fa
Feedback
TMPC 1917

TMPC 1917

کانال بسته
1 156
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
-67 روز
-2130 روز
آرشیو پست ها
በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአመራሮችን አቅም ለመገንባት ያለመ በኢዝ ፕሮጀክት ድጋፍ የተዘጋጀው የሊደርሺፕ ስልጠና ተጀመረ ። 🇪🇹11/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በየደረጃው ለሚገኙ ከፍተኛ እና መካከለኛ አመራሮች የተዘጋጀ የሊደርሺፕ (የአመራርነት) ስልጠና በዛሬው ዕለት መሰጠት ተጀመረ። ይህ ስልጠና በኢዝ (Ease) ፕሮጀክት ሙሉ ድጋፍ የተዘጋጀ ሲሆን ዋና ዓላማውም የተቋሙን መዋቅራዊ ብቃት ማጎልበትና የአመራሩን የአፈጻጸም አቅም በየጊዜው ማዳበር እንደሆነ ታውቋል። የኮሌጁ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ በስልጠናው መክፈቻ ላይ እንደተገለጹት ስልጠናው አመራሮቹ እራሳቸውን ወቅቱ ከሚጠይቀውና በአሁኑ ወቅት ዓለም ከደረሰበት የዘመናዊ ሊደርሺፕ (Modern Leadership) ደረጃና ሳይንሳዊ እውቀት ጋር እራሳቸውን እንዲያበቁ ለማድረግ ታስቦ የተዘጋጀ ነው። በተጨማሪም አመራሩ ተለዋዋጭ የሆኑ ተቋማዊና አካባቢያዊ ሁኔታዎችን በአግባቡ በመረዳት፣ ራሳቸውን ዘወትር ብቁና ዝግጁ እንዲያደርጉ ያስችላቸዋል ተብሏል። የዚህ ስልጠና መጀመር ኮሌጁ የጀመራቸውን የሪፎርም ሥራዎች ለማገዝ፣ የአሠራር ክፍተቶችን ለመሙላት እንዲሁም ተቋማዊ ውጤታማነትንና የአገልግሎት አሰጣጥ ጥራትን ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ ሚና እንደሚጫወት ይታመናል ። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+8

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የ“ዙንባራ” (ዋዛ) ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ ጥናትና የሙዚቃ ትርኢት ቀረበ ። 🇪🇹10/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የእስቴቲክስ (Aesthetics) የስልጠና ክፍል ምሩቅ በሆነው ሙዚቀኛና በሙዚቃ ባልደረቦቹ የተጠናው የ“ዙንባራ” ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ ጥናትና የምርምር ስራ በኮሌጁ ውስጥ በልዩ ፕሮግራም ቀረበ ። በአረብኛ ቋንቋ “ዙንባራ”በመባል የሚታወቀውና በባለቤቶቹ ማህበረሰብ ዘንድ “ዋዛ” ተብሎ የሚጠራው ይህ ጥንታዊ ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ፣ አወቃቀሩና የአጫዋች ስልቱ ምን እንደሚመስል በጥናታዊ ስራው ላይ በሰፊው ተብራርቷል። የመሳሪያው ልዩ ባህሪና አጫዋች ስልት እንደ ጥናቱ ማብራሪያ ይህንን ባህላዊ የሙዚቃ መሳሪያ በጋራ የሚጫወቱት 12 ሰዎች ሲሆኑ በጨዋታው ላይ የሚሳተፉት አስራ ሁለቱም ተጫዋቾች በግል የሚያወጡት የራሳቸው የሆነ የተለየ የድምፅ ቅኝት (Tone) ያላቸው ሲሆን፣ ለእያንዳንዱ የሙዚቃ መሳሪያም የየራሱ መጠሪያ እንዳለው ተገልጿል። በጥናቱ ላይ ትልቅ ትኩረት የተሰጠው ጉዳይ ይህንን ጥንታዊ የዜማ ስልት ከዘመናዊ የሙዚቃ መሳሪያዎች ጋር በማዋሃድ (Fusion) አዲስ የሙዚቃ ይዘት መፍጠር መቻሉ ሲሆን፣ ይህም በፕሮግራሙ ላይ በተግባር ቀርቦ ለታዳሚው ተደራሽ ሆኗል ። በዕለቱ በተዘጋጀው በዚህ ደማቅ ፕሮግራም ላይ የጥናት ውጤቱ መቅረብ ብቻ ሳይሆን፣ በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ በመሰልጠን ላይ የሚገኙ ወጣቶችም ያዘጋጇቸውን የተለያዩ የሙዚቃ ዝግጅቶች ለታዳሚው አቅርበዋል። ይህም ኮሌጁ ለባህል፣ ለጥናትና ምርምር እንዲሁም ለተግባራዊ ክህሎት የሚሰጠውን ከፍተኛ ትኩረት ያሳየ መድረክ ሆኖ አልፏል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+6

የወይዘሮ ስኂን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ አደረጉ። 🇪🇹10/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ከደሴ ከተማ በመጡት የወይዘሮ ስኂን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና የስራ ክፍል ኃላፊዎች መካከል ፍሬያማ የሆነ የስራ ላይ ልምድ ልውውጥ ተካሄደ። ይህ በሁለቱ አንጋፋ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መካከል የተደረገው የልምድ ልውውጥበተለይም በISO 21001:2018 EOMS ትግበራ እና በእስቴቲክስ (Aesthetics) የስልጠና ዘርፍ ላይ ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገ እንደነበር ታውቋል። የልምድ ልውውጥ ቡድኑ በኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጅ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ደማቅና ሞቅ ያለ አቀባበል የተደረጉላቸው ሲሆን የቡድኑ አባላት በኮሌጁ የእስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ ላይ የመስክ ምልከታና ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝቱም ወቅት ስለ ስልጠናው ሂደትና ተያያዥ አሰራሮች ሰፊ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን፣ ከአመራሮቹ ለተነሱ ጥያቄዎችም ዝርዝር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። በተጨማሪም ልዑኩ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር በሚያስችሉ በርካታ ዘርፎች ዙሪያ ሰፊ የልምድ ልውውጥ አድርጓል። ከእነዚህም መካከልበተቋማት ልማት (Institutional Development)፣በአካዳሚክ ጉዳዮች (Academic Affairs)፣ በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን (Industry Extension) አቅርቦት እና በሌሎች ቁልፍ የስራ ክፍሎች ዙሪያ የሃሳብና የልምድ ልውውጥ ተደርጓል። ይህ መሰሉ በፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መካከል የሚደረግ የልምድ ልውውጥ፣ በሀገሪቱ ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራት ለማሳደግ፣ መልካም ተሞክሮዎችን ለመቀመርና የተቋማትን የአሰራር ብቃት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በውይይቱ ወቅት ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+2

የወይዘሮ ስኂን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮች በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የስራ ልምድ ልውውጥ አደረጉ። 🇪🇹10/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እና ከደሴ ከተማ በመጡት የወይዘሮ ስኂን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ አመራሮችና የስራ ክፍል ኃላፊዎች መካከል ፍሬያማ የሆነ የስራ ላይ ልምድ ልውውጥ ተካሄደ። ይህ በሁለቱ አንጋፋ የቴክኒክና ሙያ ተቋማት መካከል የተደረገው የልምድ ልውውጥበተለይም በISO 21001:2018 EOMS ትግበራ እና በእስቴቲክስ (Aesthetics) የስልጠና ዘርፍ ላይ ይበልጥ ትኩረቱን ያደረገ እንደነበር ታውቋል። የልምድ ልውውጥ ቡድኑ በኮሌጁ ሲደርስ በኮሌጅ ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ ደማቅና ሞቅ ያለ አቀባበል የተደረጉላቸው ሲሆን የቡድኑ አባላት በኮሌጁ የእስቴቲክስ የስልጠና ዘርፍ ላይ የመስክ ምልከታና ጉብኝት አድርገዋል። በጉብኝቱም ወቅት ስለ ስልጠናው ሂደትና ተያያዥ አሰራሮች ሰፊ ገለጻ የተደረገላቸው ሲሆን፣ ከአመራሮቹ ለተነሱ ጥያቄዎችም ዝርዝር ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቷል። በተጨማሪም ልዑኩ በሁለቱ ተቋማት መካከል ያለውን ግንኙነት ይበልጥ ለማጠናከር በሚያስችሉ በርካታ ዘርፎች ዙሪያ ሰፊ የልምድ ልውውጥ አድርጓል። ከእነዚህም መካከልበተቋማት ልማት (Institutional Development)፣በአካዳሚክ ጉዳዮች (Academic Affairs)፣ በኢንደስትሪ ኤክስቴንሽን (Industry Extension) አቅርቦት እና በሌሎች ቁልፍ የስራ ክፍሎች ዙሪያ የሃሳብና የልምድ ልውውጥ ተደርጓል። ይህ መሰሉ በፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆች መካከል የሚደረግ የልምድ ልውውጥ፣ በሀገሪቱ ያለውን የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ጥራት ለማሳደግ፣ መልካም ተሞክሮዎችን ለመቀመርና የተቋማትን የአሰራር ብቃት ወደ ላቀ ደረጃ ለማሸጋገር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው በውይይቱ ወቅት ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+7

photo content
+3

በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ የአፍሪካን እጣፈንታ የዳሰሰ “የወርቃማው ሰኞ” የልምድ ልውውጥ መድረክ ተካሄደ። 🇪🇹10/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 በተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ ዘንድሮ የሚከበረውን የ100ኛ ዓመት የምስረታ በዓል (ሴንተነሪ) እና ተያያዥ ሀገራዊና አህጉራዊ ኩነቶችን በማስመለከት፣ ተቋማዊ ባህል የሆነው መደበኛው “የወርቃማው ሰኞ” የጋራ የልምድ ልውውጥ መድረክ ዛሬ በደመቀ ሁኔታ ተካሂዷል። የዕለቱ የውይይት መድረክ “አፍሪካ፡ የትላንት፣ የዛሬና የነገ እጣፈንታዎች”በሚል አህጉራዊና ወቅታዊ ርዕሰ-ጉዳይ ላይ ያተኮረ ሲሆን፣ ለኮሌጁ አጠቃላይ ማህበረሰብ ሰፊ ግንዛቤ የተፈጠረበት ውይይት ተካሂዷል። በመድረኩ ላይ ሰፊ ማብራሪያና የልምድ ልውውጥ ያደረጉት የኮሌጁ የከተማ ግብርና ስልጠና ዘርፍ አሰልጣኝ አቶ ካሳዬ ኢሞሻ ባቀረቡት ጥናታዊ ማብራሪያ፣ አፍሪካ በትላንትናው ታሪኳ የገጠሟትን ተግዳሮቶች በማንሳት፣ በአሁኑ ወቅት እየታዩ ስላሉት የሚከተሉት መሰረታዊ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ትንተና ሰጥተዋል፦የዘመናዊ ቀኝ ግዛት (Neo-colonialism)ስልቶችና በአህጉሪቱ ላይ እያሳደሩ ያሉት ተጽዕኖ፣በውጭ ንግድ ላይ የሚጣሉ የዋጋ ቀረጥ ጭማሪዎች እና የገበያ መዛባቶች፣ የሀገር ውስጥ አምራቾችን አቅም የሚያዳክመው የዳምፒንግ (Damping)ወይም ጥራታቸውን ያልጠበቁ ምርቶችን በርካሽ ዋጋ ወደ ገበያ የማስገባት የንግድ ሴራ እና ተያያዥ ኢኮኖሚያዊ ጉዳዮች ግንዛቤ የፈጠሩ ሲሆን ሲያጠቃልሉም፣ አፍሪካ ያሉባትን ተግዳሮቶች ተቋቁማ ልታድግ የምትችልበትን ብሩህ ተስፋ አመላክተዋል። በተለይም አህጉሪቱ ያላትን እምቅ የተፈጥሮ ሀብት፣ የሰው ኃይል እና የወደፊት መልካም አጋጣሚዎችን በአግባቡ መጠቀም ከተቻለ፣ አፍሪካ የነገ እጣፈንታዋ እጅግ አስተማማኝና ስኬታማ እንደሚሆን አስገንዝበዋል። በመጨረሻም የመድረኩ ተሳታፊዎች በቀረበው ሃሳብ ላይ ሰፊ ውይይት ያደረጉ ሲሆን፣ ይህ መሰሉ የ"ወርቃማው ሰኞ" መድረክ አሰልጣኞችና ሰራተኞች ከሙያዊ ክህሎት ባለፈ፣ አህጉራዊና አለምአቀፋዊ እውቀታቸውን እንዲያሳድጉ ትልቅ ሚና እየተጫወተ እንደሚገኝ ተገልጿል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፤ "ማርሽ ቀያሪው" የክህሎት ማዕከልና የስውር ጸጋዎች መፍለቂያ ። 🇪🇹10/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ (TMS) ባለፉት መቶ ዓመታት ያካበታቸውን ስውር ጸጋዎች ከአዲሱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር "ማርሽ ቀያሪ" ስትራቴጂ ጋር በማሰናሰል፣ ዘመኑ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂና የጥበብ ሽግግር እያረጋገጠ መሆኑን ገለጸ። የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንዳሉት፣ ተቋሙ ከሕንፃና ከመማሪያ ክፍል ባለፈ ለሀገር የሚተርፍ ያልተነካ "ኢንተለክቿል ካፒታል" (Intellectual Capital) ባለቤት ነው። 1. "ስውር ጸጋዎች" እና የታሪክ ዘረ-መል (DNA) ተቋሙ ሚያዝያ 1917 ዓ.ም ሲመሰረት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመጡ 50 ተማሪዎች የጀመረ ቢሆንም፣ ዛሬ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል። "መቶ ዓመት መቆየት ለሞት መቅረብ ሳይሆን፣ ያልተገደበ የተግባር እውቀት (Tacit Knowledge) ማከማቻ መሆን ነው" የሚሉት አቶ ተሾመ፤ ይህንን እውቀት "Knowledge Exploit" በማድረግ ለዘመናዊው ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተጠቀሙበት መሆኑን ያስረዳሉ። ይህም በስትራቴጂው ከተቀመጠው "የክህሎትና የቴክኖሎጂ ባንክ" DNA ጋር ፍጹም የተጣጣመ መሆኑ ተመልክቷል። 2. የኤስቴቲክስ (Aesthetics) DNA፤ የብቃት ሞኖፖሊ እንደ ሀገር በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የኪነ ጥበብ፣ ሙዚቃና ቴአትር ስልጠና የሚሰጥበት ብቸኛው ተቋም ተፈሪ መኮንን ነው። ይህ ልዩ ጸጋ ተቋሙን በስትራቴጂው ላይ እንደተቀመጠው "የመልማት ፀጋንና የአካባቢዎችን አንፃራዊ ጠቀሜታ መሠረት ያደረገ ስልጠና" DNA ተምሳሌት አድርጎታል። ከአፋር፣ ከድሬዳዋና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚመጡ ሰልጣኞች የጥበብና የቴክኖሎጂ ሚዛኑን የጠበቀ ክህሎት እንዲጨብጡ በማድረግ ተቋሙ የ"ሴንተር ኦፍ ኤክሰለንስ" ደረጃውን አረጋግጧል። 3. ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና የላይፕዚግ ድል የኮሌጁ ብቃት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን በዓለም አቀፍ መድረክ መታየት መጀመሩ ተገልጿል። በጀርመኑ የላይፕዚግ (Leipzig) የቅርጻ ቅርጽ ውድድር ላይ የኮሌጁ ተማሪዎች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ማሸነፋቸው፣ ተቋሙ በስትራቴጂው ከተቀመጡት 34 DNAs አንዱ የሆነውን "ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት" (Global Competitiveness) በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን ያሳያል። 4. ፐብሊክ ኢንተርፕርነርሽፕ (Public Entrepreneurship) እና የPPP ራዕይ ተቋሙ ከመንግሥት በጀት ጥገኝነት በመውጣት ራሱን የማብቃት ስልታዊ ለውጥ እያደረገ ይገኛል። ጠንካራው የቀድሞ ተማሪዎች ማኅበር (Alumni) በራሱ አቅም ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ የG+3 ሕንፃ ግንባታ መጀመሩ፣ በስትራቴጂው የተመለከተውን "ፐብሊክ ኢንተርፕርነርሽፕ" DNA በተጨባጭ የገለጸ እርምጃ ነው። በተጨማሪም፣ በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛው ሊሆን የሚችል "አርት ሬዝደንሲ" (Art Residency) ለመገንባት የታቀደው ግዙፍ ፕሮጀክት፣ በ"መንግሥትና የግል አጋርነት" (PPP) DNA አማካኝነት ተቋሙን ወደ ላቀ የገቢ ምንጭና የኢኖቬሽን ማዕከልነት የሚያሸጋግር "ማርሽ ቀያሪ" ራዕይ መሆኑ ተጠቁሟል። ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንደ እነ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስና ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ያሉ ታላላቅ ዜጎችን ያፈራ ተቋም እንደመሆኑ፣ አዲሱ ሪፎርም ይህንን የታሪክ ክብር ከዘመናዊው የፋብሪኬሽንና የዲጂታል አሠራር ጋር በማሰናሰል፣ ተቋሙን ለቀጣዩ አንድ ክፍለ ዘመን በድፍረት እያዘጋጀው ይገኛል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+5

photo content
+5

photo content

ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ፤ "ማርሽ ቀያሪው" የክህሎት ማዕከልና የስውር ጸጋዎች መፍለቂያ ። 🇪🇹10/09/2018 ዓ.ም🇪🇹 የተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ (TMS) ባለፉት መቶ ዓመታት ያካበታቸውን ስውር ጸጋዎች ከአዲሱ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር "ማርሽ ቀያሪ" ስትራቴጂ ጋር በማሰናሰል፣ ዘመኑ የሚጠይቀውን የቴክኖሎጂና የጥበብ ሽግግር እያረጋገጠ መሆኑን ገለጸ። የኮሌጁ ዋና ዲን አቶ ተሾመ ፈይሳ እንዳሉት፣ ተቋሙ ከሕንፃና ከመማሪያ ክፍል ባለፈ ለሀገር የሚተርፍ ያልተነካ "ኢንተለክቿል ካፒታል" (Intellectual Capital) ባለቤት ነው። 1. "ስውር ጸጋዎች" እና የታሪክ ዘረ-መል (DNA) ተቋሙ ሚያዝያ 1917 ዓ.ም ሲመሰረት ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች በመጡ 50 ተማሪዎች የጀመረ ቢሆንም፣ ዛሬ ላይ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ዜጎችን በማሰልጠን ላይ ይገኛል። "መቶ ዓመት መቆየት ለሞት መቅረብ ሳይሆን፣ ያልተገደበ የተግባር እውቀት (Tacit Knowledge) ማከማቻ መሆን ነው" የሚሉት አቶ ተሾመ፤ ይህንን እውቀት "Knowledge Exploit" በማድረግ ለዘመናዊው ቴክኖሎጂ ሽግግር እየተጠቀሙበት መሆኑን ያስረዳሉ። ይህም በስትራቴጂው ከተቀመጠው "የክህሎትና የቴክኖሎጂ ባንክ" DNA ጋር ፍጹም የተጣጣመ መሆኑ ተመልክቷል። 2. የኤስቴቲክስ (Aesthetics) DNA፤ የብቃት ሞኖፖሊ እንደ ሀገር በቴክኒክና ሙያ ዘርፍ የኪነ ጥበብ፣ ሙዚቃና ቴአትር ስልጠና የሚሰጥበት ብቸኛው ተቋም ተፈሪ መኮንን ነው። ይህ ልዩ ጸጋ ተቋሙን በስትራቴጂው ላይ እንደተቀመጠው "የመልማት ፀጋንና የአካባቢዎችን አንፃራዊ ጠቀሜታ መሠረት ያደረገ ስልጠና" DNA ተምሳሌት አድርጎታል። ከአፋር፣ ከድሬዳዋና ከተለያዩ የሀገሪቱ ክፍሎች የሚመጡ ሰልጣኞች የጥበብና የቴክኖሎጂ ሚዛኑን የጠበቀ ክህሎት እንዲጨብጡ በማድረግ ተቋሙ የ"ሴንተር ኦፍ ኤክሰለንስ" ደረጃውን አረጋግጧል። 3. ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነትና የላይፕዚግ ድል የኮሌጁ ብቃት በአገር ውስጥ ብቻ ሳይወሰን በዓለም አቀፍ መድረክ መታየት መጀመሩ ተገልጿል። በጀርመኑ የላይፕዚግ (Leipzig) የቅርጻ ቅርጽ ውድድር ላይ የኮሌጁ ተማሪዎች ከአንደኛ እስከ አራተኛ ያለውን ደረጃ በመያዝ ማሸነፋቸው፣ ተቋሙ በስትራቴጂው ከተቀመጡት 34 DNAs አንዱ የሆነውን "ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነት" (Global Competitiveness) በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን ያሳያል። 4. ፐብሊክ ኢንተርፕርነርሽፕ (Public Entrepreneurship) እና የPPP ራዕይ ተቋሙ ከመንግሥት በጀት ጥገኝነት በመውጣት ራሱን የማብቃት ስልታዊ ለውጥ እያደረገ ይገኛል። ጠንካራው የቀድሞ ተማሪዎች ማኅበር (Alumni) በራሱ አቅም ከ70 ሚሊዮን ብር በላይ በማሰባሰብ የG+3 ሕንፃ ግንባታ መጀመሩ፣ በስትራቴጂው የተመለከተውን "ፐብሊክ ኢንተርፕርነርሽፕ" DNA በተጨባጭ የገለጸ እርምጃ ነው። በተጨማሪም፣ በምስራቅ አፍሪካ ብቸኛው ሊሆን የሚችል "አርት ሬዝደንሲ" (Art Residency) ለመገንባት የታቀደው ግዙፍ ፕሮጀክት፣ በ"መንግሥትና የግል አጋርነት" (PPP) DNA አማካኝነት ተቋሙን ወደ ላቀ የገቢ ምንጭና የኢኖቬሽን ማዕከልነት የሚያሸጋግር "ማርሽ ቀያሪ" ራዕይ መሆኑ ተጠቁሟል። ተፈሪ መኮንን ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጅ እንደ እነ ፕሬዝዳንት ግርማ ወልደጊዮርጊስና ደራሲ ስብሐት ገብረእግዚአብሔር ያሉ ታላላቅ ዜጎችን ያፈራ ተቋም እንደመሆኑ፣ አዲሱ ሪፎርም ይህንን የታሪክ ክብር ከዘመናዊው የፋብሪኬሽንና የዲጂታል አሠራር ጋር በማሰናሰል፣ ተቋሙን ለቀጣዩ አንድ ክፍለ ዘመን በድፍረት እያዘጋጀው ይገኛል። መረጃዎችን በፍጥነት ለማግኘት ማሰፈንጠሪያውን ይጫኑ! https://vm.tiktok.com https://t.me/EntotoPtc1917 https://youtube.com/@entototms https://www.facebook.com ከኮሚኒኬሽን ቡድን

photo content
+4

የስልጠና ተሳታፊዎች.docx0.55 KB

photo content
+1

የስልጠና ተሳታፊዎች.docx0.55 KB