fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፭ (15) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያውያኑ ጻድቃን ለታላቁ አባት ለአቡነ ኤዎስጣቴዎስ ከፋሌ ባሕር አጽፋቸውን እንደጀልባ ተጠቅመው የኢያሪኮን ባሕር ለተሻገሩት መታሰቢያ በዓል፣ እጅና እግር የሌላቸውና የእኔ ቢጤ ለነበሩት ጽድቃቸውን ማንም ሳያውቅባቸው ለኖሩት ለታላቁ ጻድቅ ለአባ ቆራይ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ አቡነ ኤዎስጣቴዎስ የኢያሪኮን ባሕር በዓጽፍቸው ስለመሻገራቸው፦ ወደ አርማንያ ሔደ ወደኢያሪኮ ባሕርም ሲደርስ በመርከባቸው ያሳፍሩት ዘንድ መርከበኞችን ለመናቸው በከለከሉትም ጊዜ ዓጽፉን በባሕሩ ላይ ዘረጋ በቅድስት ሥላሴ ስም በላዩ ባረከ ራሱንም በመስቀል ምልክት አማተበ እንደ መርከብም ሁኖለት በላዩ ተጫነ ሁለት መላእክትም ቀዛፊዎች ጌታችንም እንደ ሊቀ ሐመር ሆኑለት። ከባሕሩም ግርማ የተነሣ እንዳይፈሩ ልጆቹን አጽናናቸው። ግን እንዲህ አላቸው "ልጆቼ በልባችሁ ቂምንና ሽንገላን እንዳታኖሩ ተጠበቁ ለኔ ግን ከእናንተ አንዱ እንደ ሚጠፋ ይመስለኛል" ይህን ሲናገረሰ ልቡ የቂም የበቀል ማከማቻ ስለሆነ ወዲያውኑ አንዱ ከእነርሱ መካከል ሠጠመ። በእግዚአብሔርም ፍቃድ ባሕሩን ተሻግሮ ወደ አርማንያ ከተማ ደርሶ ከሊቀ ጳጳሳቱ ጋር ተገናኘ ሰገደለትም ከእርሱም ቡራኬን ተቀበለ ሊቀ ጳጳሱም በአየ ጊዜ ታላቅ ደስታ ደስ አለው በፍቅርም ተቀበለው። አባታችን ኤዎስጣቴዎስም ሁሉም በትምህርቱ አንድ እስከሆኑ ድረስ የአርማንያን ሰዎች ሐዋርያት በሲኖዶሳቸው የሠሩትን ሥርዓት እያስተማራቸው ኖረ። ከአባታችን ከአቡነ ኤዎስጣቴዎስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ የመስከረም18 ስንክሳር። + + + ❤ የእኔ ቢጤው አባ ቆራይ፡- እጅና እግር የሌላቸውና የእኔ ቢጤ የነበሩት ጽድቃቸውን ማንም ሳያውቅባቸው የኖሩት አባ ቆራይ ጻድቅ መሆናቸው ካረፉ በኋላ ነው የታወቀው፡፡ ገዳማቸው ትግራይ ተንቤን ውስጥ ይገኛል፡፡ ቅዱሱ በዐፄ ልብነ ድንግል ዘመነ መንግሥት በትግራይ ተንቤን አውራጃ አዲ ራእሶት-የራሶች (የታላላቅ ሰዎች አገር) በሚባለው ቦታ የእግርና የእጅ ጣቶች የሌሏቸው አባ ቆራይ ወንበር በምትመስል ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ተገለጡ፡፡ ❤ አንድ የአካባቢው ሰው በመንገድ ሲያልፍ አባ ቆራይ ድንጋይ ላይ ተቀምጠው ጸሎት ሲያደርጉ አያቸውና በሁኔታው ተገርሞ ወደ እርሳቸው ጠጋ ብሎ ስማቸውንና የመጡበትን አገር ጠየቃቸው፡፡ እርሳቸውም "ስሜ አባ ቆራይ ይባላል፣ አገር ግን የለኝም" አሉት፡፡ እርሱም "እባክዎን ወደ መንደር እንሂድና የጸሎትና ቤት ሠርተንልዎት በዚያ ይቀመጡ" አላቸው፡፡ አባ ቆራይ ግን "ማረፊያዬ ይህቺ ናት፣ ከዚህች ሥፍራ አልነሣም" አሉት፡፡ አባ ቆራይም በዚያው እንደተቀመጡ ዝናቸው በሁሉ ዘንድ ተሰማና ሰዎች መጥተው በተቀመጡበት ድንጋይ ዙሪያ ጎጆ ቀለሱላቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ መንደርተኞቹ በየተራ በምግብ ሊረዷቸው ዕጣ ተጣጥለው ወደየቤታቸወ ሄዱ፡፡ በመጀመሪያ ተራ የደረሰው ሰው ከአንድ ሰዓት በኋላ ምግብ ይዞ ቢመለስ የአባ ቆራይ ጎጆ በብርሃን ተሞልታ አገኘ፡፡ ወደ ጎጆዋም ሲጠጋ ነበልባሉ እየፈጀው አላስቀርበው አለ፡፡ እርሱም በድንጋጤ ወደ መንደሩ ተመልሶ ለአካባቢው ሰው ነግሮ ሁሉም ተሰብስበው መጡ፡፡ መንደርተኛውም ካህናትን ይዘው ብዙ የምሕላ ጸሎትና እግዚኦታ ካደረሱ በኋላ እግዚአብሔር ወደ ጎጆዋ እንዲገቡ ፈቀደላቸውና ገቡ፡፡ ነገር ግን አባ ቆራይን በሕይወት አላገኟቸውም፡፡ አስክሬናቸውን ብርሃን ከቦት አገኙት፡፡ ከአስክሬናቸው አጠገብ "የአባ ቆራይን አስክሬን ከዚህች ጎጆ ውስጥ እንድትቀብሩት፤ ወደ ሌላ ቦታ ወይም ቤተ ክርስቲያን ወስደን እንቀብራለን ብላችሁ እንዳታስቡ፡፡ ነገሩን በድፍረት ብትፈጽሙት በሀገሩ ላይ እግዚአብሔርን ቁጣ ታመጣላችሁ" የሚል ትእዛዝ በብራና ተጽፎ ተገኘ፡፡ በዚሁ ትእዛዝ መሠረት የአሀሩ ሕዝብ ተሰብስቦ አባ ቆራይን ታኅሣሥ 15 ቀን እዚያው ቀበሯቸው፡፡ ❤ ከጥቂት ዘመናት በኋላ ባልና ሚስት የሆኑ ሰዎች መቆመም ሆነ መራመድ የማይችል ድውይ ልጃቸውን ይዘው ወደ ጸበል ሲሄዱ መሸባቸውና በአካባቢው ማደሪያ ሲፈልጉ የአባ ቆራይ ጎጆ ክፍት ሆኖ ታያቸውና ልጃቸውን ይዘው ሄደው ገቡ፡፡ ድውይ ልጃቸውን በአባ ቆራይ መቃብር ላይ ቢያስተኙት የኤልሳዕን አጥንት እንደነካውና ፈጥኖ እንደተነሣው ሙት ይህ ድውይ ልጅም በአባ ቆራይ መቃብር ላይ እንዳረፈ ወዲያው አፈፍ ብሎ በመነሣት እንደ እንቦሳ ጥጃ መዝለል ጀመረ፡፡ ወላጆቹም እልልታቸውን አቀለጡት፡፡ ወላጆቹም በነጋ ጊዜ ወደ መንደርተኛው ሄደው የተደረገላቸውን ተአምር ተናገሩ፡፡ ከዚያም ጊዜ ጀምሮ የአባ ቆራይ በዓል በአካባቢውና አጎራባች ቦታዎች ሁሉ ዘንድ መከበር ጀመረ፡፡ የዕረፍታቸውም በዓል ታኅሣሥ 15 ቀን ሆነ፡፡ ❤ አባ ቆራይ ራሳቸውን ለእግዚአብሔር ለይተው እንደ ቅዱስ አልዓዛር (ሉቃ 16፡19-35) ለዚህ ዓለም ውዳቂ መስለው ለታላቅ ክብር የበቁ ጻድቅ አባት ናቸው፡፡ ዛሬም ልብሳቸውንና አካላቸውን ብቻ እያየን የምንንቃቸው ሰዎች እንደ አባ ቆራይ ያሉ ቅዱሳን ሊሆኑ ይችላሉ፡፡ ከልዑል እግዚአብሔር በቀር ማንም ማንንም የሚያውቅ የለም። ከባታችን አባ ቆራይ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን። በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ ከገድላት አንደበት። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

+2
ዘብርሃን ከዋዜማ-ሰላም @EOTCW

ብርሃን (ከታኀሳስ 14 እስከ ታኅሳስ 20) ነቢያት የአምላክን ማዳን ከጠበቁባቸው እና ከገለጡባቸው መንገዶች አንዱ ብርሃን ነው፡፡ ዘመነ ብሉይ መከራ ሥጋ፣ መከራ ነፍስ የፀናበት፣ ሁሉ ነገር አስጨናቂ የሆነበት፣ ሰው ብርሃን ከሆነው አምላክ ጋር የተራራቀበት ስለነበር ያሉበትን ዘመን «ጨለማ» ብለው በመግለጥ ይህንን ጨለማ የሚያስወግድና ወደ ትክክለኛው መንገድ የሚመራ ብርሃን እንዲመጣ እንዲህ እያሉ ይፀልዩ ነበር፡፡ «ብርሃንህንና ጽድቅህን ላክ፣ እነርሱም ይምሩኝ፣ አቤቱ ወደ መቅደስህ ተራራና ወደ ማደራያህ ይውሰዱኝ» /መዝ. 42.3/ ጌታችንም ወደዚህ ዓለም በመጣ ጊዜ ለዚህ መልስ ሰጥቷል፤ «እኔ የዓለም ብርሃን ነኝ» /ዮሐ. 8.12/ ደቀመዛሙርቱም ስለ ብርሃንነቱ በመመስከር ተባብረዋል፤ - ቅዱስ ዮሐንስ ስለጌታችን ሰው መሆን /ሥጋዌ/ በተናገረበት በወንጌሉ የመጀመሪያ ክፍል ጌታችንን ብርሃን ብሎታል፤ «ሕይወት በእርሱ ነበረ፣ ሕይወትም የሰው ብርሃን ነበረ፤ ብርሃንም በጨለማ ያበራል፤ ጨለማም አላሰነፈውም» /ዮሐ. 1.4-5/ ቅዱስ ጳውሎስም ጌታችን በሚያንፀባርቅ ብርሃን አምሳል እንደተገለጠበት ተናግሯል፡፡ «እኩል ቀን በሆነ ጊዜ በመንገድ በሄደ ከፀሐይ ይልቅ የሚበራ መብረቅ በእኔና ከእኔ ጋር ይሄዱ በነበሩት ላይ ከሰማይ ሲያንፀባርቅ አየሁ፤ ... አንተ የምታሳድደኝ የናዝሬቱ ኢየሱስ ነኝ አለኝ፡፡» /ሐዋ. 26.13/ ✞✞✞✞✞✞✞ሰናይ

photo content

አባቶቻችን የሚሉትን በንቃት እየሰማን ነው። የሚያዙንንም ያለፍርሃት እንፈጽማለን። ለዚች ኩላዊት ሉዓላዊት፣ ብሔራዊት እና ዓለም አቀፋዊ ለሆነችው ቤተክርስቲያን አንገት እንሰጣለን። ይኼው ነው!
አባቶቻችን የሚሉትን በንቃት እየሰማን ነው። የሚያዙንንም ያለፍርሃት እንፈጽማለን። ለዚች ኩላዊት ሉዓላዊት፣ ብሔራዊት እና ዓለም አቀፋዊ ለሆነችው ቤተክርስቲያን አንገት እንሰጣለን። ይኼው ነው!

የግብፅ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ! +++++++++++++++++++ ታኅሣሥ 13 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) በግብፅ ኮፕ
+1
የግብፅ ኮፕቲክ ቤተ ክርስቲያን ሊቀ ጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ! +++++++++++++++++++ ታኅሣሥ 13 ቀን 2015 ዓ.ም አዲስ አበባ-ኢትዮጵያ) በግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን የናግሃማዲ ሀገረ ስብከት ሊቀጳጳስ የነበሩት ብፁዕ አቡነ ቄርሎስ በተወለዱ በ72 ዓመታቸው ከዚህ ዓለም ድካም አረፉ። እ.ኤ.አ 1948 ዓ.ምየተወለዱት ብፁዕነታቸው በንግድ ሥራ ትምህርት የመጀመሪያ ዲግሪ ያገኙ ሲሆን ጥቅምት 1973 እ.ኤ.አ ሥርዓተ ምንኩስናን ፈጽመው በ1975 እ.ኤ.አ መዓርገ ቅስና ተቀብለዋል። የግብፅ ኮፕቲክ ኦርቶዶክስ ቤተ ክርስቲያን 117ኛ ፓትርያርክ በነበሩት በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ሺኖዳ ሣልሣዊ እጅ በ1977 እ.ኤ.አ ኤጲስ ቆጶስ ሆነው የተሾሙት ብፁዕነታቸው በዛሬው ዕለት ከዚህ ዓለም ድካም አርፈዋል።

የበዓለ ጥምቀት አከባበርን አስመልክቶ በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ውይይት ተደረገ። ታኅሣሥ 13 ቀን 2015 ዓ.ም (ተ.ሚ.ማ/አዲስ አበባ) የ2015 ዓ.ም የከተራና የጥምቀት በዓላትን አስመልክቶ ከአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት የገዳማትና አድባራት አስተዳዳሪዎች ጋር በጠቅላይ ቤተ ክህነት ጽርሐ ተዋሕዶ አዳራሽ ወይይት ተካሒዷል። በመርሐ ግብሩ ላይ ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ቀዳማዊ ፓትርያርክ ርእሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወዕጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት፣ ብፁዕ አቡነ አብርሃም የመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ጽሕፈት ቤት ዋና ሥራ አስኪያጅና የባሕር ዳር ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡ ጴጥሮስ የቅዱስ ሲኖዶስ ዋና ፀሐፊና የኒውዮርክና አካባቢው ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ፣ ብፁዕ አቡነ ሄኖክ የአዲስ አበባ ሀገረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ እንዲሁም የጠቅላይ ቤተ ክህነት የመምሪያ ኃላፊዎች ተገኝተዋል። በመንበረ ፓትርያርክ ጠቅላይ ቤተ ክህነት የካህናት አስተዳደር መምሪያ አዘጋጅነት 'የጥምቀት ክብረ በዓል የአከባበሩ ፈተናዎች(ተግዳሮቶች)  እና  የመፍትሔ ሐሳቦች ' በሚል ርእስ በዲ/ን ዶ/ር በለጠ ባሕሩ ጥናታዊ ጽሑፍ የቀረበ ሲሆን ከክብረ በዓሉ አጀማመር ታሪካዊ ዳራ ጀምሮ አሁን እስካለንበት ጊዜ ድረስ ያለው ሁኔታ ተዳስሶበታል። በጥናታዊ ጽሑፉ ላይ እንደተግዳሮት ከተነሱ ጉዳዮች መካከል በተለይ በወጣቶች በኩል ሥልጣነ ክህነት ሳይኖር ዕጣንን የማጠን፣ ከሃይማኖታዊው ይልቅ ባህላዊው ጉዳይ ላይ ማተኮር እንዲሁም ለበዓሉ የሚጠቀሟቸው ቅዱሳት ሥዕላት ከበዓሉ ፍጻሜ በኋላ ክብራቸውን ባልጠበቀ መልኩ ማስቀመጥ እንደ ዓይነተኛ ችግር ተነስቷል። በሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶችም በኩል የሚጠቀሙት አልባሳት ከካህናት አባቶች ጋር የሚመሳሰል መሆኑ አግባብ አለመሆኑ የተጠቀሰ ሲሆን ካህናት አባቶችም ኃላፊነቱን ሁሉ ለሰንበት ትምህርት ቤት ወጣቶች መሥጠታቸው ልክ አለመሆኑ እንዲሁ ተጠቁሟል። ሚዲያዎችም ኃላፊነት በጎደለው መልኩ ስለበዓሉ ትክክለኛ መልእክት ማስተላለፍ የማይችሉ ሰዎችን ቃለ መጠይቅ ማድረግና ያልተገቡ መርሐ ግብራትን መሥራት የበዓሉን ገጽታ ከሚያበላሹ ጉዳዮች አንዱ መሆኑን አቅራቢው ገልጸዋል። በመርሐ ግብሩ ላይ መልክት ያስተላለፉት ብፁዕ አቡነ አብርሃም አባቶቻችን የእምነታችንን ቀኖና ደንግገው ቢያስረክቡንም በኛ ዘመን ግን መስመር እየለቀቀ ነው ያሉ ሲሆን ካህናት አባቶችም ይህ ጥሰት እያስጨነቀን አይደለም ብለዋል። ብፁዕ አቡነ ሄኖክ በበኩላቸው በዓላቱ መንፈሳዊ ልእልናቸው እንዲመለስ የማድረግ ሥራ ይጠበቅብናል ያሉ ሲሆን እየታየ ያለው ሥርዓት አልበኝነት መስተካከል እንደሚገባውም አስገንዝበዋል። የታየው ችግር ሁሉ መነሻው የመንፈሳዊነት ጉድለት ነው ያሉት ደግሞ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ናቸው። ብፁዕነታቸው ትልቁ ችግር ቤተ ክርስቲያንን ያየንበት መንገድ ልክ አለመሆኑ ነው ሲሉ የገለጹ ሲሆን በእግዚአብሔርና በምናገለግለው ሕዝብ ፊት እውነተኞች እንሁን በማለት አባታዊ ምክራቸውን ለግሰዋል። በመጨረሻ አባታዊ ቃለ ምዕዳንና ቡራኬ የሰጡት ብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ባስተላለፉት መልእክት ሁሉም ነገር በዓላቱን በሚመጥን ሁኔታ መከናወን አለበት ያሉ ሲሆን በዓሉ ሰላማዊ እንዲሆን ሰላምና ጸጥታን በተላበሰ መልኩ መንቀሳቀስ እንደሚገባ አሳስበዋል። አክለውም የቤተ ክርስቲያንን ስም የሚያጠፉ ሰዎች ከድርጊታቸው መታቀብ ይገባቸዋል በማለት የተናገሩት ቅዱስነታቸው ምእመናንንም መልስ ሲሰጡ ቤተ ክርስቲያንን በሚመጥን መልኩ መሆን እንዳለበት ገልጸዋል። ተዋሕዶ ሚዲያ ማዕከል እውነተኛ የተዋሕዶ ድምፅ

photo content
+1

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ሰላም ለመርምህናም ሰማዕት ፍጹም ኄር ገባሬ ተአምር። ሰላም ለ፵ መስተጽዕናነ አፍራስ እሊኣሁ፤ ወለእኅቱ ሳራ እለ ዘክርስቶስ ሐራ"። ትርጉም፦ ፍጹም ደግ ተአምራትን አድርጊ ለኾነ ለሰማዕቱ መርምህናም ሰላምታ ይገባል። የክርስቶስ ጭፍሮች ለኾኑ 40 ፈረሰኞች ወገኖችና ለእኅቱ ለሳራም ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም ሰላም ዕደወ ኃይል ሐራ። ዘኊላቌሆሙ ካዕበተ እስራ። በእንተ ክርስቶስ ዘፆሩ ለከበደ ዕለት ፃዕራ። ዘመርምህናም እግዚኦሙ ሶበ ነጸሩ መከራ። ወዘምስሌሁ እንተ ሐመት ሣራ። ትርጉም፦ የጌታቸው የመርምህናምን መከራና ከእርሱ ጋርም መከራን የተቀበለች ሳራን ባዩ ጊዜ ስለ ክርስቶስ የዕለቲቱን ብርቱ ጻዕር የተሸከሙ ቊጥራቸው የኻያ ዕጥፍ (40) የኃይል አዛዦች ለኾኑ ጭፍሮች ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 14። https://t.me/Eotcw

photo content
+2

ስለዚህም ከፈትኩለትና ወደ ማደሪያዬ አስገባሁት መብልንም አመጣሁለት እርሱም "ከነገ ከቊርባን በኋላ በቀር እኔ አልበላም" በማለት እምቢ አለኝ። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ ቤተ ክርስቲያን ገባና በጨለማ ቦታ ቆመ ከዚያ ያሉ መነኰሳትም እስከ አደነቁ ድረስ የዳዊትን መዝሙር ሲያነብ ድምፁን እንደ መላእክት ድምፅ ሁኖ ሰማሁት በነጋም ጊዜ በእግሮቹ ላይ ተቀመጠ ምንም ምን ማንበብ አልሻም። እኛ ግን ይጸልይልን ዘንድ ልንለምነው ቀረብን እርሱም "አባቴቼ ሆይ በበደሌ ብዛት ፊቴን ያጨለምኩ ስሆን ስለ እናንተ እንዴት እጸልያለሁ" አለን። ቊርባንንም በምናሳርግ ጊዜ በእግሩ ቁሞ የቅዱስ ጳውሎስን መልእክት፣ የሐዋርያትንም መልእክትና የሐዋርያትን ሥራ ማንበብ ጀምረ በአራተኛም ጊዜ በመሠዊያው ፊት ቁሞ የቅዱስ ዮሐንስን ወንጌል ማንበብ ጀመረ በፊቱም ላይ የተከናነበውን ልብስ አስወግደ ከፊቱም ብርሃን ገናናነት የተነሣ ሊያዩት አልተቻላቸውም። እኛ ቊርባንን ከተቀበልን በኋላ ቆረበ ከነገሥታት ልጆች ወገንም እንደሆነ ተጠራጠርን መብልንም በአቀረብንለት ጊዜ ከእኛ አልተቀበለም ነገር ግን ሰይጣን በእነርሱ ከሚያስትባቸው ሴቶችን ከማየት እንርቅ ዘንድ መከረን። ❤ ሮማዊ የሆነ አንድ ደግ ጻድቅ አረጋዊ መነኵስ ነበር እርሱም "አባቴ ያዕቆብ ሆይ ይቺ ከነገሥታት ልጆች ውስጥ የሆነች ሴት ናት ስለዚህም እንዳትታወቅ ፊቷን ከሰው ትሠውራለች" አለኝ። ከዚህም በኋላ ሥራዋን ከእኔ ሳትሠውር እንድትነግረኝ በክርስቶስ ስም አምላት ዘንድ ወደርሷ ሔድሁ። ግን አላገኘኋትም ከአምስት ወርም በኋላ ከንጉሥ አባቷ ዘንድ የተላኩ ብዙ ሰዎች እርሷን እየፈለጉ መጡ። እነርሱም ቤተሶቦቿ ከተኙ በኋኋ በሌሊት እንደወጣች እነርሱም እርሷን ሲፈልጉ ዐሥራ ሁለት ዓመት እንደሆናቸው ሥራዋን ነገሩን። ከዚህም በኋላ መጻተኞች ሰዎች በዚች ቀን እንዳረፈች ነገሩን። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅድስት ነሳሒት በጸሎቷ ይማረን በረከቷም ከእኛ ጋራ ይኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 14 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "ወሌሊትኒ ብሩህ ከመ መዓልት። በአምጣነ ጽልመታ ከማሁ ብርሃና። እስመ አንተ ፈጠርከ ኵልያትየ እግዚኦ"። መዝ 138፥12-13። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ 11፥1-17፣ 1ኛ ጴጥ 1፥13-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 8፥18-26። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥16-23። የሚቀደሰው ቅዳሴ የሠለስቱ ምዕት ቅዳሴ ነው። መልካም በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፬ (14) ቀን። ❤ እንኳን ለቅዱሳን መርምህናምና ለእኅቱ ቅድስት ሣራ ለአርባ አገልጋዮቹም ሰማዕትነት ለተቀበሉበት ለዕረፍት በዓላቸው፣ ለቅዱስ መርምህናም አባት ለአቶር ንጉሥ ለሰናክሬም ሠራዊት ለዐሥራ ሰባት እልፍ ሰማዕታት ለመታሰቢያቸው በዓላቸው፣ ከመ ከተማ በሰማዕትነት ለዐረፈ ለቅዱስ ስምዖን ለዕረፍት በዓል፣ ለሀገረ እስና ኤጲስቆጶስ ለአባ አሞንዮስ ሰማዕትነት ለተቀበለበት ለዕረፍቱ በዓል ፣ለእስክድርያ ስልሳ ስድስተኛ ሊቀ ጳጳስ ለአባ ገብረ ክርስቶስ ለዕረፍት በዓልና የአውሲም ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ ስለርሷ እንደተናገረ ለሮሜ ንጉሥ ልጅ ስሟ ቅድስት ነሳሒት ለተባለች ለዕረፍቷ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ መድኃኒታችን በዓለም ውስጥ ብርሃንን ከገለጠበት፣ ከቅዱሳን ከአባ ብሑርና ከአረጋዊ ሚናስ በሰማዕትነት ከዐረፉ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ቅዱሳን መርምህናምና እኅቱ ሣራ አርባ አገልጋዩቹ፦ የዚህም ቅዱስ አባት የአቶር ንጉሥ የተቀረጹ ስማቸው ቤል አጵሎን የሚባሉ ጣዖታትን የሚያመልክ ነው እናቱ ግን ክርስቲያን ናት። ይህም ቅዱስ መርምህናም ወደ ዱር ሒዶ አራዊትን ያድን ዘንድ እንዲፈቅድለት አባቱን ለመነው በፈቀደለትም ጊዜ ወደ እናቱ ሒዶ "አራዊትን ለማደን ወደ በረሀ እሔዳለሁ" አላት እናቱም "የሰማይና የምድር አምላክ እግዚአብሔር በላይህ በረከትን ያሳድር" አለችው። ❤ ከዚህም በኋላ ከአርባ ፈረሰኞች አገልጋዮቹ ጋር ወጥቶ ሔደ መቅሉብ ወደሚባል ተራራም ደርሶ በዚያ አደረ። በሌሊትም የእግዚአብሔር መልአክ ጠራው እንዲህም አለው "መርምህናም ሆይ ተነሥተህ ወደዚህ ተራራ ላይ ውጣ ስሙ ማቴዎስ የሚባል ቅዱስ ሰው ታገኛለህ እርሱም የሕይወትን ነገር ይነግርሃል" ሲነጋም ወደ ተራራው ወጣ እንደ በግ ጠጉር ለብሶ አባ ማቴዎስን አገኘው መርምህናም በአየው ጊዜ ፈራ ቅዱስ አባ ማቴዎስ "ልጄ ሆይ ወደ እኔ ቅረብ እኔም የእግዚአብሔር ፍጥረቱ የሆንኩ እንዳንተ ሰው ነኝ" አለው። መርምህናምም "ከአባቴ አማልክቶች በቀር አምላክ አለን?" አለው አባ ማቴዎስም የክርስትና ሃይማኖትን ከአባቱና ከመንፈስ ቅዱስ ጋር ክርስቶስን ህልውና በተለየ አካሉ ሰው መሆኑንና መከራ ተቀብሎ መሞቱን መነሣቱን ወደ ሰማይ ማረጉንም የፍርድ ቀንም እንዳ ለጻድቃን በጎ ዋጋ ለኃጢአተኞች ቅጣት እንዳለ አስተማረው። መርምህናምም "ከራስዋ እስከ እግርዋ ለምጽ የያዛት እኅት አለችኝ የአምላክህን ስም ጠርተህ በጸሎትህ ብታድናት እኔ አምንበታለሁ" አለው አባ ማቴዎስም "እኔ አድናታለሁ ና በአንድነት እንውረድ" አለው ከተራራው በወረዱ ጊዜ አባ ማቴዎስን በመንገድ ትቶ ቅዱስ መርምህናም ወደ እናቱ ሒዶ ሁሉን ነገራት እኅቱንም በሥውር ወደ አባ ማቴዎስ ወሰዳት አባ ማቴዎስም ወደ እግዚአብሔር ጸለየና ምድሪቱን አመሳቅሎ መታት በዚያን ጊዜ ውኃ መንጭቶ እንደ ባሕር ሆነ ወደ ባሕሩም አውርዶ እጁን በራሳቸው ላይ አድርጎ በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም አጠመቃቸው አሽከሮቹን አርባ ሰዎችንም ሥጋውንና ደሙንም አቀበላቸው ወዲያውኑ ሣራ ከለምጽዋ ነጻች። ❤ ከዚህም በኋላ አባ ማቴዎስ ስለ ከበረ ስሙ በላያቸው የሚመጣውን መከራ በሚቀበሉ ጊዜ ክብር ይግባውና ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስን በማመን እንዲጸኑ መከራቸው ከዚህም በኋላ በላያቸው ጸለየና በፍቅ አንድነት አሰናበታቸው። ቅዱስ መርምህናምም በመጣ ጊዜ ወደ እናቱ ቤት ገባ ወደ አባቱ ወይም ወደ አማልክቶቹ አልሔደም አባቱም ሰምቶ ተቆጣ ወደ አማልክቶቹ ቤትም እንዲጠሩት አዘዘ ቅዱስ መርምህናም ግን ከእኅቱና ከሠራዊቱ ጋር ስሟ ቅሳር ወደ ምትባል ተራራ ሒዶ ከላይ ወጥቶ በዚያ ተቀመጠ። ❤ አባቱም በሰማ ጊዜ ከልብሰ መንግሥትና ከዘውድ ጋር መኳንንቱን "የመንግሥቴን ሥልጣን ተረከብ ብሎሃል" እንዲሉት ላካቸው እርሱ ግን በቊጣ ተመለከታቸውና "እኔ ክብር ይግባውና የጌታዬ ኢየሱስ ክርስቶስን ፈጽሞ የማይጠፋ መንግሥት እሻለሁ" አላቸው። የአቶር ንጉሥ አባቱም በዚያን ጊዜ ተቆጣ ልቡ ፈርቶ ይመለስ ዘንድ አገልጋዮቹን በፊቱ እንዲገድሏቸው ካልተመለሰ ግን እርሱንም እኅቱንም እንዲገድሉ አዘዘ። ቅዱስ መርምህናምም ሰምቶ የተመኘውን ይሰጠው ዘንድ ወደ እግዚአብሔር ጸለየ "ጸሎትህን ሰማሁ ልብህ የወደደውንም ሰጠሁህ" የሚል ቃል ከሰማይ መጣ። ከዚህም በኋላ የቅዱሳኑን ራሳቸውን በሰይፍ ቆረጡና ከጒድጓድ ውስጥ ጣሏቸው ሥጋቸውንም ያቃጥሉ ዘንድ ብዙ ዕንጨቶችን ሰበሰቡ ግን አላገኙአቸውም እግዚአብሔር ሠውሮዋቸዋልና። ❤ ወዲያውኑ ንውጽውጽታ ሆነ ፀሐይም ጨለመ ወታደሮችም ፈርተው ሸሹ ሰይጣንም በአቶር ንጉሥ በሰናክሬም ላይ አድሮ አሳበደው እንደእሪያም ጮኸ የቅዱስ መርምህናምም እናት አይታ ወደ አባ ማቴዎስ ልካ አስመጣችውና የንጉሡን ነገር ነገረችው እርሱም በዘይት ላይ ጸልዮ ቀባው ሰይጣንም በእሪያ አምሳል ከርሱ ወጣ። በዚንም ጊዜ ንጉሥ ክብር ይግባውና በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ አመነ ከቤተ ሰቦቹና በሚገዛው አገር ካሉ ሰዎች ሁሉ ጋር ተጠመቀ። ❤ ከዚህም በኋላ አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ስም ቤተ ክርስቲያን እንዲሠሩ ገንዘብንም ለድኆችና ለችግረኞች እንዲበትኑ አዘዘ ሁሉንም እንዳዘዛቸው አደረጉ። የቅዱስ መርምህናምም እናት ከከበሩ ደንጊያዎች አርባ ሣጥኖችን አሠራች የልጅዋ ጭፍራ የነበሩ የእነዚያን አርባ ሰማዕታት አጥንቶቻቸውን አሰብስባ በየአንዳንዱ ሣጥን ጨመረቻቸው ለልጆቿም ብርሌ ከሚመስል ዕንቊ ሁለት ሣጥን አሠርታ በውስጣቸው አድርጋ በሠራችው ቤተ ክርስቲያን ውስጥ አኖረቻቸው ከሥጋቸውም ታላላቅ የሆኑ ቊጥር የሌላቸው ተአምራት ተገለጡ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱሳን ሰማዕታት ጸሎት ይማረን በረከታቸውም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅዱስ ስምዖን፦ እርሱም በእስላሞች ዘመን ከመሳፍንቶቻቸው ከአንዱ ጋር ተከራከረና ቅዱስ ስምዖን ረትቶ አሳፈረው ያም እስላም ወደ መሳፍንቱ አለቃ ሒዶ "ይህ ስምዖን የእስላሞች ሃይማኖት ያቃልላል" ብሎ ወነጀለው ስለዚህም ይዘው በጽነዕ ሥቃይ አሠቃዩት ከዚያም በኋላ ራሱን በሰይፍ ቆረጡት የሰማዕትነት አክሊል በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ስምዖን በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋራ ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ የውሲም ኤጲስቆጶስ አባ ያዕቆብ ስርሷ የተናገረላት የሮሜ ንጉሥ ልጅ ቅድስት ነሳሒት፦ እንዲህም አለ በአንዲት ዕለት አምላክን በወለደች በእመቤታችን በቅድስት ድንግል ማርያም ቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያለሁ የገዳሙን ደጅ ሰው ሲያንኳኳ ሰማሁ ተነሥቼም ወደ በሩ ሔድኩ ያረጀ ዓጽፍ የለበሰ ፊቱንም የተሸፋፈነ ሰው አየሁ "ከወዴት መጣህ? ወዴትስ ትሔዳለህ?" አልሁት። "ከአባ መቃርዮስ ገዳም መጣሁ በዚች ሌሊት ከዚህ ገዳም አድሬ ቊርባንን መቀበል እሻለሁ" አለኝ። ያን ጊዜ ቀዳሚት ሰንበት ነበረች እኔም "ፊትህን ካላሳየኸኝ አልከፋትልህም" አልሁት እርሱም "ፊቴን ማየት አትሻ ፊቴ በኃጢአቴ የጨለመ ነውና ፊቴንም ለሚያይ የከፋች ሥራዬ ትታየዋለች" አለኝ። በከለከልኩትም ጊዜ ወደ ዱር ሊመለስ ወደደ እኔም ተርቦ ወይም ተጠምቶ እንደሆነ ብዬ በልቤ አሰብኩ

Share የጥምቀት መዝሙሮችን-WPS Office.docx

🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃🍃 ስርአተ ማህሌት ዘታህሳስ 13 ቅዱስ ሩፋኤል 🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵🏵 ነግሥ (የማንኛውም ወርኃ  በዓልና ክብረ በዓል ሥርዐተ ማኅሌት መጀመሪያ) ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፤ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ወኢትሚጥ ገጽከ እምኔየ፡፡በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ እዝነከ ኅቤየ፤ሃሌ ሉያ  ሃሌ ሉያእመ ዕለተ አጽውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡፡ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ ለዓለመ ወለዓለመ ዓለም፡፡ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡፡ንወድሶ ለዘሀሎ እግዚአብሔር ልዑል፡፡ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኵሉ ዓለመ በአሐቲ ቃል፡፡ @EOTCW @EOTCW ገባሬ ኩሉ፦ ሰላም ለአብ ገባሬ ኩሉ ዓለም፤ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም፤ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም፤ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም፤ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም። @EOTCW ዚk እስመ ዘይሬእየነ ብነ አብ ብርሃን ምስለ ወልዱ፤ወመላእክቲሁ ቅዱሳን፤እለ ይሔውፁ ቤተክርስቲያን @EOTCW መልክዐ ሚካኤል ሰላም ለአዕጋሪከ በክነፈ ነፋስ እለ ይረውፃ፤አብያተ ግፉአን የሐውፃ፤ሚካኤል የዋህ ወኅሩም እምነ ዓመፃ፤ተኖለው አዕጋርየ ለፍኖተ ስህተት እምዳኅፃ፤ወኀበ ምድረ ጽድቅ ምርሐኒ ከመ እብላዕ ሠርፃ @EOTCW ዚቅ ይሔውፅዋ መላእክት አንተ በሰማያት፤ይሔውፅዋ መላእክት እስመ ማኅደረ መለኮተ ዖድክዋ ዖድክዋ ዖድክዋ ወርኢኩ ስነ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምስእል ወምስጋድ፤ወምለት ሥራየ ኀጢአት ይዕቲ ቅድስት ደብተራ @EOTCW @EOTCW ነግሥ ሰላም ለሩፋኤል ለዓይነ ጦቢት ዘፈወሳ፤ዓይኖ ኩሂሎ በሐሞተ ዓሣ፤ለእስማንድዮስ አሠሮ ለመርዓ ጦቢያ ከመ ኢያርኩሳ፤ቤተ ክርስቲያኑ ሜላተ በግዑ ለቢሳ፤በዛቲ ዕለት ቴዎፍሎስ ሐነፃ @EOTCW ዚቅ፦ ሃሌ ሃሌ ሉያ ለቤተክርስትያን ቴዎፍሎስ ሐነፃ በጽድቁ ሐወፃ፤እምነ ፀሐይ ይበርህ ገጻ @EOTCW @EOTCW መልክአ ሩፋኤል ሰላም ለዝክረ ስምከ ተጸውዖ ዘቀደመ: በአፈ አምላክ አዳም እንበለ ይሰመይ ስመ: ሩፋኤል ምልዓኒ ወወስከኒ ዳግመ: መንፈስ ቅዱሳዌ አዕምሮ እንተ ይፈሪ ሰላመ: ወአምላካዌ ጥበበ ዘየአዱ አቅመ፡፡ @EOTCW @EOTCW ዚቅ፦ ሀበነ ጥበበ፤ጥበበ ወምክረ አእምሮ ሠናየ፤ጸግወነ እግዚኦ @EOTCW ወረብ ጥበበ ወምክረ ሀበነ ጥበበ/2/ አእምሮ ሠናየ ሩፋኤል መልአክ/2/ @EOTCW @EOTCW መልክአ ሩፋኤል ሰላም ለቃልከ ዘይደምፅ እመብረቅ: ለእስትንፋስከኒ እስትንፋሰ መንፈስ ረቂቅ: ሩፋኤል ሐዋርያ ወመልአከ ጽድቅ: ይጸንሑከ እግዚኦ ዕሡራነ በዓል በጻሕቅ: ነዓ ነዓ እምሕላዌከ ምጡቅ ውስተ ቤትከ ዛቲ ክርስቶሳዊት ምርፋቅ፡፡ @EOTCW አመላለስ ሩፋኤል ሐዋርያ/፪/ ወመልአከ ጽድቅ/፪/ @EOTCW ዚቅ እስመ ለአለም ምሕረቱ ሐውፀነ በበዓልከ፤ሩፋኤል ክቡር አርውየነ እምጣዕመ ቃልከ፤ስፍሐ እዴከ ዲበ ዝንቱ መቅደስ ወካህናት @EOTCW ወረብ እስመ ለአለም ምሕረቱ ሐውፀነ በበዓልከ/2/ ሊቀ መላእክት ሩፋኤል አርውየነ እምጣዕመ ቃልከ/2/ @EOTCW መልክአ ሩፋኤል ተወኪፈከ እግዚኦ ዘንተ አምኃየ: ዘአቅረብኩ ለከ መጠነ ክሂል ዘብየ: ሩፋኤል ባዕል እንተ ታብዕል ነዳየ: ዕስየኒ ለፍቁርከ ዕሤተ ሠናየ: ዘዕዝነ መዋቲ ኢሰምዐ ወዘዐይን ኢርእየ፡፡ @EOTCW ዚቅ አንተ ዕሥየነ፤ዕሤተ ሠናየ፣ዘዓይን ኢርእየ ወዕዝን ኢሰምዓ፤በውስተ ልበ ሰብእ ዘኢተኃለየ፤ዘአስተዳለወ እግዚአብሔር ለእለ ያፈቅርዎ @EOTCW ወረብ አንተ ዕሥየነ ሊቀ መላእክት ዕሤተ ሠናየ ዘአስተዳለወ እግዚአብሔር/2/ ዘዓይን ኢርእየ ወዕዝን ኢሰምዓ በውስተ ልበ ሰብእ ዘኢተኃለየ/2/ @EOTCW @EOTCW ወረብ(ዓዲ) አንተ ዕሥየነ ሊቀ መላእክት/2/ ዕሤተ ሠናየ ወዕዝን ኢሰምዓ ወዓይን ኢርእየ/2/ @EOTCW @EOTCW ምልጣን፦ ሃሌ ሉያ ይሰግዱ በብረኪሆሙ ወያሌዕሉ ኅሊናሆሙ በጥንቃቄ ወበሐሢሥ፡ ኀበ እግዚኦሙ ንጉሥ፤ቀዋምያን ለነፍሳት፡ እሙንቱ ሊቃናት፡ ዑራኤል ወሩፋኤል፡ ይትፌነዉ ለሣህል: እምኀበ ልዑል። @EOTCW @EOTCW አመላለስ፦ ይትፌነዉ ለሣህል/2/ ለሣህል እምኀበ ልዑል/4/ @EOTCW ወረብ፦ ይሰግዱ በብረኪሆሙ ወያሌዕሉ ኅሊናሆሙ በጥንቃቄ ወበሐሢሥ/2/ ኀበ እግዚኦሙ ንጉሥ ቀዋምያን ለነፍሳት እሙንቱ ሊቃናት ዑራኤል ወሩፋኤል/2/ @EOTCW @EOTCW እስመ ለአለም ይሔውፅዋ መላእክት አንተ በሰማያት፤ይሔውፅዋ መላእክት እስመ ማኅደረ መለኮተ ዖድክዋ ዖድክዋ ዖድክዋ ወርኢኩ ስነ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን ምስእል ወምስጋድ፤ወምለት ሥራየ ኀጢአት ይዕቲ ቅድስት ደብተራ @EOTCW @EOTCW ወረብ ይሔውፅዋ መላእክት አንተ በሰማያት ይሔውፅዋ መላእክት እስመ ማኅደረ መለኮተ/2/ ዖድክዋ ዖድክዋ ወርኢኩ ስነ ሕንጼሃ ለቤተ ክርስቲያን/2/ @EOTCW https://t.me/Eotcw     # Join & share

photo content
+5

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፫ (13) ቀን። ❤ እንኳን ለታላቁ አባት ቆቅ ሲመገብ ለነበሩት ለአባ መቃርስ ወደ ብሔረ ሕያዋን ለገባበት በዓል፣ በስላሞች ዘመን በሰማዕትነት ለዐረፈ ለአባ በጽንፍርዮስና ከላይኛው ግብጽ ለሆነ ለቅዱስ አባት ለአብራኮስ ለዕረፍታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ቅድስት ሐና እመቤታችንን ቅድስት ድንግል ማርያም ጸነሰቻት የሚሉ አሉ፣ በደብረ ቀልሞን ከሚኖር ከገዳማዊ ከአባ ሚካኤል ዕረፍት፣ ከሰማዕት አብራቂስ፣ ከሐርስፎስ፣ ከመኰንኑ ቆርኔሌዎስ፣ ከወርቅጥጶስና ከአፍሬ ከመታሰቢያቸው እግዚአብሔር አምላክ ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ ቆቅ ሲመገብ የነበረው አባ መቃርስ፦ ይህም ቅዱስ ከታናሽነቱ ጀምሮ ሕያው እግዚአብሔርን መከተል ፈልገ የቤተ ክርስቲያንንም ትምህርት መጻሕፍትንም ተማረ የዚህንም ዓለም ኃላፊነቱን ለጻድቃንም በጎ ዋጋ ለኃጥአን ቅጣት እንዳለም አስተዋለ ስለዚህም ዓለምን ትቶ በአንድ ገዳም ውስጥ መነኰሰ ከዚያም ወጥቶ የዐሥር ቀን ጎዳና ተጓዘና በውስጡ ኲዕንትና ቆቆች ውኃም ካለበት ተራራ ደረሰ። አስቦ እንዲህ አለ "ኵዕንት ወደመልቀም ብሰማራ የስግደቴና የጸሎቴ ሥራ ይቋረጣል ሰብስቦ የሚያስገባልኝ ረዳት የለኝም ብቸኛ ነኝኛ ሥጋ አትብላ ያለውስ የባልንጀራችንን ሥጋ በሐሜት የምንበላውን አይደለምን ሌላ ምግብም እንደሌለኝ ፈጣሪዬ ያውቃል" ብሎ ከዚያችም ዕለት ወዲህ ቆቆችን የሚያጠምድ ሁኖ በየቀኑ አንዳንድ የሚያዙለት ሆነ። እርሳቸውንም እየተመገበ ከዚያ ውኃም እየጠጣ በማመስገን ኖረ በቀንና በሌሊትም በጸሎትና በስግደት በመትጋት ወደ እግዚአብሔርም እየለመነ ብዙ ዘመናት ኖረ የሰውንም ጽምፅ አይሰማም የሰውንም ፊት አያይም ሐሜትንም ሆነ ስድብን በማንም ላይ አብሮ አይነጋገርም ከሰው ጋር ከልሆነ በቀር ሰይጣን አይመጣም ይባላልና። ❤ ከዚህም በኋላ ከቊስጥንጥንያ ከተማ አንድ መነኵሴ ዋሻ እየፈለገ አባ መቃርስ ከአለበት ደርሶ ቆቅን ሲያጠምድ አየው ያን ጊዜ አልታገሠም ግን ወንድሙን በሐሜት እስከሚገድለው ቸኰለ ወደ የቊስጥንጥንያ ከተማ ወደ ሊቀ ጳሳሳቱ ተመልሶ እንዲህ ብሎ ነገረው "እኔ ዋሻ እየፈለግሁ ወደ በረሀ ሔድሁ በዚያም ሥጋ ሊበላ ቆቅን ሲያጠምድ መነኵሴውን አየሁት የሚሠራውን ሲያዩ በአሕዛብ ዘንድ ሊያስነቅፈን ነው" አለው። ❤ ሊቀ ጳጳሳቱም ይህን ነገር በሰማ ጊዜ ነገሩ እውነት እንደሆነ ያውቅ ይረዳ ዘንድ ከዚያ ከነገረው መነኰሴ ጋር ሌላ መነኵሴ ላከ። እነርሱም በጒዞ ላይ በጐዳና ሳሉ ገና ሳይደርሱ አባ መቃርስ እንደልማዱ ወደ ወጥመዱ ሔደ በአንዲት ወጥመድ የተያዙ ሦስት ቆቆችን አገኘ እንዲህም ብሎ አሰበ "ጌታዬ እሊህን የሰጠኝ እኔን ሊፈትነኝ ነውን። ወይስ ከዚች ዕለት በፊት ሆዴ ያልጠገበች ኑራለችን ወይስ ለሌላ ነው እንዳልል በዚህ በረሀ ውስጥ ከሰው ወገን ያየሁት የለም"። እንዲህም እያሰበ ሳለ ከሊቀ ጳጳሳቱ የተላኩት እሊህ መነኰሳት ደረሱ በአያቸው ጊዜ ደስ አለው "ችግረኞነቴን አውቀህ ለአገልጋዩችህ ቅዱሳን ምግባቸውን የሰጠኸኝ አቤቱ አመሰግንሃለሁ" ብሎ ሰገደ። እነርሱ ግን ማዕድ ሠርቶ አዘጋጅቶ እስከአቀረበላቸው ድረስ ይጠቃቀሱበት ነበር። ❤ ከዚህም በኋላ አቅርቦላቸው "ንሱ አባቶቼ ባርኩና ተመገቡ" አላቸው እርሱም የራሱን ድርሻ ይዞ እስከጨርስ ያለ መነጋገር በጸጥታ ተመገበ። ከዚህም በኋላ ዓይኖቹን ቀና ቢያደርግ እንዳልበሉ አየ "አባቶቼ እንዴት አልበላችሁም" አላቸው "እኛ መንኰሳት ስለሆን ሥጋ አንበላም ትኅርምትም አለን" አሉት እርሱም ተዋቸው አላስገደዳቸውም እነዚያን ያበሰላቸውን ቆቆች አንሥቶ ሦስት ጊዜ እፍ አለባቸው ያን ጊዜም ድነው በረሩ ወደ ቦታቸውም ሔዱ እነዚያ መነኰሳትም ይህን ተአምር አይተው ደነገጡ "የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ በደላችንን ይቅር በለን ብለው" ሰገዱለት እርሱም "የሁላችንንም በደል እግዚአብሔር ይቅር ይበለን" አላቸው። ❤ ከዚህም በኋላ ወደ አገራቸው ተመልሰው ያዩትን ይህን ድንቅ ተአምር ለሊቀ ጳጳሳቱ ነገሩት እርሱም ሰምቶ አደነቀ ወደ ንጉሡም እንዲህ ብሎ ላከ "በዘመናችን ጻድቅ ሰው መነኰስ ተገኝቷልና አንተም ና ሒደን በረከቱን እንድንቀበል" አለው። ወዲያውኑ ንጉሥ ከሠራዊቱ ጋር ተነሣ ሊቀ ጳጳሳቱም ከካህናቱ ጋር አባ መቃርስ ወዳለበት እነዚያ መነኰሳት እየመሩአቸው ሔዱ ወደርሱም ሲቀርቡ ወደ ብሔረ ሕያዋን ያደርሰው ዘንድ መልአክ አንሥቶ በክንፎቹ ተሽክመው ሲያርግም በአዩ ጊዜ "የእግዚአብሔር ቅዱስ ሆይ ባርከን የምንድንበትን አንዲት ቃል ንገረን" ብለው ጮኹ። እርሱም "ከሐሜትና ከነገር ሥራ አንደበታችሁ ይከልከል። ካህን ብዙ ባይማር ትዕቢትና መታጀር ባልመጣበት ነበር መነኵሴም ትኅርምት ባያበዛ ባልተመካም ነበር ርስበርሳችሁ ተፋቀሩ እግዚአብሔርም አድሮባችሁ ይኑር" አላቸው። ይህንንም ብሎ ዐረገ ከዐይናቸውም ተሠወረ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ መቃርስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ በጽንፍርዮስ፦ ይህም የከበረ መነኰስ በምስር አገር በወንዝ ዳር በአለች በሊቀ መላእክት በቅዱስ ገብርኤል ቤተ ክርስቲያን ውስጥ መንኵሶ ታላቅ ተጋድሎን ሲጋደል ኖረ ስቀናች ሃይማኖትም ከእስላሞች መሳፍንት ጋር ተከራከረ የጌታችን ክርስቶስንም መለኮቱን ገለጠላቸው አምላክነቱንም አስረዳቸው ስለዚህም እስላሞች በአፈሩ ጊዜ ተቆጡ ጽኑዕ ሥቃይንም አሠቃዩት ራሱንም በሰይፍ ቆረጡ የሰማዕትነት አክሊልን በመንግሥተ ሰማያት ተቀበለ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም አባ በጽንፍርዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባ አብራኮስ፦ ይህም ቅዱስ አባት ከላይኛው ግብጽ ነው። ዕድሜው ሃያ ዓመት ሲሆን መንኵሶ መልካም የሆነ ታላቅ ተጋድሎን ተጋደለ። ሰይጣንም ከእርሱ ጋር በመጣላት በተሸነፈና በደከመ ጊዜ በእርሱም ላይ ምንም ምን ማድረግ ባልተቻለው ጊዜ ፊት ለፊት ተገልጦ መጥቶ "እነሆ ከዚህ ዕድሜህ ሌላ ኀምሳ ዓመት ቀረህ" አለው። በዚህም ወደ ስንፍና ሊጥለው ወዶ ነው ሽማግሌውም እንዲህ ብሎ መለሰለት "አሳዘንከኝ እኔ ሌላ መቶ ዓመት እኖር ዘንድ ስለአሰብኩ ቸለል ብያለሁ አንተ እንዳልከው ከሆነ ከቀድሞው እጅግ አብዝቼ እጋደል ዘንድ ይገባኛል"። ከዚህም በኋላ ተጋድሎውንና በገድል መጸመድ አበዛ ሰባ ዓመታትም ከተጋደለ በኋላ በዚያች ዓመት ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ አብራኮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ13 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለመቃርዮስ ዘተመሥጠ መልዕልተ። በቅድመ ጉቡአን ይንብብ ዘይብል ቃላተ። እምኢያእመሩ ትዕቢተ ወዘይመስሎ ትምክህተ። እመ ኢያፈድፈደ ካህን ትምህርተ። ወእመ ኢያብዝኀ ካዕበ መነኰስ ትኅርምተ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የታኅሣሥ 13። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፲፫ (13) ቀን። ❤ እንኳን ለሊቀ መላእክት ለፈታሔ ማሕፀን ለቅዱስ ሩፋኤል ለቅዳሴ ቤቱና ተአምር ላደረገበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ "ሰላም ለሩፋኤል መልአከ ነፍስ"። ትርጉም፦ የነፍስ (የሰውነት) መልአክ ለኾነ ለቅዱስ ሩፋኤል ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ የመላእክት አለቃ የከበረ መልአክ የቅዱስ የሩፋኤል የቅዳሴ ቤት ክብርና ያደረገው ተአምር፦ ከእስክድርያ ውጭ በደሴት የታነፀች ቤተ ክርስቲያኑ በከበረ ሊቀ ጳጳሳት ቴዎፍሎስ ዘመን በውስጧ ተአምር የተገለጸባት የከበረችበት፦ ይህም እንዲህ ነው ሀብታም ሴት ወደ ሊቀ ጳጳሳት አባ ቴዎፍሎስ መጥታ ሳለ ከእርሷ ጋርም ብዙ ሰው ነበር። ከባሏም የወረሰችው ብዙ ገንዘብ አላት በሊቀ ጳጳሳቱ ቤት አንጻር ያለውን ኮረብታ አስቆፈረች በጥቅምት ወር ዐሥራ ስምንት ቀን እንደጻፍን የወርቅ መዝገብ ተገለጠ። ❤ በዚያም ወርቅ ብዙዎች አብያተ ክርስቲያናትን አነፀ ከእርሳቸውም አንዲቱ የመላእክት አለቃ በሆነ በከበረ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል በስሙ የታነፀች ይህች ናት። ሥራዋንም በፈጸመ ጊዜ እንደዛሬው በዚች ቀን አከበራት። ብዙ ምእመናንም በቤተ ክርስቲያን ውስጥ እያሉ ቤተ ክርስቲያኒቱ ፈጽማ ተናወጸች ያቺ ደሴት በታላቅ አንበሪ ጀርባ ላይ የቆመች ናትና። የሰዎች ብዛትም በከበደው ጊዜ ቤተ ክርስቲያኒቱን ያፈርሳት ዘንድ ሰይጣን አነሣሣው። ወደ ክብር ባለቤት እግዚአብሔርም በከበረ መልአክ ቅዱስ ሩፋኤል ስም ጮኹ ያን ጊዜ ይህ የከበረ ቅዱስ ሩፋኤል ያንን አንበሪ በጦሩ ወግቶ እንዲህ አለው "እግዚአብሔር አዞሃልና ከቦታህ ሳትናወጽ ጸጥ ብለህ ቁም"። አንበሪውም ጸጥ ብሎ ቆመ አልታወከም በውስጧም ድንቆች ተአምራቶች ተገለጡ ለሕሙማንም ፈውስ ሆነ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ሩፋኤል አማላጅነት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጳጒሜን 3 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "እስመ ለመላእክቲሁ ይኤዝዞሙ በእንቲአከ። ከመ ይዕቀቡከ በኵሉ ፍናዊከ። ወበእደሆሙ ያነሥኡከ"። መዝ 90፥10-11 ወይም 36፥4 የሚነበበው ወንጌል ዮሐ 16፥16-25። + + + ❤ የዕለቱ ምስባክ፦ "እስመ ቆመ ላዕሌየ ሰማዕተ ዓመፃ። ወሐሰት ርእሰ ዓመፃ። እትአመን ከመ እርአይ ሠናይቶ በእግዚአብሔር በብሔረ ሕያዋን"። መዝ 26፥12-13 ወይም መዝ 86፥1-2። የሚነበቡት መልዕክታት 1ኛ ተሰ 4፥15-ፍ.ም፣ 1ኛ ጴጥ 1፥10-13 ወይም ያዕ 1፥21-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 10፥9-17። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 10፥26-34። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ወይም የቅዱስ ያዕቆብ ዘሥሩግ ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ ሩፋኤል በዓልና የነቢያት (የገና) የጾም ጊዜ። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw