cookie

ما از کوکی‌ها برای بهبود تجربه مرور شما استفاده می‌کنیم. با کلیک کردن بر روی «پذیرش همه»، شما با استفاده از کوکی‌ها موافقت می‌کنید.

avatar

ተዘከረነ እግዝኦ በዉስተ መንግስትከ

አምላካችን ሆይ እንደ ቸርነት ነው እንጅ እንደ በደላችን አይሁን ።

نمایش بیشتر
پست‌های تبلیغاتی
2 847
مشترکین
+124 ساعت
-67 روز
-5030 روز

در حال بارگیری داده...

معدل نمو المشتركين

در حال بارگیری داده...

Photo unavailableShow in Telegram
“በመከራዬ ቀን ፊትህን ከኔ አትመልስ፤ ጆሮህን ወደ እኔ አዘንብል፤ በጠራሁህ ቀን ፈጥነህ ስማኝ።” — መዝሙር 102፥2
نمایش همه...
11
እንደዚህ ሁሌ ማረግ ያለብን ፣ የሚከተሉትን ነገሮች ማድረግ እንችላለን! ••• 1) መጸለይ እንችላለን። “ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።” — ፊልጵስዩስ 4፥6 2) አለመፍራት እንችላለን። “እኔ ከአንተ ጋር ነኝና አትፍራ፤ እኔ አምላክህ ነኝና አትደንግጥ፤ አበረታሃለሁ፥ እረዳህማለሁ፥ በጽድቄም ቀኝ ደግፌ እይዝሃለሁ።” — ኢሳይያስ 41፥10 3) ጊዜያችንን እና ትኩረታችንን የሚወስዱትን ነገሮች መወሰን እንችላለን። “በቀረውስ፥ ወንድሞች ሆይ፥ እውነተኛ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ጭምትነት ያለበትን ነገር ሁሉ፥ ጽድቅ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ንጹሕ የሆነውን ነገር ሁሉ፥ ፍቅር ያለበትን ነገር ሁሉ፥ መልካም ወሬ ያለበትን ነገር ሁሉ፥ በጎነት ቢሆን ምስጋናም ቢሆን፥ እነዚህን አስቡ፤” — ፊልጵስዩስ 4፥8 4) እኛን የማይወዱንንም ሰዎች እንኳን ሳይቀር ለመውደድ መጣር እንችላለን። “እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ፥ እንደ ወደድኋችሁ እናንተ ደግሞ እርስ በርሳችሁ ትዋደዱ ዘንድ አዲስ ትእዛዝ እሰጣችኋለሁ።” — ዮሐንስ 13፥34 5) ለእኛ የሚያስፈልገውን ነገር ብቻ መውሰድ እንችላለን። “የሚጐመጅ ሰው ክርክርን ያነሣሣል፤ በእግዚአብሔር የሚታመን ግን ይጠግባል።” — ምሳሌ 28፥25 6) ለተቸገሩ ልንሰጥ እንችላለን። “እንዲሁ እየደከማችሁ ድውዮችን ልትረዱና እርሱ ራሱ፦ ከሚቀበል ይልቅ የሚሰጥ ብፁዕ ነው እንዳለ የጌታን የኢየሱስን ቃል ልታስቡ ይገባችሁ ዘንድ በሁሉ አሳየኋችሁ።” — ሐዋርያት 20፥35 7) ከሁሉም በላይ በጌታ መታመን እንችላለን። "በፍጹም ልብህ በእግዚአብሔር ታመን፥ በራስህም ማስተዋል አትደገፍ፤በመንገድህ ሁሉ እርሱን እወቅ፥ እርሱም ጎዳናህን ያቀናልሃል።" — ምሳሌ 3 5-6 “ከክፉ ነገር አይፈራም፤ በእግዚአብሔር ለመታመን ልቡ የጸና ነው።” — መዝሙር 112፥7 በመጨረሻም ወዳጆቼ ! “የሰላምም ጌታ ራሱ በሁሉ መንገድ ዘወትር ሰላምን ይስጣችሁ። ጌታ ከሁላችሁ ጋር ይሁን።” — 2ኛ ተሰሎንቄ 3፥16 በፍጹም አንደናገጥ፣ ሁሉም ነገር በእግዚአብሔር እጅ ነው፣ እሱ ሁሉንም ነገር በቁጥጥሩ ስር ያደርገዋል። ••• ☞ 🅢🅗🅐🅡🅔
نمایش همه...
8👍 3
Watch "MH|| የሰኔ ሚካኤል ወረብ | አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእ| በናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት መዘምራን" on YouTube https://youtu.be/dK07ZfhqvkA?si=1hJNwHQYHjF_SMaF
نمایش همه...
MH|| የሰኔ ሚካኤል ወረብ | አመ ይሰቅልዎ አይሁድ ለእግዚእ| በናይሮቢ መሠረተ ሃይማኖት ሰንበት ት/ቤት መዘምራን

5
Photo unavailableShow in Telegram
#ቃሉን_የምታደርጉ ሁኑ እንጂ ራሳችሁን እያሳታችሁ #የምትሰሙ_ብቻ_አትሁኑ። ቃሉን የሚሰማ የማያደርገውም ቢኖር የተፈጥሮ ፊቱን በመስተዋት የሚያይን ሰው #ይመስላል፤ ራሱን አይቶ ይሄዳልና፥ ወዲያውም እንደ ምን እንደ ሆነ #ይረሳል። ነገር ግን ነጻ የሚያወጣውን ፍጹሙን ሕግ ተመልክቶ #የሚጸናበት፥ #ሥራንም&የሚሠራ እንጂ ሰምቶ የሚረሳ ያልሆነው፥ #በሥራው_የተባረከ_ይሆናል። ✥✥✥ያዕቆብ 1:22-25✥✥✥
نمایش همه...
13
#ምክረ_አበው🌷🌷🌷          🍀🍀🍀🍀🍀🍀 "ብቸኝነት የሚሰማን ከሰው ሳይሆን ከእግዚአብሔር ስንርቅ ነው"!! : ☞«ሰው የለኝም፤» በማለት በተሟጠጠ ተስፋ ይህንን ቃል የተናገረው መጻጉዕ ነው።(ዮሐ 5፥7) : ►"ወዳጄ " አንተም እንደ መፃጉዕ በዙርያህ ሰው አጥተህ ሰው የለኝም ብለህ ተስፋ ቆርጠህ ይሆናል ። : ►የሚቀርብህ ሁሉ ያለህን ነገር ብቻ አይቶ እንደሚጠጋህ አውቀህ የልብ ወዳጅ በማጣትህ አዝነህ ይሆናል። : ►ብትወድቅ ቀና የሚያረግህ ብትደናቀፍ ከልቡ እኔን የሚልህ የልብ ጓደኛ የለኝም ትል ይሆናል። : ►ትናንትና በሰርግህ ላይ ነጭ ለብሰው ካንተ ጋር "ሲዘምሩ" የነበሩ ሰዎች ዛሬ በለቅሶክ ላይ ብን ብለው ጠፍተው ከሰው ተስፋ እንድትቆርጥ አድርገውክ ይሆናል ። : ►ትናንት አጀቢ የበዛልህ ሰው ዛሬ ብቻህን ቆመህ ይሆናል ። ፡ ☞ወንድሜ በዚህ አትደነቅ ። ፡ ♦ከክርስቶስ እጅ እንጀራና አሳ በበረከት ሲበሉ የነበሩ ሰዎች መች በ"መስቀሉ" ቀን ከእርሱ ጋር ቆሙ። ፡ ♦ውሃው ወደ ወይን ጠጅ ሲቀየር በሰርጉ ላይ ነበሩ ፤ ደሙ ሲፈስ ግን በቀራኒዮ አልነበሩም ። ፡ ☞ታዲያ ህይወት ለሰጣቸውና ለሞተላቸው ምግበ ነፍስ ምግበ ስጋ ለሰጣቸው ለክርስቶስ ያልሆነ ሰው ላንተ ይሆናል ብለህ ታስባለህ ።በፍፁም አይሆንም !! ፡ ✿ሰው ሸንበቆ ነው ከተደገፍከው ይሰበራል ። : ✿ተሰብሮም አይቀርም ይወጋሀል ። ፡ ☞ወንድሜ ያንተም ነገር ይሄ ነው !! ፡ ★ወዳጆችህ ቀን አይተው ቢከዱህ ፣ : ★ዘመዶችህ ማጣትህን አይተው ገሸሽ ቢያረጉህ ፣ : ★ብቻህን ከራስህ ጋር ብትቆም አትደነቅ። ፡ ☞ ግን በዚህ መካከል አንድ ነገር አስተዉል:- : ✔ጊዜን አይቶ የማይከዳ ፣ ፡ ✔በሁኔታዎች የማይለዋወጥ ፣ : ✔ሁል ጊዜ ሰው ለሌላቸው ቀድሞ የሚደርስ ፣ : ✔የጭንቅ ቀን ባለ ውለታ፣ : ✔የቁርጥ ቀን ወዳጅ እግዚአብሔር ካንተ ጋር ነው። ፡ ☞ እርሱ ካንተ ጋር መሆኑን ካመንክ ሰው የለኝም እያልክ የምታንጎራጉረው መዝሙር ግጥሙም ዜማውም ይቀየራል !!! ፡ ♠♠<>♠♠<>♠♠<>♠♠<>♠♠<>♠♠ #ወዳጄ፥ ፡ ☞ወደ ዋላ ተመለስና ታሪክ አጥና ፦ ፡ ➊.ዮሴፍን ወንድሞቹ ሸጠውት ወደ ግብፅ ሲወርድ ሰው አልነበረውም፥ እግዚአብሔር ግን በጌታው በጲጥፋራ ቤት ከፍ ከፍ አደረገው። : ➋.በጌታው ሚስት ተንኰል ወደ ወኅኒ ቤት በተወረወረ ጊዜም ሰው አልነበረውም፥ እግዚአብሔር ግን ከወኅኒ ቤት አውጥቶ በባዕድ ሀገር ገዥ አደረገው። : ➌.ሙሴ በሕፃንነቱ ወንዝ ዳር ሲጣል ሰው አልነበረውም፥ እግዚአብሔር ግን ከተጣለበት አንሥቶ በፈርዖን ቤተ መንግሥት፥ የንጉሥ የልጅ ልጅ ተብሎ እንዲያድግ አደረገው። (ዘፍ 39፥1-23፤ 41፥1-50።) : ➍ ብላቴናው ዳዊት በኃያሉ በጐልያድ ፊት በቆመ ጊዜ ሰው አልነበረውም፥ ከወንጭፉ በስተቀር መሣሪያም አልነበረውም፥ እግዚአብሔር ግን ጐልያድን በአንዲት ጠጠር ግንባሩን ፈርክሶ ጣለለት።( ዘጸ 2፥1-10) : ➎.ዳንኤልና ሠለስቱ ደቂቅ ተማርከው ወደ ባቢሎን ሲወርዱሰው አልነበራቸውም፥ እግዚአብሔር ግን ጥበብን ሰጥቶ በባቢሎን ጠቢባን እና አውራጃዎች ላይ እንዲሾሙ አደረጋቸው።(1ኛሳሙ 17፥35-55።) : ➏ በሰዎች ተንኰል፥ ሠለስቱ ደቂቅ ወደ ዕቶነ እሳት፥ ዳንኤል ደግሞ ወደ አናብስት ጉድጓድ በተጣሉም ጊዜ ሰው አልነበራቸውም፤ እግዚአብሔር ግን ቅዱስ ሚካኤልን እና ቅዱስ ገብርኤልን ልኮ አዳናቸው።(ዳን 1 እና 2፤ ) : ➐.አልዓዛር በሞት ተይዞ፥ ተገንዞ፥ ወደ መቃብር በወረደ ጊዜ ሰው አልነበረውም፤ ጌታ ግን ከመቃብር አወጣው። (ዳን 3፥24፣6፥6 ) : ➑.ቅዱስ ጴጥሮስ በሰንሰለት ታስሮ ወደ ጨለማው ወኅኒ ቤት ሲወረወር ሰው አልነበረውም፥ ጌታ ግን መልአኩን ልኰ ከወኅኒ ቤት አወጣው።(ዮሐ 11፥28-34) : ➒.ቅዱስ ጳውሎስና ሲላስ ወደ ወኅኒ ቤት ተወርውረው፥ ከግንድ ጋርም አጣብቀው ሲያስሯቸው ሰው አልነበራቸውም።(የሐዋ 12፥1-11) : ►በመንፈቀ ሌሊትም ይጸልዩ፥ እግዚአብሔርንም በዜማ ያመሰግኑ ነበር። : ►ጌታም የእግር ብረቱን፥ የእጅ ሰንሰለቱን ፈትቶ፥ በሩንም ከፍቶ አውጥቶአቸዋል።(የሐዋ 16፥16-30።) : ♠♠<>♠♠<>♠ cc♠<>♠♠<>♠♠<>♠♠ : ☞ታዲያ ወዳጄ ይህ ላንተም ነው ።ይህ ህግ ዛሬም በህይወትህ ዉስጥ ይሰራል ። ብቻህን አይደለህም ። : ♣ዘመድ ላይኖርህ ይችላል ታማኝ ጓደኛ ላይወጣልህ ይችላል : ♣እናት ወይም የስጋ አባት ላይኖርህ ይችላል : ♣ግን ከሁሉ በላይ የሆነውን ወዳጅ ፣ ዘመድ ጓደኛ የሚተካ ፤ ከሁሉ በላይ ሆኖ ሁሉም በእርሱ ለእርሱ የሆነ ወዳጅ "አባት" አለህ!! በዚህ ኩራት ይሰማህ !!! : #ክብር ምስጋና ለዚህ ጌታ ለአባታችን ለፈጣሪያችን ለአምላካችን ቅዱስ እግዚአብሔር ይሁን !!(አሜን)      🕊ለወዳጅ ለዘመዶ ያካፍሉ
نمایش همه...
7👏 2👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
አምላኬ ሆይ.... ለሰጠኽኝ ነገር ሁሉ አመሰግንሃለሁ በከለከልከኝ ነገር ደሞ አብዝቼ አመሰግንሃለሁ ምክንያቱም የከለከልከኝ የሚያጠፋኝ ይሆናል 🙏🙏🙏🙏🙏
نمایش همه...
21👏 2🥰 1
Photo unavailableShow in Telegram
የቀደመውን በደላችንን #አታስብብን፥ ምሕረትህ በቶሎ #ታግኘን፥ እጅግ ተቸግረናልና። አምላካችንና መድኃኒታችን ሆይ፥ #እርዳን፤ ስለ ስምህ ክብር፥ አቤቱ፥ #ታደገን፥ ስለ ስምህም ኃጢአታችንን #አስተሰርይልን። አሕዛብ፦ አምላካቸው ወዴት ነው? እንዳይሉ፥ የፈሰሰውን የባሪያዎችህን ደም በቀል በዓይኖቻችን ፊት አሕዛብ #ይወቁ። የእስረኞች ጩኸት ወደ ፊትህ #ይግባ፤ እንደ ክንድህም ታላቅነት #ሊገደሉ_የተፈረደባቸውን_አድን። አቤቱ፥ የተዘባበቱብህን መዘባበታቸውን ለጎረቤቶቻችን ሰባት እጥፍ በብብታቸው #ክፈላቸው። እኛ ሕዝብህ ግን፥ የማሰማርያህም በጎች፥ ለዘላለም #እናመሰግንሃለን፤ ለልጅ ልጅም ምስጋናህን #እንናገራለን። መዝሙር 79:8-13🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏🙏
نمایش همه...
14👍 1
Photo unavailableShow in Telegram
“አላዋቂዎች ሰዎች ስንፍናን ይወርሳሉ፤ ብልሆች ግን እውቀትን እንደ ዘውድ ይጭናሉ።” — ምሳሌ 14፥18
نمایش همه...
14👏 1
📕ያለፍክበት የህይወት መንገድ አስሮ ሊይዝህ አይገባም ፤ ነገህን መወሰን የራስህ ምርጫ ነው፡፡ 📕በህይወትህ የደስታ ምንጭ መሆን ባትችል እንኳን ለሌሎች የሐዘን ምክንያት አትሁን፡፡ 📕ዝምታ ፣ በውስጡ ትልቅ ጩኸት የያዘ የማይጠየቅ ጠያቂ ፣ የማይመረመር መርማሪ ነውና ከዙሪያህ ካለ የሰዎች ጫጫታ በላይ የውስጥ ዝምታህን አድምጥ ፡፡ 📕በምድር ላይ ምንም ፍፁም ነገር የለምና አንተም ፍፁም ለመሆን አትሞክር ሰዎችም ፍፁም እንዲሆኑ አትጠብቅ ነገር ግን ሁሉን በመልካምነትና በቅን ልቦና አከናውን ፡፡ 📕ያለህን ችሎታ ፣ አቅም ፣ ዕውቀት አንተ ካላከበርከውና ካላወጣኸው ማንም መቶ ሊያከብርልህና ሊያወጣልህ አይችልም ፡፡ ስለዚህ ከተቀምጥክበት ተነሳና ከምኞት ወተህ ወደ ተግባር ተሻገር ፡፡ 📕በህይወትህ ትልቅ መከራ ፣ ችግር ፣ ሀዘን ደርሶ ሊሆን ይችላል ፤ "ሰው እንዴት በዚህ ውስጥ ያልፋል?" ብለህ አዝነህ ፣ ተክዘህ ሊሆንም ይችላል ፡፡ ግን በሕይወት ዘመን መዘንጋት የሌለብህ ነገር "ተስፋ" የሚባል ነገር መኖሩን ነው ፡፡
نمایش همه...
11👍 4🥱 1
Photo unavailableShow in Telegram
#ግንቦት *1*[#ዮም_ፍስኃ_ኮነ_በእንተ_ልደታ_ለ_ማርያም] እመቤታችን ተወለደች ማለት ጌታ ሊወለድ 15 ዓመት ቀረው ፣ የዘመኑ ፍጻሜ ደረሰ ማለት ነበር። እግዚአብሔር ሃና እና ኢያቄምን ሳይወልዱ ያዘገያቸውም ለዚህ ታላቅ ክብር እንዲበቁ ነበር። ክርስቶስ ፀሐይ ከሆነ የዛሬው ዕለት ሰማይዋ የተዘረጋችበት ዕለት ነው። ክርስቶስ የሕይወት ውኃ ከሆነ ዛሬ ምንጯ የፈለቀችበት ዕለት ነው። ወንጌል በመጥምቁ ዮሐንስ መወለድ ብዙዎች ደስ ይላቸዋል ይላል። በእመቤታችን መወለድ ምን ያህል ሰዎች ደስ ይላቸው ይሆን? የእመቤታችን ልደት በብዙ ሀገራት ብሔራዊ በዓል ሆኖ ይከበራል። እኛም በሊባኖስ ተራሮች (አድባረ ሊባኖስ) መወለዷን በማሰብ ከደጅ ወጥተን ቅድም አያቶቿ በጨረቃ ተመስላ በህልማቸው ያዩአትን የጨረቃችንን (በግሪኩ ሶልያና) ልደት ጨረቃን እያየን እናከብራለን። የልደቷ ቀን ልደታችን ነው! #እንኳን_ለእመቤታችን_ልደት_በዓል_በሰላም_አደረሳችሁ::
نمایش همه...
12🙏 8👏 1
یک طرح متفاوت انتخاب کنید

طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.