fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለተላስስ ሰማዕት ዘተዐገሠ ሥቃያተ ብዙኅ ወዴገነ ፍኖተ ንጹሕ"። ትርጉም፦ ብዙ ሥቃይን የታገሠና መልካም መንገድንም የተከተለ ለኾነ ለሰማዕቱ ለተላስስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለክሙ ተላስስ ቅሡፍ። ወአልዓዛር ዓዲ በውሳጤ ነድ ግዱፍ። አድኅኑኒ ሊተ እመሥገርተ ልሳን ወአፍ። ከመ ያመሥጥ ወይጠል እምሥገርት ገሪፍ። ወከመ ይድኅን እምጽንፍርት ዖፍ"። ትርጉም፦ ለተገረፈኸው ተላስስና ዳግመኛ በሚነድድ እሳት ውስጥ ለተጣልኸው ለአልዛር ሰላምታ ይገባችኋል፤ ፌቆ ከፍጹም ወጥመድ እንዲያመልጥ ዎፍም ከወጥመድ (ከወስፈንጠር፣ ከጠጠር፣ ከዐረር) እንዲድን ከአንደበትና ከልሳን ወጥመድ አድኑኝ። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 10። https://t.me/Eotcw

photo content
+3

+ + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ዘረወ ወወሀበ ለነዳይ። ወጽድቁኒ ይነብር ለዓለም። ወይትሌዓል ቀርኑ በክብር"። መዝ 109፥9። የሚነበቡት መልዕክታት ቲቶ 1፥5-12 ወይም 1ኛ ቆሮ 9፥1-15፣ 1ኛ ዮሐ 2፥20-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 20፥16-22። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 6፥1-5። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም የአባ ኒቆላዎስ፣ የአባ ጥዋሽ የቅድስት ሱርስት፣ ቅዱሳን ሰማዕታት ተላስስና አልዓዛር የዕረፍታቸው በዓል፣ አቡነ ሳዊሮስ የሥጋ ፍልሰት በዓልና የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

+ + + ❤ የአንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት የቅዱስ አባ ሳዊሮስ የሥጋ ፍልሰት ከእስክድርያ ወጪ ወደሆነች ደብረ ዝጋግ ገዳም፦ እንዲህም ሆነ ይህ ቅዱስ አባት በአገረ ስሓ አምላክን በሚወድ ክርስቲያን ባለጸጋ ስሙ ዱራታዎስ በሚባል ሰው ዘንድ በዐረፈ ጊዜ እርሱም ከምእመናን ሰዎች ጋር በመርከብ አሳፍሮ ላከው በጥልቅ ባሕር ላይ እንጂ በአነስተኛ ሸለቆ እንዳይሔዱ ከዚያም በወደቡ እንዲወጡ አዘዛቸው። ❤ ወደ ደቡባዊ ባሕረ ቅርጣስ በደረሱ ጊዜ የቅዱሱም ሥጋ ከእርሳቸው ጋር ሳለ ወደ ምዕራብ አቅጣጫ ጥቂት እንደተጓዙ መርከቡን የሚሸከም ውኃ አላገኙም መርከቡንም እየጐተቱ ታላቅ ድካምን ደከሙ መርከባቸውንም ወደ ኋላ ይመልሱ ዘንድ አሰቡ ግን አልተቻላቸውም ፈጽሞ አዘኑ ደነገጡም ዕውቀታቸውም ተሠወራቸው ሰውን የሚወድ እግዚአብሔር የእስራኤል ልጆች ከጠላቶቻቸው ፊት ሰውሮ በኤርትራ ባሕር ውስጥ መንገድ ገልጦ ያላለፋቸው እርሱ የቅዱስ ሳዊሮስን ሥጋ መለካውያን ከሆኑ ከከሀድያን ሰዎች ሠወረ እነርሱ በሕይወቱ ሳለ ይጠሉት ነበርና እንዲሁ ከሞተ በኋላ ቃሉ እንደ ሰይፍ የሚቆራርጣቸው ሆነ። ❤ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ከተአምራቱ ገለጠ ያቺን መርከብ ወደሚወጡበት ወደብ እስከምትደርስ በጥቂት ውኃ ላይ ሰባት ምዕራፍ ያህል እንድትጓዝ አደረጋት ገዳም ከዚያም ተሸክመው ወደ ደብረ ዝጋግ ገዳም አድርሰው ያ ባለጸጋ ዱራታዎስ በሠራለት ቦታ ውስጥ አኖሩት በግብጽ አገርም ታላቅ ደስታ ሆነ ይልቁንም በእስክንድርያ ከተማ። እግዚአብሔርም ታላላቅ የሆኑ ድንቆች ተአምራቶችን ገለጠ በሕይወቱ ሳለ ከጥርሶቹ የወደቀች አንዲት ነበረች የደብረ ዝጋግ ገዳም አንድ መነኵሴ አንሥቶ በሐር ጨርቅ ጠቅልሎ አኖራት እርሷም ለታመሙ ሕዝቦች የምትፈውስ ሆነች እነርሱም ወደ እስክንድርያ አገር ያመጧትና በበሽተኞች ላይ ያኖሩዋታል እነርሱም ይድናሉ። እግዚአብሔርም ቅዱስ ሳዊሮስን በሕይወቱ ካለበት ጊዜ ይልቅ ከሞተ በኋላ እጅግ ከፍ ከፍ አደረገው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሳዊሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ ኒቆላዎስ፡- አባቱ ኤጲፋንዮስ እናቱ ዮና ይባላሉ፡፡ እርሱም ሜራ በምትባል አገር እጅግ ባለጸጎች ሆነው የሚኖሩ ደጋግ ሰዎች ናቸው፡፡ እጅግ ባለጸጎች ቢሆኑም ልጅ ስላልነበራቸው እያዘኑ እግዚአብሔርን በመለመን ብዙ ዘመን ኖሩ፡፡ የመውለጃ ጊዜአቸውም ባለፈ ጊዜ ስለ ልጅ መለመናቸውን አቆሙ፡፡ እግዚአብሔር ግን በመጨረሻ ዘመናቸው የተባረከ ይህን ኒቆላዎስን ሰጣቸው፡፡ እግዚአብሔርም በልጃቸው ላይ የጽቅን ሥራ ገለጠ፡፡ ልጁ ገና እንደተወለደ ተነሥቶ በእግሮቹ ቆሞ በሰዎች መካከል ለሁለት ሰዓት ያህል ቆመ፡፡ ይህም ለመንደሳዊ ሥራ የተነሣ ቅዱስ መሆኑን ያጠይቃል፡፡ በሕፃንነቱም የሐዋርያትን ትምህርት ፈጽሞ ረቡንና ዓርብን በመጾም እስከ ዘጠኝ ሰዓት የእናቱን ጡት አይጠባም ነበር፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ወላጆቹ ለመምህር ሰጥተውት የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት ሁሉ ተማረ፡፡ ወደ ገዳምም ገብቶ ማንም እንደ እርሱ ሊሠራው የማይችለውን ጽኑ ገድል ተጋደለ፡፡ ዘጠኝ ዓመትም በሆነው ጊዜ ቅስና ተሾመና ድንቅ ድንቅ የሆኑ ተአምራትን ማድረግ ጀመረና ሕመምተኞችን ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ፡፡ አንድ ባለጸጋ በሀገሩ ነበር፡፡ እርሱም የዕለት እራት ድረስ ፈጽሞ ድኃ ሆነ፡፡ አራት ሴት ልጆችም ነበሩትና እነርሱን ስለድኅነቱ የሚያገባቸው ጠፋ፡፡ ባለጸጋ የነበረውም ሰው የዝሙት ሙት ሠርቶ በዚያ ልጆቹ እያመነዘሩ በዝሙት ዋጋ ይኖሩ ዘንድ ይህንን የረከሰ ሀሳብ ሰይጣን አሳሰበው፡፡ ❤ እግዚአብሔር ግን የዚያን ባለጸጋ የነበረ ሰው ክፉ ሀሳብ ለአባ ኒቆላዎስ ገለጠለት፡፡ አባ ኒቆላዎስም ከአባቱ ገንዘብ ላይ መቶ የወርቅ ዲናር ወስዶ በሌሊት ማንም ሳያየው ወደዚያ ባለጸጋ ወደነበረው ሰው ቤት ሄዶ በበሩ ሥር አስቀምጦለት ተመለሰ፡፡ ባለጸጋ የነበረውም ሰው ወርቁን ወስዶ እጅግ ደስ ብሎት ታላቂቱን ልጁን አጋባት፡፡ አሁንም ለ2ኛ ጊዜ አባ ኒቆላዎስ መቶ የወርቅ ዲናር አስቀመጠለትና ሰውየውም ሌላኛዋን ታላቅ ልጁን ዳራት፡፡ አባ ኒቆላዎስም ለ3ኛ ጊዜ እንዲሁ አደረገ፡፡ ባለጸጋውም በስተመጨረሻ ‹‹ይህን የሚያደርግልኝ የእግዚአብሔርን ሰው ማየት አለብኝ›› ብሎ ቁጭ ብሎ እያደረ በሌሊት የሚመጣውን መጠበቅ ጀመረ፡፡ አባ ኒቆላዎስም ለ4ኛ ጊዜ ወርቁን ሲያኖርለት አገኘውና ወድቆ ሰገደለት፡፡ "ከገንዘብና በኃጢአት ከመውደቅ አድነኸኛልና ዋጋህ ፍጹም ነው" ብሎ አመሰገነው፡፡ አባ ኒቆላዎስ በአካባቢው ባለው ዛፍ ላይ አድረው በሰውየው ላይ መከራ ያመጡበትን አጋንንት አባረራቸው፡፡ በዚያ የነበሩ ሕመምተኞችንም አዳናቸው፡፡ ዳግመኛም ጥቂት እንጀራን አበርክቶ ብዙ ሕዝቦችን አጠገባቸው፡፡ እጅግ የበዛ ትራፊም ተመልሶ ተነሣ፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ ኒቆላዎስ ኤጲስቆጶስነት ከመሾሙ አስቀድሞ የክህነት ልብስንና ብርሃንን የለበሰ ሰው በዙፋን ላይ ተቀምጦ በራእይ አየና "ይህንን የክህነት ልብስ ለብሰህ በዙፋኑ ተቀመጥ" የሚል ድምጽ ሰማ፡፡ ለሁለተኛ ጊዜም እመቤታችን ተገልጣለት የክህነትን ልብስ ስትሰጠው ጌታችንም የከበረች ወንጌልን ሲሰጠው አየ፡፡ ከዚህም በኋላ የሜራ አገር ኤጲስቆጶስ በሞት ባረፈ ጊዜ የታዘዘ መልአክ ለሮሜው አገር ሊቀ ጳጳስ ተገለጠለትና ስለ አባ ኒቆላዎስ መልኩንና ስሙን በዝርዝር ነገረው፡፡ እርሱም ለሕዝቡ ሁሉ ነገራቸው አባ ኒቆላዎስን ወስደው በሜራ አገር ላይ ኤጲስቆጶስነት ሾሙት፡፡ ❤ ከሃዲው ንጉሥ ዲዮቅልጥያኖስ አምለኮ ጣዖትን በግዛቱ ሁሉ ሲያውጅና የክርስቲያኖችን ደም እንደውኃ ሲያፈስ አባ ኒቆላዎስ ደግሞ ክርስቲያኖችን ያስተምራቸውና በሃይማኖት ያጸናቸው ነበር፡፡ ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ አባ ኒቆላዎስን ይዞ እጅግ ብዙ አሠቃየው፡፡ ነገር ግን ጌታችን ከመከራው ሁሉ እያዳነው ከቁስሉም ይፈውሰው ነበር፡፡ ንጉሡም እጅግ ቢያሠቃየውም ቅዱሱ ደግሞ መልሶ ጤነኛ ሆኖ ያገኘዋል፡፡ በዚህም ማሠቃየት ቢሰለቸው ወደ እሥር ቤት ጨመረው፡፡ እግዚአብሔርም ዲየቅልጥያኖስን አጥፍቶት ጻደቁን ቆስጠንጢኖስን እስካነገሰው ድረስ አባ ኒቆላዎስ በእሥር ቤት ብዙ ዓመታት ኖረ፡፡ ❤ ንጉሥ ቆስጠንጢኖስም የታሰሩትን ቅዱሳን ሁሉ በፈታቸው ጊዜ አባ ኒቆላዎስ ከእሥር ወጥቶ ወደ መንበረ ጵጵስናው ተመለሰ፡፡ ሕዝቡንም ስለቀናች ሃይማኖት አስተማራቸው፡፡ ሃይማኖታቸው የቀና እጅግ የከበሩ 318 ቅዱሳን በአርዮስ ጉዳይ በተሰበሰቡ ጊዜ ይህ ቅዱስ አባት አባ ኒቆላዎስ ከእነርሱ ውስጥ አንዱ ነው፡፡ እርሱም ከሌሎቹ ቅዱሳን ጋር ሆኖ አርዮስን አሳዶ የቀናች ሃይማኖትን ደነገገልን፣ ሥርዓትን ሠራልን፡፡ እርሱም ተጋድሎውን ፈጽሞ በዚህች ዕለት ታኅሣሥ10 በሰላም ዐረፈ፡፡ ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ኒቆላዎስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ትደርብን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 10 ስንክሳር።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲ (10) ቀን። ❤ እንኳን ለቅዱሳን ሰማዕታት ለተላስስና ለአልዓዛር ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍት በዓል፣ ከታናሽነቱ ጀምሮ ጃንደረባ ለሆነ ለአባ ጥዋሽ ለዕረፍት በዓል፣ ከቊጥስጥንጥንያ አገር ለከበሩ ሰዎች ልጅ ለሆነች ለቅድስት ሱርስት ለዕረፍት በዓል፣ ለአንጾኪያ አገር ሊቀ ጳጳሳት ለነበረ ለቅዱስ አባ ሳዊሮስ ከእስክንድርያ አገር ወጪ ወደሆነች ደብረ ዝጋግ ገዳም ሥጋው ለፈለሰበት በዓልና ለከበረ አባት ጻድቅ ኤጲስቆጶስ የስሙ ትርጓሜ የሕዝብ አሸናፊ ለሆነ ለአባ ኒቆላዎስ ለዕረፍት በዓልና በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከ እስክንድርያ አገር ስልሣኛ ሊቀ ጳጳሳት ከአባ ታውፋኔዎስ ዕረፍት፣ ከቅዱሳን ከሜልዮስና ከታውፍያ ከዕረፍታቸው መታሰቢያ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ቅዱሳን ሰማዕታት ተላስስና አልዓዛር፦ ይህም ተላስስ ከነነዌ አውራጃ ከባቢሎን ሰዎች ወገን ነው የፋርስ ንጉሥ ሳቦርም ይዞት "ለእሳት ስገድ ለአማልክትም ሠዋ" አለው ቅዱስ ተላስስም " እኔስ ለፈጣሪዬ እግዚአብሔር እሰግዳለሁ ለእርሱም እሠዋለሁ እንጂ ለጣዖት አልሠዋም" አለው። ያስፈራውም ዘንድ የቅጣት መሣሪያዎችን አስመጣ እርሱ ግን አለሰፈራም መቶ ግርፋትም ለረዥም ጊዜ እንዲገርፋት አዘዘ ከዚህም በኋላ "ተላስስ ሆይ ከዚህ ሥቃይ እንድታርፍ ለአማልክት ሠዋ" አለው እርሱም "ፈጣሪዬ ስለሚጠብቀኝ ለእኔ ሥቃይህ አልታወቀኝም" አለው። ❤ በዚያንም ጊዜ ሁለት መቶ ጊዜ ገረፉት በዐይኖቹም ውስጥ የብረት ችንካሮችን ተከሉ መናገርም እስከሚሳነው በነሐስ መክደኛ ሸፍነው ደበደቡት ራሱንም በሰይፍ ቆረጡ። ከዚህም በኋላ አልዓዛርን አቀረቡት ንጉሥ ሳቦርም "ለአማልክት ሠዋ" አለው ለረከሱ አማልክቶቹም መሠዋትን እምቢ ባለው ጊዜ ወዲያውኑ ወደ እሳት ወረወረው ያማረ ምስክነቱንም ፈጸመ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሰማዕታት ቅዱሳን ተላስስና አልዓዛር ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ ጥዋሽ፡- ይኽም ቅዱስ ከልጅነቱ ጀምሮ ድንግል ሆኖ በምንኵስና በታላቅ ተጋድሎ የኖረ ነው፡፡ ከዕለታትም በአንደኛው ቀን ወደ እስክንድርያ ሲጓዝ በመንገድ ላይ አንዲት አይሁዳዊት ሴት ስታለቅስ አገኛትና ምን እንደሆነች ጠየቃት፡፡ እርሷም "ክርስቲያን መሆን እሻ ነበር" አለችው፡፡ አባ ጥዋሽ የነፍሱን ጥቅም አስቦ ሊተዋት ነበር ግን ሴቲቱ መዳን እየፈለገች ቢተዋት በእግዚአብሔር ዘንድ ታላቅ በደል እንዳይሆንበት ከእርሱ ጋር ወሰዳትና የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃት፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ አባ ጥዋሽ ከሴቲቱ ጋር ሆኖ በየገበያው ቦታ ሁሉ እየዞሩ ነለዳያን ይመጸውቱ ጀመር፡፡ የእስክንድርያ መነኰሳትም እርሷ ሚስቱ እንደሆነች አስበው በዚህ ተሰነካከሉበት፡፡ ይዘውትም ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ዮሐንስ ዘንድ አቀረቡት፡፡ አባ ዮሐንስም ሁለቱን ተያይተው እንዲታሰሩ አዘዙ፡፡ በዚያችም ሌሊት ሊቀ ጳጳሳቱ አባ ዮሐንስ በሕልማቸው አባ ጥዋሽ የቆሰለ ጀርባውን እያሳያቸው "ያለበደሌ ለምን አቆሰልከኝ?" ሲላቸው ተመለከቱ፡፡ አባ ዮሐንስም በነቁ ጊዜ አባ ጥዋሽን አስመጥተው በግርፋት ብዛት የቆሰለ ጀመርባውንና ፍጹም ድንግል መሆኑን አይተው እጅግ አዝነው አለቀሱ፡፡ "ይቅር በለኝ" ብለው በፊቱ ወደቁ፡፡ ከዚያም አባ ጥዋሽን ያመጡትንና የደበደቡትን ሰዎች ከማዕረጋቸው አውርደው ለ3 ዓመታት ቅዱስ ሥጋውንና ክቡር ደሙን ከመቀበል ከለከሏቸው፡፡ ካሳ ይሆነውም ዘንደ ለአባ ጥዋሽ ብዙ ገንዘብ ቢሰጡት እርሱ ግን ምንም ሳይቀበል ወደ በዓቱ ተመልሶ ሄዶ ተጋድሎውን ፈጽሞ በዚህች ዕለት ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ጥዋሽ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅድስት ሱርስት፡- ይኽችም ቅድስት ከቁስጥንጥንያ አገር እጅግ ከከበሩ ወገኖች የአንዱ ልጅ ናት፡፡ ለአንድ ለከበረ ሰው ልጅ በታጨች ጊዜ አባቷን "አባቴ ሆይ! አስቀድሜ ወደ ቤተ መቅደስ ሄጄ እሰግድ ዘንድ ፍቀድልኝ በምመለስበት ጊዜ እግዚአብሔር እንደፈቀደ ይሁን" አለችው፡፡ አባቷም "አስቀድመሽ ወደ ባልሽ ግቢ፣ ሰርግሽ ከተፈጸመ በኋላ ከእርሱ ጋር ወደ ወደድሽው ሄደሽ ስዕለትሽን ትፈጽሚያለሽ" አላት፡፡ እርሷም መልሳ "በድንግልናዬ ሳለሁ ወደዚያች የከበረች ቦታ ሄጄ ልጸልይ ለእግዚአብሔር ቃል ገብቻለሁና ቃሌን ብዋሽ ፈጣሪ በእኔ ላይ ይቆጣል" ስትለው አባቷ ከሚያገለግሏት ወንዶችና ሴቶች አሽከሮች ጋር ለምጽዋትም የምትሰጠው 300 የወርቅ ዲናር ሰጥቶ ላካት፡፡ ❤ ቅድስት ሱርስትም እዚያ በደረሰች ጊዜ የከበሩ ቦታዎችን ሁሉ እየዞረች ተሳለመች፣ ወደ ግብጻውያን ገዳምም በደረሰች ጊዜ አንድ አረጋዊ መነኩሴ ማቅ ለብሶ አገኘችውና የልቧን ሀሳብ ሁሉ ማለትም ልትመነኩስ እንደምትፈልግ ነገረችው፡፡ እርሱም "የእግዚአብሔር ፈቃድ ይሁን" አላት፡፡ ከዚህም በኋላ ወደ ሀገራቸው ተመልሰው ሊሄዱ በተዘጋጁ ጊዜ ወደ ስውር ቦታ ገብታ ለወላጆቿ "እኔ ሰውነቴን ለእግዚአብሔር አቅርቤያለሁ አታገኙኝምና አትፈልጉኝ" ብላ ደብዳቤ ጻፈች፡፡ ደብዳቤውንም በልብሷ አሥራ ከዕቃ ውስጥ አኖረችው፡፡ ሰዎቹም ከእነርሱ ጋር አብራ የምትሄድ መስሏቸው ዕቃ ጭነው በቀደሟት ጊዜ አንዱን አገልጋይ ይዛ አስቀረችውና "ወደ ጎልጎታ ገብቼ ልጸልይ እሻለሁና" ብላ ምሥጢሯን እንዲጠብቅ ነገረችው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ ወደዚያ ሽማግሌ መነኩሴ ዘንድ ተመልሳ የያዘችውን 300 የወርቅ ዲናር ለድኆችና ጦም አዳሪዎቸ እንዲያከፋፍለው ሰጠችውና ያመነኵሳት ዘንድ ለመነችው፡፡ እርሱም ጽናቷን አይቶ ፈቃደ እግዚአብሔርም መሆኑን ዐውቆ ራሷን ላጭቶ የምንኩስና ልብስ አለበሳት፡፡ እርሷም እግዚአብሔር ወደፈቀደላት ወደ አንዲት ዋሻ ሄዳ በዚያ በታላቅ ተጋድሎ መኖር ጀመረች፡፡ በዚህም ጊዜ ዕድሜዋ ገና 12 ዓመት የነበረ ቢሆንም የሰውን ፊት ሳታይ በዚያች ዋሻ ውስጥ ለ27 ዓመታት በተጋድሎ ኖረች፡፡ ❤ ቃህራ ከሚባል አገር በገድል ሥራ የሚኖር ሲላስ የሚባል መነኰስ ነበር፡፡ በቀልሞን ዋሻ የሚኖር አንድ ጓደኛ መነኰስ አለውና ፋሲካ በደረሰ ጊዜ እርሱን ጎብኝቶ በረከት ለመቀበል ሄደ፡፡ በሄደም ጊዜ አላገኘውምና እርሱን ፍለጋ ተራራ ለተራራ ዞረ፡፡ በዚያም የእግር ዱካ አገኘና ዱካውን ተከትሎ በመሄድ መግቢያው ላይ ሲደርስ "የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ባርከኝ" አለ፡፡ ከውስጥም ያለው ድምጽ ስሙን ጠርቶት "ሲላስ ሆይ አንተ ካህን ነህና ልትባርከኝ ይገባል" አለው፡፡ ሲላስም ወደ ውስጥ እንደገባ ቅድስት ሱርስትን አገኛት፡፡ እርሷም ምሥጢሯን ሁሉ በዝርዝር ነገረችው፡፡ ወዲያውም በዚች ቀን ታኅሣሥ10 በሰላም ዐረፈች፡፡ ሲላስም በዚያች ዋሻ ውስጥ በክብር ገንዞ ቀበራት፡፡ ገድሏንም ጻፈላት፡፡ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ሱርስት ጸሎት ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።

samina 21 .mp31.03 MB

ትምህርተ ኅቡዓት ዜማ @EOTCW

ትምህርተ ኅቡዓት እዚህ ላይ የለቀኩት ቀጣይ ባሉ በዓላት በስብከት:በኖላዊ፡በጥምቀት በእነዚህ በዓላት ስለሚባል እንድታጠኑት ነው፡፡ስለዚህ እናንተም እንድታጠኑት ለሌሎችም እንድታደርሱ አሳስባለሁ፡፡

ትምህርተ ኅቡዓት እዚህ ላይ የለቀኩት ቀጣይ ባሉ በዓላት በስብከት:በኖላዊ፡በጥምቀት በእነዚህ በዓላት ስለሚባል እንድታጠኑት ነው፡፡ስለዚህ እናንተም እንድታጠኑት ለሌሎችም እንድታደርሱ አሳስባለሁ፡፡

🍀🍀🍀🍀🍀🍀 መዝሙር ዘስብከት 🌸🌸🌸🌸🌸🌸 (በ፪/ዩ) ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኮሳት ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ወልዶ መድኅነ ንሰብክ

ለበለጠ መረጃ ስልክ 0923257837 ቴሌግራም @Hoping7
ለበለጠ መረጃ ስልክ 0923257837 ቴሌግራም @Hoping7

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለአባ በአሚን ከመ አበው ምእመን ፍጹመ ፍኖት ከመ ጻድቃን"። ትርጉም፦ እንደ ጻድቃን መንገዱ የቀና እንደ አባቶች ታማኝ ለኾነው ለአባ በአሚን ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለከ በአሚን ስኩብ። በዐራተ ኀፂን ልሁብ። ለዕጓለ ማውታ ቀዋሚ ወለመዓስብ። ወሰላም ለእለ ምስሌሁ በቤተ መከራ ወጻሕብ። በእንተ ክርስቶስ ሙቁሐን ሕዝብ"። ትርጉም፦ በጋለ የብረት አልገጋ ላይ የተኛኽ፤ አጋር ለሌላት እና ለሙት ልጅ ጠበቃን ለኾንኽ በአሚን ሰላም ላንተ ይኹን፤ ከርሱ ጋር በጭንቅና መከራ ቤት ላሉ ስለ ክርስቶስ የታሰሩ ለኾኑ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 9። https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን ለጌታችን ለአምላካች ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለንዑስ በዓል ለአንዱ ለስብከት በሰላም አደረሰን። + + + ❤ በዚህ ሳምንት መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ በ፪ "ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ዘእምቅድመ ዓለም ሀሎ፣ አዝ፤ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ወተስፋ መነኰሳት ወልዶ መድኅነ ንሰብክ ወልዶ መድኅነ ንሰብከ"። ትርጉም፦ ቅድመ ዓለም በክብር በጌትነት የነበረ ዛሬም ያለ ወደ ፊትም ዓለምን አሳልፎ የሚኖር መድኃኒት ልጁን እንሰብካለን እርሱም የሰማዕታት ዘውድ ነው የካህናት ሿሚ ነው፣ የመነኰሳት ተስፋ ነው። + + + ❤ የዚህ ሳምንት እግ ነግ፦ "ሰበክዎ በኦሪት ወበነቢያት ለንጉሠ ስብሐት አክሊሎሙ አንተ ለሰማዕታት ሠያሜ ካህናት ክርስቶስ"። ትርጉም፦ ለክብር ንጉሥ (ለሚመሰገነው ንጉሥ) በኦሪትና በነቢያት አስተማሩት የሰማዕታት አክሊላቸው አንተ ነህ ካህናት የምትሾም ክርስቶስ አንተ ነህ። + + + ❤ ስብከት፦ ይህች ዕለት በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን ትውፊት "ስብከት" ትባላለች:: ስብከት ማለት በቁሙ "የምስራች አዲስ ዜና መንገርን" የሚመለከት ሲሆን ዋናው ምሥጢር ግን ከነገረ ድኅነት (ከመዳን ትምሕርት) ጋር የተገናኘ ነው። ❤ በዚህ ዕለት (ሳምንት) ሁሉም ነቢያት ከነ ትንቢታቸው ይታሰባሉ። ዘመነ ስብከትም ከታኅሣሥ 7 እስከ 13 ያለውን ይይዛል። በእነዚህ ቀናት ውስጥ በአንዱ እሑድ በሚውለበት ቀን ማኅሌት ተቁሞ ስብከት ተብሎ ይከበራል። ❤ ይሕስ እንደ ምን ነው ቢሉ:- እግዚአብሔር አዳምን በ7 ሃብታት አክብሮ በገነት ቢያኖረው "አትብላ" የተባለውን ዕፀ በለስ በላ። በዚህም ከፈጣሪው ተጣልቶ በሞተ ሥጋ ሞተ ነፍስ፤ በርደተ መቃብር ርደተ ገሃነም ተፈረደበት። በኋላ ግን ንስሃ ስለ ገባ "ከ5 ቀን ተኩል (5,500 ዘመን) በኋላ ከልጅ ልጅህ ተወልጄ አድንሃለሁ" የሚል ቃል ኪዳንን ሰጠው። ❤ ከዚህ በኋላ ለ5,500 ዘመናት ጊዜ ወደ ታች ይቆጠር ጀመር። ስለ እግዚአብሔር ሰው መሆንና ዓለምን ማዳንም ትንቢት ይነገር፤ ሱባኤ ይቆጠር፤ ምሳሌም ይመሰል ገባ። ❤ ከአዳም እስከ ሙሴ (ዘመነ አበው) ምሳሌያት ይበዛሉ። ከሙሴ እስከ ዳዊት (ዘመነ መሣፍንት) ምሳሌያቱ እየጐሉ መጥተዋል። ከልበ አምላክ ቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ሚልክያስ ድረስ (በዘመነ ነቢያት/ነገሥት) ግን ትንቢቶች ስለ ክርስቶስና ስለ ማደሪያ እናቱ እንደ ጐርፍ ፈሰዋል። ❤ ነቢያትም የመሲህን መምጣት እየጠበቁ በጾም፤ በጸሎትና በትሕርምት ኑረዋል። እንባቸውንም አፍሰው ቅድመ እግዚአብሔር ደርሶላቸዋል። መድኅን ክርስቶስም ተወልዶ አድኗቸዋል:: ❤ ነቢይ ማለት በቁሙ ኃላፍያትን (አልፎ የተሠወረውን ምሥጢር)፤ መጻዕያትን (ለወደ ፊት የሚሆነውን) የሚያውቅ ሰው ማለት ነው። ሃብተ ትንቢት የእግዚአብሔር የባሕርይ ገንዘቡ ሲሆን እርሱ ለወደደው በጸጋ ይሰጠዋል። እነዚህም ከጌታ ሃብተ ትንቢት የተሰጣቸው አባቶችና እናቶች "ቅዱሳን ነቢያት" በመባል ይታወቃሉ። ❤ ዘመነ ነቢያት ተብሎ የሚታወቀው ብሉይ ኪዳን ቢሆንም እስከ ምጽዓት ድረስ ጸጋውን እግዚአብሔር ለፈቀደላቸው አይነሳቸውም። በሐዋርያት መካከልም ቅዱስ አጋቦስን የመሰሉ ነቢያት ነበሩ። (የሐዋ ሥራ 11፥27) ቅዱሳን ነቢያት ከእግዚአብሔር እየተላኩ ሰውን ከፈጣሪው እንዲታረቅ ይመክራሉ፣ ይገስጻሉ። ከበጐ ሃይማኖታቸውና ንጽሕናቸው የተነሳም እግዚአብሔርን በተለያየ አርአያና አምሳል አይተውታል:: "እስመ በአንጽሖ መንፈስ ርዕይዎ ነቢያት ለእግዚአብሔር፤ ወተናጸሩ ገጸ በገጽ፤ መንፈስን ንጹሕ በማድረግ ነቢያት እግዚአብሔር አይተውታልና ፊት ለፊት ተያይተዋልና"። እንዳለ አባ ሕርያቆስ በቅዳሴ ማርያም። ❤ የብዙ ነቢያት ፍጻሜአቸው መከራን መቀበል ነው:: እውነትን ስለ ተናገሩ፤ አንዳንዶቹም በእሳት፣ አንዳንዶቹም በሰይፍ፣ አንዳንዶቹም በመጋዝ ተፈትነዋል። ሌሎቹ ለአናብስት ሲጣሉ ቀሪዎቹ ደግሞ በድንጋይ ተወግረዋል። ❤ ስለዚህም መከራቸው ለቤተ ክርስቲያን መሠረት ተብለዋል:: ጌታም ለደቀ መዛሙርቱ "ሌሎች ደከሙ፤ እናንተ በድካማቸው ገባችሁ" ብሎ የነቢያቱን መከራ ተናግሯል። ዮሐ. 4፥36 ❤ ነቢያት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን እና ድንግል እናቱን ለማየት ብዙ ጥረዋል፣ ሽተዋልም። "ብዙ ነቢያትና ጻድቃን እናንተ የምታዩትን ሊያዩ ሹ" እንዳለ ጌታ በወንጌል። (ማቴ. 13፥16፣ 1ኛ ጴጥ 1፥10) ዛሬ ግን በሰማያት ጸጋ በዝቶላቸው፤ ክብር ተሰጥቷቸው ሐሴትን ያደርጋሉ። ቅዱሳን ነቢያት በዋነኝነት 15ቱ አበው ነቢያት፣ 4ቱ ዐበይት ነቢያት፣ 12ቱ ደቂቀ ነቢያትና ካልአን ነቢያት ተብለው በ4 ይከፈላሉ። ❤ "15ቱ አበው ነቢያት" ማለት፦ 1 ቅዱስ አዳም አባታችን 2 ቅዱስ ሴት 3 ቅዱስ ሔኖስ 4 ቅዱስ ቃይናን 5 ቅዱስ መላልኤል 6 ቅዱሴ ያሬድ 7 ቅዱስ ኄኖክ 8 ቅዱስ ማቱሳላ 9 ቅዱስ ላሜሕ 10 ቅዱስ ኖኅ 11 ቅዱስ አብርሃም 12 ቅዱስ ይስሐቅ 13 ቅዱስ ያዕቆብ 14 ቅዱስ ሙሴና 15 ሳሙኤል ናቸው። ❤ "4ቱ ዐበይት ነቢያት" 1 ቅዱስ ኢሳይያስ ልዑለ ቃል 2 ቅዱስ ኤርምያስ 3 ቅዱስ ሕዝቅኤልና 4 ቅዱስ ዳንኤል ናቸው። ❤ "12ቱ ደቂቀ ነቢያት" 1 ቅዱስ ሆሴዕ 2 ቅዱስ አሞጽ 3 ቅዱስ ሚክያስ 4 ቅዱሴ ዮናስ 5 ቅዱስ ናሆም 6 ቅዱስ አብድዩ 7 ቅዱስ ሶፎንያስ 8 ቅዱስ ሐጌ 9 ቅዱስ ኢዩኤል 10 ቅዱስ ዕንባቆም 11 ቅዱስ ዘካርያስ 12 ቅዱስ ሚልክያስ ናቸው። ❤ "ካልአን ነቢያት" ደግሞ፦ 1 ቅዱስ ኢያሱ 2 ቅዱስ ሶምሶን 3 ቅዱስ ዮፍታሔ 4 ቅዱስ ጌዴዎን 5 ቅዱስ ዳዊት 6 ቅዱስ ሰሎሞን 7 ቅዱስ ኤልያስ 8 ኤልሳዕ ሌሎችም ናቸው። ❤ ነቢያት በከተማም ይከፈላሉ፦ 1 የይሁዳ (ኢየሩሳሌም) 2 የሰማርያ (እሥራኤል) 3 የባቢሎን (በምርኮ ጊዜ) ተብለው ይጠራሉ። ❤ በዘመን አከፋፈል ደግሞ፦ 1 ከቅዱስ አዳም እስከ ቅዱስ ዮሴፍ (የዘመነ አበው ነቢያት)። 2 ከሊቀ ነቢያት ቅዱስ ሙሴ እስከ ነቢዩ ቅዱስ ሳሙኤል (የዘመነ መሳፍንት ነቢያት)። 3 ከቅዱስ ዳዊት እስከ ቅዱስ ዘሩባቤል ያሉት (የዘመነ ነገሥት ነቢያት)። 4 ከቅዱስ ዘሩባቤል ዕረፍት እስከ መጥምቁ ቅዱስ ዮሐንስ ያሉት ደግሞ (የዘመነ ካህናት ነቢያት) ይባላሉ። ምንጭ፦ ከዲያቆን ዮርዳኖስ አበበ ፔጅ። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ፈኑ እዴከ እምአርያም። አድኅነኒ ወባልሐኒ እማይ ብዙኅ። ወእምእዴሆሙ ለደቂቀ ነኪር"። መዝ 143፥7። የሚነበቡት መልዕክታት ዕብ 1፥1-ፍ.ም፣ 2ኛ ጴጥ 3፥1-10 እና የሐዋ ሥራ 3፥17-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 1፥44-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ እግዚእነ ነው። መልካም የስብከት በዓልና የነቢያት (የገና) ጾም ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ ቅዱስ አባ በአሚንም ፈጽሞ በአረጀ ጊዜ የሞት ደዌን ታመመ መነኰሳቱንም ሁሉ ሰብስቦ ዕድሜው እንደ ቀረበ ነገራቸውና አጽናናቸው እነርሱም ከእርሱ ስለመለየታቸው አዘኑ ከዚህም በኋላ በፈጣሪው እግዚአብሔር እጅ ነፍሱን ሰጠ። መነኰሳቱም እንደሚገባ እያመሰገኑና እየዘመሩ መልካም አገናነዝን ገንዙት ሥጋው በእምነት ወደርሱ ለሚመጣ ሁሉ መጠጊያ ሆነ ወይም በቀናች ሃይማኖት ጸንቶ ወደ ቤተ ክርስቲያን ሒዶ በስሙ ለሚለምን ሁሉ የለመነው ይሆንለታል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ በአሚን ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 9 ስንክሳር። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ሊኩን ይጫኑት https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፱ (9) ቀን። ❤ እንኳን ያለደምን መፍሰስ ሰማዕትነት ለተቀበለ ታማኝ ለሆነ ለቅዱስ አባት ለአባ በአሚን ለዕረፍት በዓል በሰላም ደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከቅዱሳን ከበድላም፣ ከአርምያና ከዘካርያስ ከዕረፍታቸው መታሰቢያ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ አባ በአሚን፦ እርሱም በደቡብ ግብጽ በእስሙናይን አውራጃ ለአገረ ቴርሳ አቅራቢያ ከሆኑ ከሐፂብ ተወላጆች ወገን ነው ለአንድ ባለጸጋም በጅሮንድ ሆኖ ሳለ ስለ ንጽሕናውና ስለ ቅድስናው በሁሉ ዘንድ ተወዳጅ ሆነ የባለ ጸጋውም ሚስት አባ በአሚንን እጅግ የምትወደውና የምትተማመንበት ሆነች። ❤ እርሱ ግን የዚህን ዓለም ፍጻሜ አሰበ የባለ ጸጋውንም አገልግሎት ትቶ ወደ ገዳም ሒዶ መነኰሰ ባለጸጋውም መሔዱን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ ሚስቱንም ይዞ አባ በአሚን ወዳለበት በአንድነት ሔዱ ወደ እርሳቸው እንዲመለስም ለመኑት እንዲህም አሉት "ከአንተ እንለይ ዘንድ ከቶ አንችልም ስለዚህ አንተውህም" አሉት። አባ በአሚንም "እኔ ራሴን ብፅዓት አድርጌ ለእግዚአብሔር ሰጥቻለሁ እኮን" አላቸው። ይህንንም ሲሰሙ ከእርሱ በመለየታቸው እያዘኑ ትተውት ተመለሱ። ❤ ከዚህም በኋላ በአማረ ተጋድሎ ሁሉ ታላቅ ተጋድሎን በመጋደል ብዙ ዘመናት እግዚአብሔርን አገለገለው። ከዚህም በኋላ ክብር ይግባውና ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ ምስክር ሁኖ ደሙን ሊአፈስ ወዶ ወደ እንዴናው ከተማ ሒደ ብዙዎች ምእመናንንም ሲአሠቃዩአቸው አገኛቸው እርሱም ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ ጽኑ ሥቃይንም አሠቃዩት ሥጋውን በእሳት ለበለቡ ሕዋሳቱንም ሠነጣጥቀው ከመንኰራኵር ውስጥ ጨመሩት ዳግመኛም በአጋሏቸው የብረት ዘነሰጎች አቃጠሉት በዚህም ሁሉ ጸና ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስን ክርስቶስም ያለ ጉዳት በጤና ያስነሣው ነበር። ❤ እንዲህም እየተሠቃየ ሳለ ጣዖት የሚመለክበት ወራት አለፈና ጻድቁ ቈስጠንጢኖስ ነገሠ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ስም ዲዮቅልጥያኖስ ያሠራቸውን እሥረኞች ሁሉ እንዲፈቷቸው አዘዘ ጌታችንም ለአባ በአሚን ተገለጠና ከሰማዕታት ጋር እንደቆጠረው አስረዳው። ንጉሥ ቈስጠንጢኖም ከእርሳቸው ቡራኬ ሊቀበል ሽቶ ከውጣቸው ሰባ ሁለት እሥረኞችን ወደርሱ ያመጡ ዘንድ አዘዘ አባ ኖብ ከእርሳቸው ጋር በዚያ ነበር ከእርሳቸውም አንዱ ይህ አባ በአሚን ነው። ❤ ከዚህም በኋላ ከእሥሙናይን ውጭ በሆነች ገዳም የሚኖር ሆነ ጌታችንም ታላቅ ጸጋን ሰጥቶት በሽተኞችን ሁሉ የሚፈውሳቸው ሆነ ዜናውም ቦታው ሁሉ ተሰማ። በዚያም ወራት የሮሜ ንጉሥ ሚስት የሆነች አንዲት ንግሥት ነበረች እርሷም ከእርሷ ጋር ስለሚኖር የወንጌላዊውን ዮሐንስ የራእዩን መጽሐፍ ሁል ጊዜ የሚያነብላት የሆነ እግዚአብሔርን ስለሚፈራ ስለ አንድ ዲያቆን እጅግ የታመመች ናት ከንጉሥ ሹሞች አንዱ በቀናበት ጊዜ ወደ ንጉሡ ሒዶ "ጌታዬ ሁል ጊዜ የዮሐንስ የራእዩን መጽሐፍ በማንበብ እያመካኘ ከእመቤቴ ንግሥት ጋር ይተኛል" አለው። ❤ ንጉሡም ይህን በሰማ ጊዜ እጅግ አዘነ በዚያንም ጊዜ ተነሥቶ ንግሥቲቱ ወዳለችበት ቤተ መንግሥት ገባ ያንንም ዲያቆን በፊቱ ቁሞ የዮሐንስን የራእይ መጽሐፍ ሲያነብ አገኘውና ከነመጽሐፉ ወስደው ዲያቆኑን ከባሕር እንዲአሠጥሙት አዘዘ ሁለት ሰዎችም በታናሽ ጀልባ ጭነው ወስደው ከባሕር መካከል ወረወሩት ወዲያውኑ ብርሃንን የለበሰ ሰው ከሰማይ ወርዶ ያንን ዲያቆን ከመጽሐፉ ጋር ነጥቆ ወስዶ ከአንዲት ደሴት ላይ አኖረው እነዚያ ሁለት ሰዎች ሲያዩ ነበር እጅግም እያደነቁ ተመለሱ ያዩትንም ለንጉሡ አልነገሩትም። ❤ ንግሥቲቱም በዲያቆኑ ላይ የተደረገውን በአየች ጊዜ እጅግ አዘነች በእርሷም ደዌ ጸናባት ሆድዋም ቈስሎ ዐሥራ አምስት ዓመት ኖረች ወደርሷም ብዙ ጥበበኞች ባለመድኃኒቶች መጥተው ነበር ግን ሊፈውሷት አልቻሉም አንድ አዋቂ ሰውም እንዲህ ብሎ መከራት "በግብጽ አገር ወደሚኖሩ ቅዱሳን ብትሔጂ ከደዌሽ በተፈወስሽ ነበር"። በዚያን ጊዜ ተነሣች ከእርሷም ጋር ብዙ ሠራዊት አለ ወደ ግብጽ አገርም ደርሳ ገዳማቱንና አብያተ ክርስቲያንንም ሁሉ ዞረች ግን አልዳነችም። ❤ ወደ እንዴናው ከተማም በደረሰች ጊዜ ስለ መምጧቷ የአገሩ መኳንንት አደነቁ እርሷም ችግርዋን ሁሉ ነገረቻቸው እነርሱም ወደ ቅዱስ አባ በአሚን እንድትሔድ መከሩዋት በመርከብም ተሳፍራ ወዲያውኑ ቅዱስ አባ በአሚን ወዳለበት ገዳም ደረሰች "እንሆ ንግሥት ወዳንተ መጥታለች ከአንተም ልትባረክ ትሻለች" ብለው ነገሩት እርሱም "ከምድር ንግሥት ጋር ምን አለኝ" ብሎ መውጣትን እምቢ አለ መነኰሳትወደርሷ እንዲወጣ አጽንተው ለመኑትና ወጣ በአየችውም ጊዜ ከእግሩ በታች ወድቃ ሰገደችለት እርሱም በዘይት ላይ ጸልዮ ቀባት በዚያንም ጊዜ ዳነች። ቅዱስ አባ በአሚንም "ንጉሥ ከባሕር በአሠጠመው በዚያ ዲያቆን ምክንያት ይሁ ሁሉ እንደደረሰብሽ ዕወቂ እርሱ ግን በአንዲት ደሴት ውስጥ በሕይወት ይኖራል የአቡቀለምሲስ ዮሐንስ የራእይ መጽሐፍም ከእርሱ ጋር አለ" አላት። ንግሥቲቱም ሰምታ እጅግ አደነቀች ደስ አላትም ስለዚያ ዲያቆን በሕይወት መኖርና እርሷም ፈውስ ስለማግኘቷ ለቅዱስ አባ በአሚንም እጅ መንሻ ብዙ ገንዘብ አቀረበችለት ከንዋየ ቅድሳት በቀር ምንም ምን ገንዘብ አልተቀበለም። ❤ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔርን እያመሰገነች ወደ ሮሜ አገር ተመለሰች በእርሷ ላይ የሆነውን ሁሉ ወደ ባሕር ስለ አሠጠሙት ስለዚያ ዲያቆንም እርሱም እስከ ዛሬ በአንዲት ደሴት ውስጥ በሕይወት እንዳለ ለንጉሡ ነገረች። ንጉሡም ይህን ነገር ሰምቶ እጅግ አደነቀ ይፈልጉትም ዘንድ መልክተኞችን ላከ በደሴትም ውስጥ በሕይወት አገኙት መጽሐፉም ከርሱ ጋር አለ ተመልሰውም ለንጉሡ ነገሩት ሁለተኛም ወደርሱ እንዲመጣ እየማለደ ላከ ከመልክተኞችም ጋር ወደ ንጉሡ መጣ ንጉሡም በአየው ጊዜ ታላቅ ደስታ አደረገ ከእግሩ በታችም ወድቆ "በአንተ ላይ ስለአደረግሁት በደል ይቅር በለኝ" አለው እርሱም "በአንድነት እግዚአብሔር ይቅር ይበለን" አለ። ከዚህም በኋላ ያ ዲያቆን በሮሜ አገር ላይ ሊቀ ጵጵስና ተሾመ ያንንም የዮሐንስ አቡቀለምሲስ ራእይ ተረጐመው። ❤ ቅዱስ አባ በአሚንም በቀንና በሌሊት ያለማቋረጥ የሚጋደል ሆነ። በአቅራቢያውም አንድ ደግ ኤጲስቆጶስ አለ በአንዲት የሰማዕታት ገዳም ከምእመናን ጋር በዓልን ሲያደርግ አርዮሳውያንም ለራሳቸው ሐሰተኛ ኤጲስቆጶስ ይዘው ሕዝቡን የሚያስቱ ሆኑ የአገሩም ኤጲስቆጶስ ወደ አባ በአሚን መጥቶ ስለ እሊህ ከሀድያን ምክር የደረሰበትን ኃዘኑን ሁሉ ነገረው። የሰማዕታትም በዓል በሆነ ጊዜ የእሊህን ከሀድያን ምክር እግዚአብሔር ይበትን ዘንድ ቅዱስ አባ በአሚን ከሕዝቡ ጋር በመለመንና በመስገድ ጸለየ ከዚህም በኋላ የሽመል በትር ያዘ ሕዝቡም ሁሉ እየአንዳዱ በትሮችን ይዘው ወደእነዚያ ከሀድያን ሔዱ ከሀድያንም በአዩ ጊዜ ተበተኑ ወደዚያ ዳግመኛ አልተመለሱም እግዚአብሔር ምክራቸውን በትኖባቸዋልና።