fa
Feedback
ሰዋስው ☘☘☘☘

ሰዋስው ☘☘☘☘

رفتن به کانال در Telegram

በሰዋስወ ብርሀን ቅዱስ ዻውሎስ ገዳም እና ለተለያዩ ቤተክርስቲያን ለክብረ በአላት ማውጫ ። በተጨማሪም-ዋዜማ ሥርዓተ ማኅሌት - መዝሙራት ስንክሳር - የየእለቱን ምስባክ ቅኔያት ጥያቄዎች እንዲሁም የወቅታዊ ነገር መወያያ በተጨማሪም @eotcww ብለው ይቀላቀሉን ለወዳጅ ዘመድዎ share#Share#Share# ያድርጉ።

نمایش بیشتر
1 161
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
اطلاعاتی وجود ندارد7 روز
اطلاعاتی وجود ندارد30 روز
آرشیو پست ها
photo content
+1

❤ ነቢዩ ኢዩኤልም እንዲህ ተናገረ የእግዚአብሔር ዙፋን የሆነች ብላቴና ድንግልን አየሁ እርሷም እንደ እሳት ያልባት ነበር ስለርሷም ይቺ ማናት ብዬ ኪሩብን ጠየቅሁት ከአዳም ልጆች የተመረጠች የእግዚአብሔር ዙፋን ይች ድንግል ናት በርሷም የተጎሳቈሉ ይድናሉ ለአመነባትም ረድኤትና መጠጊያ ናት። ❤ ዳዊትም በመዝሙሩ እንዲህ አለ "እግዚአብሔር አንተ ልጄ ነህ በተዋሕዶም ወለድኩህ አለኝ። ለምን አሕዛብን ርስት አድርጌ እሰጥሃለሁ ግዛትህም በመላው ዓለም ነው"። ዳግመኛ "አብ አለ ቀዳማዊ ወልድ በኃይል ቀን ከአንተ ጋር ሳለሁ ከአጥብያ ኮከብ በፊት ከሆድ ወለድኩህ እንደ መልከጼዴቅ አንተ የዓለም አገልጋይ ካህን ነህ ብሎ እግዚአብሔር ማለ ከማለም አይፀፀትም"። ❤ ቤዛ ይስሐቅ በግዕ ከኅቱም ዕፀ ሳቤቅ እንደገኘ በእስራኤል በበርሃ ውስጥ ከኅቱም ዐለት ውኃ እንደ ፈለቀ የደረቀች የአሮን በትርም እንደለመለመችና እንደአፈራች። በሶምሶንም እጅ ወስጥ ከአህያ መንጋጋ ዐጥንት ውኃ እንደፈሰሰ። እንዲሁ የጌታችን ልደት በህቱም ድንግልና ሆነ። በዕፀ ጳጦስ ውስጥ እሳት እንደነደደች እጺቱም እንዳልተቃጠለች እንዲሁም የመለኮት እሳት ድንግልን አላቃጠላትም። ለርሱም ከቸር አባቱ ከማሕየዊ መንፈስ ቅዱስ ጋር ጌትነት ክብር ምስጋና ሰጊድ ከርሱ ጋር በትክክል ይገባል ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ29 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ነገሥተ ተርሴስ ወደሰያት አምኃ ያበውዑ። ነገሥተ ሳባ ወዓረብ ጋዳ ያመጽኡ። ወይሰግዱ ሎቱ ኵሎሙ ነገሥተ ምድር"። መዝ71፥10-11። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-18። + + + ❤ የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ገላ 4፥4-12፣ 1ኛ ዮሐ 4፥9-ፍ.ም እና የሐዋ ሥራ 13፥16-22። የሚነበበው ወንጌል ሉቃ2፥1-21። የሚቀደሰው ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልእ ነው። መልካም የብርሃነ ልደቱ በዓል። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ታኅሣሥ ፳፱ (29) ቀን። ❤ እንኳን ለጌታችን ለአምላካችን ለመድኃኒታችን ለኢየሱስ ክርስቶስ ከእናቱ ከእመቤታች ከቅድስት ድንግል ማርያም በሥጋ ለተወለደበት የበዓላት ሁሉ ራስ ለሆነች ለብርሃነ ልደቱ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በእዚህ ቀን ከሚታሰቡ፦ ከጻድቁ ንጉሥ ከቅዱስ ላሊበላ ከልደት በዓል መታሰብያ፣ ከታላቁ አባት ከአቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ከልደታቸ ቀን መታሰቢያ፣ ከኤፍሬም ወገን ከመስፋኑ ከቅዱስ ኢያሱ ልደት፣ ከከበሩ ከያዕቆብ፣ ከፈሊስ ከሌላው ሰማዕት፣ ከቴዎድሮስ ከመታሰቢያቸው፣ ከሮሀ ንጉሥ ከአቃርዮስ ዕረፍት፣ ሰምኑድ ከሚባል አገር ከሆነ ከገመላዊው ከቅዱስ ቆሪል ዕረፍትና ከአክሚም ሰማዕታት ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ "ዮም ፍሥሐ ኮነ በእንተ ልደቱ ለክርስቶስ እምቅድስት ድንግል ውእቱ ኢየሱስ ክርስቶስ ዘሎቱ ሰብአ ሰገል ሰገዱ ሎቱ አማን መንክር ስብሐተ ልደቱ"፡፡ ትርጉም፦ ከቅድስት ድንግል ክርስቶስ ስለተወለደ ዛሬ ደስታ ሆነ ለእርሱ ሰብአ ሰገል (የጥበብ፡ሰዎች) ሰገዱለት በእውነት የልደቱ ምስጋና ድንቅ ክቡር ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ በዚች ቀን የከበረና የተመሰገነ ታላቅ የልደት በዓል ሆነ የጌታችንና የመድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም የተወለደባት ዕለት ከበዓላት ሁሉ ተለይታ ከፍ ከፍ ያለች ናት። ❤ የቤተ ክርስቲያን መምህራን አባቶቻችን የከበረ የልደትን በዓል በሁለት ቀኖች ያከብሩ ዘንድ በምክራቸው ተስማሙ ከወደኋላ ባለ በሃያ ስምንት ሌሊቱ የልደት በዓል ነው በሃያ ዘጠኝ መዓልቱ ጳጒሜን ስድስት በሆነ ጊዜ በዚያች ዓመት የልደት በዓል በሃያ ስምንት ከሆነ ግን በሃያ ዘጠኝ ይሆናል ስለዚህ የበዓላት ሁሉ ራስ የሆነ የከበረ የልደት በዓል በሁለት ቀኖች እንዲከበር አዘዙ ወሠኑ። ❤ የበዓላት ራስ ስለሆነ ስለ ከበረ የልደት በዓል የከበረ ወንጌል እንዲህ አለ "በንጉሥ በኄሮድስ ዘመን በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ጌታ ኢየሱስ በተወለደ ጊዜ እነሆ የፍልስፍና ሰዎች ከምሥራቅ መጥተው ወደ ኢየሩሳሌም ደረሱ። ኮከብን በምሥራቅ አይተን እንሰግድለት ዘንድ መጥተናልና የተወለደው የአይሁድ ንጉሥ ወዴት ነው እያሉ። እሊህ ፈላስፎች ከበለዓም ወገን ናቸው እነርሱም በከዋክብት የሚፈላሰፉ ናቸው በመጽሐፋቸው በበለዓም መጽሐፍም የአይሁድ ንጉሥ ሊወለድ እንዳለው ተጽፎአል እርሱ በለዓም ከያዕቆብ ኮከብ ይወጣል ከእስራኤልም ንጉሥ ብሎ ነበርና። ❤ ይቅር ባይ እግዚአብሔር በረቀቀ ጥበቡ አለበማቸው በሚያምኑበትም ሳባቸው እነርሱ ከዋክብትን በመጠባበቅ የሚፈላሰፉ ናቸውና ይህንንም ኮከብ ገለጠላቸው በአዩትም ጊዜ ደስ አላቸው መልኩ በብዙ አይነት ልውጥ ነውና። ሕፃን የታቀፈች ድንግል ብላቴናን ይመስላል እርሱም በቀን ይጓዛል በሌሊትም ይሠወራል ከሰውም ሲገናኙ ይሠወርና ሲቆሙ በሌላ አንጻር ይገለጥላቸዋል። ❤ እነርሱም ወደ ኢየሩሳሌም ሲደርሱ ያ ኮከብ ተሠወራቸው እጅግ አዘኑ የሚያድረጉትንም አላወቁም ከዚህም በኋላ ወደ ኢየሩሳሌም ከተማ ገብተው ስለተወለደው ንጉሥ ጠየቁ። የእሊህም ሰዎች ቊጥራቸው ሠላሳ ሽህ ነው ነገሥታቱ ሦስት ናቸው ለእያንዳንዳንዱ ንጉሥ ዐሥር ዐሥር ሺህ ሠራዊት አለው። ንጉሡ ኄሮድስም በሰማ ጊዜ ደነገጠ ኢየሩሳሌምም በመላዋ ከእርሱ ጋር ደነገጠች። የካህናት አለቆችና የሕዝቡን ጸሐፊዎች ሁሉ ሰብስቦ "ክርስቶስ በየት ይወለዳል?" ብሎ ጠየቃቸው። "በይሁዳ ዕፃ በቤተልሔም ነው" አሉት በነቢይ እንዲህ ተብሎ ተጽፏልና። "የኤፍራታ ዕፃ ቤተ ልሔም አንቺም ከይሁዳ ነገሥታት አታንሺም ወገኖቼ እስራኤልን የሚጠብቅ ንጉሥ ካንቺ ይወለዳልና"። ❤ ከዚህም በኋላ ኄሮድስ ሰብአ ሰገልን በጭልታ ጠርቶ ኮከቡ የታየበትን ዘመን ከነሱ ተረዳ። "ሔዳችሁ የዚያን ሕፃን ነገር እርግጡን መርምሩ ያገኛችሁትም እንደሆነ እኔም መጥቼ እሰግደለት ዘንድ በኔ በኩል ተመልሳችሁ ንገሩኝ" ብሎ ወደ ቤተልሔም ሰደዳቸው የነገራቸውንም ሰምተው ከንጉሡ ሔዱ እነሆ በምሥራቅ ያዩት ኮከብ ወደ ቤተልሔም እስኪያደርሳቸው ይመራቸው ነበር ሕፃኑ ካለበትም ዋሻ ላይ ደርሶ ቆመ። ኮከቡንም ባዩ ጊዜ እጅግ ደስ አላቸው ወደ ቤትም በገቡ ጊዜ ሕፃኑን ከእናቱ ከድንግል ማርያም ጋር አገኙት ወድቀውም ሰገዱለት ሣጥናቸውንም ከፍተው ወርቅ ከርቤ ዕጣን እጅ መንሻ አቀረቡለት። ❤ በእግዚአብሔርም ፈቃድ ዮሴፍ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ሕፃኑ ጌታ ኢየሱስ በዚያች ዕለት ወደ ቤተልሔም መጡ ስለዚህም ሰብአ ሰገል አገኙአቸው የክብር ባለቤት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ያለ ናዝሬት በሌላ ቦታ አላደገምና ከተወለደም ዕድሜው ሁለት ዓመት ሁኖት ነበር። አምላክ ነውና ስለ መንግሥቱ ወርቅን ገበሩለት ክህነትም ገንዘቡ ነውና ዕጣንን ገበሩለት ማሕያዊ ለሆ ሞቱ ምልክትም ከርቤን ገበሩለት። ወደ ኄሮድስም እንዳይመለሱ በሕልም ነገራቸው በሌላ መንገድም ወደ አገራቸው ተመልሰው ገቡ። አምላክ በሥጋ ስለመገለጡ ዓዋጅ ነጋሪዎችና ሰባኪዎች ሆኑ። ❤ ይችም ዕለት ነቢዩ ኢሳይያስ ትንቢት ስለርሷ የተናገረላት ናት እንዲህ ብሎ "እነሆ ድንግል ፀንሳ ወንድ ልጅን ትወልዳለች ስሙንም አማኑኤል ትለዋለች ትርጓሜውም እግዚአብሔር ከእኛ ጋር ማለት ነው"። ስለዚችም የከበረች ድንግል ነቢይ ሕዝቅኤል እንዲህ ብሎ ትንቢት ተናገረ "እግዚአብሔርም አለኝ ይህች በር ተዘግታ ትኖራለች አትከፈትም የሚገባበትም የለም የእስራኤል ፈጣሪ እግዚአብሔር እንደተዘጋች ይገባባታልና ተዘግታ ትኑር" አለ። ❤ ነቢዩ ዳንኤልም አለ "ሌሊት በራእይ አየሁ እነሆ ታላቁ እንደ ሰው ልጅ በሰማይ ደመና መጣ ዘመኑን ወደ ሚያስረጅ ደረሰ ከፊቱም አቀረቡት የዘላለም አገዛዝ ጌትነት መንግሥት ተሰጠው ሕዝቡና አሕዛቡ ሁሉ መንደር መንድረው የሚኖሩትና ነገዱም ነገሥታቱም ሁሉ ይገዙለታል አገዛዙም የዘላለም አገዛዝ ነው መንግሥቱም የማያልፍ የማይጠፋ ነው። ❤ ዳግመኛም ኢሳይያስ "እግዚአብሔር እንደእኔ የሥጋ መጋረጃ በመጋረድ ተገለጸልኝ" አለ። "አሁኑም ደግሞ አዲስ ሰማይ አዲስ ምድር እሠራ ዘንድ አለኝ" አለ ሁለተኛም "ከዕሴይ ሥር በትር ትወጣለች ከእርሷም ጽጌ አበባ ይወጣል" አለ። ዳግመኛም "ሕፃን ተወልዶልናልና ወንድ ልጅም ተሰጥቶናልና ይኸውም ሥልጣን በጫንቃው የሆነ ክርስቶስ ነው። ስሙም ድንቅ መካር የዘላዓለም አባት የሰላም አለቃ ይባላል" አለ። ❤ ኤርምያስም አለ "እግዚአብሔር እንዲህ አለ ለዳዊት ብርሃንን አወጣለሁ በምድር የቀና ፍርድ ያደርጋል እግዚአብሔር ያመኑበትን ያድናቸዋል"። ኤልሳዕም እንዲህ አለ "እግዚአብሔር ከሰማ ይወርዳል በእስራኤል ልጆች አደባባይም በመመላለስ ለሕዝቡ እውነትን ያስተምራቸዋል ከአብርሃም ልጅነት ልዩ ከሆነች ወገኖቹ በቀር አሕዛብ ሁሉ ይታዘዙለታል"። ናሆም ነቢይም እንዲህ አለ "እግዚአብሔር በእኔ አርአያ ይመጣል ልብሱም እንደ ልብሴ ነው"።

✝#ጾሙስ_አበቃ.....?✝ አንብቡት 😌 🥀ጾሙስ አበቃ የነፍስ ረሃባችን መቼ ያበቃ ይሆን? ነፍሳችን ሥጋውን ደሙን እስከመቼ ነው የምትጾመው? ጾሙስ ተደመደመ። የእኛ በደል መቼ ይሆን የሚቋጨው? ስግብግብነታችን መቼ ነው ዳር የሚደርሰው? በዚህ ጾም መጨረሻ የአብ አንድያ ልጁ ተወልዶ መለያየት ተወገደ ሰውና መላእክት አንድ ሆኑ፤ መቼ ይሆን ጎጠኝነታችን የሚጠፋው? መቼ ይሆን ሰማያዊ ዘመድ የምናበጀው። ጾም ተፈጽሟልና ለሥጋ ሥጋ ተገዛለት። ለዚህ ጾሞ ፋሲካ ለነፍስ ምን ቅመም ተቀመመላት? ምን ንብረት ተመደበላት? ምን ሙክት ተገዛላት? ምን ወይን ተጠመቀላት? ምን ልብስ ተሠራላት? ምን ድግሥ ተደገሠላት? እነማንን ድግሥ ጠራንላት? አጋንንትን ወይስ መላእክትን? ዛሬ ዛሬ የጾም መግቢያና መውጫ ይገርማል። የጾም መግቢያ ሥጋ ይበላል የጾም ፍጻሜ ሥጋ ይበላል። በሥጋ ጀምረን በሥጋ መጨረስን ተያይዘነዋል! ሥጋው በደል ሆኖ አይደለም መጀመሪያችን መፈጸሚያችን የሥጋ ብቻ መሆኑ ግን የነፍስ ያለህ ያሰኛል! 🥀አንዳንድ ሰው የዘንድሮው በዓል ልዩ የሚያደርገው ዓመቱ መሆኑ ይመስለዋል። ልዩ የሚያደርገው ከአምናው በተለየ ነፍስ ያገኘችው ነገር ሲኖር ነው። ለሥጋ ተበድሮ ሳይቀር ይደገሳል። ቢያንስ ድኃ ቢያጣ ያለችውን አጥቦ ለብሶ ከጎረቤት ሥጋ እየሸተተው ይውላል። ነፍሳችንስ ቢያንስ የሚቆርቡትን እያየች የክርስቶስ መዐዛ ቢናፍቃትም ባይሆን ተናዝዘን ታጥበን ብንውል ምን አለ? 🥀 የጸሎት ረሀብ መቼ ነው የምንፈስከው? የንጽሕና ረሀብ መቼ ነው የምንገድፈው? መፈሰክ ማለት መሻገር ነው? ዝሙትን የተሻገርን ዕለት ያን ጊዜ ነበር ፋሲካ! 🥀ሱባኤው ደረሠ ቀጠሮው ተፈጸመ ጌታ ተወለደ። የእኛ ቀጠሮ መቼ ነው የሚደርሰው? በዚህን ጊዜ...ን አደርጋለሁ ብቻ! ጸሎቱ ቀጠሮ ጾሙ ቀጠሮ ትጋቱ ቀጠሮ አሥራቱ ቀጠሮ ኑዛዜው ቀጠሮ መታረቁ ቀጠሮ ቁርባኑ ቀጠሮ ሁሉ ቀጠሮ!ማን አለ የእኛስ ቀጠሮ ቢደርስ ምን አለ ጽኑዕ ቀጠሯችን ሳይደርስ እኛ የቀጠርነውን ጽድቅ ብንጀምረው! ምን አለ የእኛም ሱባኤ አብቅቶ የእግዚአብሔርና የቅዱሳን ልጆች ሆነን በምግባር ብንወለድ! 🥀የጾመ ነቢያት ፍጻሜ ጌታ ተወለደ። እኛም ከንስሐ ማኅፀን እንድንወለድ ይርዳን። ከጾሙ መጨረሻ ክርስቶስ ከእነርሱ በሥጋ መጣ። ከጾማችን ፍጻሜ ጌታ በሰውነቴችን እንዲያድር ንስሐ ብንገባ ይህ ነው የጾም ፍጻሜ። ጌታ ሲወለድ አሮጌው ዘመን አበቃ። ሐዲስ ሕይወት፡ተወጠነ። እኛም ኃጢአታችን በንስሐ አልቆ አዲስ ከዘንድሮው ልደት ጀምሮ አዲስ ሕይወት ለመኖር ያብቃን። ኃጢአታችን ይለቅልን! መጋቤ ሐዲስ ወብሉይ አባ ገብረኪዳን ወስብሐት ለእግዚአብሔር ወለወላዲቱ ድንግል ወለመስቀሉ ክብር አሜን ይቆየን

✞ በኤፍራታ ምድር ✞ በኤፍራታ ምድር/በቤተልሄም/(፪) ጌታ ተወለደ/ከድንግል ማርያም/(፪) ብርሃናዊው ኮከብ/ከሰማይ ዝቅ አለ/(፪) ፍጥረትም ዘመረ /ሃሌ ሉያ እያለ/(፪) መንጋውን በሌሊት ሲጠብቁ እረኞች ከሰማይም ሰሙ ታላቅ የምስራች በመልአኩ ግርማ ምድር ስታበራ የሚያስጨንቅ ነበር እጅግ የሚያስፈራ አዝ= = = = = ድንገትም የሰማይ ሰራዊት ተገልጠው ባንድነት ዘመሩ ከኖሎት ጋር ሆነው ክብር ለእግዚአብሔር በአርያም ብለው ሰላምም በምድር በጎ ፍቃድ ለሰው አዝ= = = = = ቤተልሄም ሄደው ጌታን ተሳለሙት ከእናቱ ጋራ ሆነው በግርግም አገኙት የመላእክትን ዜማ እረኞች አወሩ በልዩ ምስጋና አምላክን ሲያከብሩ አዝ= = = = = ለሕዝብ ሁሉ የሚሆን ፍስሐ ደስታ በዳዊት ከተማ ተወለደ ጌታ ህፃን ከእናቱ ጋር በግርግም ፈለጉት እርሱ ነው ለሰዎች የድነት ምልክት መዝሙር ይልማ ኃይሉ "እንግዲህ እስከ ቤተልሔም ድረስ እንሂድ እግዚአብሔር የገለጠልንን ይህን የሆነውን እንይ..." ╭══•|❀:✧๑♡๑✧❀|: ══╮ @yamazemur_getemoche ╰══•ೋ•✧๑♡๑✧• ══╯

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በቅዳሴ ሰዓት የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ማቴ. 1:1-18 "መጽሐፈ ልደቱ ለእግዚእነ" - "የዳዊት፡ልጅ፡የአብርሃም፡ልጅ፡የኢየሱስ፡ክርስቶስ፡ትውልድ፡መጽሐፍ። አብርሃም፡ይሥሐቅን፡ወለደ፤ይሥሐቅም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ያዕቆብም፡ይሁዳንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ፤ ይሁዳም፡ከትዕማር፡ፋሬስንና፡ዛራን፡ወለደ፤ፋሬስም፡ኤስሮምን፡ወለደ፤ ኤስሮምም፡አራምን፡ወለደ፤አራምም፡ዐሚናዳብን፡ወለደ፤ዐሚናዳብም፡ነአሶንን፡ወለደ፤ነአሶንም፡ ሰልሞንን፡ወለደ፤ ሰልሞንም፡ከራኬብ፡ቦኤዝን፡ወለደ፤ቦኤዝም፡ከሩት፡ኢዮቤድን፡ወለደ፤ኢዮቤድም፡እሴይን፡ወለደ፤ እሴይም፡ንጉሥ፡ዳዊትን፡ወለደ። ሰሎሞንም፡ሮብዓምን፡ወለደ፤ሮብዓምም፡አቢያን፡ወለደ፤አቢያም፡አሣፍን፡ወለደ፤ አሣፍም፡ኢዮሳፍጥን፡ወለደ፤ኢዮሳፍጥም፡ኢዮራምን፡ወለደ፤ኢዮራምም፡ዖዝያንን፡ወለደ፤ 9፤ዖዝያንም፡ኢዮአታምን፡ወለደ፤ኢዮአታምም፡አካዝን፡ወለደ፤ አካዝም፡ሕዝቅያስን፡ወለደ፤ሕዝቅያስም፡ምናሴን፡ወለደ፤ምናሴም፡አሞፅን፡ወለደ፤ አሞፅም፡ኢዮስያስን፡ወለደ፤ኢዮስያስም፡በባቢሎን፡ምርኮ፡ጊዜ፡ኢኮንያንንና፡ወንድሞቹን፡ወለደ። ከባቢሎንም፡ምርኮ፡በዃላ፡ኢኮንያን፡ሰላትያልን፡ወለደ፤ሰላትያልም፡ዘሩባቤልን፡ወለደ፤ ዘሩባቤልም፡አብዩድን፡ወለደ፤አብዩድም፡ኤልያቄምን፡ወለደ፤ኤልያቄምም፡አዛርን፡ወለደ፤ አዛርም፡ሳዶቅን፡ወለደ፤ሳዶቅም፡አኪምን፡ወለደ፤አኪምም፡ኤልዩድን፡ወለደ፤ ኤልዩድም፡አልዓዛርን፡ወለደ፤አልዓዛርም፡ማታንን፡ወለደ፤ማታንም፡ያዕቆብን፡ወለደ፤ ያዕቆብም፡ክርስቶስ፡የተባለውን፡ኢየሱስን፡የወለደች፡የማርያምን፡ዕጮኛ፡ዮሴፍን፡ወለደ። እንግዲህ፡ትውልድ፡ሁሉ፡ከአብርሃም፡እስከ፡ዳዊት፡አሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከዳዊትም፡እስከባቢሎን፡ምርኮ፡ዐሥራ፡አራት፡ትውልድ፥ከባቢሎንም፡ምርኮ፡እስከ፡ክርስቶስ፡አሥራ፡አራት፡ትውልድ፡ነው።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

ታኅሣሥ 28 በቅዳሴ ጊዜ #ምንባባት ገላ ም ፬ ቊ፩-፲፪ ፩ዮሐ ም ፬ ቊ ፱-ፍጻ ግብ ሐዋ ም ፲፫ ቊ ፲፮ #ምስባክ የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቀ ዓረብ ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ ወኲሎ አሚረ ይድኅርዎ #ትርጉም እርሱ ይኖራል ከዓረብም ወርቅን ይሰጡታል ሁልጊዜም ስለ እርሱ ይጽልያዩ ዘወትርም ይባርኩታል መዝ ፸፩ቊ ፲፭ #ወንጌል የሉቃስ ወንጌል ም ፪ ቊ ፩ #ቅዳሴ ቅዳሴ የቅዱስ ጎርጎርዮስ ካልእ ወእንዘ ሀለው ህየ በጽሐ ዕለተ ወሊዶታ "በዚያ ሳሉ የመውለጅዋ ጊዜ ደረሰ" https://t.me/Eotcw

✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ በእለቱ በነግህ የሚነበብ ወንጌል ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨ ሉቃ. 1:26-57፡ "ወበሳድስ ወርኀ ተፈነወ" - "በስድስተኛውም፡ወር፡መልአኩ፡ገብርኤል፡ናዝሬት፡ወደምትባል፡ወደ፡ገሊላ፡ከተማ፥ ከዳዊት፡ወገን፡ለኾነው፡ዮሴፍ፡ለሚባል፡ሰው፡ወደ፡ታጨች፡ወደ፡አንዲት፡ድንግል፡ከእግዚአብሔር፡ዘንድ፡ተላከ፥የድንግሊቱም፡ስም፡ማርያም፡ነበረ። መልአኩም፡ወደ፡ርሷ፡ገብቶ፦ደስ፡ይበልሽ፥ጸጋ፡የሞላብሽ፡ሆይ፥ጌታ፡ከአንቺ፡ጋራ፡ነው፤አንቺ፡ ከሴቶች፡መካከል፡የተባረክሽ፡ነሽ፡አላት። እርሷም፡ባየችው፡ጊዜ፡ከንግግሩ፡በጣም፡ደነገጠችና፦ይህ፡እንዴት፡ያለ፡ሰላምታ፡ነው፧ብላ፡አሰበች። መልአኩም፡እንዲህ፡አላት፦ማርያም፡ሆይ፥በእግዚአብሔር፡ፊት፡ጸጋ፡አግኝተሻልና፥አትፍሪ። እንሆም፥ትፀንሻለሽ፡ወንድ፡ልጅም፡ትወልጃለሽ፥ስሙንም፡ኢየሱስ፡ትዪዋለሽ። እርሱ፡ታላቅ፡ይኾናል፡የልዑል፡ልጅም፡ይባላል፥ጌታ፡አምላክም፡የአባቱን፡የዳዊትን፡ዙፋን፡ይሰጠዋል። በያዕቆብ፡ቤትም፡ላይ፡ለዘለዓለም፡ይነግሣል፥ለመንግሥቱም፡መጨረሻ፡የለውም። ማርያምም፡መልአኩን፦ወንድ፡ስለማላውቅ፡ይህ፡እንዴት፡ይሆናል? አለችው። መልአኩም፡መልሶ፡እንዲህ፡አላት፦መንፈስ፡ቅዱስ፡ባንቺ፡ላይ፡ይመጣል፥የልዑልም፡ኀይል፡ይጸልልሻል፡ስለዚህ፡ደግሞ፡ከአንቺ፡የሚወለደው፡ቅዱስ፡የእግዚአብሔር፡ልጅ፡ይባላል። እንሆም፡ዘመድሽ፡ኤልሳቤጥ፥ርሷ፡ደግሞ፡በእርጅናዋ፡ወንድ፡ልጅ፡ፀንሳለች፥ለርሷም፡መካን፡ትባል፡ለነበረችው፡ይህ፡ስድስተኛ፡ወር፡ነው፤ለእግዚአብሔር፡የሚሳነው፡ነገር፡የለምና። ማርያምም፡በዚያ፡ወራት፡ተነሥታ፡ወደ፡ተራራማው፡አገር፡ወደ፡ይሁዳ፡ከተማ፡ፈጥና፡ወጣች፥ ወደዘካርያስም፡ቤት፡ገብታ፡ኤልሳቤጥን፡ተሳለመቻት። ኤልሳቤጥም፡የማርያምን፡ሰላምታ፡በሰማች፡ጊዜ፡ፅንሱ፡በማሕፀኗ፡ውስጥ፡ዘለለ፤በኤልሳቤጥም፡መንፈስ፡ቅዱስ፡ሞላባት፥ በታላቅ፡ድምፅም፡ጮኻ፡እንዲህ፡አለች፦አንቺ፡ከሴቶች፡መካከል፡የተባረክሽ፡ነሽ፥የማሕፀንሽም፡ፍሬ፡የተባረከ፡ነው። የጌታዬ፡እናት፡ወደ፡እኔ፡ትመጣ፡ዘንድ፡እንዴት፡ይሆንልኛል? እነሆ፥የሰላምታሽ፡ድምፅ፡በጆሮዬ፡በመጣ፡ጊዜ፡ፅንሱ፡በማሕፀኔ፡በደስታ፡ዘሏልና። ከጌታ፡የተነገረላት፡ቃል፡ይፈጸማልና፥ያመነች፡ብፅዕት፡ናት። ማርያምም፡እንዲህ፡አለች፦ ነፍሴ፡ጌታን፡ታከብረዋለች፥መንፈሴም፡በአምላኬ፡በመድኀኒቴ፡ሐሴት፡ታደርጋለች፤ የባሪያዪቱን፡ውርደት፡ተመልክቷልና።እንሆም፥ከዛሬ፡ጀምሮ፡ትውልድ፡ሁሉ፦ብፅዕት፡ይሉኛል፤ ብርቱ፡የሆነ፡እርሱ፡በእኔ፡ታላቅ፡ሥራ፡አድርጓልና፤ስሙም፡ቅዱስ፡ነው። ምሕረቱም፡ለሚፈሩት፡እስከ፡ትውልድና፡ትውልድ፡ይኖራል። በክንዱ፡ኃይል፡አድርጓል፤ትዕቢተኛዎችን፡በልባቸው፡ዐሳብ፡በትኗል፤ ገዢዎችን፡ከዙፋናቸው፡አዋርዷል፤ትሑታንንም፡ከፍ፡አድርጓል፤ የተራቡትን፡በበጎ፡ነገር፡አጥግቧል፤ባለጠጋዎችንም፡ባዷቸውን፡ሰዷቸዋል። ለአባቶቻችን፡እንደ፡ተናገረ፥ለአብርሃምና፡ለዘሩ፡ለዘለዓለም፡ምሕረቱ፡ትዝ፡እያለው፡እስራኤልን፡ብላቴናውን፡ረድቷል። ማርያምም፡ሦስት፡ወር፡የሚያህል፡በእርሷ፡ዘንድ፡ተቀመጠች፡ወደ፡ቤቷም፡ተመለሰች። የኤልሳቤጥም፡የመውለጃዋ፡ጊዜ፡ደረሰ፥ወንድ፡ልጅም፡ወለደች።" ✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨✨

1.28 KB

28/4/2015 ዓ.ም (፳፰/፬/፳፻፲፭ ዓ.ም) 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 በእለቱ በነግህ የሚሰበክ ምስባክ 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯 ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለተ ኃይል። በብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ፡፡ መዝ. 109፥3 🕯 ትርጉም ከአንተ ጋር ቀድሞ በኃይልህ ቀን። በቅዱሳን ብርሃን። ከአጥቢያ ኮከብ አስቀድሞ ከሆድ ወለድሁህ። 🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯🕯

ማኅሌቱን ለምትቆሙ መልካም አገልግሎት

🌟🌟🌟በገና አባት የተሸፈነ ቅዱስ አባት🌟🌟🌟 +++ቅዱስ ኒቆላዎስ ገባሬ መንክራት (St.Nicholas the wonder worker)+++ ቅዱስ ኒቆላዎስ (St.Nicholas-Santa Claus) በሮማ መንግስት ዘመን በኤዥያ ውስጥ በምትገኝ ሜራ በምትባል ሃገር (የአሁኗ ቱርክ) ግሪካዊ ከሆኑ ክርስቲያን ቤተሰቦቹ ተወለደ፡፡የዚህም ቅዱስ እናቱ ጦና (Tona) አባቱ ኤጲፋንዮስ ይባላሉ፡፡እኒህም የእግዚአብሔርን የሚፈሩ እና ባዕለ ጸጎችም ነበሩ፡፡ነገር ግን ከሞቱ በኋላ ንብረታቸውን የሚያወርሱት ለልባቸውም ደስታን የሚመግብ ልጅ አልነበራቸውም፡፡ዕድሜያቸውም እየገፋ በመምጣቱ ምክንያት በተስፋ መቁረጥ ተከበው ይኖሩ ነበር፡፡በልብ መታሰቡ በቃል መነገሩ ከፍ ከፍ ያለ አምላክ በዕርጅና ዘመናቸው በቸርነቱ ጎበኛው፡፡ቅዱስ የሆነም ልጅን ሰጣቸው፡፡ይህም ልጅ ገና ታናሽ ሳለ መንፈሰ እግዚአብሔር የሞላበት ነበር፡፡ዕድሜውም ለትምህርት በደረሰ ጊዜ እውቀትና ጥበብን ይቀስም ዘንድ ወደ መምህራን የተላከ ቢሆንም ከመምህሩ ከተማረው ይልቅ ከመንፈስ ቅዱስ የተረዳው ይበልጥ ነበር፡፡ መሠረታዊ የሆኑትን የቤተ ክርስቲያንን ትምህርት በልጅነቱ ተምሮ በማጠናቀቁ በዲቁና መዓርግ ተሾመ፡፡በኋላም የአጎቱ ልጅ አበምኔት በሆነበት በአንዱ ገዳም አርዑተ ምንኩስናን (የምንኩስናን ቆብ) ጭኖ የቅድስና እና የትሕርምት ሕይወትን ኖሯል፡፡በአሥራ ዘጠኝ ዓመቱም የቆሞስነትን መዓርግ አግኝቷል፡፡ ለዚህም ቅዱስ አባት እግዚአብሔር ተአምር እና ድንቅን የማድረግ ፤ሕሙማንንም የመፈወስ ታላቅ ጸጋ ሰጥቶታል፡፡ ለጋስ (የስጦታ) አባት በሞራ ከተማ የሚኖር ቀድሞ ባዕለ ጸጋ የነበረ በኋላ ግን ሃብት ንብረቱን ያጣ አንድ ሰው ነበረ፡፡በድህነቱ ምክንያት ሊድራቸው ያልቻለ ሦስት ዕድሜያቸው ለጋብቻ የደረሱ ልጆች ነበሩት፡፡ሰይጣንም ሴት ልጆቹን በዝሙት ሥራ ገንዘብ እየሰበሰቡ ሕይወታቸውን እንዲመሩ ያደርጋቸው ዘንድ ክፉ ሃሳብን በሕሊናው አመጣበት፡፡እግዚአብሔርም በዚህ ሰው ልቡና ውስጥ ሰይጣን የተከለበትን ክፉ ሃሳብ እና ምን ሊያደርግ እንደተነሣሣ ለቅዱስ ኒኮላስ ገለጠለት፡፡ ቅዱስ ኒቆላዎስም የእናት የአባቱ ገንዘብ ከሆነው ላይ መቶ ዲናር ወስዶ በስልቻ (sack) ጠቅልሎ ማንም ሳያየው በምሽት ወደዚያ ደሃ ሰው ቤት በመሄድ በመስኮት በኩል ወረወረለት፡፡ያሃም ደሃ ከየት እንደመጣ ያላወቀውን 100 ዲናር በቤቱ ባገኘ ጊዜ ተደነቀ አምላኩንም አመሰገነ፡፡ያሰበውንም ክፉ ሃሳብ ትቶ በገንዘብ እጦት ምክንያትም ከትዳር የዘገየችውን የመጀመሪያ ልጁን ዳረ፡፡በሌላም ቀን ቅዱስ ኒቆላዎስ ሁለተኛ ልጁን መዳር ይችል ዘንድ አሁንም ተጨማሪ መቶ ዲናር ገንዘብ በጥቅል ስልቻ አድርጎ በመስኮቱ በኩል ወረወረለት፡፡ይህንም ገንዘብ ዳግመኛ በቤቱ ያገኘው ያሃም ደሃ ሰው እንዲህ ያለውን ቸርነት በስውር የሚያደርገው ምን አይነት ሰው እንደሆነ አይቶ ያውቅ ዘንድ ጉጉት አደረበት፡፡ቤቱንም በንቃት መከታተል ጀመረ፡፡ቅዱስ ኒቆላዎስም እንደለመደው ለሦስተኛ ጊዜ መቶውን ዲናር የያዘውን ስልቻ በመስኮት ሲወረውር ወዲያው ተዘጋጅቶ ይጠብቀው የነበረው ሰው ፈጥኖ በሩጫ ከቤቱ ወጣ ሊያየው ይመኘው የነበረ ያሃንንም ቸር ሰው ሊቀ ጳጳሱ ኒቆላዎስ ሆኖ አገኘው፡፡ከእግሩ ስርም ተደፍቶ ልጆቹን ከድህነት እና ከኃጢአት ሕይወት ስለታደገለት ሊያመሰግነው ቢሞክርም ቅዱስ ኒቆላዎስ ግን ምስጋናውን እምቢ አለ፡፡ይህን ሃሳብ በልቡ ያኖረ እግዚአብሔርንም ያመሰግን ዘንድ ለመነው፡፡ ከዚህ ታሪክ በተጨማሪም ለሕጻናት እና ለተቸገሩ ሰዎች ያደረገው ልግስና የብዙ ብዙ ነው።ለዚህም ይመስላል በአንዳንድ አቢያተ ክርስቲያናት መታሰቢያውን በልግስና የሚያከብሩት። በአጠቃላይ ይህ ቅዱስ አባት በዘመነ ዲዮቅልጥያኖስ ስለ እምነቱ ብዙ ስቃይ እና እስራት ደርሶበታል፡፡ፋታ በማይሰጥ መከራ እና ግርፋት ውስጥ እያለ የራሱን ሕመም ከማዳመጥ ይልቅ በውጪ ላሉ ለልጆቹ ምዕመናን የሚያበረታታ እና በእምነታቸው እንዲጸኑ የሚያደርግ መልእክትን ይጽፍላቸው ነበር፡፡በ325 ዓ.ም ለአውግዞተ አርዮስ ከተበሰቡት 318ቱ ሊቃውንት መካከል አንዱ የነበረ የዚህች ኦርቶዶክሳዊት እምነት ባለውለታ ነው፡፡ከዓርባ ዓመታት በላይ በሊቀ ጵጵስና መንበር በጎቹን ከነጣቂ ተኩላ እየጠበቀ ቤተ ክርስቲያንን ካገለገለ በኋላ በሰማንያ ዓመቱ አርፏል፡፡ (ይህም አባት በእኛ (በኢትዮጽያ) የስንክሳር መጽሐፍ ላይ የእረፍቱ መታሰቢያ የጥር ወር በገባ በአስራ ስምንተኛው ቀን እንደሆነ ይነግረናል፡፡ኒቆላዎስም ማለት ‹መዋኤ ሕዝብ - ሕዝብን የሚያሸንፍ› ማለት እንደሆነ ስሙን ይተረጉምልናል።) የልደት በዓል እግዚአብሔር አብ ልጁን ለዓለም የሰጠበት በመሆኑ ‹የሥጦታ በዓል› በመባል ይጠራል፡፡ይህንንም በማሰብ ለድሆች በመራራት ለተቸገሩት ቸርነት በማድረግ እናከብረው ዘንድ ምሳሌ እንዲሆነን ቅዱስ ኒቆላዎስን እናስባለን፡፡ምንም ዓለም አፈ ታሪክ አድርጋ ብታወራውም የዚህንም ቅዱስ ማንነት እንዳይታወቅ በፈጠረቻቸው ተረቶች ብታጠለሸውም እኛ ግን የ‹ገና አባት› ብላ ከሰየመቻቸው የፈጠራ ሰው ጀርባ እውነተኛ የሆነውን ይህን ቅዱስ አባት እናስበዋለን፡፡ +++++ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን! እኛ ኃጢአተኞቹንም በዚህ ጻድቅ ሰው ጸሎት ይማረን!!!+++ ምንጭ:– -መጽሐፈ ስንክሳር @eotcy @eotcy @eotcy

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "ኢኮነ ነግደ ወፈላሴ ሀገሪቶሙ ለቅዱሳን ንሕነ ሰብአ ቤቱ ለእግዚአብሔር ኲልነ አምላክ ኀደረ ውስተ ሥጋ ተዓቁረ እንዘ ኢይትጋባዕ በሙላድ ዘድንግል መናሥግተ እያርኂዎ ዘኪሩቤል ኢርእዩ"። ትርጉም፦ እኛ የእግዚአብሔር የቤቱ ሰው እንግዳና መፃተኛ አልሆንም።፤ የቅዱሳን ሀገር የሆነው አምላክ ክርስቶስ በሥጋ ተወሰነ፤ ኪሩቤል ያላየው ያልመረመረው የእመቤታችን ማኅተመ ድንግልናዋን ሳይከፍት በመወለዱም ከምልአቱ ሳይወሰን ተወለደ። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። https://t.me/Eotcw

photo content
+2

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ ❤ ዛሬ ታኅሣሥ ፳፰ (28) ቀን። ❤ እንኳን ለቅዱስ አማኑኤል ለልደቱ (ለጌና) መታሰቢያ ዓመታዊ በዓል በሰላም አደረሰን። በተጨማሪ በዚች ቀን ከሚታሰቡ፦ ከእንዴናው አገር ሰዎች ከሆኑ በሰማዕትነት ካዐረፉ ከመቶ ሃምሳ ወንዶችና ከሃያ አራት ሴቶች፣ ከአባቶቻች ከአብርሃም፣ ከይስሐቅና ከያዕቆብ ከመታሰቢያቸው ረድኤትና በረከትን ያሳትፈን። + + + ❤ የታኅሣሥ 28 ዚቅ፦ "በጎለ እንስሳ ተወድየ አምኃ ንግሡ ተወፈየ፤ ወከመ ሕፃናት በከየ፤ እንዘ ይስእል እምአጥባተ እሙ ሲሳየ"። ትርጉም፦ በእስሳት በረት ተጨመረ የንግሡንም እጅ መንሻ ተቀበለ ከእናቱ ጡቶች ምግብን እየለመነ እንደ ሕፃናት አለቀሰ። የቅዳሴ ዲዮስቆሮስ። + + + ❤ በዚች ዕለት የጌና በዓል ሆነ። ይኸውም የልደት በዓል ነው”። ይህም እንዲህ ነው በአምላካችን በረቀቀ ጥበቡ ሰዎች ሁሉ ይቈጠሩ ዘንድ ስማቸውንም ይጻፋና ይመዘገቡ ዘንድ ከንጉሥ ቄሣር ትእዛዝ መጣ። ስለዚህም ከእመቤታችን ከከበረች ድንግል ማርያም ጋር ሊቆጠር ዮሴፍ ከናዝሬት ወደ ቤተልሔም የርሱንና የቡርክት ድንግል ማርያምን ስም ሊስመዘግብ ወጣ እርሱ ከይሁዳ ነገድ ከዳዊት ወገን ነውና ቤተልሔምሜ የዳዊት ቦታው ናትና። ❤ የከበረ ወንጌል እንደተናገረ ከዚህም በኋላ ከዚያ ሳሉ የምትወልድበት ቀን ደረሰ የበኵር ልጇንም ወለደች አውራ ጣቱንም አሠረችው በጨርቅም ጠቅልላ በበረት አስተኛችው ለማደሪያቸውም ቦታ አልነበራቸውምና። በዚያ ሰፈር እረኞች ነበሩ ሌሊትም በየተራቸው ተግተው መንጋቸውን ይጠብቁ ነበር። እነሆ የእግዚአብሔር መልአክ አጠገባቸው ቆመ የእግዚአብሔርም ብርሃን በላያቸው በራ ታላቅ ፍርሀትም ፈሩ መልአኩም "ለእናንተና ለመላው ዓለም ደስታ የሚሆን ታላቅ የምሥራች እነግራችኋለሁና አትፍሩ" አላቸው። ❤ "እነሆ ዛሬ በዳዊት አገር መድኅን የሆነ ጌታ ክርስቶስ ተወልዶላችኋልና። ለእናንተም ምልክት እንዲህ ነው ሕፃኑ አውራ ጣቱን ታሥሮ በጨርቅ ተጠቅልሎ በበረት ውስጥ ተኝቶ ታገኙታላችሁ" አላቸው። ድንገትም ከዚያ መልአክ ጋር ብዙ የሰማይ ሠራዊት እግዚአብሔርን እያመሰገኑ "በሰማይ ለእግዚአብሔር ምስጋና ይሁን በምድርም ሰላም በሰው በጎ ፈቃድ እያለ መጡ። ❤ ከዚህም በኋላ መላእክት ከእነርሱ ዘንድ ባረጉ ጊዜ እነዚህ እረኞች ሰዎች እርስበርሳቸው "ኑ ወደ ቤተ ልሔም ሔደን ይህን እግዚአብሔር የገለጠውንን ነገር እንወቅ" አሉ። ፈጥነውም ሔዱ ማርያምንና ዮሴፍን ሕፃኑንም በበረት ውስጥ ተኝተ አገኟቸው። አይተውም የነገሩዋቸው ስለዚህ ሕፃን እንደሆነ አወቁ እረኞች የነገሩዋቸውን የሰሙ ሁሉ አደነቁ። እረኞችም ለሕፃኑ ሰግደው እግዚአብሔርን እያመሰገኑ ወደ ቦታቸውም ተመለሱ። ከወገኖችን ሰው ሁኖ ለጐበኘንና ይቅር ላለን እግዚአብሔር ምስጋና ይሁን ለዘላለሙ አሜን። ምንጭ፦ የታኅሣሥ 28 ስንክሳር። + + + ❤ የዕለቱ የማኅሌት ምስባክ፦ "ምስሌከ ቀዳማዊ በዕለ ኃይል። ወብርሃኖሙ ለቅዱሳን። ወለድኩከ እምከርሥ እምቅድመ ኮከበ ጽባሕ"። መዝ109፥3።የሚነበበው ወንጌል ሉቃ 1፥26-57። + + + ❤የዕለቱ የቅዳሴ ምስባክ፦ "የሐዩ ወይሁብዎ እምወርቅ ዓረብ። ወዘልፈ ይጼልዩ በእንቲአሁ። ወኵሎ አሚረ ይድኅርዎ"። መዝ 71፥15። የሚነበቡት መልዕክታት ሮሜ 8፥3-18፣ 1ኛ ዮሐ 4፥1-9 የሐዋ ሥራ 3፥22-ፍ.ም። የሚነበበው ወንጌል ማቴ1፥1-18። የሚቀደሰው ቅዳሴ የእመቤታችን የማርያም ቅዳሴ ነው። መልካም የቅዱስ አማኑኤል በዓልና የገሐድ ጾም። ለሁላችንም ይሁንልን። ❤ በየቀኑ ይህን ቴሌግራም ላይ ማግት ከፈለጉ ከታች ያለውን ሊኩን ይጫኑት። https://t.me/Eotcw

ማኅሌቱን ለምትቆሙ መልካም አገልግሎት

photo content

❤ "በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን"። ❤ + + + ❤ የዕለቱ አንገርጋሪ ግእዝ ዜማ፦ ሃሌ ሉያ "አባ አቡነ አቡነ መምህርነ እምአዕላፍ ኅሩይ ሐውጽ እምሰማይ ብርሃነከ ከመ ንርአይ አማን ተክለ ሃይማኖት ፀሐይ"። ትርጉም፦ ከአእላፍ የተመረጥኽ መምህራችን አባታችን ሆይ ብርሃንህን እናይ ዘንድ ከሰማይ ኾነኽ ጎበኝ፤ በእውነት ተክለ ሃይማኖት ፀሓይ ነው። ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በድጓው ላይ። + + + ❤ "ሰላም ለፅንሰትከ ወለልደትከ እምከርሥ። አመ እሥራ ወረቡዑ ለወርኀ ታኅሣሥ። ተክለ ሃይማኖት በኵሉ ወበውስተ ኵሉ ውዱስ። ናሁ ወጠንኩ ወእቤ ለስብሐቲከ ሐዲስ በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ"። ትርጉም፦ ተክለ ሃይማኖት ሆይ፤ አስቀድሞ በማኅፀን ለተፀነሰከው ፅንሰትህና በታኅሣሥ ሃያ አራት ቀን ለተኸለድክበት መወለድህ ሰላም እላለሁ። ቅዱስ አባት፤ ሁሉ በሁሉ የተመሰገንህ ነህና እኔም በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ብዬ እነሆ አዲስ ምስጋናን እጀምራለሁ። መልክአ አቡነ ተክለ ሃይማኖት። https://t.me/Eotcw

photo content
+5