WES Incubator
رفتن به کانال در Telegram
969
مشترکین
-124 ساعت
-47 روز
-1730 روز
آرشیو پست ها
+2
ሰላም ፋርማችን የማስፈልፈል አቅሙን ወደ 10,560 ለማሳደግ ዝግጅት ላይ ነን በመሆኑም አሁን ላይ ያለንን ባለ 3168 ኢንኩቤተር እና 160 የሚሆኑ የኮኮክ parents stock 10ወር የጣሉ አንድ ላይ መሸጥ እንፈልጋለን እንዲሁም 3kw ጀነሬተር
0912290883
New research from The Roslin Institute has provided fresh insight into how light exposure during incubation can shape chick behaviour, development and welfare. The findings, which build on a growing body of avian developmental science, indicate that simple changes to incubation practices could support healthier, more adaptable birds in commercial poultry systems.
Repost from Ministry of Labor and Skills - Ethiopia
የአላጌ ግብርና ኮሌጅ የዓለም አቀፍ የጥራት ደረጃ (ISO) እውቅና ባለቤት ሆነ
የአላጌ ግብርና ቴክኒክና ሙያ ሥልጠና ኮሌጅ በትምህርት ተቋማት ሥራ አመራር ሥርዓት የ ISO 21001:2018 የዓለም አቀፍ የብቃት ማረጋገጫ ሰርተፊኬት አገኘ።
ኮሌጁ ይህንን እውቅና ያገኘው በትምህርትና ሥልጠና አሰጣጥ፣ በተቋማዊ አመራር እና በተገልጋይ እርካታ ዓለም አቀፍ መመዘኛዎችን ማሟላቱ በገለልተኛ ኦዲት በመረጋገጡ ነው።
የኢትዮጵያ የተስማሚነት ምዘና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መዓዛ አበራ በእውቅና አሰጣጥ መርሃ ግብሩ ላይ ባስተላለፉት መልዕክት፤ እውቅናው ኮሌጁ የሚሰጠው አገልግሎት በሀገር ውስጥና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪና ተመራጭ እንዲሆን ያስችለዋል ብለዋል።
ይህ እውቅና የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር በበጀት ዓመቱ 36 ፖሊ ቴክኒክ ኮሌጆችን ዓለም አቀፍ ደረጃቸውን የጠበቁ ለማድረግ የያዘው ዕቅድ አካል ሲሆን አላጌን ጨምሮ እሰከአሁን 20 ኮሌጆች የጥራት ማረጋገጫውን ማግኘት ችለዋል።
ይህም የኢትዮጵያን የክህሎት ልማት ከዓለም የሥራ ገበያና የኢንዱስትሪ ደረጃዎች ጋር የማስተሳሰር ስትራቴጂያዊ ጉዞ ዋነኛ የዘርፉ የሪፎርም አጀንዳ ነው፡፡
ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቱ የዓለም አቀፍ የጥራት ሥራ አመራር ሥርዓት ISO 9001:2015ን በማሟላት የመጀመሪያው የሚኒስቴር መሥሪያ ቤት መሆን የቻለ ሲሆን በፌዴራል ደረጃ የሚገኙ ሁለት ተጠሪ ተቋማቱ የጥራት ማረጋገጫውን ማግኘት ችለዋል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ሁሉም የሙያ ብቃት ምዘና ማዕከላትን ጨምሮ በዕቅድ የተያዙ የሥልጠና ኮሌጆች ዓለም አቀፍ ደረጃዎችን እንዲያሟሉ በልዩ ትኩረት እየተሰራ ይገኛል።
የካቲት 10/2018 ዓ.ም ፤ የሥራና ክህሎት ሚኒስቴር
