fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
Repost

🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 ሥርዓተ ማኅሌት ዘሥላሴ 'ጥር ፯ 🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂🍂 የማንኛውም ወርኃ በዓልና ክብረ በዓል ሥርዓተ ማኅሌት መጀመሪያ "ሥርዓተ ነግሥ" ስምዓኒ እግዚኦ ጸሎትየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወይብጻሕ ቅድሜከ ገዓርየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ወኢትሚጥ ገፀከ እምኔየ፡ በዕለተ ምንዳቤየ አጽምእ ዕዝነከ ኃቤየ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ አመ ዕለተ እጼውአከ ፍጡነ ስምዓኒ፡ ሃሌ ሉያ ሃሌ ሉያ፡ ለዓለም ወለዓለመ ዓለም፡ ሃሌ ሉያ ዘውእቱ ብሂል፡ ንወድሶ ለዘሃሎ እግዚአብሔር ልዑል፡ ስቡሕ ወውዱስ ዘሣረረ ኲሎ ዓለመ፡ በአሐቲ ቃል። @EOTCW @EOTCW ነግሥ ሰላም ለአብ ዘእምቅድመ ዓለም ነጋሢ፤ ለወልድ ሰላም ሥጋ ማርያም ለባሲ፤ ለመንፈስ ቅዱስ ሰላም ኃጢአተ ዓለም ደምሳሲ፤ ኃይልየ ሥላሴ ወጸወንየ ሥላሴ፤ በስመ ሥላሴ እቀጠቅጥ ከይሴ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ዘለብሰ ስብሐተ፤ ሀሎ ሰማያተ፤ እምድንግል ቃል ሥጋ ኮነ፤ በቤተ ልሔም ተወልደ። ወረብ፦ ዘለብሰ ስብሐተ ዘለብሰ ስብሐተ ሀሎ ሰማያተ፤ እምድንግል ቃል ሥጋ ኮነእምድንግል ቃል። @EOTCW @EOTCW መልክአ ሚካኤል ሰላም ለአጽፋረ እግርከ ፍናዋተ ረድኤት በተኃልፎ፤ ዘኢተዳደቆን እብነ አዕቅፎ፤ ሚካኤል ቀዳሲ ትሥልስተ አካላት በኢያዕርፎ፤ ኢትኅድገኒ በዓለም እስመ ኪያከ እሴፎ፤ አልቦ ብእሲ ዘየኀድግ ሱታፎ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ቅዱስ ቅዱስ ቅዱስ እግዚአብሔር፤ ዘበተዋሕዶ ይሤለስ፤ እምኀበ ትጉሃን ይትቄደስ፤ እሳተ ሕይወት ዘኢይትገሠሥ፤ ወዘኢይጤየቅ ለዓይን ረቂቅ መንፈስ፤ ንሰግድ ለትሥልስቱ አሐተ ስግደተ፤ ወሎቱ ናቄርብ ስብሐታተ። @EOTCW ማኅሌተ ጽጌ ተፈሥሒ ማርያም እንተ ኢተአምሪ ብእሴ፤ ዘጸገይኪ ለነ አሐደ እምነ ሥላሴ፤ እንዘ ትዘብጥ ከበሮ ቅድመ አዕላፈ ኤፍሬም ወምናሴ፤ ለተአምርኪ ትነግር ውዳሴ፤ ማርያም እኅቱ ለሙሴ። @EOTCW ዚቅ በፈቃደ አቡሁ ወረደ ኀበ ማርያም ተአንገደ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ። @EOTCW @EOTCW ወረብ፦ በፈቃደ አቡሁ ወረደ ተአንገደ በደብረ ብርሀን ፤ በድንግልናሃ ንጹሕ በድንግልናሃ ንጹሕ እግዚአብሔር ተወልደ። @EOTCW @EOTCW መልክአ ሥላሴ ሰላም ለህላዌክሙ ዘይመውዕ ህላውያተ፤ ለረኪበ ስሙ ኅቡዕ አመ ወጠንኩ ተምኔተ፤ እምግብርክሙ ሥላሴ ሶበ ረከብኩ አስማተ፤ መለኮተ ለለአሐዱ ዘዚአክሙ ገጻተ፤ እንበለ ትድምርት እሰሚ ወእሁብ ትድምርተ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ፤ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ፤ ነአምን ዘንተ ሥላሴ ፩ ውእቱ አምላክ ፍጹም፤ ዘእምኔሁ ለአብ ወልድ ተወልደ፤ በአምሳለ ዚአሁ፤ ኅቡር ኅላዌሁ፤ ነአምን ንሕነ ነአምን። @EOTCW ወረብ ነአምን በአብ ወነአምን በወልድ ወነአምን በመንፈስ ቅዱስ/፪/ ፩ ውእቱ አምላክ ፍጹም ፩ ውእቱ/፪/ @EOTCW መልክአ ሥላሴ ሰላም ለአጻብኢክሙ እለ እምአጽፋር ኢይትሌለዩ፤ ለቤትክሙ ሥላሴ ዘኢየኃልቅ ንዋዩ፤ አመ አብዓልክሙ ሰብአ ድኅረ አንደዩ ጌጋዩ፤ ዘኢርእዩ እምቅድመ ዮም መላእክተ ሰማይ ርእዩ፤ ወአግብርተ ሰብእ መላእክት ተሰምዩ። @EOTCW @EOTCW ዚቅ ርእይዎ ኖሎት አእኮትዎ መላእክት፤ ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል፤ ዮም ሰማያዊ በጎል ሰከበ። @EOTCW @EOTCW ወረብ ርእይዎ 'ኖሎት'/፪/ ርእይዎ አእኮትዎ/፪/ ለዘተወልደ እማርያም እምቅድስት ድንግል/፪/ @EOTCW መልክአ ሥላሴ ለዘበነጊድ አቅረብኩ መካልየ ልሳን ስብሐታተ፤ መጠነ ራብዕ ዐሥር እንዘ አተሉ ሰብዓተ፤ ህየንተ አሐዱ ሥላሴ እለ ትፈድዩ ምዕተ፤ ጸግዉኒ እምገጽክሙ ንዋየ ገጽ ትፍሥሕተ፤ ወዲበ ዐሠርቱ አህጉር ሀቡኒ ሢመተ። @EOTCW @EOTCW ወረብ ጸግዉኒ አጋዕዝትየ እምገጽክሙ ንዋየ ገጽ/፪/ ወዲበ ዐሠርቱ አህጉር ሀቡኒ ሢመተ/፪/ @EOTCW ዚቅ ስብሐት ለከ ስብሐት ለዘወለደከ፤ ስብሐት ለዘሠረፀ እምአቡከ፤ ዘዕሩይ ምስሌሁ ወምስሌከ፤ በከዊነ ዘሀሎ ወይሄሉ፤ ለዓለመ ዓለም። @EOTCW ወረብ ስብሐት ለከ ስብሐት ለዘወለደከ ስብሐት ለዘሠረፀ እምአቡከ/፪/ ዘሀሎ ወይሄሉ ዘዕሩይ ምስሌሁ/፪/ @EOTCW @EOTCW አንገርጋሪ ኲሉ ይሰግድ ለሥላሴ፤ ወይትቀነይ ኲሉ ለመንግሥተ ሥላሴ፤ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል፤ ወበዓይኑ ይኔጽር ቀላያተ። @EOTCW @EOTCW አመላለስ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል እስመ ኮነ/፪/ ወበዓይኑ 'ይኔጽር'/፪/ ቀላያተ/፪/ @EOTCW @EOTCW ወረብ ኲሉ ይሰግድ 'ለሥላሴ'/፪/ ኲሉ ይሰግድ/፪/ ወይትቀነይ ኲሉ ለመንግሥተ 'ሥላሴ'/፪/ ኲሉ ይሰግድ/፪/ @EOTCW @EOTCW እስመ ለዓለም ዘሰንበት፦ ዘዲበ ኪሩቤል ይነብር ወበአርያም ይሴባሕ፤እምሰማያት እምልዑላን ወረደ፤አምላክ ያድኅን ዓለመ መጽአ ይክሥት ብርሐነ ይቤዙ ዓለመ፤ ወልድ ተወልደ ለነ፤ ሠርዓ ሰንበት ለሰብአ ዕረፍት ፤ወልድ ዋህድ ውእቱ 🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿🌿 መዝሙር 🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹🌹 (በ፪/ሩ) ንጉሥኪ ጽዮን ለትውልደ ትውልድ መጽአ ኀቤነ ዘኪያሁ ይሴፈዉ ሰማያት ወምድር ዕበይ ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይጸመድዎ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ዓምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ፍሥሐ ኮነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። ምልጣን፦ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ። ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይጸመድዎ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ዓምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ ኢተዘኪሮ አበሳነ ኢኀደገነ ፍሥሐ ኮነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ https://t.me/Eotcw #Join & share

09 tir.mp32.45 MB

photo content

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ የዚህ ሳምንት መዝሙር፦ ሃሌ ሉያ "ንጉሥኪ ጽዮን ለትውልደ ትውልደ መጽአ ኀቤነ ዘኪያሁ ይሴፈው ሰማያት ወምድር ዕበይ ለነገሥት ብርሃኖሙ ለእለ ይፀመድዎ አክሊለ ሰማዕት ሠያሜ ካህናት ዐምዳ ወድዳ ለቅድስት ቤተ ክርስቲያን በቤተ ልሔም ተወልደ ወበናዝሬት ተሐፅነ፣ ኢተዘኪሮ አበሳ አኃደገነ ፍሥሓ ኮነ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ"። ትርጉም፦ ጽዮን ሆይ ንጉሥሽ ለልጅሽ ልጅ ወደ እኛ መጣ፣ ሰማያትና ምድር እርሱን ተስፋ የሚያደርጉ፣ የነገሥታት ልዕልና ከእርሱ ጋር ለሚጠመዱ ብርሃናቸው የሆነ የሰማዕታት አክሊላቸው የካህናት ሹመታቸው የቅድስት ቤተ ክርስቲያን አምዷና መሠረቷ የሆነ ክርስቶስ በቤተ ልሔም ተወለደ በናዝሬት አደገ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content
+1

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ "ንስግድ ለአብ ንስግድ ለወልድ ንስግድ ለመንፈስ ቅዱስ ሥላሴ ዋሕድ ለዘአሐዱ ሠለስቱ ወለዘሠለስቱ አሐዱ በአሐዱ ስግደት"። ትርጉም፦ በአንድነት በሦስነት ላለ ለአብ እንስገድ፤ ለወልድ እንስገድ፤ ለመንፈስ ቅዱስም እንስገድ፤ አንድነት ላለው ሦስትነት፤ ሦስትነት ላለው አንድነት አንድ ስግደት እንስገድ። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content
+3

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፯ (7) ቀን። ❤ እንኳን ለአጋዕዝተ ዓለም ለቅድስት ሥላሴ የሰናዖር (የባቢሎንን) ቋንቋቸው ለደባለቁበትና የሰሩት ግንብ ላፈረሱበት ዓመታዊ መታሰቢያ በዓል (ታሪኩ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ ዘፍ11፥1-9)፣ ታላቁ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን የክርስትና ጥምቀት ላጠመቀው ለሮሜ አገር ሊቀ ጳጳስ ለከበረ አባት ለአቡነ ሶል ጴጥሮስ ለዕረፍት በዓልና ለታላቁ አባት ለቅዱስ ኤፍሬም ሶርያዊ ለመታሰቢያው በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከሰሎሞን፣ ከጎርጎርዮስ፣ ከማርቆስ ከአትያኖስ፣ ከሉያ፣ ከመልይን፣ ከሱስዮስና ከማርትይ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ኵሉ ይሰግድ ለሥላሴ ወይትቀነይ ኵሉ ለመንግሥተ ሥላሴ እስመ ኮነ ዘይነብር ዲበ ኪሩቤል ወበዓይኑ ይኔጽር ቀላያተ"። ትርጉም፦ ሁሉ ለሥላሴ ይስገድ፤ ለሥላሴም መንግሥት ይገዛ፤ በኪሩቤል ላይ ተቀምጦ በዐይኑ ጥልቆችን የሚያይ ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ የሮሜ አገር ሊቀ ጳጳስ አባ ሶል ጴጥሮስ፦ ይህንንም አባት ስለ ተጋድሎው ገናናነት ስለ አገልግሎቱም ስለ ትሩፋቱ ስለ አዋቂነቱና ስለ ደግነቱ ከእርሱ በፊት የነበረ ሊቀ ጳጳሳት አባ መልጥያኖስ ከዐረፈ በኋላ መርጠው ሊቀ ጵጵስና በሮሜ አገር ላይ ሾሙት። በሐዋርያት አለቃ በጴጥሮስ ወንበር በተቀመጠ ጊዜ የዕሊኒ ልጅ የሆነ ንጉሥ ቈስጠንጢኖስን የክርስትና ጥምቀትን አጠመቀው ከከሀድያን ጋር ስለሚያደርገው ጦርነት ምክንያት ገና አልተጠመቀም ነበርና የጣዖታትንም ቤቶች አፍርሶ የእግዚአብሔር አብያተ ክርስቲያናት ሠራላቸው። ❤ የዚህም አባት ሶል ጴጥሮስ ገድሉ እጅግ ብሩህ የሆነ ነው እርሱ ሁል ጊዜ ሕዝቡን ያስተምራቸዋልና ከልቡናቸውም ከሰይጣን የሆነ ጥርጥርንና ክፉ ሐሳብን ያርቃል። ከእነርሳቸው ሥውር የሆነውንም የመጻሕፍት ምሥጢር ተርጒሞ ያስገነዘባቸው። አይሁድንና ዮናናውያንን ሁል ጊዜ ይከራከራቸው ነበር ከእርሳቸውም ብዙዎችን መልሶ ወደ ቀናች ሃይማኖት አስገባቸው የክርስትና ጥምቀትንም አጠመቃቸው ስሙም በምእመናን ዘንድ ፈጽሞ የሚያስፈራ ሆነ። እግዚአብሔርን ስለ ማወቅና ስለ ወልደ እግዚአብሔር ሰው መሆን ብዙ ድርሳናትን ደረሰ። ❤ በተሾመ በሰባተኛውም ዓመት ስለ አርዮስ በኒቅያ ከተማ ሃይማኖታቸው የቀና የሦስት መቶ ዐሥራ ስምንት የከበሩ አባቶች የአንድነት ስብሰባ ሆነ ይህም አባት ሶል ጴጥሮስ ከእርሳቸው አንዱ ነበር አርዮስንም ከተከታዮቹ ጋር ረገመው አውግዞም ለየው። በሹመቱም ዐሥራ አንድ ዓመት ኖረ መልካም ተጋድሎን ፈጽሞ እግዚአብሔርንም አገልግሎ ጥር7 ቀን በሰላም ዐረፈ። ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን እኛንም በአባ ሶል ጴጥሮስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር7 ስንክሳር። + + + ❤ "ሰላም ለኤፍሬም ደራሲ ዘጽሩይ ልሳኑ፤ አብያተ ክርስቲያናት ይሰርገዉ በድርሳኑ"። ትርጉም፦ አብያተ ክርስቲያናት በድርሳኑ ያጌጡ ዘንድ አንደበቱ የጠራና ደራሲ ለኾነ ለኤፍሬም ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለከ ጴጥሮስ ሶል። መጥምቀ ቈስጠንጢኖስ ንጉሥ ከሣቴ መስቀል። መዋዕለ ዕብሬትከ ኮነ ዕብሬተ ርትዕ ወሣህል። እስመ ተቀጥቀጠ ዳጎል ወወድቀ ቤል። በከመ ቀዳሜ ኢሳይያስ ይብል"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር7። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ሣህሉ ለእግዚአብሔር መልአ ምድረ። ወበቃለ ለእግዚአብሔር ፀንዐ ሰማያት። ወእስትንፋሰ አፉሁ ኵሉ ኃይሎሙ"። መዝ 32፥5-6 ወይምመዝ 71፥15። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 28፥16-20 ወይም ማቴ 2፥21-ፍ.ሜ። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ናሁ ሰማዕናሁ በኤፍራታ። ወረከብናሁ ውስተ ኦመ ገዳም። ንበውዕ እንከሰ ውስተ አብያቲሁ ለእግዚአብሔር"። መዝ 131፥6-7። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 15፥1-14፣ 1ኛ ዮሐ 4፥14-ፍ.ም፣ የሐዋ ሥራ 13፥32-44። የሚነበበው ወንጌል ማቴ 2፥19-ፍ.ም። የሚቀደሰው ቅዳሴ ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ነው። መልካም የቅድስት ሥላሴ በዓል ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

#ጥር ➏ በዓለ ግዝረት ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ዘጠኙ ንዑሳን በዓላት አንዱ እና የመጀመሪያው ይህ የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ግዝረት ነው። ሉቃ1 :21 ሊገርዙትም ስምንት ቀን በሞላው ጊዜ በማኅፀን ሳይገረዝ በመልዐኩ እንደተባለው ስሙ ኢየሱስ ተብሎ ተጠራ። እመቤታችንም ወደ ወደ ግዝረት ቤት ወሰደችው ገራዡም ምላጩን ይዞ ቀረበ ነገር ግን ምላጩ እጁ ላይ ሳለ ውሀ ሆኖ ፈሰሰ ጌታችንም በተዓምር የተገረዘ ሆኖ ተገኘ ይላል ምነዋ ቢባል ጌታችን ደሙ የሚፈሰው ስጋውም የሚቆረሰው አንዴ እና እርሱም በእለተ አርብ ስለሆነ ብቻ ነው። ጌታችን የሰውን ስርአት ሁሉ ጠብቋል እራሱ እንደተናገረው እኔ ህግን እና ነብያት ልሽር የመጣሁ አይምሰላችሁ ፤ ልፈፅም እንጂ ልሽር አልመጣሁም። ማቴ 5 :17 ብሎ እንደተናገረው ነው። ከድንግል ማርያም የመወለዱ ሚስጢር ሊመረመር እንደማይችል ሁሉ እናም ሲወለድም ድንግልናዋን እንዳለወጠው ሁሉ ግዝረቱም በማይመረመር ምስጢሩ እንዲሁ ሆነ ። እንደዚሁም በር ተዘግቶ ሳለ ወደ ሀዋርያት እንደገባ ሁሉ ግዝረቱም እንደዚያው ከሰውነቱ ምንም ሳይቆረጥ ህግን ይፈፅም ዘንድ በድንቅ ሚስጢሩ ይህን አደረገ ምክንያቱም የሚገረዝባቸው ምላጮች ቀልጠው እንደ ውሀ ሆነዋልና። በእውነቱ እርሱ የእስራኤል ገዢ ሲሆን የእግዚአብሔር ልጅ ነውና ። እንኳን ለጌታችን ለመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዓለ ግዝረት በሰላም አደረሰን ። #_ሰናይ__ቀን

photo content

Share 'ሥርዓተ_ማኅሌት_ዘበዓለ_ግዝረት_ጥር_፮.pdf'

+ + + ❤ "ሰላም እብል ለኖኅ በሕቁ። ምስለ ብእሲቱ ወደቂቁ። በገቢረ ታቦት ላዕሌሁ እለ ተሣለቁ። በዝናመ ድምሳሴ ወበማየ አይኅ ኀልቁ። ውእቱሰ እምሠጠ በጽድቁ"። ሊቁ አርከ ሥሉስ (አርኬ) የጥር 6። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ በዚህም በከበረ ባስልዮስ ላይ መንፈስ ቅዱስ መልቶበት በሁሉ ዘንድ የታወቀች ቅዳሴውን ደረሰ፡፡ እግዚአብሔርም በእጆቹ ብዙ አስደናቂ ተአምራትን አድርጓል፡፡ ቤተ ክርስቲያንን ሊሠርቁ የመጡትን ሌቦች ወደ ቤተ ክርስቲያን እንዳይገቡ በጸሎቱ በሩን ዘግቶባቸዋል፡፡ በኋላም ምእመናን ሲመጡ በሩን ከፍቶላቸዋል፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ከ318ቱ ሊቃውንት አንዱ መሆኑን ነው፡፡ የታላቁ አባት የቅዱስ ኤፍሬምም መምህሩ ነው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ ያደረጋቸው ተአምራት ስፍር ቁጥር የላቸውም፡፡ ❤ ወንድሙ የስብስጥያ ኤጲስቆጶስ ከሚስቱ ጋር በድንግልና ሲኖር ሕዝቡ ግን ያሙት ነበርና ቅዱስ ባስልዮስ መላእክት ሲጠብቋቸው እንደተመለከተ ለሕዝቡ ገልጦላቸው ሕዝቡ ከሐሜት ርቀው ንስሓ እንዲገቡ አድርጓቸዋል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ከምድር እስከ ሰማይ የሚደርስ የብርሃን ምሰሶ በተመለከተ ጊዜ "ይህ የቂሳርያው የባስልዮስ ነው" የሚል ቃልን ሰምቷል፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም ወደ ቂሳርያ ሄዶ ከቅዱስ ባስልዮስ ዘንድ ዲቁናና ቅስና ተቀብሏል፡፡ ቅዱስ ባልዩስም በቅዱስ ኤፍሬም በላዩ ጸልዮለት የማያውቀውን አዲስ የዮናኒን ቋንቋን እንዲናገር አድርጎታል፡፡ ❤ ቅዱስ ባስልዮስ ሰው ሁሉ የሚያምንበትና በአቆጣጠሩም የሚታወቀውን ጠንቋይም በተአምሩ አሳምኖታል፡፡ ይኸውም ቅዱስ ባስልዮስ በታመመ ጊዜ የሚሞትበትን ጊዜ ዐውቆ ይህን ጠንቋይ ጠርቶ "ንገረኝ እስቲ መቼ እሞታለሁ?" አለው፡፡ ጠንቋዩም "ማታ ነፍስህ ከሥጋህ ትለያለች" አለው፡፡ እርሱም "እስከ ጠዋት ካልሞትኩ ክርስቲያን ትሆናለህ?" በማለት ቃል አስገባው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ወደ ጌታችን በመጸለይ በዕድሜው ላይ ሦስት ቀናት አስጨመረ፡፡ ያም ጠንቋይ ሥራው ከንቱ እንደሆነ ታወቀበትና እርሱም አምኖ ከነቤተሰቦቹ ተጠምቆ ክርስቲያን ሆነ፡፡ ❤ ሌላው ተአምር ለቅዱስ ባስልዮስ እመቤታችን ስለ ሥዕሏ የነገረችው ነው፡፡ ይህም ቅዱስ ባስልዮስ የእመቤታችንን ቤተ ክርስቲያን ከሠራ በኋላ በውስጧ የሚያኖረውን የእመቤታችንን ሥዕል ሊያሠራ መሳያ ሠሌዳ ፈለገ፡፡ ሰዎችም በአንድ ባለጸጋ ቤት ጥሩ ሠሌዳ እንዳለ ነገሩትና ሄዶ ባለጸጋውን ሠሌዳውን እንዲሰጠው ለመነው፡፡ ባለጸጋውም የልጆቼ ነው አልሰጥም አለው፡፡ በትዕቢትም ሆኖ በታነጸቸው ቤተ ክርስቲያን ላይ የስድብን ነገር ተናገረ፡፡ ወዲያውም ወድቆ ክፉ አሟሟት ሞተና ልጆቹ ፈርተው ሠሌዳውን አምጥተው ለባስልዮስ ሰጡት፡፡ እርሱም ያንን ሠሌዳ የእመቤታችንን ሥዕል አሳምሮ ይስልበት ዘንድ ለሰዓሊ ወስዶ ሰጠው፡፡ በዚህም ጊዜ እመቤታችን በራእይ ለቅዱስ ባስልዮስ ተገለጠችለትና ከአመፀኛ ሰው የተገኘ ነውና በዚያ ሰው ሠሌዳ ሥዕሏን እንዳያስል ከለከለችው፡፡ ሥዕሏ የተሳለበትን ሠሌዳም የት እንደሚገኝ ነገረችውና ሄዶ በታላቅ ክብር አምጥቶ በቤተ ክርስቲያኑ አስቀመጠው፡፡ ከሥዕሉም ሥር ድውያንን ሁሉ የሚፈውስ የዘይት ቅባት መፍሰስ ጀመረ፡፡ በዚህም ብዙዎች ድንቅ የሆነ ፈውስን አገኙ፡፡ ይህም የተፈጸመው ሰኔ 21 ቀን ነው፡፡ ❤ ሌላም እንዲሁ ቅዱስ ባስልዮስ ያደረገው ተአምር የሰይጣንን የጽሕፈት ደብዳቤ በጸሎቱ የደመሰሰ መሆኑ ነው፡፡ አንድ ጎልማሳ አገልጋይ የጌታውን ልጅ ስለወደዳት ወደ አንድ ሥራይኛ ዘንድ ሄደ፡፡ ሥራይኛውም የክህደት ደብዳቤ ጽፎ ሰጠውና ወደ አረሚ መቃብር ሄዶ በመንፈቀ ሌሊት ደብዳቤዋን ይዞ በመቃብሩ እንዲቆ ላይ አዘዘው፡፡ ወጣቱም እንደታዘዘው አደረገ፡፡ ከሰይጣናትም አንዱ መጥቶ ወደ ወደ አለቃቸው አደረሰው፡፡ ያችንም የክህደት ደብዳቤ ከእጁ ወሰዳት፡፡ ሰይጣንም "የፈለከውን አደርግልሃለሁ ነገር ግን አምላክህን ክርስቶስን ትክደዋለህ ፈቃድህን ከፈጸምኩልህ በኋላም ወደ እርሱ አትምለስም" ሲለው ወጣቱም በልጅቷ ፍቅር አብዶ ነበርና "አዎን ጌታዬ ያዝከኝን ሁሉ አደርጋለሁ" አለው፡፡ ሰይጣኑም "ይህን ልታደርግ በእጅህ ጻፍልኝ" አለውና አጻፈው፡፡ ከዚህም በኋላ ሰይጣን በጌታው ሴት ልጅ ልብ ውስጥ አደረና ያንን ወጣት እጅግ ወደደችው፡፡ የፍትወት እሳትንም በልቧ ላይ ስላነደደባት መታገስ አልቻለችምና ወደ አባቷ ቀርባ ልጁን አጋባኝ አለችው፡፡ የልጁም ፍቅር በየዕለቱ ይጨምርባት ነበርና ራሷን እንዳታጠፋ ቤተሰቦቿ አጋቧት፡፡ ከእርሱ ጋር መኖር ከጀመረች በኋላ ሲያማትብ እንኳን አይታው አታውቅም ነበርና ስትመረምረው ክርስቲያን አለመሆኑንና ያደረገውንም ሁሉ ነገራት፡፡ ይህንንም ስትሰማ እጅግ ደንግጣ ወደ አገሯ ሊቀ ጳጳስ ወደ ባስልዮስ ዘንድ ሄዳ ከእግሩ ሥር በመውደቅ የደረሰባትን በመንገር ከሰይጣን እጅ እንዲያድናት ለመነችው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም በሏ የሆነውን የአባቷን ባርያ አስመጣውና በንስሓ ተመልሶ ክርስቲያን መሆን እንደሚፈልግ ጠየቀው፡፡ ወጣቱም ፈቃደኝነቱን ሲገልጥለት በአንድ ቦታ ውስጥ አስገብቶ ዘጋበትና ከላይ በመስቀል ምልክት አተመበት፡፡ እንዲጸልይም አዘዘው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ስለ ወጣቱ ብዙ ጸለየ፡፡ ከሦስት ቀንም በኋላ ጎበኘውና በ3ቱ ቀን የደሰበትን ጠየቀው፡፡ ወጣቱም በላዩ በመጮህ ሰይጣናት ሲያስፈራሩት ያንንም ደብዳቤ ሲያሳዩትና በእርሱ ላይ ሲቆጡ በመከራ ውስጥ እንደኖረ ነገረው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም "ከሰይጣናቱ ቁጣ የተነሣ አትፍራ አይዞህ እግዚአብሔር ይረዳናል" ብሎ ጥቂት ከመገበው በኋላ መልሶ ዘጋበትና ሄዶ ይጸልይለት ጀመር፡፡ ❤ ዳግመኛም ከ3 ቀን በኋላ መጥቶ ጠየቀው፡፡ ወጣቱም "የአጋንንቱን ጩኸታቸውን እሰማዋለሁ ነገር ግን አላያቸውም" አለው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስ አሁንም ጥቂት ከመገበው በኋላ መልሶ ዘጋበትና እስከ 40 ቀን ድረስ እንዲሁ አደረገ፡፡ ከ40 ቀንም በኋላ መልሶ ሲጠይቀው ወጣቱ "ቅዱስ አባቴ ሆይ ስለ እኔ ሰይጣንን ስትጣላውና ድል አድርገህ ጥለህ ስትረግጠው በዛሬዋ ሌሊት አየሁ" አለው፡፡ ቅዱስ ባስልዮስም ይህን ሲሰማ እጅግ ደስ አለው፡፡ የቤተ ክርስቲያን አገልጋዮችንም ጠርቶ እግዚኦታ አደረሱና ከእግዚኦታው በኋላ ያ ወጣት ጽፎ ለሰይጣን የሰጠው የክህደት ደብዳቤ ከሰይጣን እጅ ተወስዶ በሕዝቡ ሁሉ ፊት ወደቀ፡፡ ሁሉም ደስ ብሏቸው እግዚአብሔርን አመሰገኑት፡፡ ይኸውም የተደረገው መስከረም 13 ቀን ነው፡፡ ❤ አንዲት ሴት ኃጢአቷን ሁሉ በዝርዝር ጽፋ በክርስታስ አሽጋ እንዲጸልይላት ቅዱስ ባስልዮስን ለመነችው፡፡ እርሱም ከአንዲት ኃጢአቷ በቀር ሁሉንም በጸሎቱ ደመሰሰላት፡፡ ስለ አንዲቱም ኃጢአቷ ወደ ቅዱስ ኤፍሬም እንዲትሄድ አዘዛት፡፡ ቅዱስ ኤፍሬምም "ወደ ቅዱስ ባስልዮስ ሳይሞት ፈጥነሽ ተመለሽ የካህናት ሁሉ አለቃ ስለሆነ የቀረች ኃጢአትሽን የሚደመስስልሽ እርሱ ነው" ብሎ መለሳት፡፡ በተመለሰችም ጊዜ ቅዱስ ባስልዮስ ዐርፎ ሊቀብሩት ሲወስዱት አገኘችው፡፡ እርሷም መሪር ልቅሶን ካለቀሰች በኋላ በእምነት ሆና ያንን ክርስታስ ከአስክሬኑ ላይ ጣለችው፡፡ ስለ እምነቷም ጽናት ያች የቀረች በደሏ ተደመሰሰችላት፡፡ ❤ ይህም የከበረ ቅዱስ ባስልዮስ በዚህ መጽሐፍ ውስጥ ከጻፍነው ሌላ ብዙዎች ድንቆች ተአምራቶችን አድርጓል ብዙዎችንም ተግሣጻትንና ድርሳናትንና ለመነኰሳትም ትምህርቶችን ደርሷል፡፡ ከብሉይና ከሐዲስም አምላካውያን የሆኑ ብዙ መጻሕፍቶችን ተርጒሟል ሥርዓቶችንም ሠራ እነርሱም በሁሉ ቦታ ይገኛሉ ከዚህም በኋላ ጥር6 በሰላም ዐረፈ በክብር በብዙ ምስጋና ቀበሩት። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በቅዱስ ባስልዮስ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 6 ስንክሳር።

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን ከአዳም ዐሥረኛ ትውልድ ለሆነው ለታላቁ አባት ለጻድቁ ለቅዱስ ኖኅ ለዕረፍቱ መታሰቢያ፣ ለታላቁ ነቢይ ለቅዱስ ኤልያስ በሕይወት ሳለ በእሳት ሠረገላ ወደ ሰማይ ለዐረገበት (ከሞት ለተሰወረበት) በዓል፣ ለታላቋ ሰማዕት ለቅድስት አርሴማ ለልደቷ በዓልና ለከበረና ለታላቁ አባት ለቂሣርያ ኤጲስቆጶስ ለአቡነ ባስልዮስ ለዕረፍት በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእስክድርያ ስምንተኛ ሊቀ ጳጳስ ከአባ ወርክያኖስ ዕረፍትና በበረሀ ስልሳ ዘመናት ከኖረ ከአባ ሙሴ ዕረፍት ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ "ሰላም ለኤልያስ ነቢይ ቴስብያዊ ኮሬባዊ ታቦራዊ ሰማየ ዘለጐመ ወከልአ ዝናመ፤ ቃለ ጸሎቱ ዘተሰምዐ ውስተ ዕዝኑ ለአዶናይ ወአውረደ እሳት እምሰማይ እስከ በልዖ ለማይ፤ ዘዐደወ ብሔረ ተድላ ተጽኢኖ ዘእሳት ሠረገላ። ትርጉም፦ ቴስቢያዊ (የቴስቢያ ሰው)፤ ኮሬባዊ (ወደ ኮሬብ ተራራ የወጣ)፤ ታቦራዊ (በታቦር ተራራ የተገኘ) ፤ ዝናብ እን ዳይዘንብ ሰማይን የለጐመ ለኾነ፤ የጸሎቱ ቃልም በአዶናይ ዦሮ ውስጥ ለተሰማ፤ ውሃውን እስካበላ ደርሶ እሳትን ከሰማይ ያወረደ ለኾነ፤ በእሳት ሠረገላ ተጭኖ ወደ ተድላ ደስታ ቦታ ለገባ ለነቢዩ ለኤልያስ ሰላምታ ይገባል። ሊቁ አባ ጊዮርጊስ ዘጋስጫ በተአምኆ ቅዱሳን ላይ። + + + ❤ የነቢዩ ቅዱስ ኤልያስ ዕረገት፦ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ኤልያስን ወደ ሰማይ በሚወጣባት ጊዜ ኤልሳና ኤልያስ ከገልገላ ተነሥተው ሔደወሰ ወደ ዮርዳኖስ ደረሱ ኤልያስም መጠምጠሚያውን አውርዶ ጠቅሎ የዮርድያኖስ ውኃ መታበት ውኃውም ተከፍሎ ወዲያና ወዲህ ቆመ ሁለቱም ሁሉ በደረቅ ተሻገሩ ወጥተውም በምድረ በዳ ቆመ። ❤ ኤልያስ ኤልሳን "ካንተ ተለይቼ ወደ ሰማይ ሳልወጣ አደርግልህ ዘንድ የምትሻውን ለምነኝ" አለው ኤልሳዕም ኤልያስን "በአንተ ያደረ ሀብተ መንፈስ ቅዱስ ዕጥፍ ሁኖ ይደርብኝ" አለው። ኤልያስም ኤልሳን "ድንቅ ነገርን ለመንከኝ ነገር ግን ካንተ ተለይቼ ወደ ሰማይ ሳርግ ብታየኝ ይሁንልህ ባታየኝ ግን አይሆንልህ" አለው። በዚያንም ጊዜ የእሳት ሠረገላና የእሳት ፈረስ መጣ ወደ መካከላቸውም ገብቶ አራራቃቸው ኤልያስም እንደዚህ በንውጽውጽታና በጥቅል ነፋስ ወደ ሰማይ ዐረገ። ኤልሳዕም አይቶ "የእስራኤል ኃይላቸውና ጽናታቸው አባ አባ ብሎ ጮኸ ከዚህ በኋላ ዳግመኛ አላየውም ልብሶቹንም ለሁለት አድርጎ ከፈላቸው ኤልያስም ለኤልሳዕ መጠምጠሚያውን ጣለለት በኤልሳዕም ራስ ላይ ወረደ የኤልያስም ሀብተ መንፈስ ቅዱስ በኤልሳዕ ላይ ዕጥፍ ሁኖ አደረ ኤልያስም የሠራውን ተአምራት ኤልሳዕ ዕጥፍ አድርጎ ሠራ። ❤ ይህም ኤልያስ በኋላ ዘመን ከኄኖክ ጋር ይመጣ ዘንድ አለው ሐሳዊ መሢሕንም ይቃወሙታል እርሱም ይገድላቸዋል በድናቸውም በአደባባይ ተጥሎ ሦስት መዓልት ሦስት ሌሊት ይቆያል ከዚህም በኋላ ይነሣሉ የሙታን ትንሣኤም ይሆናል ይህም ኤልያስ እውነተኛ ነቢይ አስቀድሞ የነበረ በኋላም የሚገለጽ ነው በብሉይ ዘመንም ኑሮው በበረሃ ውስጥ ነበር። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በነቢይ በቅዱስ ኤልያስ ጸሎት ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ አባታችን ጻድቁ ቅዱስ ኖኅ፦ እርሱም ከአባታችን አዳም ዐሥረኛ ትውልድ ነው። እርሱም ከታናሽነቱ ጀምሮ ኃጢአት እንደሚበዛ ክፋትም እንደሚመላ ደጋጎች እንደሚያንሱ ሥጋ የለበሰ ሁሉ በጥፋት ውኃ እንደሚመሰስ አምላካዊ ምሥጢርን የሚያይ ሆነ ስለዚህም ፊቱ የተቋጠረ ሁኖ ፈጽሞ ያለቅስ ነበር። ❤ አምስት ዓመት ድንግልናውን ጠብቆ በእግዚአብሔር ትእዛዝ ለአባታችን አዳም ሥጋ ሲያገለግል ኖረ፡፡ ከዚህም በኋላ ሚስት እንዲያገባ እግዚአብሔር አዘዘው፡፡ ሥጋ የለበሰ ሁሉ እንደሚደመሰስ ከእርሱ ዘር በቀር የሚተርፍ እንደሌለ ነገረው፡፡ ጻድቁ ኖኅም የአቡዚር ልጅ የሆነች ሐይከል የምትባል ሴት አግብቶ ወደ እርሷ ሦስት ጊዜ ቢገባ ሦስት ልጆችን ሴም ካም ያፌትን ወለዳቸው፡፡ ❤ ከዚህም በኋላ እግዚአብሔር ለኖኅ ከደብር ቅዱስ ዕንጨት ቆርጦ መርከብን እንዲያሠራ ካዘዘው በኋላ አሠራሯን በዝርዝርና በጥልቀት አስረዳው፡፡ የቃየል ልጆችም ኖኅን መርከብ ሲሠራ አይተው ዘበቱበት፡፡ የአዳምንም ሥጋ ወስዶ በውስጡ አኖረ፡፡ ሴም ወርቁን፣ ካም ከርቤውን፣ ያፌት ዕጣኑን ወስደው ወደ መርከብ አስገቡ፡፡ ኖኅም ከልጆቹና ከሚስቶቻቸው ጋራ ወደ መርከቡ ገባ፡፡ ንጹሐን የሆኑት እንስሳትና አእዋፋት ሴትና ወንድ ሰባት ሰባት፣ ንጹሐን ካልሆኑት ደግሞ ሁለት ሁለት ሴትና ወንድ አስገባ፡፡ ከዚያም ሰማይ ተከፍቶ የምድርም ምንጮች ሁሉ ተነድለው ራጃጅም ተራራዎችም እስኪሸፈኑ ድረስ 40 ቀንና 40 ሌሊት ዘነመ፡፡ ውኃውም በላያቸው 15 ክንድ ከፍ አለና ሥጋ የለበሰ ሁሉ ሞተ፡፡ ❤ ከመቶ ሃምሳ ቀንም በኋላ እግዚአብሔር ኖኅን አስቦ ነፋስን በምድር ላይ አመጣና ውኃውን አጎደለ፡፡ ምንጮች ተደፍነው የሰማይ መስኮት ተዘጋ፡፡ መርከቢቱም በ7ኛው በ12ው ቀን አራራት ተራራ ላይ አረፈች፡፡ ከጊዜም በኋላ እግዚአብሔር ኖኅን ከነቤተሰቡ አንድ ላይ ከመርከቡ እንዲወርዱ አዘዘው፡፡ ኖኅም መሠዊያን ሠርቶ ንጹሕ ከሆኑት ሁሉ ወስዶ መሥዋዕት ባቀረበ ጊዜ እግዚአብሔር መልካም መዓዛን አሸተተ፡፡ ዳግመኛም ምድርን በንፍር ውኃ እንዳያጠፋ ቃልኪዳን ገባለት፡፡ ምድር ፀንታ በምትኖርበት ዘመን ሁሉ ዘር መከር፣ ቅዝቃዜና ሙቀት፣ በጋና ክረምት፣ መዓልትና ሌሊት እንደማይቋረጥ ቃልኪዳን ገባለት፡፡ እግዚአብሔርም ኖኅንና ልጆቹን ባረካቸው፡፡ ብዙ ተባዙ ምድርንም ምሉዋት ግዟት አላቸው፡፡ ❤ ኖኅም ምድርን ያርሳት ይቆፍራም ጀመር፡፡ ወይንም ተክሎ ከእርሶ ፍሬውን አድርሶ ወይን ጠጥቶ በሰከረና ራሱን በሳተ ጊዜ የከነዓን አባት ካም የኖኅን ራቁትነት አይቶ ሳቀ፣ ሄዶም ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው፡፡ ያፌትና ሴምም ልብስ ወስደው የአባታቸውን ርቃን ሸፈኑ፡፡ ኖኅም ከስካሩ በነቃ ጊዜ ሁሉም ያደረጉትን ዐወቀ፡፡ "ከነዓን የተረገመ ይሁን፣ ለወንድሞቹም ተገዥ አገልጋይ ይሁን" ብሎ ከረገመው በኋላ "የሴም ፈጣሪ እግዚአብሔር ይመስገን፣ እግዚአብሔርም የያፌትን አገር ያስፋ፣ በሴም ቤትም ይደር ከነአንም አገልጋይ ይሁን"። ❤ አባታችን ቅዱስ ኖኅም ከጥፋት ውኃ በኋላ ሦስት መቶ ኅምሳ ዓመት ኖረ የኖኅም መላ ዕድሜው ዘጠኝ መቶ ኃምሳ ሆነ በሰላምም ዐረፈ። ለእግዚአብሔርም ምስጋና ይሁን እኛንም በአባታችን በጻድቁ ኖኅ በጸሎቱ ይማረን በረከቱም ከእኛ ጋር ትኑር ለዘላለሙ አሜን። + + + ❤ ቅዱስ ባስልዮስ ዘቂሣርያ፦ የዚህም ቅዱስ የአባቱ ስም ኤስድሮስ ይባላል እርሱም ከአንጾኪያ አገር ሰዎች ንጹሕና ቅዱስ የሆነ ቄስ ነው አምስት ልጆችንም ወልዶአል እነርሱም ባስልዮስ፣ ጎርጎርዮስ፣ ጴጥሮስ፣ ኬርዮን፣ መክርዮን ናቸው ሁሉም ከፍጹማንነት የደረሱ ቅዱሳን ናቸው።

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ለንዑስ በዓል ለአንዱ ለግዝረት (ለኢየሱስ) ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ፦ ሃሌ ሉያ "ተወልደ እምድንግል ሰከበ ውስተ ጐል እሙነ ኮነ ልደቱ ለክብረ ቅዱሳን ወለቤዛ ብዙኃን አብ ፈነዎ ለበኲሩ ውስተ ዓለም"። ትርጉም፦ ከድንግል ተወለደ፣ በዋሻ ውስጥ ተኛ፣ በእውነት ልደቱ ለቅዱሳኑ ክብር ለብዙኃንም ቤዛ ሆናቸው፣ አብ አንድያ ልጁን ወደ ዓለም ላከው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ በዚች ቀን የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በሥጋው ወደ ቤተ ግዝረት በመግባት የኦሪትን ሕግ ፈጸመ ልሳነ ዕረፍት ሐዋርያው ቅዱስ ጳውሎስ "ጌታ ክርስቶስ በሥጋው ግዝረትን ተቀበለ ለአባቶች የተሰጠውን ቃል ኪዳን ይፈጽም ዘንድ" ብሎ እንደተናገረ። ለብዙዎችም ጌታችን ወደ ቤተ ግዝረት እንዳልገባና እንዳልተገረዘ ይመስላቸው ነበር እነርሱ እንዳሰቡት ሁኖ ቢሆን ኑሮ አይሁድ ታላቅ ምክንያትን የሚያገኙ በሆኑ ነበር ጌታችን ግን ግዝረትን ሕግ ፈጸመ ለእኛ በግዝረት ፈንታ የክርስትና ጥምቀትን ሰጠን የፋሲካውንም ቂጣ በላ በእርሱም ፈንታ ሥጋውንና ደሙን ሰጠን። ❤ የከበረ ወንጌል "ስምንተኛው ቀን በተፈጸመ ጊዜም ሕፃኑን ሊገዝሩት ወሰዱት ሳትፀንሰው መልአኩ እንዳወጣለት ስሙን ኢየሱስ አሉት" እንዳለ ንጽሕት ድንግል እመቤታችን ማርያም ጻድቅ አረጋዊ ዮሴፍን "እንደ ሕጉ ልጄን እንዲገርዘውና ስሙንም እንድንሰይመው ብልህ የሆነ ገራዥ ሰው አምጣልኝ" አለችው። ዮሴፍም ሔዶ የሚገርዝ ባለሙያ አመጣ ያ ባለሙያም ሕፃኑን ጌታችንን ኢየሱስ ክርስቶስ በእናቱ በንጽሕት ድንግል ማርያም ክንድ ላይ አየው "እንድገርዘው ሕፃኑን በጥንቃቆ ያዙት" አላቸው። ሕፃን ጌታ ኢየሱስ ክርስቶስ መልሶ እንዲህ አለው "ባለሙያ ገራዥ ሆይ ደሜ ሳይፈስ ትገርዘኝ ዘንድ ትችላለህን በዚያች ዕለት ካልሆነ በቀር ደሜ አይፈስምና ጐኔን በጦር ሲወጉኝ ያን ጊዜ ውኃና ደም ይፈሳል ለአዳምና ለሚያምኑ ልጆች መድኃኒት ይሆናል"። ❤ የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የተናገረውን ያ ባለሙያ በሰማ ጊዜ አደነቀ ዕቃውንም ሰብስቦ ተነሥቶ ከሕፃኑ ጌታ እግር በታች ሰገደ ያንጊዜም ምላጮቹ በእጆቹ ላይ ቀልጠው እንደ ውኃ ሆኑ የከበረች ድንግል እመቤታችን ማርያም "ከሴቶች ተለይተሽ አንቺ የተባረክሽ ነሽ የማሕፀንሽ ፍሬ የተባረከ ነው ይህ ልጅሽ ስለርሱ ነቢያት ትንቢት የተናገሩለት የሕያው አምላክ ልጅ ነው" አላት። ❤ ሕፃኑም ለዚያ ባለሙያ ዳግመኛ መልሶ እንዲህ አለው "እኔ ነኝ ትገዝረኛለህ ወይስ ተውክ ወይም ያባቶቼ አባቶች እንዳደረጉ እኔ ላድርግ" ያም ባለሙያ "የአባቶችህ አባቶች እነማን ናቸው?" አለው ሕፃን ጌታችንም "አብርሃም፣ይስሐቅ ያዕቆብ የሕዝቡ ሁሉ አባቶች የሆኑ ናቸው ለእነርሱም ይህ ግዝረት አስቀድሞ ከአባቴ ዘንድ ተሰጣቸው" ባለሙያውም "እኔ ከአንተ ጋር እናገር ዘንድ አልችልም በአንተ ህልውና መንፈስ ቅዱስ አለና" አለው። በዚያንም ጊዜ ሕፃኑ ጌታችን ዐይኖቹን ወደ ሰማይ አቅንቶ "አባት ሆይ ለአብርሃም፣ለይስሐቅ ለያዕቆብ አስቀድሞ ግዝረትን የሰጠሃቸው ያቺን ግዝረት ዛሬ ለእኔ ስጠኝ" አለ። ያን ጊዜ ያለ ሰው እጅ በሕፃኑ ሥጋ ላይ ግዝረት ተገለጠች። ❤ ድንግልናዋ ሳይለወጥ ከድንግል ማሕፀን እንደ መውጣቱ የጌታችን ግዝረቱ የማይመረመር ሆነ እንዲሁ ወደ ሐዋርያት በተዘጋ አዳራሽ መግባቱና መውጣቱ እንደማይመረመር እንዲሁ እንደ ፈቀደ ከረቀቀ ጥበቡ ችሎታውን በመገረዝ ከሥጋው ምንም ምን ሳይቆረጥ ገለጠ። አዳምንና ልጆቹን ያድናቸው ዘንድ በፈቃዱ ከጐኑ በመስቀል ላይ የሚፈሰው ደምና ውኃ ካልሆነ በቀር ብዙም ሆነ ጥቂት ሊሆን አይችልም እርሱ በፈቃዱ ሕጉ እንዲፈጸም አስቀድሞ አዘዘ እንጂ። ❤ ያም ባለሙያው ገራዥ ይህን ተአምር ባየ ጊዜ የሕፃኑንም ነገር በሰማ ጊዜ እጅግ አደነቀ የክብር ባለቤት ከሆነ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ እግር በታች ሦስት ጊዜ ሰገደና "በእውነት አንተ የእግዚአብሔር ልጅ የእስራኤልም ንጉሥ ነህ" አለው። ከዚህም በኋላ ከጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከተአምራቱ ያየውንና የሰማውን እየተናገረ ወደ ቦታው ሔደ ለእርሱም ለጌታችን ከቸር አባቱ ጋራ ማሕየዊ ከሆነ መንፈስ ቅዱስም ጋራ ክብር ምስጋና ስግደትም ይሁን ዛሬም ዘወትርም ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የጥር 6 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ወይከውን ቡሩከ ስሙ ለዓለም። እምቅድመ ፀሐይ ሀሎ ስሙ። ወይትባረኩ ቦቱ ኵሎሙ አሕዛብ ምድር። መዝ 71፥17-18። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 2፥8-22። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "ወገሠጸ ነገሥተ በእንቲአሆሙ። ወኢትግሥሡ መሲሐንየ። ወኢታሕስሙ ዲበ ነቢያትየ"። መዝ 104፥14-15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 15፥8-14፣ 2ኛ ጴጥ 2፥1-9፣ የሐዋ ሥራ 7፥2-9። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 4፥24-33። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ዲዮስቆሮስ ቅዳሴ ነው። መልካም የኢየሱስ ክርስቶስ በዓል፣ የነቢዩ ኤልያስ የዕረገት በዓል፣ የጻድቁ ኖኅ የዕረፍት በዓል፣ የቅዱስ ባስልዮስ የዕረፍት በዓልና የቅዱስ አርሴማ የልደት በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

photo content
+2

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ጥር ፮ (6) ቀን። ❤ እንኳን ለኢትዮጵያዊው ጻድቅ ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ እስከ ዛሬ ድረስ ዓሣ ከሰማይ ለሚዘንብላቸው ለመናኔ መንግሥት አቡነ ኢዮስያስ ለልደታቸው በዓል በሰላም አደረሰን። + + + ❤ መናኔ መንግሥት አቡነ ኢዮስያስ፡- ትውልዳቸው ሸዋ ሲሆን የንጉሥ ዓምደ ጽዮን ልጅ ናቸው፡፡ ጥር 6 ቀን ሲወለዱ ቅዱሳን መላእክት ከበዋቸው ታይተዋል፡፡የንጉሥ ልጅ ቢሆኑም በዓለም ነግሠው መኖርን ንቀው በመመነን በመጀመሪያ ወደ ሐይቅ እስጢፋኖስ ገዳም ገቡ፡፡ አቡነ ኢዮስያስ በሐይቅ ገዳም ለ14 ዓመታት በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡ በዚያም ብሉይንና ሐዲስን፣ መጽሐፈ መነኰሳትንና መጽሐፈ ሊቃውንትን አጠናቀው ተምረዋል፡፡ በኋላም በእግዚአብሔር ትእዛዝ ወደ ትግራይ ደብረ በንኰል ገዳም ሄዱ፡፡ በደብረ በንኰልም በታላቅ ተጋድሎ ኖረው በታላቁ አባት በአቡነ መድኃኒነ እግዚእ እጅ መነኰሱ፡፡ ቆብ የተቀበሉት ግን ከአቡነ ተክለሃይማኖት ነው፡፡ ❤ አቡነ መድኃኒነ እግዚእም ሰባት ዓመት ከእሳቸው ጋር ካቆዩአቸው በኋላ አቡነ ኢዮስያስን ወንጌልን ዞረው እንዲሰብኩና ገዳም እንዲገድሙ በማዘዝ መርቀው ሸኝተዋቸዋል፡፡ አቡነ ኢዮስያስም ወደ አዱዋ አውራጃ ዛሬ በስማቸው ወደተጠራው ገዳም ሄደው በቦታው ላይ በተጋድሎ ኖሩ፡፡ ገዳሙንም ከገደሙት በኋላ በርካታ መነኰሳትን አፍርተዋል፡፡ ጻድቁ ያፈለቁት ጠበል በፈዋሽነቱ የታወቀ ነው፡፡ በየዓመቱ በዕረፍታቸው ዕለት ነሐሴ 6 ቀን ሶሀባ በሚባለው ቦታ ቆመው በጸለዩበት ወንዝ ላይ ዓሣ ከሰማይ ይዘንባል፡፡ ይህ አሁንም ድረስ በየዓመቱ ነሐሴ 6 ቀን በግልጽ እየታየ ይገኛል፡፡ ❤ አቡነ ኢዮስያስን ከሃዲያን የሆኑ አረማውያን ቢያስቸግሯቸው ጻድቁም በጸሎት ቢያመለክቱ ከየት እንደመጣ የማይታወቅ ነጭ የንብ መንጋ መጥቶ አረማውያኑን አንጥፍቶላቸዋል፡፡ ጻድቁ በጸሎታቸው አራት ሙታንን በአንድ ጊዜ ከሞት ያስነሡ ታላቅ አባት ናቸው፡፡ በገዳማቸው ውስጥ በበዓላቸው ቀን ገድላቸው ሲነበብ አጋንንት ከሰው ልቡና እንደ ትቢያ በነው ይጠፋሉ፡፡ ❤ ጻድቁን እንደ ረድእ ሆኖ የሚያገለግላቸው አንበሳ ነበራቸው፡፡ ወደ ገዳማቸው መጥቶ መካነ ዐፅማቸውን የተሳለመውን እስከ 14 ትውልድ ድረስ እንደሚምርላቸው ጌታችን ቃልኪዳን ገብቶላቸዋል፡፡ ልጁን በስማቸው የሰየመ ቢኖር የሰይጣንን ፊት ፈጽሞ እንደማያይ ገድላቸው ይናገራል፡፡ ከአቡነ ኢዮስያስ እግዚአብሔር አምላክ ረድኤት በረከትን ያሳትፈን በጸሎታቸው ይማረን!። ምንጭ፦ መዝገበ ቅዱሳን ከሚለው መጽሐፍ የተወሰደ። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw