ሚናችን ምንድን ነው ? ሀላፊነትን መወጣት ስንል ሰልጣኞችንና የአካባቢውን ማህበረሰብን በቅን ማገልገል ፣ ከሚመለከታቸው አካላት ጋር ተግባብቶ መስራት ፣ ጥናትና ምርምርና ፈጠራ ማካሄድ እና ከመንግስት የተቀበልነውን ሀላፊነት መወጣት እንደሆኑ ተብራርተዋል ። የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ የእውቀት ሽግግር የሚደረግበት በሀገር አቀፍም ሆነ በአለም አቀፍ ደረጃ የሚሰራበት የራሱ አሰራር እንዳለው ገልፀዋል ።የኮሌጁ አካዳሚክ ዲን ፣ የማኔጅመንት እና የወርቃማው ሰኞ የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ በድርጊት መርሀ ግብር መሰረት መገኘት ተገቢም ግዴታም እንደሆነ የገለፁ ሲሆን የወርቃማው ሰኞ መድረክን የኮሌጅ ማህበረሰብ እውቀትና ልምድ እርስ በእርሱ የሚካፈልበትና ተግባብቶ የሚሰራበትን አቅም የሚያጎለብትበት እንደሆነ አስገንዝበዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 የግማሽ ዓመት የስራ አፈፃፀም ግምገማ ተካሄደ ። 🇪🇹ጥር 15/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 የግማሽ ዓመት በሀያ አራቱ አላማ ስር በተቀመጡት ተግባሮች የኮሌጅ የስራ አፈፃፀም ተገመገመ ። ኮሌጅ በ2018 ዓ/ም በስድስት ወር ውስጥ ያከናወናቸው ተግባሮችን በተጠየቀው መረጃ ላይ በዝርዝር በተደራጀ መልኩ አቅርቧል ። የአዲስ አበባ ስራና ክህሎት የግምገማ ብድን በአጠቃላይ ኮሌጅ የተሻለ አፈፃፀም ያሳየበት መሆኑን ገልፀው ስለነበረው አቀባበልና ቅንጅታዊ አሰራር ምስጋናቸውን አቅርበዋል ። የኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ በነበረው ቆይታ ደስተኛ እንደነበሩ የገለፁ ሲሆን በእያንዳንድ አላማዎች ላይ በብድኑ የተሰጡት ግብአቶች እና በደንብ መታየቱ ለቀጣይ ለላቀ ውጤት ኮሌጅ እንዲሰራ አቅም እንደሚሆነው ገልፀዋል ። በተጨማሪም ለኮሌጁ አመራሮች ፣ ዳሬክቶሬቶች እና አስተባባሪዎች ስላሳዩት ቁርጠኝነት አመስግነው ቀጣይ ብዙ እንደሚጠበቅበት መልክት አስተላልፈዋል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+1

photo content
+2

photo content
+2

ድጋፋዊ ክትትል፤ ለዘርፉ ዘላቂ ስኬትና ውጤታማነት! የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ መሐመድ የሚመሩትና የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተው የድጋፍና ክትትል ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ እያደረገ የሚገኘውን የመስክ ምልከታ አጠናክሮ ቀጥሏል። የምልከታው ዋና ዓላማ በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ረገድ የተከናወኑ ተግባራት መሬት ላይ መውረዳቸውን ለማረጋገጥ፣ መልካም ተሞክሮዎችን ለይቶ ለማስፋት እና ክፍተቶችን ለማረም መሆኑ ተገልጿል። የልዑካን ቡድኑ በምልከታው ወቅት እንደገለጸው፤ እየተከናወኑ ያሉ የክህሎት ልማት ሥራዎች የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ሊደግፉ የሚችሉ፣ ፈጠራንና ፍጥነትን ያማከሉ ናቸው። የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀብታሙ ሙሉጌታ፤ በዘርፉ የታየው የሰልጣኞች ስብጥር፣ በተለይም የሴቶች ተሳትፎ መጨመርና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ የሪፎርሙ ተጨባጭ ውጤት ነው ብለዋል። በተለይም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን 82 በመቶ ድረስ ከሥራ ጋር ማስተሳሰር የቻሉ ተቋማት መኖራቸው ሥልጠናው ከገበያው ፍላጎት ጋር መጣጣሙን የሚያሳይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ስልጠናና ተቋማት አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ በበኩላቸው፤ ቢሮው ተቋማትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ከሁዋዌ (Huawei) እና ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። ልዑካኑ በተለያዩ ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች የተገነቡ የሕፃናት ማቆያዎችን፣ የሠራተኞች የጤና ማዕከላትንና የስፖርት ማዘውተሪያዎችን ጎብኝተዋል። ይህ ተግባር የሠራተኛውን ደህንነት በማስጠበቅ ለሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈንና ለምርታማነትን መጨመር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተመልክቷል። በበጀት ዓመቱ በሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ የታየው መነቃቃትና በተለይም የሴፍቲኔት ተጠቃሚ የነበሩ ዜጎች ወደ ሥራ እንዲሰማሩ መደረጉ በጉብኝቱ ወቅት በጥንካሬ ከተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው። በመስክ ምልከታው የታዩ መልካም ተሞክሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ የሰጠ ሲሆን፤ በተለይም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የጀመሩትን የኩባንያ መፈልፈያ (Incubation Center) የመሆን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉና የፈጠራ ሥራዎችን ወደ ገበያ የማውጣት ሥራ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ጥር 9/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtT

photo content
+2

photo content
+9

ድጋፋዊ ክትትል፤ ለዘርፉ ዘላቂ ስኬትና ውጤታማነት! የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ክብርት ወ/ሮ ነቢሃ መሐመድ የሚመሩትና የፌዴራልና የክልል ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎችን ያካተተው የድጋፍና ክትትል ቡድን በአዲስ አበባ ከተማ እያደረገ የሚገኘውን የመስክ ምልከታ አጠናክሮ ቀጥሏል። የምልከታው ዋና ዓላማ በክህሎት ልማት፣ በሥራ ዕድል ፈጠራ እና በሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ረገድ የተከናወኑ ተግባራት መሬት ላይ መውረዳቸውን ለማረጋገጥ፣ መልካም ተሞክሮዎችን ለይቶ ለማስፋት እና ክፍተቶችን ለማረም መሆኑ ተገልጿል። የልዑካን ቡድኑ በምልከታው ወቅት እንደገለጸው፤ እየተከናወኑ ያሉ የክህሎት ልማት ሥራዎች የሀገሪቱን የኢኮኖሚ መዋቅራዊ ሽግግር ሊደግፉ የሚችሉ፣ ፈጠራንና ፍጥነትን ያማከሉ ናቸው። የኢፌዴሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ም/ዋና ዳይሬክተር ዶ/ር ሀብታሙ ሙሉጌታ፤ በዘርፉ የታየው የሰልጣኞች ስብጥር፣ በተለይም የሴቶች ተሳትፎ መጨመርና ለአካል ጉዳተኞች ምቹ ሁኔታ መፈጠሩ የሪፎርሙ ተጨባጭ ውጤት ነው ብለዋል። በተለይም ስልጠናቸውን ያጠናቀቁ ሰልጣኞችን 82 በመቶ ድረስ ከሥራ ጋር ማስተሳሰር የቻሉ ተቋማት መኖራቸው ሥልጠናው ከገበያው ፍላጎት ጋር መጣጣሙን የሚያሳይ ትልቅ ስኬት መሆኑን ዳይሬክተሩ አክለዋል። የአዲስ አበባ ሥራና ክህሎት ቢሮ የውጤት ተኮር ስልጠናና ተቋማት አቅም ግንባታ ዘርፍ ኃላፊ ወ/ሮ ዳግማዊት ግርማ በበኩላቸው፤ ቢሮው ተቋማትን በቴክኖሎጂ ለማዘመን ከሁዋዌ (Huawei) እና ከኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ሚኒስቴር ጋር በቅንጅት እየሠራ መሆኑን ጠቁመዋል። ልዑካኑ በተለያዩ ተቋማትና ኢንዱስትሪዎች የተገነቡ የሕፃናት ማቆያዎችን፣ የሠራተኞች የጤና ማዕከላትንና የስፖርት ማዘውተሪያዎችን ጎብኝተዋል። ይህ ተግባር የሠራተኛውን ደህንነት በማስጠበቅ ለሰላማዊ ኢንዱስትሪ ግንኙነት ለማስፈንና ለምርታማነትን መጨመር ያለው ፋይዳ ከፍተኛ መሆኑ ተመልክቷል። በበጀት ዓመቱ በሥራ ዕድል ፈጠራ መስኩ የታየው መነቃቃትና በተለይም የሴፍቲኔት ተጠቃሚ የነበሩ ዜጎች ወደ ሥራ እንዲሰማሩ መደረጉ በጉብኝቱ ወቅት በጥንካሬ ከተነሱ ዋና ዋና ጉዳዮች መካከል አንዱ ነው። በመስክ ምልከታው የታዩ መልካም ተሞክሮዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ አቅጣጫ የሰጠ ሲሆን፤ በተለይም የቴክኒክና ሙያ ተቋማት የጀመሩትን የኩባንያ መፈልፈያ (Incubation Center) የመሆን ሚና አጠናክረው እንዲቀጥሉና የፈጠራ ሥራዎችን ወደ ገበያ የማውጣት ሥራ ላይ ትኩረት እንዲያደርጉ አሳስቧል። ጥር 9/2018 ዓ.ም፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር ለወቅታዊ ትኩስ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር Official Website: mols.gov.et Facebook: https://web.facebook.com/MolsFDRE Telegram: https://t.me/FDRE_MoLSofficial TikTok: tiktok.com/@mols_official Twitter / X: twitter.com/Jobs_ሚኒስቴር WhatsApp: whatsapp.com/channel/0029VakCgcYIyPtT

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈፃፀም ምልከታ ተካሄደ ። 🇪🇹ጥር 07/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለህብረተሰቡ እየሰጠ ያለውን መጠነ ሰፊ አገልግሎት ከጥራትና ተደራሽነት ፣ ከሙያ ልህቀት ፣ አዲስ ፈጠራ ማመንጨትና ከጠንካራ የስራ በአል አንፃር የደረሰበትንና እየሰጠ ያለውን ቀልጣፋ አገልግሎት ከሚንስትር መስርያ ቤት ለመጡ የክትትልና ድጋፍ ብድን አቅርቧል ።በኮሌጅ ያለውን የአዳዲስ ሰልጣኞች ቅበላና የLIMS ምዝገባ ፣ የነባር ሰልጣኞች መረጃ አደረጃጀት ፣ የውጭ ሀገር ስራ ስምሪት፣ አጫጭር ስልጠና እና ስልጠና የሚሰጥባቸውን ወርክሾፖች አደረጃጀት ፤ በኮሌጅ ሰልጥነው የተደራጅ ኢንተርፕራይዞች በምግብ አቅርቦት እና የሳሙና ምርት ፤ በኮሌጅ የከተማ ግብርና ዘርፍ አሰልጣኞች የተሰራ የመኖ ማቀነባበሪያ ማሽንና የዶሮ መኖ ምርት ፤ ለሰራተኞች ምቹ የስራ አካባቢ ከመፍጠር የካፌ አገልግሎትና የስፖርት ማዘውተሪያዎች እና በEASE አሮጀክት እየተሰራ ያለውን የግቢው ሙሉ ለሙሉ የቀልጣፋ ኢንተርኔት ዝርጋታ ፣በቀድሞ የተፈሪ መኮንን ት/ቤት ተማሪዎች ማህበር እየተሰራ ያለውን የኮሌጅን ግቢ ምቹና ማራኪ የማድረግ ፣ የኮሌጅ ዋና መግቢያ በር ስራ እና ትልቅ የግንባታ ስራ እንደተሰሩ ተገልጾል ። በኮሌጅ ስልጠና አካ/ጉ/ም/ዲን እና ጊዚያዊ የኮሌጁ ዋና ዲን ተወካይ አቶ ደመላሽ ተስፋዬ የእንኳን ደና መጣችሁ መልክት በማስተላለፍ ኮሌጅ የ2018 የመጀመሪያ ግማሽ አመት አፈፃፀም በዝርዝር አቅርበዋል በእለቱ ለተነሱ ሀሳቦች ማብራሪያ ሰጥተዋል ። በተጨማሪም በኮሌጁ እየተተገበሩ ያሉ የኢንኩቤሽንና የበለፀጉ ቴክኖሎጂዎች ፣ ሬጅስትራል LIMS ምዝገባ ፣ የኢዝ ፕሮጀክት የስራ ቦታ ፣ የሰራተኛ ካፌና የዕስፖርት ማዘውተሪያዎች ፣ የቀድሞ ተፈሪ መኮንን ት/ቤት ተማሪዎች ማህበር ሚናና የስራ ቦታ ፣ ኤሌክትሮኒክስ እና እንደከተማ ብሎም እንደ ሀገር በኮሌጅ እየተሰጠ ያለውን የእስቴቲክስ ትምህርት ዘርፍ ስልጠና ክፍል የመስክ ጉብኝት ተካሂዷል ። በመጨረሻም የኢንድስትሪ ኤክስቴንሽን ክትትልና ድጋፍ በኮሌጅ የሚደረግላቸውን ኢንድስትሪዎችና ኢንተርፕራይዞች ጉብኝት ተደርጓል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+7