Financial _ Ethiopia
Finance is a term for the management, creation, and study of money and investments. https://t.me/financialethiopia https://t.me/stockethiopia https://t.me/sthare101 https://t.me/stargemstone https://t.me/Saligebeya https://t.me/madeinethiopia1
نمایش بیشتر1 538
مشترکین
اطلاعاتی وجود ندارد24 ساعت
+187 روز
+7730 روز
- مشترکین
- پوشش پست
- ER - نسبت تعامل
در حال بارگیری داده...
معدل نمو المشتركين
در حال بارگیری داده...
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
Photo unavailableShow in Telegram
" ' የቤት ኪራይ ጨምሩ ' ወይም ' ቤቱን ልቀቁ ' የሚል ግፊት ከደረሰባችሁ ደውላችሁ ጠቁሙኝ " - የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ
በአዲስ አበባ ፤ ' ከአከራይ ተከራይ የውል ስምምነት ' ጋር በተያያዘ ተከራዮች የሚገጥማቸውን ማንኛውም ችግር ጥቆማ ሊሰጡ እንደሚችሉ የከተማው የቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ አሳውቋል።
ቢሮው ማንኛውም አከራይ ከመጋቢት 24 ቀን 2016 ዓ/ም ጀምሮ የቤት ኪራይ መጨመርም ሆነ ተከራይን ማስወጣት ፈፅሞ የተከለከለ መሆኑን አስገንዝቧል።
ከዚህም ጋር በተያያዘ ተከራዮች የቤት ኪራይ ጭማሪ አልያም ' ቤቱን ይልቀቁልኝ ' የሚል ግፊት ከአከራዮች ከደረሰባቸው በስልክ ቁጥር +251118722917 / +251118553820 ላይ በመደወልና ጥቆማቸውን በመስጠት መብታቸውን ማስከበር እንደሚችሉ ገልጿል።
በሌላ በኩል ፤ ሰኔ 1 ላይ የጀመረው የአከራይ ተከራይ የውል ስምምነት ሊጠናቀቅ 14 ቀናት የቀሩት ሲሆን ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙት ወረዳዎች በማቅናት ምዝገባ እንዲያካሂዱ ማሳሰቢያ ተላልፏል።
አከራዮች የውል ስምምነቱን ሳይፈጽሙ እስከ ሶስት ወር ድረስ ከቆዩ የሁለት ወር የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ እንደሚደረግ ተገልጿል።
መንግስት ጥናት በማድረግ በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ እንደሚሆን ተነግሯል።
#TikvahEthiopia
#HousingDevelopmentandAdministration
@tikvahethiopia
Repost from TIKVAH-ETHIOPIA
Photo unavailableShow in Telegram
#AddisAbaba
" ... የቤት አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ ነው " - ቤቶች ልማትና አስተዳደር
የአዲስ አበባ ቤቶች ልማትና አስተዳደር ቢሮ የአከራይ ተከራይ ውል ምዝገባን በተመለከተ ዛሬ መግለጫ ሰጥቷል።
ቢሮው ከሰኔ 1/2016 ዓ/ም ጀምሮ በ120 ወረዳዎች ምዝገባ እየተከናወነ እንደሆነ ገልጿል።
በቀሪ የ15 ቀናት ጊዜ ዜጎች በአቅራቢያቸው በሚገኙ ወረዳዎች በማቅናት ምዝገባ እንዲያካሂዱ አሳስቧል።
አከራዮች የውል ስምምነቱን ሳይፈጽሙ እስከ 3 ወር ድረስ ከቆዩ የ2 ወር የቤት ኪራይ እንዲከፍሉ ይደረጋል ተብሏል።
ይህንን ስራ ብቻ የሚያከናውን ቡድን መቋቋሙንም ቢሮው ገልጿል።
የውል ምዝገባው ቅዳሜ እና እሁድን ጨምሮ በምሽት ጭምር እየተሰጠ እንደሆነ ያመለከተው ቢሮው ፥ " የተሰጠው የምዝገባ ጊዜ በቂ በመሆኑ የቀን ጭማሪ ላይኖር ይችላል " ሲል አሳውቋል።
ቢሮው በመግለጫው ከመጋቢት 24 ጀምሮ የሚደረግ የቤት ኪራይ ጭማሪ እና ውል ማቋረጥ ክልክል እንደሆነ እና ተቀባይነትም እንደሌለው አመልክቷል።
መንግስት ጥናት በማድረግ በሚቀጥለው ዓመት ሰኔ ወር ላይ የዋጋ ጭማሪ እንደሚያደርግ አሳውቋል።
አከራይ የቤት ኪራይ ዋጋ ጭማሪ ማድረግ የሚችለው በዓመት አንዴ መንግስት በሚያወጣው ተመን ብቻ እንደሚሆን አስገንዝቧል።
#FBC
#AddisAbaba #HousingDevelopmentandAdministration
#AddisAbaba
@tikvahethiopia
❤ 1
Photo unavailableShow in Telegram
መንግሥት ከብሔራዊ ባንክ መበደር የሚችለው የገንዘብ መጠን በአዲስ ረቂቅ ሕግ ሊገደብ ነው
ላለፉት 16 ዓመታት ያለገደብ ከብሔራዊ ባንክ ገንዘብ ሲበደር የነበረው የፌደራል መንግሥት፤ ከአገር ውስጥ ገቢ ከ15 በመቶ የበለጠ ገንዘብ በብድር ማግኘት እንዳይችል የሚገድብ ረቂቅ አዋጅ ለሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት ቀረበ።
ረቂቅ አዋጁ መንግሥት የተበደረውን ገንዘብ በአንድ ዓመት ውስጥ ካልመለሰ ከተቋሙ ሌላ ብድር መውሰድ እንደማይችልም ያስቀመጠ ሲሆን፤ መንግሥት ከብሔራዊ ባንክ ያለገደብ ብድር እንዲወስድ ለመጀመሪያ ጊዜ የፈቀደውን በ2000 ዓ.ም. የወጣውን አዋጅ የሚቀይር እንደሆነ ተነግሯል።
የአገሪቱን ማዕከላዊ ባንክ ለመምራት ከ1955 ዓ.ም. ጀምሮ አራት አዋጆች የጸደቁ ሲሆን፣ አሁን በሥራ ላይ ካለው አዋጅ በስተቀር ቀሪዎቹ አራት አዋጆች ለመንግሥት በሚሰጥ የቀጥታ ብድር ላይ ገደብ ያስቀመጡ እና ገንዘቡ የሚመለስበት ጊዜ የወሰኑ ነበር።
በሥራ ላይ ያለው አዋጅ በአንጻሩ፤ “ባንኩ ለመንግሥት እና ለፋይናንስ ተቋማት ብቻ ብድር እንደሚሰጥ ከመግለጽ ውጭ ለመንግሥት በሚሰጠው ቀጥታ ብድር ላይ ግን ምንም ገደብ ሳይጥል በለሆሳስ ያለፈ የመጀመሪያው አዋጅ” እንደሆነ ከአዲሱ ረቂቅ ጋር የቀረበው ማብራሪያ ጠቅሷል።
Credit: BBC Amharic
Photo unavailableShow in Telegram
ኢትዮጵያ በኩንታል 2 ሚሊየን ብር የሚሸጥ አልጌ ማምረት ጀመረች
ሰኔ 13/2016 (አዲስ ዋልታ) ኢትዮጵያ በኪሎ 20 ሺሕ ብር በኩንታል ደግሞ እስከ 2 ሚሊየን ብር የሚሸጥ ዋቅላሚ (አልጌ) በስፋት ማምረት የሚያስችላት የማይክሮ አልጌ (ስፓይሩሊና) ምርምርና ማምረቻ ማዕከል ተመርቆ ሥራ ጀምሯል።
በኢትዮጵያ የመጀመርያ የሆነው የማይክሮ አልጌ (ስፓይሩሊና) ምርምርና ማምረቻ ማዕከል በባዮ እና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት አማካኝነት ባለፉት 3 ዓመታት የምርምርና የማምረቻ ሥራው ሲጠና ቆይቶ ስኬታማነቱ ተረጋግጧል።
በዚህም በኩንታል 2 ሚሊየን ብር የሚሸጥ የማይክሮ አልጌ (ስፓይሩሊና) ምርት መመረት ተጀምሯል።
የዚህ ደቂቅ ህዋስ ሳይንሳዊ አጠራር ስፓይሩሊና (spirulina) የተሰኘ ሲሆን በዓለም አቀፍ ደረጃ እጅግ ተፈላጊ ብሎም በዋጋው ውድ መሆኑ ይነገራል፡፡
በባዮና ኢመርጂንግ ቴክኖሎጂ ኢንስቲትዩት የማይክሮ አልጌ ተመራማሪ የሆኑት ሀብቴ ጀቤሳ (ዶ/ር) ከዚህ ቀደም ከአዲስ ዋልታ ዲጂታል ሚዲያ ጋር በነበራቸው ቆይታ እንደገለጹት እነዚህ ደቂቅ ህዋስ በውሀ ውስጥ የሚበቅሉ ሲሆን በስምጥ ሸለቆ ሀይቆች ውስጥ በብዛት ይገኛሉ፡፡
ስፓይሩሊና ከ90 በመቶ በላይ ለሰው ልጅ የሚያስፈልገውን የምግብ ንጥረ ነገሮችን የያዘ ሲሆን በዓለም ላይ አምስቱንም ንጥረነገሮች በነጠላ ህዋስ (single cell) የያዘ ብቸኛው ማይክሮ አልጌ ነው፡፡
👌 4
Photo unavailableShow in Telegram
It Is A Beautiful Day!!!
“ዛሬ ለቀረው የህይወት ዘመኔ የመጀመሪያው ቀን ነው” (John Denver)
• ዛሬ ትበረታላችሁ እንጂ በፍጹም አትደክሙም!
• ዛሬ ቀና ትላላችሁ እንጁ በፍጹም አታቀረቅሩም!
• ዛሬ ከወደቃችበት ትነሳላችሁ እንጂ በፍጹም ወድቃችሁ አትቀሩም!
• ዛሬ ደስተኞች ትሆናላችሁ እንጂ በማንም ሰውና በምንም ሁኔታ ምክንያት ኃዘንተኞች አትሆኑም!
• ዛሬ ጊዜ ያላችሁ ለተስፋ እና ለወደፊት ለማቀድ እንጂ በፍጹም ለድብርትና ለጭንቀት ጊዜ የላችሁም!
/Dr-Eyob-Mamo
Repost from ሸገር የገንዘብ ቁጠባ እና ብድር ኃ/የተ/መሠረታዊ ኅብረት ሥራ ማኅበር
Photo unavailableShow in Telegram
👉 ለበለጠ መረጃ ከስር ያሉትን ሊንኮች በመጫን እና በመቀላቀል የተቋማችንን ይፋዊ የማህበራዊ ትስስር ገጾች ይጎብኙ፡፡
📌 www.shegersacco.com
📌https://www.facebook.com/shegesacco
📌 www.tiktok.com/@shegersacco
Photo unavailableShow in Telegram
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ የኦንላይን ግብይት ሊጀምር መሆኑን ገለጸ፡፡
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ ከዚህ በፊት ያገበያይ የነበረበትን የኤሌክትሮኒክስ ስርዓት በኦንላይን ለመቀየር እየሰራ መሆኑን ሰምተናል፡፡
ከጣቢያችን ጋር ቆይታ ያደረጉት የምርት ገበያዉ የኮርፖሬት ኮሚኒኬሽን ሃላፊ አቶ ዳዊት ሙራ፤ ከሚቀጥለዉ ዓመት ጀምሮ በኦንላይን የግብይት ስርዓት ማገበያየት እንደሚጀመር ነግረዉናል፡፡
ከዚህ በፊት በተለያዩ የአገሪቱ ክፍሎች ባሉ 6 የኤሌክትሮኒክስ የመገበያያ ማዕከላት ደንበኞች ወደ ተቋሙ ሳይመጡ መገበያየት ይችሉ እንደነበር ገልጸዉ፤ አሁን ላይ ግን ወደ የትኛዉም ማዕከል መምጣት ሳይጠበቅባቸዉ ባሉበት ሆነዉ መገበያየት የሚችሉበትን ስርዓት ከሚቀጥለዉ ዓመት ጀምሮ ለማስጀመር መታሰቡን ነዉ የነገሩን፡፡
እስካሁን ባለዉ ሂደት ሶፍትዌር እያበለጸጉ መሆናቸዉን ገልጸዉ፤ ግልጽ የሆነ ጊዜ ባያስቀምጡም በሚቀጥለዉ ዓመት ግን አገልግሎት መስጠት እንደሚጀመር ገልጸዋል፡፡
ምርት ገበያዉ በዚህ ዓመት 11 ወራት ጊዜ ዉስጥ ከ23.7 ቢሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸዉን ከ 2 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ማገበያየቱንም አቶ ዳዊት ነግረዉናል፡፡
የኢትዮጵያ ምርት ገበያ በቀጣይ ዓመት ኑግ፣ ባቄላ እና ሽምብራን በአዲስ መልክ ማገበያየት እንደሚጀምር የገለጹት ሃላፊዉ፤ የቢራ ገብስ ለማገበያየት የሚያስችል ረቂቅ አልቆ ወደ ስራ መገባቱንም ነግረዉናል፡፡
ከተመሰረተ 16 ዓመት የሞላዉ የኢትዮጵያ ምርት ገበያ እስካሁን ድረስ ከ3መቶ84 ቢሊየን ብር በላይ ዋጋ ያላቸዉን 8 ሚሊየን ሜትሪክ ቶን እህል ማገበያየቱንም ለማወቅ ችለናል፡፡
እስከዳር ግርማ
ሰኔ 13 ቀን 2016 ዓ.ም
https://t.me/hAmster_kombat_bot/start?startapp=kentId7043280196
Play with me, become cryptoexchange CEO and get a token airdrop!
💸 2k Coins as a first-time gift
🔥 25k Coins if you have Telegram Premium
Hamster Kombat
Just for you, we have developed an unrealistically cool application in the clicker genre, and no hamster was harmed! Perform simple tasks that take very little time and get the opportunity to earn money!
❤ 1
یک طرح متفاوت انتخاب کنید
طرح فعلی شما تنها برای 5 کانال تجزیه و تحلیل را مجاز می کند. برای بیشتر، لطفا یک طرح دیگر انتخاب کنید.