Construction Solution- @Consite Media[የግንባታ ሥራ ተቋራጮች]🏗
رفتن به کانال در Telegram
Addis Ababa, Ethiopia Con-Site is a Comprehensive Construction Filed Works and Materials Reference Catalogue for Architects, Engineers, Consultants and Customer service. t.me/ConsitesolutionBot ☜|]Comments Construction Solution Official Service
نمایش بیشتر3 588
مشترکین
+224 ساعت
-17 روز
+4230 روز
آرشیو پست ها
የኢፌዴሪ ገቢዎች ሚኒስቴር በንግድ ማዕከልነት የሚያገለግሉ ሕንፃዎችን በጋራ ገንብተው በባለቤትነት የሚያስተዳድሩ አክሲዮን ማኅበራት ፣ የተጨማሪ እሴት ታክስ እና የዲቪደንድ (የትርፍ ድርሻ) ታክስን ጨምሮ የተለያዩ የግብር ዓይነቶችን እንዲከፍሉ ወስኗል።
በንግድ ማዕከልነት የሚያገለግሉ ሕንፃዎችን ገንብተው በባለቤትነት የሚያስተዳድሩ አክሲዮን ማኅበራት የሕንፃውን ሱቆች በማከራየት ከሚያገኙት ገቢ ላይ ለሚገኙበት ከተማ ወይም የአካባቢ አስተዳደር የኪራይ ገቢ ግብር ብቻ ሲከፍሉ ቆይተዋል።
ሚኒስቴሩ በአክሲዮን ማኅበራት ባለቤትነት ሥር የሚገኙና የሚተዳደሩ የንግድ ማዕከላት ላይ ጥናት ያካሄደ ሲሆን የጥናቱ ግኝትም ፣ አክሲዮን ማኅበራቱ በሕግ የተጣለባቸውን ግብር በተገቢው መንገድ እየተወጡ አለመሆናቸው ያረጋገጠ ነው ተብሏል።
ገቢዎች ሚኒስቴር በጥናት የደረሰባቸውን ግኝቶች መሠረት በማድረግ ሊወሰዱ ይገባል ያላቸውን የማስተካከያ ዕርምጃዎች የተመለከተ ምክረ ሐሳብ ለመንግሥት አቅርቦ በቅርቡ ተቀባይነት ማግኘቱ ተጠቁሟል።
በዚህም መሠረት ፥ በአክሲዮን ተደራጅተው የተገነቡና በንግድ ማዕከልነት የሚያገለግሉ ሕንፃዎች ባለቤት አክሲዮን ማኅበሩ በመሆኑ፣ የንግድ ማዕከሉን የሚመለከቱ የግብር ግዴታዎች ላይ ሙሉ ኃላፊነት መውሰድ እንዳለበት ተወስኗል።
በመሆኑም በንግድ ማዕከልነት በሚያገለግለው ሕንፃ ውስጥ የሚገኙ ሱቆችን በማከራየት የሚገኘው ገቢ ላይ በግብር አዋጁ መሠረት የሚጣለውን የኪራይ ገቢ ግብር እንደ ከዚህ ቀደሙ በከተማ አስተዳደሮች እንደሚሰበሰብ የሚኒስቴሩ መረጃ ያመለክታል።
ይሁን እንጂ ሚኒስቴሩ ባካሄደው ጥናት አክሲዮን ማኅበራቱ በሚያስተዳድሯቸው የንግድ ማዕከላት ውስጥ የሚገኙ የንግድ ሱቆች ኪራይ ተመን ፦
- ከወቅታዊ ገበያው በእጅጉ አነስተኛ መሆኑ፣
- በርከት ያሉ ማኅበራትም በንግድ ማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ ሱቆችን በርካሽ ዋጋ ለማኅበሩ አባላት እንዳከራዩ ፣
- ሌሎች በርከት ያሉ አክሲዮን ማኅበራት ደግሞ የባለቤትነት ማስተላለፍ ሥርዓቶችን ሳይከተሉ በንግድ ማዕከሉ ውስጥ የሚገኙ ሱቆችን እንደ አክሲዮን ድርሻ ለማኅበሩ አባላት አከፋፍለው መገኘታቸው ተመላክቷል።
በመሆኑም ፣ ከ2016 ዓ.ም. የግብር መክፈያ ወቅት ጀምሮ በንግድ ማዕከላቱ ውስጥ የሚገኙ ሱቆች የኪራይ ተመን በገበያ ዋጋ ተሰልቶ የኪራይ ገቢ ግብር እንዲከፍሉ መወሰኑን ሪፖርተር ጋዜጣ ከገቢዎች ሚኒስቴር ያገኘውን መረጃ ዋቢ በማድረግ አስነብቧል
https://t.me/notcoin_bot?start=rp_32930160
🎁 +2.5k Notcoin as a first-time gift
🎁🎁🎁 +50k Notcoin if you have Telegram Premium @PremiumBot
Share ሕዝብ_ጥቅም_ሲባል_የመሬት_ይዞታ_የሚለቀቅበትን፣_ካሣ_የሚከፈልበት_.pdf
በየቀኑ ለሚወጡ ነፃ ጨረታዎች/🚧 እና ስራዎች የማቴሪያል/ማሽነሪ ግዥ እና ኪራይ ጨርታ እና ሌሎች ጠቃሚ ተያያዥ መረጃዎች ከስር ባለው ቴሌግራም ቻናል ዌብሳይታችን ላይ በቋሚነት ይለቀቃሉ ይከታተሉ.. .
👇የቻናል ድህረ-ገፃችን🏗http://t.me/unityCoNcatalogue1 መልካም ጊዜ ይሁንላችሁ!
የሥራ ተቋራጭ (Contractor) የሕግ ተጠያቂነት?በኮንስትራክሽን ውል ሁለት አይነት የግንባታ ስራ ርክክቦች ያሉ ሲሆን እነሱም ግዚያዊ ርክክብ እና የመጨረሻ ርክክብ በመባል ይታወቃሉ፡፡ 1/ ግዚያዊ ርክክብ ግዜአዊ ርክክብ በተለይ በኮንስትራክሽን ውል የተመለከቱ የግንባታ ስራዎች ተከናውነው ካበቁ በኋላ ወዲያውኑ ሁለቱ ወገኖች ማለትም አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በስራው ላይ የሚደረግ የምርመራ ማረጋገጫ ነው:: (የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3274(1)):: ይሄውም አሰሪው በትክክል የተገነባውን ግንባታ በእጁ አግብቶ መያዙን ጭምር ያረጋግጣል፡፡ ስለዚህ ጊዜአዊ ርክክብ በዋናነት የተሰራውን የግንባታ ስራ አሰሪው መብቱን ጠብቆ በመጀመሪያ የሚረከብበት ሂደት ነው፡፡ በስራው ላይ ምርመራ መደረጉንም የሚያረጋግጥ ነው፡፡ እንግዲህ ስራው ከተመረመረ በኋላ አሰሪው ያላመነበትን ግንባታ ፈርሶ እንደገና እንዲሰራ ወይም እንዲጠገን ተደርጐ የጥራት ደረጃውን ባሟላ ሁኔታ እንዲከናወን ለማዘዝ እንደሚችል ፒፒኤ ክሎስ 85 ይፈቅድለታል:: በዚህም መሰረት ግንባታው የስራ ምርመራውን ካለፈ አሰሪው ግንባታውን የሚረከበው ይሆናል፡፡ 2/ የመጨረሻ ርክክብ የመጨረሻ ርክክብ/Final Acceptance/ በተለይ የመድህንነት ጊዜ ካለቀ በኋላ እና ተቋራጩ ጠቅላላ ግዴታዎቹን በደህና ሁኔታ የፈጸመ መሆኑን አሰሪው ሲያረጋግጥ ግንባታውን ሙሉ በሙሉ በእጁ የሚያደርግበት ስለመሆኑ የፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279 ይደነግጋል፡፡ የመጨረሻ ርክክብ አሰሪውና ተቋራጩ ባሉበት በጽሁፍ መደረግ እንዳለበት በአስገዳጅ ሁኔታ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3279(2) ላይ ተደንግጓል፡፡ በፍትሀብሄር ህግ አንቀጽ 3282 ላይ እንደተቀመጠው ከመጨረሻ ርክክብ በኋላ ተቋራጩ እስከ 10 አመት ድረስ ስለስራው አሰራር ጉድለት ተቋራጩ ሀላፊነት አለበት ፣ ለስራው ጥራት መድህን ሆኖም ይቀጥላል፡፡ ስለሆነም በሀዋሳ ዩኒቨርሲቲ የተደረመሰውን ድልድይ የገነባው ሥራ ተቋራጭ ለደረሰው ጉዳት በሕግ ተጠያቂ የሚሆንበት አግባብ ሊኖር ይችላል:: ይሁን እንጂ በመጨረሻ ርክክብ ወቅት የሚታዩ ለነበሩ የጥራት ጉድለቶች ተቋራጩ ሀላፊነት የለበትም፡፡
የልኬት ውል (Admeasurement Contract)ይህ የውል አይነት ብዙ ጊዜ “unit rate Contract” ተብሎ ከሚታወቀው የውል አይነት ጋር እጅግ የተመሳሰለ ነው። ተቋራጩ በጨረታ ሰነዱ ላይ ያስገባው የአንድ ልኬት ዋጋ እንዳለ ሆኖ የሥራው መጠን ግን አማናዊ ሥራው (Executed works) ላይ በተከናወነው ልኬት መሰረት የሚከፈልበት የውል ስጦታ አይነት ነው። 🖱ለምሳሌ፦ አንድ ተቋራጭ በጨረታው ላይ ለተመለከተው 4.5 ኪዩቢክ ሜትር አርማታ ቢሆን እና በአንድ ኪዩቢክ ሜትር 8ooo ብር አስገባ እንበል። ነገር ግን ወደ ሥራ ከገባ በኋላ የተሰራው አርማታ 5.0 ኪዩቢክ ሜትር ቢሆን በልኬት ውል (Admeasurement Contract) ከተፈራረሙ ዋጋ ለመክፈውል የሚቆረጠው የሥራ መጠን ጨረታው ላይ የነበረው 4.5 ኪዩቢክ ሳይሆን በሥራ ላይ የተመዘገበው ልኬት ወይም 5.0 ኪዩቢክ ሜትር ነው። ነገር ግን አስቀድሞ ያስገባው የአንድ ኪዩቢክ ሜትር ማባዣ ዋጋ ወይም 8000 ብር ግን አይቀየርም። ስለዚህ ለተቋራጩ የሚከፈለው 5.0*8000 = 40,000.00 ብር ይሆናል ማለት ነው። በዚህ ውል አይነት የሥራው መጠን በጨረታው ላይ ከተሞላው መጠን ሊለይ ቢችልም የአንድ ልኬት ዋጋ ግን መቀየር አይቻልም ማለት ነው።
اکنون در دسترس! پژوهش تلگرام ۲۰۲۵ — مهمترین بینشهای سال 
