1 152
مشترکین
-124 ساعت
-87 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
1 152
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በ16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ድል ላስመዘገቡ የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት የምስጋና ፕሮግራም አካሄደ ።
🇪🇹05/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ “የቴክኖሎጂ ልህቀት ለሀገር ብልጽግና!” በሚል መሪ ቃል በደመቀ ሁኔታ በተከበረው 16ኛው የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ላይ ተሳትፎ ላደረጉና ከፍተኛ ውጤት ላስመዘገቡ የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት የምስጋናና የእውቅና መርሃ-ግብር አከናወነ።
ኮሌጁን በመወከል በስፖርት፣በፋሽን፣ በፈጠራና በጥናት ዘርፎች ለተሳተፉ አካላት በተዘጋጀው በዚህ ፕሮግራም ላይ የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በመክፈቻ ንግግራቸው ኮሌጁ በዘንድሮው የክህሎት ሳምንት ያስመዘገበው ውጤት የሚኮራ መሆኑን ገልጸዋል። በተለይም ኮሌጁ በስፖርቱ ዘርፍ ባሳየው የበላይነት በእግር ኳስ እና በመረብ ኳስ (ቮሊቦል)የፍፃሜ ጨዋታዎችን በማሸነፍ የሻምፒዮናነት ዋንጫዎችን በክብር ማንሳቱ ትልቅ ድል መሆኑን ጠቅሰዋል።
ከስፖርታዊ ድሎቹ ባሻገር፣ በጋርመንትና ቴክስታይል ዘርፍ በቀረበው የፋሽን ሾው እንዲሁም በጥናትና ምርምር ስራዎች ላይ ተሳትፈው ተወዳዳሪነታቸውን ላስመሰከሩ መምህራንና ሰልጣኞች ዋና ዲኑ በኮሌጁ ስም ምስጋና አቅርበዋል። “ይህ ውጤት የሚሰሩ እጆችና የሚፈጥሩ አዕምሮዎች ለሀገር ግንባታ ያላቸውን ሚና በተግባር ያሳየ መድረክ ነው” ያሉት ዋና ዲኑ፣ በቀጣይም በጋራ በመስራት የተመዘገቡ ድሎችን ማስቀጠል እንደሚገባ አጽንኦት ሰጥተዋል።
ለተከታታይ ሶስት ቀናት በቆየው በዚህ ዓውደ-ርዕይና የክህሎት ሳምንት፣ የከተማዋን የቴክኒክና ሙያ ተወዳዳሪነት የሚያሳዩ በርካታ ተግባራት በኮሌጅ ቀርቧል ። በእውቅና መርሃ-ግብሩ ማጠቃለያ ላይም ለተሳታፊዎች የሰርተፍኬት አሰጣጥ ስነ-ስርዓት የተከናወነ ሲሆን፣ በድል የተገኙ የሻምፒዮናነት ዋንጫዎችም ለኮሌጁ አመራሮች በይፋ ተረክበዋል። ይህ የእውቅና ፕሮግራም የኮሌጁን ማህበረሰብ ለቀጣይ ስራዎች የሚያነቃቃና ተቋማዊ ኩራትን የሚያጎለብት መሆኑ ተገልጿል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 152
Repost from N/a
የሶስተኛው መናኝ የኪነ ጥበብ ምሽት ልዩ የክብር እንግዳ ተዋናይት እታፈራሁ መብራቱ
በዕለተ አርብ ግንቦት 7/2018 ዓ.ም ከቀኑ 9:00 ጀምሮ
በተለመዱት ተወዳጅ ፕሮግራሞች
*ሙዚቃ
*ግጥም
* "እንደ ባል" የተሰኘ የሙሉ ጊዜ ቴአትር ይዞ በጥልቅ ዝግጅት ይጠብቃችኋል።
📌ማሳሰቢያ ሳቅ በነፃ ነው ። መሳቅ የማይችል እንዳይመጣ
📍አድራሻ፡ ከምስካዬ ህዙናን መድሀኔዓለም ቤተክርስቲያን አጠገብ ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የቴአትር አዳራሽ
የሶሻል ሚዲያ አካውንቶቻችን ይቀላቀሉ
Telegram
https://t.me/Menagn_tms
1 152
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ማጠናቀቂያ የእግር ኳስ የዋንጫ ጨዋታ ተካሄደ።
🇪🇹04/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት በደመቀ ሁኔታ ሲያከብር የቆየ ሲሆን፣ የክብረ በዓሉ ማጠናቀቂያ አካል የሆነው የዲፓርትመንቶች የእግር ኳስ ውድድር በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት ተቋጭቷል።
ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ በተደረገው አጓጊ የፍጻሜ ጨዋታ፣ የኤሌክትሮኒክስ እና የሆቴልና ቱሪዝም ዲፓርትመንት ቡድኖች ዋንጫውን ለመውሰድ ብርቱ ፉክክር አድርገዋል። በሁለቱም ወገኖች በኩል ጥንካሬ የታየበት ይህ ጨዋታ በኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።
በክብር እንግድነት የተገኙት የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ሰራተኞችና ሰልጣኞች ለቡድኖቻቸው ያላቸውን ደማቅ ድጋፍ የገለጹ ሲሆን፣ መላው የኮሌጁ ማህበረሰብ በዓሉን በስፖርታዊ ጨዋነትና በደስታ አክብረዋል።
የኮሌጁ አመራሮች እንደገለፁት ይህ ስፖርታዊ ውድድር የኮሌጁን የ100 ዓመት ረጅም የጉዞ ታሪክ ለማዘከር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም፣ ሰልጣኞች በቴክኒክና ሙያ ትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ጎን ለጎን በስፖርታዊ እንቅስቃሴ የታነጹና በመካከላቸውም ወንድማማችነትና አንድነት የጠነከረ እንዲሆን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 152
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል ማጠናቀቂያ የእግር ኳስ የዋንጫ ጨዋታ ተካሄደ።
🇪🇹04/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የተመሰረተበትን 100ኛ ዓመት በደመቀ ሁኔታ ሲያከብር የቆየ ሲሆን፣ የክብረ በዓሉ ማጠናቀቂያ አካል የሆነው የዲፓርትመንቶች የእግር ኳስ ውድድር በዛሬው ዕለት በታላቅ ድምቀት ተቋጭቷል።
ዛሬ ማክሰኞ ግንቦት 04 ቀን 2018 ዓ.ም ከረፋዱ 5፡00 ሰዓት ጀምሮ በተደረገው አጓጊ የፍጻሜ ጨዋታ፣ የኤሌክትሮኒክስ እና የሆቴልና ቱሪዝም ዲፓርትመንት ቡድኖች ዋንጫውን ለመውሰድ ብርቱ ፉክክር አድርገዋል። በሁለቱም ወገኖች በኩል ጥንካሬ የታየበት ይህ ጨዋታ በኤሌክትሮኒክስ ዲፓርትመንት 2 ለ 1 አሸናፊነት ተጠናቋል።
በክብር እንግድነት የተገኙት የኮሌጁ ከፍተኛ አመራሮች፣ አሰልጣኞች፣ ሰራተኞችና ሰልጣኞች ለቡድኖቻቸው ያላቸውን ደማቅ ድጋፍ የገለጹ ሲሆን፣ መላው የኮሌጁ ማህበረሰብ በዓሉን በስፖርታዊ ጨዋነትና በደስታ አክብረዋል።
የኮሌጁ አመራሮች እንደገለፁት ይህ ስፖርታዊ ውድድር የኮሌጁን የ100 ዓመት ረጅም የጉዞ ታሪክ ለማዘከር ታስቦ የተዘጋጀ መሆኑን ገልጸዋል። አክለውም፣ ሰልጣኞች በቴክኒክና ሙያ ትምህርታቸው ውጤታማ እንዲሆኑ ጎን ለጎን በስፖርታዊ እንቅስቃሴ የታነጹና በመካከላቸውም ወንድማማችነትና አንድነት የጠነከረ እንዲሆን ለማድረግ ትልቅ ሚና እንዳለው ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 152
ማስታወቂያ
የዋንጫ ጨዋታ
ነገ ማክሰኞ 04/09/2018 ሆቴልና ቱራዝም vs ኤሌክትሮኒክስ ከረፋዱ 5:00 ተጋብዛቹሃል ።
የ100ኛ ዓመት ማጠናቀቂያ የእስፖርት አዘጋጅ ኮሚቴ።
1 152
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የወርቃማው ሰኞ የልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሄደ ።
🇪🇹03/09/2018 ዓ.ም🇪🇹
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ መደበኛውን "የወርቃማው ሰኞ" የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ በስነ-ልቦና እና በአስተሳሰብ ለውጥ ዙሪያ ለኮሌጁ ማህበረሰብ ሰፊ ግንዛቤ ተፈጥሯል።
በዕለቱ የልምድ ልውውጥ ያደረጉት የኮሌጁ የስራ ትስስርና ጋይዳንስ ካውንስሊንግ አስተባባሪ አቶ ሙሉጌታ ጋሻው የአመለካከት ኃይል "The Power of Attitude" በሚል ርዕስ ገለጻ አቅርበዋል። አስተባባሪው በአቀራረባቸው የአመለካከት ምንነት ለስራ ስኬትና ለግል ህይወት ያለውን የማይተካ ሚና በዝርዝር አስረድተዋል።
በተጨማሪም ማንኛውም ሰው በስራው ውጤታማ ለመሆን ከክህሎት በላይ ቀና አመለካከት ሊኖረው እንደሚገባ እና ተግዳሮቶችን ወደ መልካም አጋጣሚ ለመቀየር እና ውጤታማ ስብዕናን ለመገንባት አመለካከትን እንዴት ማረም እና ማሳደግ እንደሚቻል ዝርዝር ትንታኔ ሰጥተዋል።
በመድረኩ ላይ የተሳተፉት የኮሌጁ ማህበረሰብ አባላት በቀረበው የልምድ ልውውጥ ለስራ ተነሳሽነታቸውና ለተቋማዊ ውጤታማነት ትልቅ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 152
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ለሁለተኛ ደረጃ ተማሪዎች የተዘጋጀው የሙያ ግንዛቤ ማስጨበጫ መርሃ-ግብር በስኬት ተጠናቀቀ ።
🇪🇹30/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ከ EASE ፕሮጀክት በጋራ በመተባበር ለተማሪዎች የወደፊት የሙያ አቅጣጫ አመላካች የሆነ ኮሌጁ በሚሰጣቸው የስልጠና ዘርፎች ላይ ለሁለት ቀናት የቆየ የግንዛቤ ማስጨበጫ እና የጉብኝት መርሃ ግብር በስኬት አጠናቀቀ።
በዚህ መርሃ-ግብር ላይ ከእንጦጦ አንባ እና ከድልበር ትምህርት ቤቶች የተጋበዙ የ11ኛ እና የ12ኛ ክፍል ተማሪዎች የተሳተፉ ሲሆን ዋና ዓላማውም ተማሪዎች በቴክኒክና ሙያ ኮሌጅ የሚሰጡ ስልጠናዎችን እንዲያውቁና የነገ ፍላጎታቸውን ከወዲሁ እንዲለዩ የሚያስችል መሆኑ ተገልጿል።
ተማሪዎቹ በኮሌጁ በሚገኙ የተለያዩ የስልጠና ዘርፎች እና ዘመናዊ ወርክሾፖች ላይ በመዘዋወር ምልከታ ያደረጉ ሲሆን፣ በኮሌጁ የሚገኙ የተለያዩ የቴክኒክና ሙያ አሰልጣኞችም ስለ በያንዳንዱ የሙያ ዘርፍ፣ ስለ ንድፍ ሃሳብ (Theory) እና የተግባር (Practical) በጽንሰ-ሀሳብ ላይ እየተሰጡ እንደሚገኙ ሰፊ ማብራሪያ ሰጥተዋል።
የኮሌጁ አሰልጣኞች በሰጡት ማብራሪያ፣ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ለሀገር ኢኮኖሚ ያለውን ፋይዳ እና ተማሪዎች በተግባር የታገዘ እውቀት ሲጨብጡ የሚኖራቸውን ተወዳዳሪነት አብራርተዋል።
ይህም ተማሪዎች ስለ ዘርፉ የነበራቸውን ግንዛቤ እንዲያሳድጉና ለወደፊት የትምህርት ህይወታቸው ግልጽ የሆነ መነሳሳት እንዲያገኙ አግዟል።
በጉብኝቱ ማጠቃለያ ላይ ተማሪዎቹ በሰጡት አስተያየት፣ በቆይታቸው እጅግ ደስተኛ መሆናቸውንና በወርክሾፖች ውስጥ የተመለከቱት የተግባር ስልጠና ሂደት ለሙያው ያላቸውን ፍላጎት እንዳነሳሳቸው ገልጸዋል።
ይህ ለሁለት ቀናት ሲከናወን የነበረው የሙያ ግንዛቤ ፈጠራ መርሃ-ግብር፣ በኮሌጁ, በኢዝ ፕሮጀክት እና በአካባቢው በሚገኙ ትምህርት ቤቶች መካከል ያለውን ትስስር በማጠናከር ረገድ ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወትም ተመልክቷል።
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድን
1 152
ኢስኩል ላይ ያለውን የፕሮፋይላቹን ፎቶ ለግዜውመቀየር ስለማችሉ ፐሮፋይላቹ ላይ ገብታቸሁ ፎቶዋቹ እንዲቀየርላቹ ምፈለጉ አሰልጣኞች ፎቶዋቸሁን ላኩልኝ ለ አንበሳ ባስ ተፈልጎ ነው አፍጥኑት በቴሌግራም ላኩልጅ@bkwana 1
1 152
ለተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ ባልደረቦች፣ በተለይም ለቴክኖሎጂስቶች፣ ለኳስ ተጫዋቾች እና ለቮሊቦል ቡድን ሻምፒዮናዎች፡-
የ16ኛው ክልላዊ የቴክኒክና ሙያ (TVET) ሳምንት በታላቅ ስኬት መጠናቀቁን ተከትሎ፣ ይህ ስኬት እውን እንዲሆን ላደረጋችሁት ሁሉ ላቅ ያለ ምስጋና እናቀርባለን። ይህ ድል የቴክኒክ ብቃታችንን እና የአሸናፊነት መንፈሳችንን ለአለም ያሳየበት አጋጣሚ ነው።
🏆 ለሻምፒዮናዎቻችን (የእግር ኳስ እና የቮሊቦል ቡድኖች)
በሜዳው ላይ ያሳያችሁት ብቃት እና ያመጣችሁት ድል ለኮሌጃችን ኩራት ሆኖናል።
ለእግር ኳስ ቡድናችን፦ ስለ ነበረችሁ የቡድን ስራ፣ ጽናት እና ኮሌጃችንን በክብር ስላስጠራችሁ እናመሰግናለን።
ለቮሊቦል ቡድናችን፦ ላሳያችሁት ቅልጥፍና እና "ተሸናፊነትን ላለመቀበል" የነበራችሁ ቁርጠኝነት ለሁላችንም አርአያ ሆኗል።
ውጤቱ፦ ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ የፈጠራ ሰዎች ብቻ ሳይሆን የአሸናፊ ስፖርተኞችም መፍለቂያ መሆኑን ለክልሉ አስመስክራችኋል።
🛠️ ለቴክኖሎጂስቶች እና ለመላው ሰራተኞች
አትሌቶቻችን በሜዳ ላይ ድል ሲቀዳጁ፣ እናንተ ደግሞ ከበስተጀርባ ለሳምንቱ ስኬት ሞተር ሆናችሁ አገልግላችኋል።
የቴክኒክ ብቃት፦ በኤግዚቢሽኑ ወቅት የኮሌጃችንን የፈጠራ ስራዎች በሚገባ በማቅረብ እና በቴክኖሎጂው ዘርፍ ያለንን አቅም በማሳየታችሁ ትልቅ ክብር ይገባችኋል።
የድጋፍ ስራዎች፦ መደበኛ ስራችሁን ከአሰልጣኝነት እና ከቡድን ድጋፍ ስራ ጋር አስተባብራችሁ በመስራት ለተገኘው ውጤት መሰረት ሆናችኋል።
ማጠቃለያ
16ኛው የክልል የቴክኒክና ሙያ ሳምንት ለኮሌጃችን የታሪክ ምዕራፍ ሆኖ ይኖራል። በቮሊቦል እና እግር ኳስ ጨዋታ ሜዳው ላይ ካሳያችሁት ድንቅ እንቅስቃሴ ጀምሮ በቴክኒክ አውደ-ርዕዩ ላይ እስከቀረቡት የፈጠራ ስራዎች ድረስ፣ ተፈሪ መኮንን ፖሊቴክኒክ ኮሌጅ በክህሎትም ሆነ በስፖርታዊ መንፈስ ቀዳሚ መሆኑን በድጋሚ አረጋግጣችኋል።
እንኳን ደስ አላችሁ! ለሁላችሁም ምስጋና ይግባችሁ!
"አንድ ላይ መሆን ጅምር ነው፤ አብሮ መቀጠል እድገት ነው፤ አብሮ መስራት ግን ስኬት ነው።" — ኤድዋርድ ኤቨረት ሄል
1 152
የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የዋንጫ ባለቤት ሆነ!
🇪🇹28/08/2018 ዓ.ም🇪🇹
ዛሬ ሚያዝያ 28 ቀን 2018 ዓ.ም በተካሄደው ታላቅ የእግር ኳስ የፍፃሜ ጨዋታ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ቡድን የምስራቅ ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አቻውን በማሸነፍ የሻምፒዮናነት ዋንጫውን በክብር አንስቷል።
በሁለቱ ኮሌጆች መካከል የተደረገው ይህ ፍልሚያ በከፍተኛ ፉክክርና በስፖርታዊ ጨዋነት የታጀበ ነበር። የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ስፖርተኞች ከመጀመሪያው ደቂቃ ጀምሮ ሜዳው ላይ በነበራቸው ብልጫና አስደናቂ የተቀናጀ የቡድን ስራ ተጋጣሚያቸውን 4 ለ 1 በሆነ ሰፊ የግብ ልዩነት ማሸነፍ ችለዋል።
ይህ ድል የቡድኑን ጥንካሬና በኮሌጁ ስፖርተኞች መካከል ያለውን ከፍተኛ ዝግጅት ያሳየ ሲሆን ተጫዋቾቹም በደጋፊዎቻቸው ፊት ደማቅ ድል አስመዝግበዋል።
እንደሚታወቀው የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የመረብ ኳስ ቡድን የሻምፒዮናው አሸናፊ በመሆን ዋንጫ ማንሳቱ ይታወቃል ።
የ16ኛው ከተማ አቀፍ የቴክኒክና ሙያ ሳምንት መዝጊያ ፕሮግራም ላይ የኮሌጅ የእግር ኳስ አና የመረብ ኳስ ብድኖች ዋንጫ በማንሳት ደስታውን እጥፍ ድርብ አድርገውታል ።
''የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አንድ ክፍለ ዘመን ለሀገር ግንባታ!''
ድሉ የተፈሪ መኮንን ፖሊ ኮሌጅ ነው!
መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ!
https://vm.tiktok.com
https://t.me/EntotoPtc1917
https://youtube.com/@entototms
https://www.facebook.com
ከኮሚኒኬሽን ቡድ
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
