ሰዋስው ☘☘☘☘
رفتن به کانال در Telegram
በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።
نمایش بیشتر1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
1 161
የ22/04/2015 ምስባክ
በቅዳሴ ጊዜ
✍"ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ
ወትሰይሚዮሙ መላዕክተ ለኩሉ ምድር
ወይዘክሩ ስመኪ በኩሉ ትውልደ ትውልድ"
📖መዝ 44፥16-18
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
+ + +
❤ "ሶበ ጸሐፈ ደቅስዮስ ተአምረኪ ቅዱሰ። መንበረ ወዐጽፈ ዕሤተ ጻማሁ ወረሰ። ማርያም ድንግል ዘታብእሊ ፅኑሰ። ዐስበ ማሕሌትየ ዐቅመ ልብየ ኀሠሠ።ጸግውኒ አትሮንሰ ወጽጉየ ልብሰ"። ትርጉም፦ ደቅስዮስ ልዩ የኾነ ተአምርሽን በጻፈ ጊዜ የድካሙን ዋጋ ልብስንና ወንበርን አገኘ፤ ድኻውን ባለጠጋ የምታደርጊ (ነዳየ አእምሮውን በቃል ኪዳንሽ ባለ አእምሮ የምታደርጊ) ድንግል ማርያም ልቡናዬ በፈለገ መጠን የምስጋናዬን ደሞዝ ወንበርንና የክብር ልብስን ስጪኝ። አባ ጽጌ ድንግልና አባ ገብረ ማርያም ዘደብረ ሐንታም በማሕሌተ ጽጌ።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ይቀላቀሉ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፳፪ (22) ቀን።
❤ እንኳን እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያምን የከበረ ሊቀ መላእክት ቅዱስ ገብርኤል በአበሠራት መሠረት ቅዱስ ደቅስዮስ በዓል ላከበረት (ለብስራት) ዓመታዊ መታሰቢያ በዓልና የእመቤታችንን ተአምረ ማርያም መጽሐፍ ለጻፈው ለቅዱስ ደቅስዮስ ለዕረፍት መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰ። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከከበረ መልአክ ከመላእክት አለቃ ከቅዱስ ገብርኤል ከበዓሉ መታሰቢያ ዳህና በሚባል አገርም ቤተ ክርስቲያኑ ከተሠራችበትና ከከበረችበት ተአምራትም ካሳየበትና ከአገር ኤጲስቆስ አርኬላዎስ ምስክር ከሆነበት፣ ከእስክድርያ አገር ሠላሳ ስድስተኛ ጳጳስ ከከበረ ከአባት ከአባ አንስጣስዮስ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ የብስራት መዝሙር፦ "አብሠራ ወይቤላ ለማርያም ገብርኤል አብሠራ መልአክ። አልቦ ማኅለቅት ለሰላሙ ዲበ መንበረ ዳዊት መንግሥቱ ትፀንዕ። ትርጉም፦ ገብርኤል ማርያምን እንዲህ ብሎ አበሠራት ለሰላሙ ፍጻሜ የለው በዳዊት መንግሥት መንበር ላይም መንግሥቱ ስልጣኑ ትፀናለች፡፡
+ + +
❤ ቅዱስ ደቅስዮስ በዓለ ብስራትን ማክበሩ፦ በዓልን የማክበሩ ምክንያትም እንዲህ ሆነ ይህ ኤጲስቆጶስ ደቅስዮስ ከፍቅሩ ጽናት የተነሣ አስቦ በመትጋት የተአምራቷን መጽሐፍ ሰብስቦ አዘጋጀላት። የምእመናን ክብር የሆነች አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ማርያምም ተገለጸችለትና መጽሐፋን በእጅዋ አንሥታ ይዛ "ወዳጄ ደቅስዮስ ሆይ ይህን መጽሐፍ ስለ ጻፍክልኝ ባንተ ደስ አለኝ አመሰገንኩህም" አለችው ከዚህም በኋላ ከእርሱ ተሠወረች። ቅዱስ ደቀስዮስም ይህን ነገር በራይ ባየ ጊዜ ክብርት ድንግል እመቤታችን ማርያምን ከመውደዱ የተነሣ ፈጽሞ ደስ አለው እርሷንም ስለ ወደደ ፍቅርዋ እንደ እሳት አቃጠለው የሷን ክብር አብዝቶ ይጨምር ዘንድ ምን እንደሚያደርግ የሚሠራውን ያስብ ጀመር።
❤ ከዚህም በኋላ በዚያን ጊዜ ጾም ስለነበር ሰዎች አስቀድመው ሊአከብሩት ያልተቻላቸውን የመላእክት አለቃ የከበረ ቅዱስ ገብርኤል ባበሠራት ቀን በዓሏን አከበረ። እርሱም የከበረ የሚሆን የልደትን በዓል ከማክበር አስቀድሞ በስምንት ቀን አደረገ ይኸውም ታኅሣሥ በባተ በሃያ ሁለት ቀን ነው በጵጵስናውም ዘመን ተሠርታ እስከዚች ቀን ጸንታ ትኖራለች። ሰዎችም በዓሉን በአከበሩት ጊዜ ፈጽሞ ደስ አላቸው።
❤ ደግነትን ምሕረትን ቸርነትን የምትወድ አምላክን የወለደች በድንጋሌ ሥጋ በድንጋሌ ነፍስ የጸናች ክብርት እመቤታችን ማርያም በእጅዋ የከበረ ልብስ ይዛ ዳግመኛ ተገለጸችለትና "አገልጋዬ የሆንክ ወዳጄ ደቅስዮስ ሆይ በእውነት አመሰገንኩህ በአንተም ደስ አለኝ ሥራህንም ወደድሁ። በእኔም ደስ እንዳለህና የከበረ መልአክ ገብርኤል እኔን በአበሠረበት ቀን በዓሌን ስለአከበርክ ሰውንም ሁሉ ስለ እኔ ደስ ስለአሰኘህ እኔም ዋጋህን ልሰጥህ አንተ በዚህ ዓለም እንዳከበርከኝም በሰው ሁሉ ፊት አከብርህ ዘንድ እወዳለሁ" አለችው። እሷም "ትለብስ ዘንድ ይችን ልብስ እነሆ አመጣሁልህ በላዩም ትቀመጥ ዘንድ ይህን ወንበር አመጣሁልህ ከሰው ወገን አንድ ስንኳ ይህችን ልብስ ሊለብሳት በዚህም ወንበር ላይ ሊቀመጥ የሚቻለው የለም። ይህን ነገሬን የሚተላለፍ ቢኖር እኔ እበቀለዋለሁ" አለችው ይህንንም ተናግራ ከእርሱ ተሠወረች።
❤ ከዚህም በኋላ ታኅሣሥ22 ቀን በዐረፈ ጊዜ ሌላ ኤጲስቆጶስ ተሾመ ያቺንም ልብስ ለበሳት በወንበሩም ላይ ተቀመጠ ወዲያውኑ ከወንበሩ ላይ ወድቆ ሞተ ይህንንም ያዩ ከእመቤታችን ማርያም ተአምር የተነሣ አደነቁ እጅግም ፈርተው እመቤታችንን አከበሩዋት ምስጉን እግዚአብሔርንም አመሰገኑት ለእርሱም ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ በዚች ቀን የከበረ መልአክ የመላእክት አለቃ የቅዱስ ገብርኤል የበዓሉ መታሰቢያ ዳህና በሚባል አገርም ቤተ ክርስቲያኑ የተሠራችበት ተአምራትም ያሳየበትና በዚች ቀን ቤተ ክርስቲያኒቱ የከበረችበት ነው የዚያች አገር ኤጲስቆጶስ አርኬላዎስ ምስክር የሆነበት ነው።
❤ ይህም መልአክ ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ምሥጢር የታመነ ሆኖ ወደ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተላከ "የደስታ መገኛ ደስ ይበልሽ ጸጋን የተመላሽ ሆይ እግዚአብሔር ካንቺ ጋር ነው አንቺም ከሴቶች ተለይተሽ የተባረክሽ ነሽ" አላት።
❤ ስለ መጥምቁ ዮሐንስ መወለድም ካህኑን ዘካርያስን ያበሠረው እርሱ ነው ይህ መልአክ እጅግ የከበረ የተመረጠ ገናና የሆነ ነውና ስለ እኛ ወደ እግዚአብሔር ይማልድ ዘንድ ልባችንን አንጽተን ወደዚህ የከበረ መልአክ እየለመንን መታሰቢያውን ልናደርግ ይገባል። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በዚህ በከበረ መልአክ በቅዱስ ገብርኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱ ረድኤቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ22 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም እብል ለደስቅዮስ ባሕርያ። ኤጺስቆጶስ ዘሀገረ ጥልጥልያ። በእንተ ዘጸሐፈ ላቲ ትምእምርተ ዜናሃ ወጸጋ ዕበያ። እንተ ወሀበቶ ወላዲተ አምላክ ማርያ። ልብሰ ሰማያዊት እስከ ዮም ነያ"። አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ22።
+ + +
❤ የዕለቱ ማኅሌቱ ምስባክ፦ "በቅድመ መላእክቲከ እዜምር ለከ። ወእሰግድ ውስተ ጽርሐ መቅደስከ። ወእገኒ ለስመከ። መዝ 137፥1-2። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ1፥26-39።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ህየንተ አበውኪ ተወልዱ ለኪ ደቂቅ። ወትሠይም(ሚ)ዮሙ መላእክተ በኵሉ ምድር። ወይዘክሩ ስመኪ በኵሉ ትውልደ ትውልድ"። መዝ 44፥16-17። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ጢሞ 1፥8-ፍ.ም፣ 1ኛ ዮሐ 4፥9-18 እና የሐዋ ሥራ 12፥7-12። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥39-57። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታች የማርያም ቅዳሴ ነው፡፡ መልካም የብስራት ቅዱስ ገብርኤል በዓል፣ የቅዱስ ደስቅዮስ የዕረፍት በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ይቀላቀሉ።
https://t.me/Eotcw
1 161
እንኳን አደረሳችሁ /ብስራተ ገብርኤል/
አብሰራ ገብርኤል ለማርያም ወይቤላ ትወልዲ ወልድ
ሚካኤል መልአክ በክነፍፁራ ( በክንፉ ከለላ) መንጦላዕት ደመና ሰወራ ንፅህት በድንግልና አልባቲ ሙስና ተወልደ ወልድ እምኔሃ፤
ገብርኤል ማርያምን አበሰራት ) ወንድ ልጅም ትወልጃለሽ አላት
ሚካኤል መልአክ በክንፉ ከለላት የሰማይ መጋረጃውን ሸፈናት ንፅህት ናትና በድንግልና ንፅህትና ጥፋት የለባትም እና ወንድ ልጅን ወልዳልናለችና💚💛❤️
በተወደደችው ዓመት እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም በአረጋዊው በዮሴፍ ቤት እያለች የትሩፋት ሥራን ትሠራ ነበርና ውሃ ለመቅዳት በሀገራቸው ወደሚገኘው ወደ ውሃ ጉድጓድ ሄዳ ስትመለስ "ሑር አብሥራ ለማርያም ከመ እትወለድ እምኔሃ ፤ከእርሷ እንድወለድ ሄደህ ለድንግል ማርያም ንገራት ብሎ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤልን ወደ እርሷ ላከው( ሉቃ፩ ፣፳፮)
ለጊዜው ዮሐንስ በመስከረም ወር ተፀንሷልና የጌታ ፅንስ ደግሞ በመጋቢት ፳፱ ነውና ከመስከረም አንስቶ እስከ መጋቢት ቢቆጥሩ ስድስት ወር ይሆናልና በስድስተኛው ወር አለ ፤ ፍፃሜው ግን በስድስተኛው ቀን በዕለተ አርብ የተፈጠረው አዳም በድሎ ነበርና እርሱን ለማዳን በእርሱ ያጣነውን ልጅነት ለመመለስ እንደመጣ ለማጠየቅ ሲሆን ዳግመኛም ፭ሺህ ፭መቶ ዘመን ተፈጽሞ በስድስተኛው ሺህ ዘመን መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ከጌታ ወደ እመቤታችን ተላከ ለማለት በስድስተኛው ወር ብሎ ጽፏል ቅዱስ ሉቃስ ።
መጋቤ ሐዲስ የተባለ ቅዱስ ገብርኤል በደስታ የብርሃን ቀበቶውን እያሰረ እየፈታ በትህትናም እየስገደ የድርቀት ዘመን አበቃ የልምላሜ ዘመን መጣ ሲል ለምለም አበባን ይዞ አንድም የጨለማው ዘመን አበቃ ብርሃንምሊገለጥ ነው ሲል በብርሃን ፀዳል ተሞልቶ ተገልጾላት ብሥራትን አሰማትፀጋ የመላብሽ ሆይ ደስ ይበልሽ አላት ፣እርሷም አይታው ሄደች ኋላም ወደ ቤት ገብታ እንስራዋን / ማድጋዋን አሳርፋ በቆመችበት ተሰውሮ ደስ ይበልሽ እንሆ ትጸንሻለሽ አላት ፣
እርሷም የነገሩን መደጋገም አስተውላ መልካም ነገርን በመልካም ቦታ ሆነው ሊረዱት ይገባል ብላ ወደ ቤተ መቅደስ ሄዳ በዚያ ወራት ለቤተ መቅደስ መጋረጃ ለመፍተል ከደናግለ እስራኤል ጋር የተካፈለችውን ሐርና ወርቅ እያስማማች ስትፈትል በደስታ እየሰገደ ተገልጾ ትጸንሲ ወትወልዲ ብሎ አበሠራት። ቅዱስ ያሬድም ሐርና ወርቅን አስማምታ ስትፈትል መላዕኩ እንዳበሠራት በድጓው ላይ ገጽ 232
"ቅዱስ ገብርኤል መልአከ ፍስሐ በእሳት ሥዑል
ሰበካ ለድንግል ምጽአቶ ለቃል
ወርቀ ወሜላተ እንዘ ትፈትል፤
በእሳት የተቀረጸ የደስታ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ወርቅንና ሐርን ስትፈትል የቃል መምጣቱን ሥጋ መሆኑን ለድንግል አበሠራት በማለት ሲገልጸው ሊቁ አባ ጽጌ ድንግልም
" ፈትለ ወርቅ ወፈትለ ሜላት አመ በአጽባእትኪ ተባየጹ
አምሳለ መለኮት ወትስብዕት እንዘ ኢየሐየፁ
ተአምረ ብርሃን ማርያም ለፀሓዬ ጽድቅ አንቀጹ
ጸገይኪዮ እንበለ አብ በሰሚአ ቃሉ ወድምፁ
ለገብርኤል መልአክኪ ዘፍሱሕ ገጹ"
የእውነት ፀሐይ መውጫ የብርሃን ምልክት ማርያም የትስብዕት እና የመለኮት ተዋሕዶ አምሳል ሳያጎድሉ የሐርንና የወርቅን ፈትሎች በጣቶች ሽ በሚፈትሉበት ጊዜ ፊቱን ደስ ያለው የተላከልሽ የገብርኤል ድምፁን በመስማት ጌታን ያለአባት ፀነሺው በማለት ገልጾታል ።
በዲ/ን የአብስራ ጌታሁን
1 161
የነቢያት /የገና/ ፆም የመጨረሻ ሳምንት ኖላዊ ተብሎ ይጠራል፡፡
ኖላዊ ማለት እረኛ ማለት ነው። ነቢያት ራሳቸውንና ሕዝበ እስራኤልን ብሎም ዓለምን
እረኛቸው እንደተዋቸው በጎች በመቁጠር እውነተኛ እረኛ ሆኖ የእግዚአብሔር ልጅ
ይገለጣል ብለው መተንበያቸውንና ኢየሱስ ክርስቶስ እውነተኛ እረኛ መሆኑን እያሰበች
ቤተ ክርስቲያን የምትዘምርበት፣ የምትቀድስበትና፣ የምታመሰግንበት ወቅት ነው። በዚህ ጊዜም ከፍልሰተ ባቢሎን እስከ ልደተ ክርስቶስ ድረስ ያለው አሥራ አራት ትውልድ
ይታሰባል። እረኛ የሌለው በግ ተኵላ ነጣቂ እንዲበረታበት በበደሉ ምክንያት ከትጉህ
እረኛው የተለየው የሰው ልጅም ሰብሳቢና የሚያሰማራ ጠባቂ እንዲኖረው ነቢያት ዮሴፍን
እንደ መንጋ የምትመራ በኪሩቤል ላይ የምትቀመጥ የእስራኤል ጠባቂ ሆይ አድምጥ
(መዝ፦79፥1) በማለት ይማፀኑ ነበር።
ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ጊዜው ሲደርስ መልካም እረኛ እኔ ነኝ፤ መልካም
እረኛ ነፍሱን ስለ በጎቹ ያኖራል" ዮሐ፣ 10፥11 በማለት መልስ ሰጥቷል። "እግዚአብሔር
እረኛዬ ነው የሚያሳጣኝ የለም በለመለመ መስክ ያሳድረኛል መዝ፥(22፦1-2) ተብሎ
እንደተጻፈ በዚህ የጾም ወቅት አቤቱ ብርሃንህንና ጽድቅህን ላክ፣ ቸሩ እረኛችን ሆይ
ተቅበዝብዘናልና እባክህ አስበን፣ የቀዘቀዘው ፍቅራችንን መልስልን፣ አንተ እውነተኛ
ሰላምህን ስጠን እያልን ምንም ወደ ማያሳጣን ወደ እውነተኛው እረኛችን ጌታ ኢየሱስ በንስሐ ልንመለስ ይገባል።እረኛችን ጌታ ኢየሱስ በቸርነቱ ይቀበለን ይጠብቀን አሜን!!
1 161
ታኅሣሥ 21
በቅዳሴ ጊዜ
#ምስባክ
መዝ ፵፬ ቊ፱-፲
ወትቀውም ንግሥት በየማንከ።
በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኁብርት።
ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወጽምዒ እዝነኪ።
#ትርጉም
የንግሥት ሴቶች ልጆች ለክብርህ ናቸው፣
በወርቅ ልብስ ተጎናጽፋና ተሸፋፍና ንግሥቲቱ በቀኝህ ተቆማለች፣
https://t.me/Eotcw
1 161
21/04/2015 ዓ.ም
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚባል ምስባክ
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯
ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ።
ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ፡፡
ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ። መዝ. 18፥4
🕯 ትርጉም
ድምፃቸው በምድር ላይ ተሰማ።
ቃላቸውም ሁሉ እስከ ዓለም ዳርቻ ወጣ።
በእነርሱም ውስጥ የፀሐይን ድንኳን አደረገ።
🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፳፩ (21) ቀን።
❤ እንኳን ከሰባ ሁለቱ አርድእት ለአንዱ የስሙ ትርጓሜ የመረጋጋት ልጅ ለሆነ ለሐዋርያው ለቅዱስ በርናባስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱና ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ለወራዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰበው፦ በበግ እረኛ (ኖላዊ) አምሳል መድኃኒታችን ከተገለጸበት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ በዚች ቀን የእመቤታችን አምላክን የወለደች የቅድስት ድንግል ማርያም የበዓልዋ መታሰቢያ ነው። እርሷ የባህርያች መመኪያ ናትና በእርሷ በእናቱ አማላጅነት ጌታችን ይጠብቀንና ያድነን ዘንድ መታሰቢያዋን እያደረግን ወደርሷ እንለምን ዘንድ ይገባል። እርሷን ሕይወትን መድኃኒትን አድርጎ ለሰጠን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ ቅዱስ በርባስ፦ ይህም ቅዱስ ሐዋርያ ከሊዊ ነገድ የሆነ አገሩ ቆጵሮስ ነው የቀድሞ ስሙ ዮሴፍ ነው ክብር ይግባውና ጌታችን ከመከራው በፊት ይሰብኩ ዘንድ ከላካቸው ከሰባ ሁለት አርድእት ጋር መረጠው ስሙንም በርናባስ ብሎ ጠራው። ከጌታ ዕርገትም በኋላ አጽናኝ መንፈስ ቅዱስ በወረደ ጊዜ እርሱም ከሐዋርያት ጋር የመንፈስ ቅዱስን ስጦታ ተቀብሎ ክብር ይግባውና በጌታችን በኢየሱስ ክርስቶስ ስም አስተማረ። የእርሻ ቦታ ነበረውና ሽጦ ዋጋውን አምጥቶ ከሐዋርያት እግር በታች አኖረው።
❤ ቅዱስ ጳውሎስም በጌታችን አምኖ ወደ ሐዋርያት በመጣ ጊዜ ክብር ይግባውና ለክርስቶስ እርሱ ደቀ መዝሙሩ እንደሆነ ሐዋርያት አላመኑትም ነበር። ይህ በርናባስ ጌታችን በመንገድ እንደ ተገለጸለትና እንደአነጋገረው እርሱም በጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ ስም በደማስቆ እንደ አስተማረ ነገራቸው። ከዚህም በኋላ የእግዚአብሔርን ሥራ ሲሠሩ ሲጾሙ ሲጸልዩ መንፈስ ቅዱስ "ሳውልና በርናባስን እኔ እነርሱን ለመረጥኩት ሥራ ለዩልኝ" አላቸው።
❤ ከዚህም በኋላ ጹመው ጸልየው እጆቻቸውን በራሳቸው ላይ ጭነው ሾሟቸው። ከመንፈስ ቅዱስም ተሹመው ወደ ሴሌውቅያ ወረዱ ከዚያም ወደ ቆጵሮስ ሔዱ የእግዚአብሔርንም ቃል በአገሩ ሁሉ አስተማሩ። ልስጥራን በተባለ አገርም ልምሾ የነበረውን ሰው በአዳኑት ጊዜ የልስጥራን ሰዎች መሥዋዕትን ሊሠዉላቸው ወደዱ። ሐዋርያት ቅዱስ ጳውሎስና በርናባስም በሰሙ ጊዜ ልብሳቸውን ቀድው ወደ ሕዝቡ ሔዱ ድምፃቸውንም ከፍ አድርገው እንዲህ አሏቸው "እናንት ሰዎች ይህ ነገር ምንድን ነው እኛማ እንደናንተ የምንሞት ሰዎች አይደለንምን ይህን ከንቱ ነገር ትታችሁ ሰማይና ምድርን ባሕርንም በውስጧቸው ያለውን ሁሉ ወደ ፈጠረ ወሕያው እግዚአብሔር ትመለሱ ዘንድ እናስተምራችኋለን" አሏቸው እንዲህም ብለው መሠዋትን በጭንቅ አስተዋቸው።
❤ ከዚያም ብዙ አገሮችን ከአስተማሩ በኋላ ቅዱስ በርናባስ ከቅዱስ ጳውሎስ ተለይቶ ቅዱስ ማርቆስን ይዞ ወደ ቆጵሮስ ሔደ በዚያም አስተማረ ብዙዎችን ክብር ይግባውና ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ወደ ማመን መለሳቸውና የክርስትና ጥምቀትን አጠመቃቸው።
❤ በቆጵሮስ አገር የሚኖሩ አይሁድም ቀኑበት በመኳንንትም ዘንድ ወነጀሉት በእግር ብረትም አሥረው ጽኑ ግርፋትን ገረፉት ከዚህም በኋላ በደንጊያ ወገሩት ዳግመኛም ወስደው ከእሳት ጨመሩት ምስክርነቱንም ፈጸመ። ቅዱስ ማርቆስም ከርሱ ጋር አለ ግን እግዚአብሔር ጠብቆ አተረፈው። እርሱም ቅዱስ በርናባስን ከእሳት ውስጥ አወጣው ሥጋውንም እሳት ከቶ አልነካውም በአማሩ ልብሶችም ገንዘውና ተሸክሞ ወስዶ ከቆጵሮስ ከተማ ውጭ በዋሻ ውስጥ አኖረው። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በሐዋርያ ቅዱስ በርናባስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን።
+ + +
❤ "ሰላም ለበርናባስ በማእሠረ ጌጋይ ዘኢትእኅዘ። ከመ መንፈስ ቅዱስ አዘዘ። ሥርዓተ ፈጺሞ ወመልእክተ ቃለ አዚዘ። በዋዕየ እሳት ሶበ እምዓለም ግዕዘ። ለወንጌላዊ ማርቆስ በእዱ ተገንዘ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 21።
+ + +
❤ የዕለቱ ማኅሌት ምስባክ፦ "ውስተ ኵሉ ምድር ወፅአ ነገሮሙ። ወእስከ አጽናፈ ዓለም በጽሐ ነቢቦሙ። ወውስተ ፀሐይ ሤመ ጽላሎቶ"። መዝ 18፥4-5። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 10፥1-12።
+ + +
❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወትቀውም ንግሥት በየማንከ። በአልባሰ ወርቅ ዑጽፍት ወኊብርት። ስምዒ ወለትየ ወርእዪ ወአጽምዒ ዕዝነኪ"። መዝ 44፥9-10። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 2፥1-14፣ ቈላ 4፥1-ፍ.ም ወይም ይሁ 1፥17-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 11፥23-ፍ.ም የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥17-34። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ በርናባስ የዕረፍት በዓልና የነቢያት የገና (ጾም) ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ይቀላቀሉ።
https://t.me/Eotcw
1 161
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤
❤ ታኅሣሥ ፳ (20) ቀን።
❤ እንኳን ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት ለአንዱ ከሌዊ ነገድ ከአሮን ትውልድ ለሆነው ለቅዱስ ሐጌ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከንግሥት ታውፊና ከመታሰቢያዋ፣ ከአውጋንዮስና ከማድዮስም ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን።
+ + +
❤ ነቢዩ ቅዱስ ሐጌ፦ እርሱም ከዐሥራ ሁለቱ ደቂቀ ነቢያት አንዱ ነው። ናቡከደነጾርም የኢየሩሳሌምን ሕዝብ በማረከ ጊዜ የዚህ ጻድቅ ነቢይ ወላጆች ከእስራኤል ልጆች ጋር ወደ ባቢሎን አገር ተማርከው ሔዱ ዳርዮስ የተባለውም ኵርዝ በነገሠ ጊዜ በሁለተኛው ዘመነ መንግሥቱ ይህ ነቢይ ትንቢት ተናገረ።
❤ የእስራኤልን ልጆች ወደ አገራቸው ይገቡ ዘንድ ኵርዝ ዳርዮስ በአሰናበታቸው ጊዜ እነርሱም ከገቡ በኋላ ቤተ መቅደስን ከመሥራት ቸለል በአሉ ጊዜ እነርሱ ግን በአማሩና በተሸለመ ቤቶች ውስጥ ይኖሩ ነበርና እንዲህ አላቸው። "ሁሉን የሚገዛ እግዚአብሔር እንዲህ አለ የኔ ቤት ፈርሷል እናንተ ግን ሁላችሁም ቤታችሁን ታጸናላችሁ" አላቸው። "ስለዚህ ከምድር በላይ ያለች ሰማይ ዝናም ለዘር ትነሣለች ምድርም ፍሬዋን አትሰጥም" አላቸው።
❤ ከሕዝቡም ደናጎቻቸው ሰምተው እጅግ ፈሩ የእግዚአብሔርንም መመስገኛ ቤት እንደሚገባ መሥራት ጀመሩ። ይህም ጻድቅ ነቢይ ሰባ ዓመት ያህል ኖረ የትንቢቱም ወራት ክብር ይግባውና ክርስቶስ ከመምጣቱ በፊት በአራት መቶ ሠላሳ ዓመት ነው። ከዚህ በኋላም በሰላም በፍቅር ታኅሣሥ20 ቀን ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢዩ ቅዱስ ሐጌ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ20 ስንክሳር።
+ + +
❤ "ሰላም ለሐጌ ዘተነበየ በፆታ። ሚጠተ ፂዉዋን ሕዝብ ወሕንፀተ መቅደስ ድኅረ ንስተታ። በእንተ ማርያምኒ ዘተደንገለት በመንታ። ለቤት ደኀሪት እንተ ትገብር ድሉታ። እምነ ቀዳሚት ይቤ ይኄይስ ትርሲታ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 20።
+ + +
❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ወገሠፀ ነገሥተ በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢታሕስሙ ዲበ ነቢያትየ"። መዝ 104፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት 2ኛ ቆሮ 4፥3-13፣ 2ኛ ጴጥ 1፥19፥ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 7፥44-51። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 7፥12-ፍ.ም ወይም ዮሐ 1፥6-15። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዮሐንስ ወልደ ነጎድጓድ ነው። መልካም ነቢዩ የቅዱስ ሐጌ የዕረፍት በዓልና ነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን።
❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊንክ ተጭነው ይቀላቀሉ።
https://t.me/Eotcw
1 161
ታህሳስ ፲፱(19)
እንኳን አደረሳቹ!!!
ከቅዱስ ገብርኤል ክብር የተነሳ ምድር በራች
{ራእ ፲፰ ÷፩ }18፥1
እንኳን ለመጋቤ ሐዲስ ሊቀ መልእክት ቅዱስ ገብርኤል አመታዊ ክብር በዓሉ በሰላም አደርሳችሁ አደርሰን አሜን!
ከሰባቱ ሊቃነ መላእክት አንዱና በእግዚአብሔር ፊት የሚቆመው ታማኝ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል ነው፡፡ በተረዳኢነቱና በአማላጅነቱ በክርስቲያኖች ዘንድ ይወደዳል፡፡ ምክንያቱም ያዘኑትን ለማጽናናት የምሥራች ለመንገር ከእግዚአብሔር ወደ ምእመናን ይላካልና፡፡
ገብርኤል ማለት የእግዚአብሔርን ልጅ የሚመስል ጌታና አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል፣ ቅዱሳን ሰማእታት ገድላቸውን እንዲፈጽሙ እሳቱንና ስለቱን ተሳቀው ወደ ኋላ እንዳይመለሱ ይረዳቸዋል፡፡
ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያናችን የቅዱሳን መላእክትን ወርኃዊና ዓመታዊ በዓላቸውን በፀሎትና በምሥጋና ታከበራለች፤ በተለይ ታህሣሥ 19 ቀን የሚከበርበት ምክንያት ብርሃናዊ መልአክ ቅዱስ ገብርኤል አናንያን፣ አዛርያን፣ ሚሳኤልን (ሠለሥቱ ደቁቅን )ከዕቶነ እሳት ( ከነደደ እሳት ) ያዳነበት ዕለት በመሆኑ ነው
ሊቀ መላአኩ ቅዱስ ገብርኤል ዛሬም ለኛም ይድረስ
በምናውቀውና በማናውቀው መንገድ በሀራችን በህዝባችን ላይ ከምነድ እሳት በምልጃው በተራዳይነቱ ያድነን አሜን
በረከት ረድኤት አይለየን
በዲ/ን የአብስራ ጌታሁን
