fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 335 مشترک است و جایگاه 2 651 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 347 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 335 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 26 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -104 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -8 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 35.99% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 158 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 808 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 30 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 27 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 335
مشترکین
-824 ساعت
-327 روز
-10430 روز
آرشیو پست ها
የዶክተር ዐቢይ መንግሥት ▬▬▬▬▬ ➔ልክ እንደ ልማት ፕሮጀክት ጦርነትን Phase 1, Phase2, Phase 3... እያለ በምዕራፍ በምዕራፍ የሚከፋፍል፤ ➔በጦር ሜዳ ተገኝቶ የቀለበሰውን ትግል ወደ
የዶክተር ዐቢይ መንግሥት ▬▬▬▬▬ ➔ልክ እንደ ልማት ፕሮጀክት ጦርነትን Phase 1, Phase2, Phase 3... እያለ በምዕራፍ በምዕራፍ የሚከፋፍል፤ ➔በጦር ሜዳ ተገኝቶ የቀለበሰውን ትግል ወደ ዘላቂ ድል ይቀይረዋል ተብሎ ሲጠበቅ ወደ ከባድ ትግል ቀይሮት የሚመለስ፤ ➔የተዳከመን ጠላት ከማክሰም ይልቅ የዝግጅት ጊዜ ሰጥቶ እንዲያገግም ማድረግ የሚመቸው፤ ➔የደብረ ጽዮንን ጦር ልክ እንደ ሞሶሎኒ ጦር ወራሪ አድርጎ የተወሰኑ ክልሎችን ተወራሪ ያደረገ፤ ➔የጦር ሜዳ ድል ሲጨብጥ ፖለቲካዊ ትግሉን እርግፍ አድርጎ የሚተው፤ ➔ሕዝብ "ተወረርኩ" ብሎ ሲጣራ የእርሻ ማሳ የሚጎበኝ፣ የሕዝብ ጩኸት ሲያባራ ደግሞ ከጦር ግንባር የሚገኝ፤ ➔የፖርክና መናፈሻ ፕሮጀክቶችን እንጂ ጦርነትን የመጨረስ ፍላጎት የሌለው፤

ጄኔራል ተፈራ ማሞ ▬▬▬▬ ➔የብአዴን መቀመጫ ከባሕር ዳር ወደ ሸገር ሲቀየር ከጦር ግንባር የተገኘ፤ ➔በአጭር ጊዜ ውስጥ በሰራው ሥራ ወራሪውን መደመሰስና ወረራውን መቀልበስ የቻለ፤ ➔በጦርነቱ ጊዜ
ጄኔራል ተፈራ ማሞ ▬▬▬▬ ➔የብአዴን መቀመጫ ከባሕር ዳር ወደ ሸገር ሲቀየር ከጦር ግንባር የተገኘ፤ ➔በአጭር ጊዜ ውስጥ በሰራው ሥራ ወራሪውን መደመሰስና ወረራውን መቀልበስ የቻለ፤ ➔በጦርነቱ ጊዜ ከቤተሰቦቻቸው ጋር ወደ ውጭ አገር ለማምለጥ የአውሮፕላን ትኬት ገዝተው በነበሩ አመራሮች ከጦርነቱ በኋላ "ሥጋታችን ነህ" ተብሎ የተሰናበተ፥ ➔መስዋዕትነት በሚጠይቅ ጊዜ ተጠርቶ የሽልማቱ ጊዜ የተዘለለ፥ ➔በዚያ የፈተና ጊዜ ባደረገው አበርክቶ በሕዝብ ልብ ውስጥ ለመግባት የታደለ፥ እናመሠግናለን‼️

የአማራ ሕዝብ የጸጥታ ችግር የሆነው አቶ ሺማይክል በጦርነቱ ላይ ለተሳተፉ የጸጥታ ኃይሎች እውቅና ለመሥጠት በተዘጋጀው መድረክ ላይ ሊሳተፍ ባሕር ዳር ገብቷል። ሆኖም ግን አዳማ የገባ መስሎት ያልሆነ
የአማራ ሕዝብ የጸጥታ ችግር የሆነው አቶ ሺማይክል በጦርነቱ ላይ ለተሳተፉ የጸጥታ ኃይሎች እውቅና ለመሥጠት በተዘጋጀው መድረክ ላይ ሊሳተፍ ባሕር ዳር ገብቷል። ሆኖም ግን አዳማ የገባ መስሎት ያልሆነ ነገር እንዳይዘባርቅ "ባሕር ዳር ነው ያለኸው" እያለ በየደቂቃው የሚያስታውስ አካል ቢመደብለት ጥሩ ነው።

photo content

እናት ዓለም ጎንደር በዛሬው እለት ሁለት ችግሮቿን በውይይት ፈትታለች። 1- በጫካ የነበሩ ወንድሞቻችን የቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ ተቀበለው በመምጣት ጭልጋ አይከል ላይ ሰፊ ውይይት ሲደረግ ውሏል። 2
እናት ዓለም ጎንደር በዛሬው እለት ሁለት ችግሮቿን በውይይት ፈትታለች። 1- በጫካ የነበሩ ወንድሞቻችን የቀረበላቸውን የሰላም ጥሪ ተቀበለው በመምጣት ጭልጋ አይከል ላይ ሰፊ ውይይት ሲደረግ ውሏል። 2- ሚያዚያ 5 ቀን በተከሰተው አሳዛኝ ክስተት ዙሪያ አጥፊዎችን እና ተጎጂዎችን በለየ መልኩ ጥልቅ ውይይት ከተደረገ በኋላ አምሥት አቋሞችን በመያዝ ተጠናቅቋል። ሰላም ለወገኖቻችን!!

"ግንቦት ልደታን በተድባበ ማሪያም ለማሳለፍ ወደ አማራ ሳይንት የሄዱችሁ ከአቶ ደርቤ ቤት ጸበል ቅመሱ" ብዬ በተጠራሁት መሠረት ጋዜጠኛ ያለለት ወንድዬና መዓዛ መሐመድ ወደ ቤት አግልለው ወላጆቼን መ
"ግንቦት ልደታን በተድባበ ማሪያም ለማሳለፍ ወደ አማራ ሳይንት የሄዱችሁ ከአቶ ደርቤ ቤት ጸበል ቅመሱ" ብዬ በተጠራሁት መሠረት ጋዜጠኛ ያለለት ወንድዬና መዓዛ መሐመድ ወደ ቤት አግልለው ወላጆቼን መተዋወቃቸውን ከምንጮቼ ያገኘሁት መረጃ ያመለክታል።😆 ፎቶ፦ ጋዜጠኛ ያለለት ወንድዬ እና የምወደው አባቴ ፎቶ አንሺ፦ መዓዛ መሐመድ ዓመት ዓመቱ ያድርስልኝ!!

ጋዜጠኛ ጎበዜ በብልጽግና መንግሥት ታግቶ ደብዛው ከጠፋ ዘጠኝ ቀን ሆነው። መንግሥት ሆይ የወንድማችን ነፍስ ከእነ ኢንጂነር ስመኘው፣ ከእነ ጄኔራል አሳምነውና ጄኔራል ሰዓረ ስለማትበልጥ ገድለኸው ከሆ
ጋዜጠኛ ጎበዜ በብልጽግና መንግሥት ታግቶ ደብዛው ከጠፋ ዘጠኝ ቀን ሆነው። መንግሥት ሆይ የወንድማችን ነፍስ ከእነ ኢንጂነር ስመኘው፣ ከእነ ጄኔራል አሳምነውና ጄኔራል ሰዓረ ስለማትበልጥ ገድለኸው ከሆነ ሸኔ ወይንም ወያኔ ገደለው ብለህ አስከሬኑን ስጠን‼️

ጎበዜ ሲሳይን ሸገር ላይ ሰውሮ "የት እንደደበቅኩት ፈልጋችሁ አግኙ" የሚል ትኩረት ነጣቂ አጀንዳ የሰጠን አካል ባሕር ዳር ላይ ተሰባስቦ አማራን ለዘላለማዊ ፍዳ የሚዳርግ ውሳኔ አስተላልፏል! እናም
ጎበዜ ሲሳይን ሸገር ላይ ሰውሮ "የት እንደደበቅኩት ፈልጋችሁ አግኙ" የሚል ትኩረት ነጣቂ አጀንዳ የሰጠን አካል ባሕር ዳር ላይ ተሰባስቦ አማራን ለዘላለማዊ ፍዳ የሚዳርግ ውሳኔ አስተላልፏል! እናም ወገኔ ሆይ ጎበዜን ስንፈልግ እራሳችንን እንዳናጣ ሁሉንም ነገር በንቃት እንከታተል!

ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በፌደራል ፖሊሶች ተከብቦ ወደ ቤርሙዳ ሲወሰድ...‼️ የወንድማችንን ደብዛ ያጠፋው አካል መታወቁም አንድ ነገር ነው።
ጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ በፌደራል ፖሊሶች ተከብቦ ወደ ቤርሙዳ ሲወሰድ...‼️ የወንድማችንን ደብዛ ያጠፋው አካል መታወቁም አንድ ነገር ነው።

https://m.youtube.com/watch?v=ECnkQTJN8pI&feature=youtu.be ከአንድ ወር በፊት ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ባደረግኩት ቆይታ መንግሥት በትሕ-ኦነግ ጥይት አማራ ሕዝብ ላይ ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት የሃይማኖት ግጭት እንደሚቀሰቅስና የአማራ ድምጽ በመሆን የሚታወቁ አክቲቪስቶችን፣ ጋዜጠኞችን እና ታዋቂ ሰዎችን እያሳደደ በሞት እና በእስራት እንደሚቀጣ ተናግሬ ነበር። ይሄም በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ላይ ተጀምሯል።

ከአንድ ወር በፊት ከምኒልክ ቴሌቪዥን ጋር ባደረግኩት ቃለ-መጠይቅ መንግሥት በትሕ-ኦነግ አማካኝነት አማራ ሕዝብ ላይ ጥቃት ከመፈጸሙ በፊት ሃይማኖትን መሠረት ያደረገ ግጭት እንደሚቀሰቅስና የአማራ ድምጽ ለመሆን የሚሞክሩ ታዋቂ ሰዎችን፣ አክቲቪስቶችን፣ ጋዜጠኞችን እያሳደደ በሞት እና በእስራት እንደሚቀጣ ተናግሬ ነበር። ይሄም በጋዜጠኛ ጎበዜ ሲሳይ ተጀምሯል።

ሰሜን ሸዋ ድረስ ለምን ተወረርን? አሳዬ ደርቤ ▬▬▬ ➔ጀግንነት አጥተን ሳይሆን በቂ ዝግጅት ባለማድረጋችን፤ ➔ዱላና ክላሽ ይዘን ታንክና ሞርታር በመግጠማችን፤ ➔በጥቂት ወጣቶች ትግል ሕዝባዊ ድል በመፈለጋችን፤ ➔"የተበተነ ዱቄት" የሚለውን ቀደዳ እውነት አድርገን በመቀበላችን፤ ➔እንደ ሕዝብ የመጣብንን ወራሪ እንደ ሕዝብ በመመከት ፈንታ በዞን ደረጃ ተወስነን በወረፋ ለመወረር ዝግጁ ሆነን በመገኘታችን፥ ➔በጠላት የትግል ሰሌዳ መሠረት በመመራታችን፥ ➔አጥቂ ሆነው ሲመጡ ተከላከይ ሆነን በመገኘታችን፤ ➔ሕዝብን ከፋፍሎ ለጠላት ካስረከበ በኋላ የፓርቲውን ብር በሚከፋፈል ድርጅት በመመራታችን፤ ➔በእነ አገኘሁ ተሻገር ፉከራ በመዘናጋታችን፤ ➔በብዛትም ሆነ በጥራት ከወረረን ኃይል ልቀን ባለመገኘታችን፤ ➔በብዙ መስዋዕትነት ትንሽ ድል ሲገኝ ወደ ከባድ ትግል ቀይሮ ከሚያስረክብ መንግሥት እጅ በመውደቃችን፥ እናስ... ከእነዚህ ድክመቶቻችን መሀከል ስንቱን መቅረፍ ቻልን? #Share

በጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት ጎበዜ ሲሳይን አፍኖ የወሰደው መንግሥት ከስምንት ቀን በኋላ በአባቶርቤዎች መታገቱንና እንደ በዓሉ ግርማ መሰወሩን ሊነግረን ይችላል። ወይም ደግሞ እራሱ የማያከብረውን ሕግ
በጸጥታ ኃይሎች አማካኝነት ጎበዜ ሲሳይን አፍኖ የወሰደው መንግሥት ከስምንት ቀን በኋላ በአባቶርቤዎች መታገቱንና እንደ በዓሉ ግርማ መሰወሩን ሊነግረን ይችላል። ወይም ደግሞ እራሱ የማያከብረውን ሕግ አስከብራለሁ የሚለው መንግሥት ከአንዱ ስርቻ አስሮ ጋዜጠኛውን ብቻ ሳይሆን ቤተሰቦቹንም ጭምር ሲያሰቃይ መክረሙን ሰበር ዜና አድርጎ ያቀርብልን ይሆናል። ሆኖም ግን በጎበዜ ላይ የተፈጸመው ድርጊት ምንም ይሁን ምን አባ ቶርቤው እና ሕግ አስከባሪው፣ ብልጽግና እና ኦነግ ሸኔው፣ ዳኛው እና ወንጀለኛው... መቀላቀሉን የሚገልጽ በመሆኑ... ነገ የመንግሥትን የጸጥታ ኃይሎች አምኖ እንደ በግ የሚነዳ ተጠርጣሪ ማግኘት ከባድ ነው። በመሆኑም "በሕግ ትፈለጋላችሁ" ሲባሉ "ከፈለጋችሁን ከቤተሰቦቻችን ፊት ግደሉን እንጂ እናንተን ተከትለን ወደ ቤርሙዳ አንሄድም" የሚሉ ዜጎች መፍጠሩ አይቀሬ ነው።

ጥብቅ ማሳሰቢያ አሳዬ ደርቤ ወሮ-በላው ቡድን ዳግም ወረራ ለመፈጸም ከድሮን ጥቃት ነጻ የሚሆንበትን የክረምት ወቅት እየጠበቀ መሆኑን የሚገልጽ መረጃ የደረሰው የፌደራል መንግሥት የወራሪውን እቅድ በማክሸፍ ፈንታ በሰው ሰራሽ መንገድ ደመና ጨምቆ ሰው አልባ ድሮን የማይጠቀምበትን የክረምት ወቅት ወደ ግንቦት ማምጣት ቢችል ደስ እንደሚለው ይታወቃል፡፡ በሌላ መልኩ ግን አሸባሪው ኃይል ከስምንት መቶ ሺህ በላይ ወራሪ ማዘጋጀቱን እየሰማ ‹‹ሰርገኛ መጣ በርበሬ ቀንጥስ›› የሚልበት ቀን እስኪደርስ ድረስ እንቅልፉን በመቸልፈስ ላይ የሚገኘው የብአዴን አመራር እንደ ትናንቱ ሁሉ ወንበር ላይ ተጎልቶ ‹‹ሁሉም ፍጡር ወደ ጦር ግንባር›› ብሎ ሲጣራ አቤት ብሎ የሚወጣው ወጣት እሱን ሳይፈነክት የሚዘምት መስሎት ከሆነ ተሳስቷል፡፡ እኛም ብንሆን ወራሪው ኃይል ያዘጋጀውን አውዳሚ ጦር በየዞኑ እና በየዙሩ ሲመረቁ በምናያቸው በመቶዎች የሚቆጠሩ ፋኖዎች መከላከል የሚቻል ከመሰለን ተሳስተናል፡፡

ጎንደር አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ➔ሰሜን እዝ ሲወጋ ቀድማ የደረሰች ➔በጀርባዋ የአልቡርሐንን፣ የአልሲሲን፣ የደብረ ጽዮንን፣ የቅማንት ኮሚቴን ጥምር ጦር የተሸከመች፣ ➔በዚህ ጥምር ጦር በአገር ላይ የተቃጣን ከሰላሳ በላይ ወረራዎች ከመከላከያ ሠራዊቱና ከአማራ ልዩ ሃይል ጋር ሆና 30 ጊዜ የመከተች፤ ➔ወራቤ ባልሰማችበት ሁኔታ ወሎ ሲወረር ሃይማኖቱን ሃይማኖቴ፣ ማንነቱን ማንነቴ ብላ ገስግሳ በመድረስ በቦሩ ሜዳ እና በጦሳ ተራራ ላይ ታሪክ የማይዘነጋው ተጋድሎ የፈጸመች፣ ➔በኢሬቻ በዓል ላይ ቄሮዎች ሲገደሉ ‹‹ኦሮሚያ ላይ የሚፈስሰው ደም ከእኔ ጅማት የሚቀዳ ነው›› በሚል መርሕ ኦሮማራን መሥርታ የ27 ዓመቱን የማፊያ ቡድን ያስወገደች፤ ➔በእራሷ መስዋዕትነትና የሰላም እጦት ላይ የአገርን ቀጣይነት ለማረጋገጥ ሦስት ዓመት ሙሉ የደከመች ጎንደር ▬▬▬ ➔አማራን እና ኢትዮጵያን ለማፈራረስ ጎንደርን ማተራመስ›› የሚል የጥፋት ፕሮጀክት ባነገቡ ኃይሎች ከማተብ ውጭ ምንም አይነት የሐሳብ ልዩነት የሌላቸው ልጆቿ በጠላት መረብ ወድቀው ሰለባ ሲሆኑ የታዘበች፤ ➔በቀጣይ ክረምት ‹‹አማራ›› በሚል ማንነት ለሚሰነዘርባት ውጫዊ ጥቃት ውስጣዊ የእምነት ልዩነት ይፈጥሩ ዘንድ ድርጎ በሚሰፈርላቸው ቆብ እና ጥምጣም ለባሽ ፖለቲከኞች መንጋጋ ውስጥ የገባች፤ ➔ገዳይም ሆነ ሟች ልጆቿ ሆነው ሳለ ወራቤ እና ወሎ ምድር በበቀሉ የትሕ-ኦነግ ፈረሶች ‹‹ወገኖቼን ገደልሽብኝ›› ተብላ የተለያዩ እምነት ያላቸውን ፋኖዎቿን ትጥቅ አስፈትታ እጇን ለትሕ-ኦነግ ታስረክብ ዘንድ የተጠየቀች፤ ➔አራት ዓመት ሙሉ አገራዊ ጠላት ተሸክማ ክርስቲያንና ሙስሊም ልጆቿን ስትገብር ማንነቷን አስታውሰው የተሳለቁባት ኃይሎች፣ በሰሞኑ ውስጣዊ ጥቃት ቱርክ ድረስ በሚሰማ ድምጽ ‹‹ጨፍጫፊ›› ተብላ የተወገዘች፣ ጎንደር ▬▬▬ ➔በፌስቡክ ፖስት ቀርቶ በታንክ ጥይት የማይበታተኑ፣ እምነትን መሰረት አድርጎ ጠላት የሚጠነስሰውን ሤራ ማንነትን መሰረት አድርገው የሚተነትኑ ብልህ እና ጀግና ልጆች ያሏት… ➔በእንዲህ አይነቱ የኢንተርኔት ዘመቻ ቀርቶ በዙሪያዋ ለከበባት እልፍ አእላፍ ጠላት እጇን አሳልፋ የማትሰጥ.. እናም እልኻለሁ… ተስፋ መቁረጥ ከከበደህ ቶምቦላ ሞክር! ↪️ስድብ Block & Ban ያስደርጋል።

የደንቢዶሎ ተማሪዎች ላይ ያዳበራችሁትን የመሰወር ልምድ ከጎበዜ ሲሳይ ላይ ተግባራዊ እንዲታደርጉ አንፈቅድም። ይሄን የሕዝብ ልጅ የደበቃችሁበትን ስርቻ የማትናገሩ ከሆነ ወደ አደባባይ ወጥተን "ወንድማ
የደንቢዶሎ ተማሪዎች ላይ ያዳበራችሁትን የመሰወር ልምድ ከጎበዜ ሲሳይ ላይ ተግባራዊ እንዲታደርጉ አንፈቅድም። ይሄን የሕዝብ ልጅ የደበቃችሁበትን ስርቻ የማትናገሩ ከሆነ ወደ አደባባይ ወጥተን "ወንድማችን የት አለ?" ለማለት እንገደዳለን።

ይህ የፌደራል ፖሊስ አማራ ባለመሆኑ እንዴት ደስ እንዳለኝ አትጠይቁኝ...!! አማራ ቢሆን እኮ "አንበላ ኡቴ" ተብሎ እንደ ግለሰብ በመጠራት ፈንታ የሚከተሉት የፍረጃ ሥሞች ይሰጡት ነበር። "በጸጥታ
ይህ የፌደራል ፖሊስ አማራ ባለመሆኑ እንዴት ደስ እንዳለኝ አትጠይቁኝ...!! አማራ ቢሆን እኮ "አንበላ ኡቴ" ተብሎ እንደ ግለሰብ በመጠራት ፈንታ የሚከተሉት የፍረጃ ሥሞች ይሰጡት ነበር። "በጸጥታ ሃይሉ ውስጥ ሰርጎ የገባ ፋኖ" "የቀድሞ ሥርዓት ናፋቂዎች ተላላኪ" 😆

ከ14ቱ ሟቾች መካከል የመጀመርያው በፅንፈኞች ተጨፍጭፎ የተገደለው የጎንደር ነዋሪ ህፃን! ቦታው ቅዳሜ ገበያ፣ ቀበሌ 07 ልዩ አካባቢው አስማማው ወፍጮ ቤት ወደ ውስጥ ገባ ብሎ፣ በአካቢው ጋሽ ታረቀኝ ተብለው የሚታወቁ ግላብ ቤት አካባቢ ነው። ልብ በሉ! የመጀመርያ ገዳዮች ፅንፈኞቹ ናቸው። ያውም እንደ እባብ ቀጥቅጠው። ያውም ምንም ያላደረገን ህፃን ልጅ። ቪዲዮውን ከላይ ቴሌግራም ገፄ ላይ ተለጥፏል። ጌታቸው ሽፈራሁ!!

የቀብር ጥሪ!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬▬ በዚች መንቻካ አገር- የሰነፍ መሪዎች- የተለመደ መልስ እንድም አጼን ገድሎ- ቀብረነዋል ማለት- ዳግም ላይመለስ ወይም በሌላ ቀን- መቃብር ቆፍሮ- የሞተን መቀስ
+1
የቀብር ጥሪ!! አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬▬ በዚች መንቻካ አገር- የሰነፍ መሪዎች- የተለመደ መልስ እንድም አጼን ገድሎ- ቀብረነዋል ማለት- ዳግም ላይመለስ ወይም በሌላ ቀን- መቃብር ቆፍሮ- የሞተን መቀስቀስ፡፡ እናም ወገኔ ሆይ- ለእልፍ አላፍ ጥያቄ- ይሄን አሰልች መልስ- ሁሌ ከምንሰማ አጼውን ገርስሰን- እንቅበረውና- በሞቱ እንስማማ፡፡