1 149
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
-1830 روز
آرشیو پست ها
1 149
Repost from N/a
ለሁሉም የTMS ሰራተኞች የ100ኛ ዓመት ክብረ ባዓል የማጠናቀቂያ የእግርኳስ የመክፈቻ ዉድድር ዛሬ ከጠዋቱ 4:00 ስለሆን በሳዓቱ ታዳሚ እንግዳ ሆነዉ እንዲገኙ በክብር ተጋብዘዋል የእስፖርት አዘጋጅ ኮሚቴዉ
1 149
የደቡብ ኮሪያው KOICA በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የሥራ ጉብኝት አደረገ ።
🇪🇹13/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
የደቡብ ኮሪያ ዓለም አቀፍ የትብብር ኤጀንሲ (KOICA) ተወካዮች በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመገኘት በ "K-POP Project Volunteers" የትብብር ፕሮጀክት ዙሪያ የመስክ ምልከታና የሥራ ውይይት አከናወኑ።
ልዑኩ በኮሌጁ በቆየበት ወቅት በተለይ በእስቴቲክስ (Esthetics) የስልጠና ዘርፍ ያለውን ዝግጁነት የተመለከተ ሲሆን፣ ከኮሌጁ ዋና ዲን ከአቶ ተሾመ ፈይሳ ጋር በፕሮጀክቱ ዝርዝር አፈጻጸም ዙሪያ መክሯል።
በውይይቱ ወቅት አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት ኮሌጁ ከመደበኛ የቴክኒክና ሙያ ስልጠናው ጎን ለጎን ተማሪዎች ዘመናዊና ዓለም አቀፋዊ እውቀቶችን እንዲቀስሙ በትኩረት እየሰራ ይገኛል። የ KOICA በጎ ፈቃደኞች ወደ ኮሌጁ መምጣታቸው በተለይ በእስቴቲክስ ዘርፍ ለሚሰለጥኑ ከ150 በላይ ተማሪዎች የባህል ልውውጥን ለማጠናከር፣ በራስ መተማመንን ለመገንባትና ዘመናዊ የአርት ክህሎቶችን ለማዳበር ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዘጠኝ ወር እቅድ አፈጻጸም የውይይት መድረክ ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር ።
🇪🇹13/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከሚመለከታቸው ባለድርሻ አካላት እና ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች ጋር የዘጠኝ ወር እቅድ አፈጻጸም የውይይት መድረክ አካሄደ።
በመድረኩ ላይ የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች፣ የአማካሪ ቦርድ አባላት እና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች በተገኙበት ባለፉት ዘጠኝ ወራት የተከናወኑ ዋና ዋና ተግባራት ቀርበው ሰፊ ውይይት ተደርጎባቸዋል።
በቀረበው ሪፖርት ላይ እንደተመለከተው ኮሌጁ በመደበኛ እና በአጭር ጊዜ ስልጠናዎች፣ በቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲሁም ከኢንዱስትሪዎች ጋር ባለው ትስስር ረገድ ውጤታማ ስራዎችን አከናውኗል። በተለይም ተማሪዎችን ለሥራና ፈጠራ ዝግጁ ከማድረግ እና የውስጥ ገቢን ከማሳደግ አኳያ የተመዘገቡ ስኬቶች በዝርዝር ቀርበዋል።
ከሲቪል ማህበረሰብ ተወካዮች እና የሚመለከታቸው አካላት በቀረበው ሪፖርት ላይ ጥልቀት ያለው ዉይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ተቋሙ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ እያሳየ ያለውን ለውጥ አድንቀዋል። በተጨማሪም ለቀጣይ ወራት አፈፃፀም ውጤታማነት የሚረዱ ሀሳቦች በስፋት የስልጠና ጥራትን ይበልጥ ማሳደግ በሚቻልባቸው መንገዶች፣ ከግል ዘርፍ እና ከታዋቂ ኢንዱስትሪዎች ጋር ያለውን አጋርነት ማጠናከር እና የኮሌጁን የረጅም ጊዜ ራዕይ ለማሳካት የሚረዱ ስትራቴጂካዊ ግብዓቶች ላይ ሰፊ ምክክር ተደርጓል።
የኮሌጁ አመራሮች በመድረኩ ላይ ለተነሱ ጥያቄዎችና አስተያየቶች ምላሽና ማብራሪያ የሰጡ ሲሆን፣ የተገኙ ስኬቶችን በማስቀጠልና የታዩ ክፍተቶችን በመሙላት የዓመቱን እቅድ በላቀ ውጤት ለማጠናቀቅ ዝግጁ መሆናቸውን ገልጸዋል።
ይህ የጋራ የምክክር መድረክ በኮሌጁ እና በአማካሪ ቦርዱ መካከል ያለውን ግልጽነት ከማሳደጉም በላይ፣ ተቋሙ በሀገር በቀል ኢኮኖሚ ግንባታ ውስጥ ያለውን ሚና ለማጎልበት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ታምኖበታል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የእግርኳስ ዉድድር እሮብ ይጀመራል
ሰላም ለእናንተ ይሁን እሮብ ሁሉም የስልጠና ዘርፍ እግርኳስ ዉድድር ስለሚጀምር ተዘጋጅተን እንምጣ
እሮብ ጠዋት :4:00 ኤሌክትሮኒክስ vs ኮንስትራክሽን
እሮብ ጠዋት 5:00 ቢዝነስ vs ቴክስታይል ጋርመንት
እሮብ ከሳዓት 9:00 አይሲቲ VS ጂኤምፍ &እስቴቲክስ
እሮብ 10:00 ሆቴልናቱሪዝም VS አስተዳደር
ማን ያሸንፋል????
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለአሰልጣኞችና ለአስተዳደር ሰራተኞች በቆራጥነትና በአገልግሎት አሰጣጥ ዙሪያ ስልጠና ተሰጠ ።
🇪🇹12/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአገልግሎት ጥራትን ለማሳደግና የተገልጋዮችን እርካታ ለማረጋገጥ ያለመ የክህሎት ማጎልበቻ ስልጠና ለአሰልጣኞችና ለአስተዳደር ሰራተኞች በአሰልጣኝ አቶ ነገሰ ተፋረደኝ ተሰጠ። ስልጠናው የአገልግሎት አሰጣጥና ፅናት በሚል ርእሰ ጉዳይ ላይ ትኩረቱን ያደረገ ሲሆን፣ የኮሌጁን የለውጥ ጉዞ ለማፋጠን ታስቦ የተዘጋጀ ነው።
ስልጠናው በዋናነት ሰራተኛው ለተገልጋዮች የሚሰጠውን ምላሽ ፈጣን፣ ግልጽና ውጤታማ ለማድረግ በሚያስችሉ ነጥቦች ላይ ያተኮረ ነበር። ከነዚህም መካከል የአገልግሎት ፅናት ማንኛውንም የስራ ጫና በመቋቋም ጥራቱን የጠበቀ አገልግሎት የመስጠት ብቃትን ማሳደግ፤ የተገልጋይ አያያዝ ተማሪዎችን፣ ወላጆችንና ሌሎች ባለድርሻ አካላትን በክብርና በታማኝነት ማገልገል ፤ የለውጥ አስተሳሰብ ተቋማዊ ግቦችን ለማሳካት የጋራ ራዕይን መሰረት በማድረግ በቆራጥነት መስራት።
በስልጠናው መድረክ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች እንደገለጹት፣ ኮሌጁ የጀመረውን የልህቀት ጉዞ ዳር ለማድረስ የሰው ኃይሉ የአስተሳሰብና የክህሎት ለውጥ ማምጣት ወሳኝ ነው። በተለይም ኮሌጁ የ100ኛ ዓመት ክብረ በዓሉን ካከበረና የጥራት ደረጃውን (ISO 21001:2018) ካረጋገጠ በኋላ፣ የላቀ አገልግሎት መስጠት አማራጭ የሌለው ተግባር መሆኑ ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በወርቃማ ሰኞ የውይይት መድረክ "የሞተ ፈረስ" (Dead Horse) በሚል ፅንሰ-ሀሳብ ላይ ያተኮረ የአመለካከት ለውጥ ስልጠና ተሰጠ ።
🇪🇹06/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየሳምንቱ ሰኞ በሚያካሂደው "ወርቃማው ሰኞ" የውይይት መድረክ ላይ፣ በስራ ሂደት ውስጥ ውጤታማነትን ስለሚገቱ አሰራሮችና የአመለካከት ለውጥ አስፈላጊነት ላይ ያተኮረ የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ለኮሌጁ ማህበረሰብ ተሰጠ።
በመድረኩ ላይ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንደገለጹት፣ "የሞተ ፈረስ" (Dead Horse Theory) የተሰኘው ፅንሰ-ሀሳብ በድርጅታዊ አሰራር ውስጥ ውጤት የማይሰጡ፣ ጊዜ ያለፈባቸውና ለተቋሙ እድገት እንቅፋት የሆኑ አሰራሮችን ወይም አስተሳሰቦችን የሚወክል ነው።
አቶ ተሾመ ፈይሳ በዝርዝር እንዳብራሩት፣ ብዙ ጊዜ በተቋማት ውስጥ አንድ ስራ ውጤት መስጠት ካቆመ (ፈረሱ ከሞተ) በኋላም ቢሆን፣ "ፈረሱን" ለመቀየር ከመሞከር ይልቅ በሚከተሉት ጊዜ ያለፈባቸው ስልቶች ለመቀጠል ይሞከራል ጠንከር ያለ አለንጋ መጠቀም (በግፊት ለመስራት መሞከር)፣ፈረሱን የቀየሩ ሰዎችን በኮሚቴ ማጥናት፣
ሌሎች ተቋማት የሞተ ፈረስን እንዴት እንደሚጋልቡ ተሞክሮ መውሰድ፣ወይም ደግሞ "ፈረሱ አልሞተም፣ የአኗኗር ዘይቤው ነው የተቀየረው" በማለት እራስን ማታለል።
እነዚህ አላስፈላጊ ልምዶች የኮሌጁን ጉዞ እንዳያደናቅፉ ሰራተኛውና አሰልጣኙ አዳዲስና ውጤታማ የሆኑ ስልቶችን በመከተል ለተገልጋዮች ፈጣን ምላሽ መስጠት እንዳለባቸው አሳስበዋል።
ይህ የውይይት መድረክ ኮሌጁ በቅርቡ የጀመረውን የሪፎርም ስራና የላቀ አገልግሎት አሰጣጥ ለማጠናከር ትልቅ ሚና እንደሚጫወት ታምኖበታል። የኮሌጁ ማህበረሰብም ጊዜ ያለፈባቸውን አሰራሮች ወደ ጎን በመተው፣ የቴክኒክና ሙያ ዘርፉን ለማዘመንና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት በቆራጥነት መስራት እንዳለባቸው ተገልጿል ።
"ወርቃማው ሰኞ" መድረክ በኮሌጁ የአሰራር ባህል ላይ ትልቅ ለውጥ እያመጣ ያለና በየሳምንቱ የተለያዩ ወቅታዊና ተቋማዊ ጉዳዮች የሚዳሰሱበት የዕውቀት መጋሪያ መድረክ ሆኖ እያገለገለ ይገኛል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
ለ፦ ለመላው የኮሌጃችን መምህራንና ሰራተኞች
ጉዳዩ፦ ስለ 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ማጠቃለያና የጋራ ግንዛቤ መፍጠር
ታሪካዊው ተፈሪ መኮንን ኮሌጅ የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል በደመቀ ሁኔታ ሲያከብር መቆየቱ ይታወቃል፡፡ የዚህ ታላቅ በዓል ማጠናቀቂያ መርሃ-ግብር በመጪው ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም በልዩ ሁኔታ እንዲከበር ዝግጅቶች በመከናወን ላይ ናቸዉ፡፡
ይህ በዓል ተቋማዊ ታሪካችንን የምናስታውስበት ብቻ ሳይሆን፣ እኛ የዛሬዎቹ ሰራተኞች ለተቋሙ ያለንን ቁርጠኝነት የምናሳይበትና የአንድነት ባህላችንን የምናጠናክርበት መድረክ ነው፡፡
በመሆኑም ሁሉም ሰራተኛ የሚከተሉትን ነጥቦች ተገንዝቦ ለበዓሉ ስኬት በጋራ እንዲቆም ጥሪ ቀርቧል፡-
የጋራ ማንነትን መገንባት፦ የኮሌጁን ታሪካዊ እሴቶችና የቆየውን የላቀ አገልግሎት የመስጠት ባህል በመረዳት፣ በበዓሉ ዕለት የጋራ ስሜት በመፍጠር ተቋማዊ ገጽታን መገንባት፤
ተመሳሳይ ግንዛቤ መያዝ፦ የበዓሉ ዓላማ ታሪካችንን ለትውልድ ማስተላለፍና የወደፊት ራዕያችንን ማሳየት መሆኑን ተረድቶ፣ በእንግዶች አቀባበልና በዝግጅቱ ሂደት ላይ ወጥ የሆነ አሰራርን መከተል፤
የባለቤትነት ስሜት፦ በዓሉ የሁላችንም እንደመሆኑ መጠን፣ እያንዳንዱ ሰራተኛ የበዓሉ አስተናጋጅና ባለቤት መሆኑን አውቆ በንቃት መሳተፍ፤
የስነ-ምግባርና የአንድነት መገለጫ፦ በዕለቱ በሚከናወኑ እንቅስቃሴዎች ሁሉ የኮሌጃችንን ስም የሚያስጠራ ጨዋነትና የአብሮነት መንፈስን ማንፀባረቅ፡፡
“ታሪካችንን እናክብር፤ ለቀጣዩ መቶ ክፍለ ዘመን በጋራ እንሰለፍ!” በሚል መሪ ቃል፣ ይህንን ታሪካዊ ዕለት በድምቀት ለመዝጋት የሁላችሁም ተሳትፎና የጋራ እንቅስቃሴ ወሳኝ ነው፡፡
ለተጨማሪ መረጃ በበዓሉ አዘጋጅ ኮሚቴ የሚወጡ ዝርዝር መመሪያዎችን እንዲከታተሉ እናሳስባለን፡፡
መልካም በዓል!
ከዝግጅት ኮሚቴው ተፈሪ መኮንን ኮሌጅ (1925 - 2025/2018 ዓ.ም)
1 149
+3
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በድል መድመቁን ቀጥሏል የንፋስ ስልክ አቻውን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸነፈ!
🇪🇹06/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
መቶኛ አመቱን እያከበረ የሚገኘው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ16ኛውን የቲቢ (TB) ሳምንት ምክንያት በማድረግ በተካሄደው ስፖርታዊ ውድድር፣ ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጥንካሬና የብቃት መገለጫ የሆነ ድንቅ ድል አስመዝግቧል። በከፍተኛ ተነሳሽነትና በደጋፊዎች ግርግር የታጀበው ይኸው ጨዋታ፣ ተፈሪ መኮንን የንፋስ ስልክ አቻውን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የድል ባለቤት ሆኗል።
ጨዋታው ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው በፉክክር የታጀበና የተመልካችን ቀልብ የሳበ ነበር። የተፈሪ መኮንን ተጫዋቾች ሜዳው ላይ ባሳዩት የተደራጀ እንቅስቃሴና ግሩም ቅንጅት፣ ተከታታይ ግቦችን ከመረብ በማሳረፍ የበላይነታቸውን አረጋግጠዋል።
የኮሌጁ ማህበረሰብ፣ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች በሙሉ በዚህ ድል ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ተፈሪ መኮንን ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በስፖርቱም ዘርፍ አሸናፊነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል!
ድል ለተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ! "እንኳን ደስ አላችሁ!"
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
+3
ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በድል መድመቁን ቀጥሏል ። የንፋስ ስልክ አቻውን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት አሸነፈ!
🇪🇹06/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
መቶኛ አመቱን እያከበረ የሚገኘው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ16ኛውን የቲቢ (TB) ሳምንት ምክንያት በማድረግ በተካሄደው ስፖርታዊ ውድድር፣ ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የጥንካሬና የብቃት መገለጫ የሆነ ድንቅ ድል አስመዝግቧል። በከፍተኛ ተነሳሽነትና በደጋፊዎች ግርግር የታጀበው ይኸው ጨዋታ፣ ተፈሪ መኮንን የንፋስ ስልክ አቻውን 3 ለ 2 በሆነ ውጤት በማሸነፍ የድል ባለቤት ሆኗል።
ጨዋታው ከመጀመሪያው እስከ መጨረሻው በፉክክር የታጀበና የተመልካችን ቀልብ የሳበ ነበር። የተፈሪ መኮንን ተጫዋቾች ሜዳው ላይ ባሳዩት የተደራጀ እንቅስቃሴና ግሩም ቅንጅት፣ ተከታታይ ግቦችን ከመረብ በማሳረፍ የበላይነታቸውን አረጋግጠዋል።
የኮሌጁ ማህበረሰብ፣ ተጫዋቾችና ደጋፊዎች በሙሉ በዚህ ድል ደስታቸውን እየገለጹ ይገኛሉ። ተፈሪ መኮንን ኮሌጅ በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ ብቻ ሳይሆን በስፖርቱም ዘርፍ አሸናፊነቱን በተግባር እያረጋገጠ ይገኛል!
ድል ለተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ! "እንኳን ደስ አላችሁ!"
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተ /ማ ጋር በመሆን የፋሲካ በዓል የማዕድ ማጋራት የአብሮነት መርሃ-ግብር አካሄደ ።
🇪🇹ሚያዝያ 01/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብ የፋሲካ በዓልን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ውስጥ ያለውን የእርስ በርስ መተሳሰብና የአብሮነት እሴት የሚያጎላ የጋራ "የማዕድ ማጋራት" መርሃ-ግብር ተካሄደ ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታይ የኮሌጁ ማህበረሰቦች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
በተጨማሪም የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ኮሌጁ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር ጋር በጋራ ያዘጋጀ መሆኑን ገልጸው ማህበሩን አመስግነዋል ። "የማዕድ ማጋራት" እና የአብሮነት መርሃ-ግብር በመካከላችን ያለውን አብሮነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክር እንደሆነ ገልፀዋል ።
በዕለቱ በኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች አማካኝነት ለሰራተኞቹ የበዓል ስጦታ የተበረከተ ሲሆን የመርሃ-ግብሩ ተሳታፊዎችም ኮሌጁ እንዲህ አይነት ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ለሰራተኞች እውቅናና ክብር መስጠቱ ለቀጣይ ስራቸው ትልቅ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 149
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተ /ማ ጋር በመሆን የረመዳን "የማዕድ ማጋራት" እና የአብሮነት መርሃ-ግብር አካሄደ ።
🇪🇹ሚያዝያ 01/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ማህበረሰብ የፋሲካ በአልን ምክንያት በማድረግ በተቋሙ ውስጥ ያለውን የእርስ በርስ መተሳሰብና የአብሮነት እሴት የሚያጎላ የጋራ "የማዕድ ማጋራት" መርሃ-ግብር ተካሄደ ።
በመርሃ-ግብሩ ላይ የመክፈቻ ንግግር ያደረጉት የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ለመላው የክርስትና እምነት ተከታዮች የኮሌጁ ሰራተኞችና ሰልጣኞች የእንኳን አደረሳችሁ መልዕክት አስተላልፈዋል።
አክለውም ይህ የማዕድ ማጋራት ፕሮግራም ኮሌጁ ከየቀድሞ የተፈሪ መኮንን ተማሪዎች ማህበር ጋር በጋራ ያዘጋጀ መሆኑን ገልጸው ማህበሩን አመስግነዋል ። "የማዕድ ማጋራት" እና የአብሮነት መርሃ-ግብር በመካከላችን ያለውን አብሮነትና ወንድማማችነት የሚያጠናክር እንደሆነ ገልፀዋል ።
በዕለቱ በኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች አማካኝነት ለሰራተኞቹ የበዓል ስጦታ የተበረከተ ሲሆን የመርሃ-ግብሩ ተሳታፊዎችም ኮሌጁ እንዲህ አይነት ባህላዊና ሃይማኖታዊ እሴቶችን በማክበር ለሰራተኞች እውቅናና ክብር መስጠቱ ለቀጣይ ስራቸው ትልቅ መነሳሳትን እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
