fa
Feedback
Ethiopian Public Service University

Ethiopian Public Service University

رفتن به کانال در Telegram

ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

نمایش بیشتر

📈 تحلیل کانال تلگرام Ethiopian Public Service University

کانال Ethiopian Public Service University (@epsutelegram) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 12 734 مشترک است و جایگاه 15 756 را در دسته آموزش و رتبه 2 642 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 12 734 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 11 ژوئیه, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر 106 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر 3 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 34.72% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 16.17% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 4 419 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 2 058 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 27 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

نویسنده این فضا را محل بیان دیدگاه‌های شخصی توصیف می‌کند:
ፐብሊክ አገልግሎት ልህቀት በተግባር ተኮር እውቀት

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 12 ژوئیه, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته آموزش تبدیل کرده‌اند.

12 734
مشترکین
+324 ساعت
+207 روز
+10630 روز
آرشیو پست ها
በኢፐሰዩ የምግብ አቅርቦት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰራ ነው የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ በተማሪዎች አገልግሎት ዲን የሚሰጠውን የተማሪዎች የምግብ አቅርቦት ጥራት ለማሻሻል፣ ከሚያዝያ ወር 2018 ዓ/ም ጀምሮ በውስጥ አቅም እንጀራ ጋግሮ ለተማሪዎች ማቅረብ መጀመሩ ተገለጸ፡፡ የተማሪዎች አገልግሎት ዲን ወ/ሮ ሙሉዓለም አዲሱ በውስጥ አቅም በተገነባው የእንጀራ መጋገሪያ ማዕከል ለተማሪዎች አቅርቦት መጀመሩን አስመልክተው እንደተናገሩት፣ ዩኒቨርሲቲው ላለፉት ሰላሳ ዓመታት በነበረው አሰራር ለተማሪዎቹ የምግብ አቅርቦት ሙሉ በሙሉ ከውጪ አቅራቢዎች በመሆኑ፣ የሚያጋጥመውን የጥራት ጉድለት ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ሆኖ መቆየቱን አስታውሰው፣ “አሁን ግን፣ ጥሬ እቃውን ገዝተን በራሳችን አቅም ስለምናዘጋጅ በምናደርገው ቅርብ ክትትል ጥራቱን ማስጠበቅ ችለናል፡፡” ብለዋል፡፡ አስከትለውም በዩኒቨርሲቲው የአመራር ለውጥ ከተደረገ ወዲህ፣ ለተማሪዎች እና ለሰልጣኞች ያለውን የምግብ አቅርቦት ለማሻሻል እንዲቻል፣ ኢንተርፕራይ የማቋቋም ስራ እየተከናወነ ሲሆን፣ ግንባታው ተጠናቆ ስራ የጀመረውን የእንጀራ መጋገሪያ ማእከል ጨምሮ፣ የዳቦ መጋገሪያ ግንባታ ተጠናቆ የመጨረሻ ምእራፍ ላይ መድረሱን፣ ለእህል ወፍጮ ቤት ግንባታው ተጠናቆ የወፍጮ ገጠማው ስራ በሂደት ላይ መሆኑን እና ሽሮ፣ በርበሬ፣ ሚጥሚጣ እና የመሳሰሰሉትን የምግብ ግብዓቶች አቀነባብሮ ጥራቱን የጠበቀ የምግብ ግብዓት ወጪ ቆጣቢ በሆነ መንገድ ለማቅረብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በተጨማሪም፣ ቀደም ባለው አሰራር በሚፈጠረው የምግብ ጥራት ጉድለት ከተማሪዎች እና ከሰልጣኞች ከፍተኛ ቅሬታ ሲቀርብ የነበረ መሆኑን ገልጸው፣ “አሁን ላይ በውስጥ አቅም የምግብ ግብዓቶችን ማቀነባበር መጀመራችን በሂደት ቅሬታውን ሊቀርፍ የሚችል ተግባር ነው፡፡” ሲሉ ተናግረዋል፡፡ የእንጀራ መጋገሪያ ማዕከሉ ዩኒቨርሲቲው ለወደፊቱ የሚኖረውን የተማሪ እና ሰልጣኖች ቁጥር ታሳቢ በማድረግ 40 (አርባ) የሚደርሱ ምጣዶች የተገጠሙለት ሲሆን፣ የመጋገሪያ ማዕከሉ የማምረት አቅም ከፍተኛ በመሆኑ፣ ኢንተርፕራይዙን የማቋቋም ሂደቱ ሲጠናቀቅ ከውስጥ አቅርቦት አልፎ፣ የአካባቢው ማህበረሰብም ተጠቃሚ ሊያደርግ የሚችል መሆኑ ተገልጿል፡፡ ማዕከሉ አገልግሎት መጀመሩን አስመልክቶ በተዘጋጀው በመርሃ-ግብር ላይ የዩኒቨርሲቲው የአስተዳደር እና ልማት ዘርፍ ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ተሸመ ዱላ እና የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ምትኩ አዲሱ ተገኝተዋል፡፡

በኢፐሰዩ የምግብ አቅርቦት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰራ ነው
+4
በኢፐሰዩ የምግብ አቅርቦት ጥራትን ለማሻሻል እየተሰራ ነው

EPSU and FUSE Forge Institutional Partnership to Advance Public Sector Capacity Building A formal strategic dialogue on partnership was convened between representatives of the Ethiopian Public Service University (EPSU) and a delegation from Florida University Southeast (FUSE) on 20 April 2026 at EPSU's campus in Addis Ababa. Dr. Dereje Teklemaram, Director of Internationalization and Partnership at EPSU, welcomed the FUSE delegation and outlined EPSU's post-reform strategic orientation. He emphasized that EPSU has aligned all activities with national public sector competency objectives, transitioning into an applied, autonomous university under the motto "We are for the public sector." He also explained that, as part of this transformation, EPSU has revised curricula, admitted new undergraduates, and established two new colleges. EPSU now comprises five colleges, one school, and one training institute, which it aspires to accredit internationally as a capacity-building hub for the Horn of Africa. Following his presentation, representatives from both institutions detailed their collaborative interests. Dr. Dereje Besufekad, Vice President of Florida University Southeast (FUSE), presented FUSE as a fully online, globally accredited institution based in Florida, USA, specializing in applied professional training within expanding business fields. FUSE comprises four graduate-level schools: the School of Information Technology (SIT), the School of Business Valuation, Investment and Real Estate (SBVIRE), the School of Management and Leadership (SML), and the School of Professional Studies (SPS). Dr. Dereje Besufekad highlighted FUSE's accreditation by the Project Management Institute (PMI) and its provision of Project Management Professional (PMP) preparation courses. He also noted FUSE's ongoing capacity-building work with Ethiopian state-owned enterprises. Both sides affirmed a strong mutual interest in pursuing joint academic programming, cooperative research, training initiatives, and consultancy services.

EPSU and FUSE Forge Institutional Partnership to Advance Public Sector Capacity Building
+1
EPSU and FUSE Forge Institutional Partnership to Advance Public Sector Capacity Building

በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ “ለተቀናጀ እና ዘላቂ ውጤት ትብብርን ማጠናከር” በሚል መሪ ቃል፣ በምርምር ፖሊሲ ክለሳ እና ፍኖተ ካርታ ረቂቅ ሰነድ ላይ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ሚያዝያ 15 ቀን 2018 ዓ/ም በህዳሴ አዳራሽ አካሄደ፡፡ በምክክር መድረኩ መክፈቻ የዩኒቨርሲቲው ፕሬዝዳንት ንጉስ ታደሰ (ዶ/ር) ባስተላለፉት የእንኳን ደህና መጣችሁ መልእክት “በአገር አቀፍ ደረጃ በተለይም በተግባር ዩኒቨርሲቲዎች፣ የምርምር ስራዎችን ለመስራት፣ የተጠቃሚውን ችግር ለይቶ ማወቅ ተቀዳሚ ተግባር ነው ብለዋል፡፡” ይህንንም ለማድረግ በምርምሩ የሚጠቀሙ አካላትን ከረቂቅ ፖሊሲው ዝግጅት ጀምሮ በማሳተፍ መረጃ መሰብሰብ አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ አስከትለውም “በየዘርፉ ያለውን ነባራዊ ችግር ከእኛ ይልቅ እናንተ ስለምትረዱት እና ሰነዱ የእኛ ብቻ ሳይሆን የእናንተም ጭምር መሆኑን ተረድታችሁ የምትሰጡት ሀሳብ እና አስተያየት ለረቂቅ ሰነዱ መዳበር ከፍተኛ አስተዋጽኦ እንደሚኖረው መገንዘብ አስፈላጊ ነው፡፡” በማለት በምክክር መድረኩ የተገኙት የአጋር የባለድርሻ አካላት ተወካዮችን በንቃት እንዲሳተፉ ጥሪያቸውን አስተላልፈዋል፡፡ የተዘጋጀውን የምርምር ፖሊሲ ረቂቅ እና የፍኖተ ካርታ ሰነዶች ለተሳታፊዎች ያቀረቡት የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት የሆኑት ዶ/ር ምትኩ አዲሱ ሲሆኑ፣ የምርምር ፖሊሲው ክለሳ የሚካሄደው የዩኒቨርሲቲውን አዲስ ተልእኮ መሰረት አድርጎ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በማስከተልም የምርምር ፖሊሲ ክለሳው እና የምርምር ፍኖተ ካርታው ዩኒቨርሲቲው የሚያካሂደው የለውጥ ስራ አካል መሆኑን አስታውሰው፣ “እየተከለሰ ያለው የምርምር ፖሊሲ ችግር ፈቺ፣ ልማቱን እና ፐብሊክ ሰርቪሱን የሚደግፍ ምርምር እንዲሆን እንፈልጋለን፤ ስለዚህ በቀጣይ የምርምር ፕሮፖዛል ስንቀርጽ እነዚህን ጉዳዮች ታሳቢ አድርገን መሆን ይኖርበታል፡፡” ብለዋል፡፡ በመቀጠልም በተዘጋጀው የምርምር ፖሊሲ ረቂቅ እና የፍኖተ ካርታ ሰነዶች ላይ ሰፊ ውይይት የተካሄደባቸው ሲሆን፣ ተሳታፊዎች የምርምር ፖሊሲው እና ፍኖተ ካርታው ለተቋማቸው ከሚሰጠው ጠቀሜታ አኳያ ሀሳብ እና አስተያየታቸውን ሰንዝረዋል፤ ከተሳታፊዎቹ ለቀረቡት ጥያቄዎችና አስተያየቶችም የአካዳሚክ ጉዳዮች ምክትል ፕሬዝደንቱ ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንቱ ዶ/ር ምትኩ ምላሽ እና ማብራሪያ ሰጥቷል፡፡ በምክክር መድረኩ ላይ የተገኙት ተሳታፊዎች ከፌደራል መስሪያ ቤቶች፣ ከአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ቢሮዎች እና ከኦሮሚያ ክልላዊ መንግስት ቢሮዎች የመጡ ተወካዮች እንዲሁም የዩኒቨርሲቲው መምህራንና ተመራማሪዎች መሆናቸው ታውቋል፡፡ በመጨረሻም ዶ/ር አማኑኤል ኩሲያ ተሳታፊዎቹ በውይይቱ ላይ ላሳዩት ንቁ ተሳትፎ አመስግነው፣ የተሰጡት ሀሳቦች እና አስተያየቶች ለሰነዱ መዳበር አስፈላጊ እና እጅግ ጠቃሚ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡

በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ
+3
በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የባለድርሻ አካላት የምክክር መድረክ ተካሄደ

በኢፐሰዩ ለቦንጋ ከተማ ፕላን ትግበራ የተካሄደው የጥናት ሪፖርት ተገመገመ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ዘርፍ ፣ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልላዊ መንግስት እና የካፋ ዞን መቀመጫ የሆነችውን፣ የቦንጋ ከተማን ፕላን ለማዘጋጀት ከከተማ አስተዳደሩ ጋር በገባው ውል መሰረት፣ በተደራጀው የጥናት ቡድን የተዘጋጀውን የመጀመሪያ ደረጃ የጥናት ሪፖርት በዩኒቨርሲቲው የስልጠና ማዕከል ሚያዝያ 13 ቀን 2018 ዓ/ም ገመገመ፡፡ በጥናት ግምገማው መክፈቻ ላይ የተገኙት የዩኒቨርሲቲው የምርምር እና የቴክኖሎጂ ሽግግር ምክትል ፕሬዝዳንት ዶ/ር ምትኩ አዲሱ፣ ዩኒቨርሲቲው በሪፎርም ስራ ላይ ከመሆኑ አንጻር፣ ያለውን ተደራራቢ የስራ ጫና ተቋቁመው በመስክ ስራ ላሳዩት ትጋት የጥናት ቡድኑን አባላት አመስግነው መርሃ ግብሩን በይፋ አስጀምረዋል፡፡ የጥናት ቡድኑ ከከተማ ልማት ኮሌጅ የተውጣጡ 16 ባለሙያዎችን ያቀፈ ሲሆን፣ የቀረቡት የጥናት ሰነዶችም በ11 የሙያ መስኮች ላይ የተካሄዱ ናቸው፡፡ በመጀመሪያ ዙር በተደረገው የግምገማ መርሀ-ግብር የሪጅናል እና ፕሪ-ኧርባን ጥናት በዶ/ር ሙሉጌታ ወርቁ፣ የስነ ህዝብ እና ማህበረሰብ ጥናት በአቶ ጥበቡ ጌትዬ ፣ የኢኮኖሚ ጥናት በወ/ሪት መንበረ በሻዬ ፣ የከተማ ፋይናንስ እና አመራር ጥናት በዶ/ር አብርሀም ካሳ እና የከተማ ቤቶች ጥናት ደግሞ በአቶ አሰፋ ቢተው ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸዋል፣ ሀሳብ እና አስተያየትም ተሰጥባቸዋል፡፡ እንዲሁም ቀጥሎ በነበረው መርሃ ግብር፣ የጂኦሎጂካል እና ኢንቫይሮንሜንታል ጥናት በአቶ ታመነ መንግስቱ፣ የትራንስፖርት እና ሞቢሊቲ ጥናት በአቶ ጊዮርጊስ ጎዳል፣ የመሬት አጠቃቀም ጥናት በአቶ መንግስቱ መኮንን እና በአቶ ክፍሌ ታደሰ፣ የመሰረተ-ልማት ጥናት በአቶ ዘለቀ ላረንጎ እንዲሁም የአጎራባች ልማት ጥናት በዶ/ር ልሳነወርቅ ስለሺ እና በአቶ ኢሳያስ ሽፈራው ቀርበው ውይይት ተካሂዶባቸው ለጥናቱ ግብዐት የሚሆኑ ሀሳብና አስተያየት ተሰብስቦባቸዋል፡፡ በጥናት ግምገማው ላይ የተገኙት የከተማ ልማት ኮሌጅ ዲን ዶ/ር ደጉ በቀለ፣ ከቤቱ በተሰጡት አስተያየቶች እና ሀሳቦች መሰረት፣ በጥናቱ መሟላት ያለባቸውን አንዳንድ መረጃዎች ተካተው፣ ስራው የተቀመጠለትን የጊዜ መርሃ ግብር ተከትሎ መጠናቀቅ እንዳለበት አስገንዝበዋል፡፡ የቡድኑ አስተባባሪ አቶ ሞላ አይናበባ በማጠቃለያው እንደተናገሩት፣ እስካሁን በነበረው ቆይታ የተከናወኑት ተግባራት ለሚዘጋጀው የቦንጋ ከተማ ፕላን በግብዓትነት የሚያገለግል መረጃ የተሰባሰበበት መሆኑን ገልጸው፣ “ስራውን አጠናቀን ለማስረከብ ያለን ጊዜ አጭር በመሆኑ፣ እስካሁን የነበረንን ጠንካራ የቡድን ስሜት ይበልጥ አጎልብተን በፍጥነት መስራት ይኖርብናል፡፡” ብለዋል፡፡ ይህ የተገመገመው የጥናት ሰነድ ከተሳታፊዎች የተሰጡት ሀሳብ እና አስተያየተች ታክለውበት እና የታዩት ጉድለቶች ተሟልተው ከተጠናቀቀ በኋላ፣ አስተያየት እና ውሳኔ እንዲሰጥበት ለቦንጋ ከተማ አስተዳደር እንደሚቀርብ ከቡድን አስተባባሪው ከአቶ ሞላ አይናበባ ገለጻ ለመረዳት ተችሏል፡፡

በኢፐሰዩ ለቦንጋ ከተማ ፕላን ትግበራ የተካሄደው የጥናት ሪፖርት ተገመገመ
+2
በኢፐሰዩ ለቦንጋ ከተማ ፕላን ትግበራ የተካሄደው የጥናት ሪፖርት ተገመገመ

በኢፐሰዩ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ግምገማ አካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የማኔጅመንት፣ የአመራር እና አስተዳደር ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚሰጡ ሶስት የትምህርት ፕሮግራሞች ያዘጋጀውን የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ረቂቅ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ/ም በስልጠና ማእከል አስገመገመ፡፡ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ የተደረገባቸው የትምህርት ፕሮግራሞች የማኔጅመንት፣ ፐብሊክ አድሚንስትሬሽን እና ዴቨሎፕመንት ማኔጅመንት ሲሆኑ፣ እያንዳንዳቸው ከስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ቡድኑ ውጪ በሆኑ ገለልተኛ የዘርፉ ምሁራን ግምገማ ተደርጎባቸዋል፡፡ በግምገማ መርሀ-ግብሩ መክፈቻ ላይ የትምህርት ፕሮግራሞች ዳይሬክቶሬት ዳይሬክተር አቶ አለባቸው ጎሽም እንደተናገሩት “የስርዓተ ትምህርት ክለሳ ስራችን ዩኒቨርሲቲው ከያዛቸው የሪፎርም ስራዎች ዋነኛው በመሆኑ ብዙ የደከምንበት ስራ ነው፤ ይህም ከአስቸኳይነቱ፣ ከአስፈላጊነቱ እና ከጥቅሙ አንጻር ከሁሉም ስራዎቻችን የመጀመሪያው ነው ማለት ይቻላል፡፡” በማለት ለስራው የተሰጠውን ትኩረት በአጽንዖት ገልጸዋል፡፡ በተያዘው መርሀ-ግብር መሰረትም የማኔጅመንት ስርዓተ-ትምህርት ክለሳ በዶ/ር ዘሪሁን ክንዴ እና በዶ/ር ዝግጁ ሳሙኤል፣ የፐብሊክ አድሚንስትሬሽን እና ገቨርናንስ ስርዓተ-ትምህርት ክለሳ በዶ/ር ራህመቶ ነጋሽ እና በዶ/ር ሊባኖስ ሰመረ እንዲሁም የዴቨሎፕመንት ማኔጅመንት ስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ደግሞ በዶ/ር ደረጀ ተክለማርያም እና በዶ/ር ዝግአለ ታምር በጥልቀት ተገምግሟል፡፡ የግምገማ ሪፖርቱን ተከትሎ ከተሳታፊዎች ጥያቄ፣ ሀሳብ እና አስተያየት ቀርቦ ውይይት የተካሄደበት ሲሆን፣ ከተሰብሳቢዎቹ ለቀረቡ ጥያቄዎች በስርዓተ ትምህርት ክለሳ ቡድን አባላቱ ምላሽና ማብራሪያ ተሰጥቶበታል፤ እንዲሁም የተሰጡት ሙያዊ አስተያየቶች እና ሀሳቦች የረቂቅ ሰነዱ ማዳበሪያ እንዲሆኑ በግብዓትነት ተወስደዋል፡፡ በመጨረሻም የኮሌጁ ምክትል ዲን ዶ/ር መሀመድ ዓሊ በስርዓተ-ትምህርት ክለሳዎቹ ለተሳተፉ የቡድን አባላት፣ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳውን ለገመገሙ ምሁራን እና ለተሳታፊዎቹ ልባዊ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡

በኢፐሰዩ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ግምገማ አካሄደ
+3
በኢፐሰዩ የማኔጅመንት፣ የአመራር እና የአስተዳደር ኮሌጅ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ግምገማ አካሄደ

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢፐሰዩ የመስክ ምልከታ አደረገ በኢፌድሪ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት የሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የመስክ ምልከታ ሚያዝያ 12 ቀን 2018 ዓ.ም አደረገ፡፡ ምልከታው ዩኒቨርሲቲው እንደ ተግባር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ የተሰጠውን ተልዕኮ ለመወጣት እያከናወናቸው ያሉ ተግባራትን የአፈጻጸም ደረጃን ለመከታተል ያለመ ነው። የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ ለቋሚ ኮሚቴው አባላት ባደረጉት ገለጻ ዩኒቨርሲቲው ቀደም ሲል የነበረው ቁመና ካለው ሀገራዊ የለውጥ ሂደት ጋር አብሮ መሄድ የማችልበት እንደነበር አስታዉሰው ይህን ሁኔታ ለመቀየር የሚያስችል ሀገራዊ የሪፎርም ጥናት ኮሚቴ ተቋቁሞ ለዘጠኝ ወራት ባካሄደው ጥናት መሰረት ወደ ለውጥ ስራ በስፋት መገባቱን ገልጸዋል፡፡ በጥናቱ መሰረትም ከምርምር ዩኒቨርሲቲነት ወደ ተግባር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲ መቀየሩንና በዚህም መሰረት ነባሩን ሲቪል ሰርቫንት ማብቃት ብቻ ሳይሆን ተተኪ የሆነ ወጣት ሲቪል ሰርቫንት ለማፍራት አስራ ሁለተኛ ክፍል ያጠናቀቁ ተማሪዎችን ተቀብሎ በማስተማር ላይ የሚገኝ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ ከዚህ ጋር ተያይዞም ቀደም ሲል የነበሩትን የትምህርት ፕሮግራሞች እንደገና የመከለስና አዳዲስ ሥርዓተ-ትምህርቶችን የመቅረጽ ስራዎች በስፋት እየተሰሩ መሆናቸውንም አስረድተዋል፡፡ በመከናወን ላይ ያሉ የለውጥ ሥራዎችንም አስመልከተውም ዩኒቨርሲቲውን ወደ ተግባር ሳይንስ ዩኒቨርሲቲነት የማሸጋገር እና ራስ-ገዝ ዩኒቨርሲቲ የማድረግ፤ እንዲሁም የመንግስትን የአገልግሎትና የአስተዳደር ማሻሻያ የለውጥ ፕሮግራምን መደገፍ አንኳር የለውጥ ስራዎች ተደርገው በትኩረት እየተሰራባቸው መሆናቸውን ገልጸው፤ ይህን የሚያግዙ እና ለውጡ የሚመራባቸው ፍኖተ ካርታዎችን የማዘጋጀት ፣ የሀብት ማመንጫ ኢንተርፕራይዞችን የመለየት፣ ያሉትን መሰረተ ልማቶች የማዘመን፣ ስማርት የሆነ የስልጠና ማዕከልን ማደራጀት እንዲሁም ተቋማዊ ዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ላይ በስፋት እየተሰራ መሆኑን አብራርተዋል፡፡ በማስከተል የቋሚ ኮሚቴው አባላት በዩኒቨርሲቲው የተለያዩ የመሰረተ-ልማት ሥራዎች፤ የተማሪዎች መማሪያ እና መገልገያዎችን ተዘዋውረው የጎበኙ ሲሆን፤ ከተማሪ ተወካዮች እና ከመምህራን እንዲሁም ከሰራተኞች ጋርም ውይይት አድርገዋል፡፡ ከውይይቱ በማስከተልም የመማር ማስተማር ሥራው ያለበት ደረጃ፣ የጥናትና ምርምር ሥራዎች በተገቢው በማከናወን ለማህበረሰብ ተደራሽ ስለመደረጋቸው፣ የአገልግሎት አሰጣጥና የመልካም አስተዳደር ከማስፈን አንፃር እየተሠሩ ያሉ ሥራዎች፣ ከ2015 ዓ.ም ጀምሮ የተማሪዎች የመውጫ ፈተና (EXIT-EXAM) ውጤትና ለ2018 ዓ.ም ያለዉ ዝግጅት እና የትምህርት ጥራትን ለማስጠበቅ ያለውን ቁርጠኝነት እንዲሁም ራስ ገዝ ዩኒቨርሲቲ ለመሆኑን እየተደረገ ያለውን ጥረትን አስመልክቶ ላነሷዋቸው ጥያቄዎችና አስተያየቶች የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚደንት ዶ/ር ንጉስና ምክትል ፕሬዚደንቶ ሰፊ ማብራሪያና ምላሽ ሰጥተዋል፡፡ በተዘጋጀው የማጠቃለያ የውይይት መድረክም የቋሚ ኮሚቴው አባላት በነበራቸው የመስክ ምልከታ እጅግ መደሰታቸውና ዩኒቨርሲቲው እያደረገ ያለው የለውጥ እንቅስቃሴ የሚበረታታ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ የለውጥ ሥራው ግልጽ በሆነ ፍኖተ ካርታ የተደገፈ መሆኑ በጣም ጥሩ እና ሊደነቅ የሚገባው ተግባር መሆኑን ያነሱት አባላቱ ያሉ ብዥታዎችን ለማጥራት በየጊዜው ወደታች ማውረድና ተግባራዊነቱ ላይ መረባረብ እንደሚገባም አሳስበዋል፡፡ አስከትለውም ሊስተካከሉና ሊታረሙ ይገባቸዋል ያሏቸው ጉዳዮች ላይም ሀሳብ አስተያየታቸውን አቅርበዋል፡፡ በመጨረሻም የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ የተከበሩ ዶ/ር ነገሪ ሌንጮ በሰጡት ማጠቃለያ ዩኒቨርሲቲው በከፍተኛ የለውጥ ጉዞ ውስጥ መሆኑን ጠቅሰው አሁን ያለው የአመራር ቁርጠኝነት እና በተቋሙ ያለው እምቅ አቅም ለውጡን በተያዘው ዕቅድ መሰረት ከዳር ለማድረስ የሚያስችል መሆኑን ተናግረል፡፡ በማስከተልም ዩኒቨርሲቲው በራሱ ቆሞ ራዕይና ተልዕኮ ለማሳካት እና የዩኒቨርሲቲውን ስምና ዝና ለመለወጥ ብሎም የጥራትና አግባብነት ጉዳዮች ላይ በትኩረት መስራት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸዋል፡፡ በነበራቸው ቆይታም ዩኒቨርሲቲው በርካታ ስራዎችን በማከናወን ላይ መሆኑን መገንዘባቸውንና በቀጣይም ለተቋሙ ስኬት አስፈላጊውን ድጋፍ ለማድረግ ዝግጁ መሆናቸውን አረጋግጠዋል።

የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢፐሰዩ የመስክ ምልከታ አደረገ
+2
የሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ሰው ኃብት ልማት፣ ሥራ ሥምሪት እና ቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ በኢፐሰዩ የመስክ ምልከታ አደረገ

የኢፐሰዩ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ወርክሾፕ አካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) ፋይናንስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚሰጡ ሰባት የ
+2
የኢፐሰዩ ፋይናንስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ወርክሾፕ አካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) ፋይናንስ እና ኢኮኖሚክስ ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚሰጡ ሰባት የትምህርት ፕሮግራሞች የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ ወርክሾፕ ሚያዝያ 9 ቀን 2018 ዓ/ም በስልጠና ማዕከል አካሄደ፡፡ የስርዓተ-ትምህርት ክለሳ የተደረገባቸው የትምህርት ፕሮግራሞች አካውንቲንግ እና ፋይናንስ፣ ፐብሊክ ፋይናንሻል ማናጅመንት፣ ፕሮኪዩርመንት እና አሴት ማናጅመንት፣ ማርኬቲንግ ማናጅመንት፣ ሎጀስቲክ እና ሰፕላይ ቼይን ማናጅመንት፣ ኢኮኖሚክስ እና ታክስ አድሚንስትሬሽን የሚሉት ናቸው፡፡ ለሁሉም የትምህርት ፕሮግራሞች የተዘጋጀው ረቂቅ የስርዓተ-ትምህርት ሰነድ በአዘጋጆቹ አማካኝነት ቀርቧል፤ እንዲሁም ስርዓተ ትምህርቱ ላይ ግምገማ እንዲያደርጉ ረቂቅ ሰነዱ አስቀድሞ የተላከላቸው የዩኒቨርሲቲው የዘርፉ ምሁራን የግምገማቸውን ውጤት ለኮሌጁ አስቀድመው በጽሁፍ የላኩ መሆኑ ታውቋል፤ በተጨማሪም በወርክሾፑ ላይ ምልከታቸውን አቅርበዋል፡፡ በመቀጠልም ከገምጋሚዎች፣ ከተሳታፊዎች እና ከባለድርሻ አካላት ለቀረቡ ጥያቄዎች እና አስተያየቶች ረቂቅ ስርዓተ- ትምህርቱን ባዘጋጁ የኮሚቴ አባላት በኩል ምላሽ እና ማብራሪያ ተሰጥቷል፡፡ በመጨረሸም የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዘላለም እጅጉ፣ በወርክሾፑ ላይ የለተሰጡት አስተያየቶች ለስርዓተ-ትምህርት ክለሳው ጠቃሚ ግብዓቶች መሆናቸውን ጠቅሰው፣ ተሳታፊዎቹን አመስግነዋል፡፡

የኢፐሰዩ የማህበራዊ ሳይንስና ልማት ጥናት ኮሌጅ የካሪኩለም ግምገማ ወርክሾፕ አካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የማህበራዊ ሳይንስና ልማት ጥናት ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚሰጡ
+1
የኢፐሰዩ የማህበራዊ ሳይንስና ልማት ጥናት ኮሌጅ የካሪኩለም ግምገማ ወርክሾፕ አካሄደ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ (ኢፐሰዩ) የማህበራዊ ሳይንስና ልማት ጥናት ኮሌጅ በመጀመሪያ ዲግሪ ለሚሰጡ አራት የትምህርት ፕሮግራሞች የስርዓተ-ትምህርት ግምገማ ወርክሾፕ ሚያዝያ 7 ቀን 2018 ዓ/ም በስልጠና ማዕከል አካሄደ፡፡ ወርክሶፑ የተዘጋጀው በፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት፣ በሶሽዎሎጂ ፣ በጆርናሊዝም እና ኮሙኒኬሽን እና በሳይኮሎጂ የትምህርት ፕሮግራሞች ላይ ሲሆን፣ ዓላማውም በዩኒቨርሲቲው አዲስ ተልዕኮ መሰረት፣ በፐብሊክ ሰርቪስ ተቋማት ላይ በተካሄደው የፍላጎት ዳሰሳ ጥናት መሰረት መዘጋጀታቸውን ለመገምገም መሆኑ በወርክሾፑ ላይ የተገኙት የኮሌጁ ዲን ዶ/ር ዋቅጋሪ ነገሪ ገልጸዋል፡፡ ለእያንዳንዱ የትምህርት ፕሮግራም የተዘጋጀው ስርዓተ-ትምህርት በየትምህርት ክፍሉ ያሉ የዩኒቨርሲቲው ምሁራን የተሳተፉበት ሲሆን፣ የፖለቲካ ሳይንስ እና ዓለም አቀፍ ግንኙነት ትምህርት ፕሮግራም ሥርዓተ-ትምህርት በዶ/ር ተመስገን አስጨንቅ፣ የሶሽዎሎጂ ትምህርት ፕሮግራም በዶ/ር ሀብታሙ መኮንን፣ የጆርናሊዝም እና ኮሙኒኬሽን ትምህርት ፕሮግራም በዶ/ር ዓለማየሁ ጆቴ እና የሳይኮሎጂ ትምህርት ፕሮግራም ሥርዓተ-ትምህርት ደግሞ በዶ/ር ቅድስት ተስፋዬ አማካኝነት ቀርቧል፡፡ እንዳንዱ የትምህርት ፕሮግራም ካሪኩለም ከቀረበ በኋላ ከተሳታፊዎች ጥያቄዎች እና ሥርዓተ-ትምህርቱ መዳበር ግብዐት የሚሆኑ አስተያየቶች ቀርበው ውይይት ተደርጎባቸዋል፡፡

photo content
+2

In closing, Dr. Nigus reaffirmed EPSU’s commitment to translating the Africa Project into lasting institutional benefits and welcomed further collaboration with Italian institutional partners in the spirit of mutual learning and shared progress.

EPSU and Italy Advance Africa Project Training for Ethiopia’s Public Service Leaders Addis Ababa, 09 April 2026 (EPSU) In a significant step toward strengthening public service capacity in Ethiopia, Ethiopian Public Service University (EPSU) today hosted His Excellency Ambassador Sem Fabrizi of Italy and His Excellency Deputy Head of Mission Luca Carpintieri for a high level preparatory visit. The focus of the visit was the imminent launch of the Africa Project, a flagship initiative under Italy’s Mattei Plan for Africa, implemented by Italy’s National School of Administration (SNA). The Africa Project aims to enhance the skills of senior Ethiopian public leaders across critical governance and administrative domains. EPSU is the designated host institution for the first round of training, which will host about 150 senior public service leaders drawn from more than 36 Ethiopian government institutions, alongside a dedicated group of competitively selected Training of Trainer (😭) participants from EPSU itself. The project reflects the deepening and mutually respectful partnership between Ethiopia and Italy in public administration capacity building. The EPSU management team, led by Dr. Nigus Tadesse, President of EPSU, welcomed the Ambassador and Deputy Ambassador in the Senate Hall. Dr. Nigus Tadesse recalled his presence at the signing of the Africa Project in Rome and Caserta, noting: “That occasion was a moment of promise. Today, we are pleased to report that we are delivering on that promise.” He also emphasised that EPSU’s Internationalization and Partnership Directorate has identified areas of mutual collaboration that will be implemented on a phase by phase basis. Consistent with EPSU’s mandate to produce competent, ethical, and transformative public servants, Dr. Nigus Tadesse respectfully offered six areas for potential future cooperation with Italian institutions: joint executive training programmes on ethical leadership and performance management; applied research on public administration reform, including decentralisation and e governance; reciprocal faculty and staff exchanges; curriculum development support for degree programmes; annual policy dialogue forums; and distance learning initiatives to reach civil servants across Ethiopia’s regions. Furthermore, Dr. Amanuel Kussia, Vice President for Academic Affairs and Dr. Mitiku Adisu, Vice President for Research and Technology Transfer outlined possible academic and research focused collaborations with the SNA or Italian universities. Dr. Dereje Teklemaram, Director of Internationalization and Partnership at EPSU, expressed gratitude to AICS, the Mattei Plan Mission Structure, the Italian Ministry of Foreign Affairs, the SNA, and all project partners. He extended his sincere appreciation to the Italian Embassy, Ambassador Sem Fabrizi, and Deputy Head of Mission Luca Carpintieri for their exemplary support. Dr. Dereje stated that EPSU has clearly outlined areas of international collaboration and the institution is ready to proceed with them. He further noted that training preparations are advancing well in close coordination with the SNA. Ambassador Sem Fabrizi expressed Italy’s commitment to supporting collaboration with EPSU across various areas. He noted that the Italian Embassy would also facilitate inter institutional cooperation in cultural and community exchanges. The Ambassador commended EPSU’s preparations and appreciated that necessary preparations including participant selections have been finalised. He expressed confidence that the training would contribute meaningfully to the capacities of Ethiopian senior public service leaders in the five targeted areas. The Africa Project training, a concrete expression of Italy’s Mattei Plan for Africa, is set to launch in late May 2026, marking a tangible milestone in Ethiopia Italy cooperation for public service transformation.

ኢፐሰዩ ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ ሰራተኞቹ የበዓል መዋያ ድጋፍ አደረገ የኢትዮጵያ ፐብሊክ ሰርቪስ ዩኒቨርሲቲ የ2018 ዓ/ም የትንሳዔ በዓልን ምክንያት በማድረግ ዝቅተኛ ገቢ ለሚያገኙ ሰራተኞች ለበዓል መዋያ የሚሆን የስንዴ ዱቄት እና የዘይት ድጋፍ አደረገ፡፡ በእለቱ ድጋፍ የተደረገላቸው ሰራተኞች 796 (ሰባት መቶ ዘጠና ስድስት) የሚሆኑ ሰራተኞች ሲሆኑ ለሁሉም እንደገቢያቸው መጠናቸው ከ50 - 25 ኪሎ ግራም የስንዴ ዱቄት እና የ5 ሊትር የምግብ ዘይት ድጋፍ ተደርጎላቸዋል፡፡ መርሃ ግብሩን በአካል ተገኝተው ያስጀመሩት የዩኒቨርሲቲው ፕሬዚዳንት ዶ/ር ንጉስ ታደሰ የዩኒቨርሲቲው ማኔጅመንት ዝቅተኛ ተከፋይ ለሆኑ ሰራተኞች ድጋፍ እንዲደረግ ባሳለፈው ውሳኔ መሰረት ድጋፉ መደረጉን ገልጸዋል፡፡ የተደረገውን ድጋፍ አስመልክቶም አስተያየታቸውን የሰጡ ሰራተኞች እንደገለጹት በአንድ አመት ውስጥ ተመሳሳይ ድጋፍ ሲደረግላቸው ለሁለተኛ ጊዜ መሆኑን አስታውሰው ማኔጅመንቱ የሰራተኞቹን ነባራዊ ሁኔታ በመገንዘብ ላደረገላቸው ደጋፍ ምስጋናቸውን አቅርበዋል፡፡ Visit our website: http://www.epsu.edu.et/ Follow our Facebook page: https://web.facebook.com/EPSUfb Follow our Telegram Channel: https://t.me/epsutelegram Follow us on LinkedIn: https://www.linkedin.com/.../ethiopian-public.../about/ Subscribe to our YouTube channel: https://www.youtube.com/@EPSUyt