fa
Feedback
Assaye Derbie

Assaye Derbie

رفتن به کانال در Telegram

📈 تحلیل کانال تلگرام Assaye Derbie

کانال Assaye Derbie (@asayede) در بخش زبانی امهری بازیگری فعال است. در حال حاضر جامعه شامل 14 333 مشترک است و جایگاه 2 647 را در دسته وبلاگ‌ها و رتبه 2 350 را در منطقه أثيوبيا دارد.

📊 شاخص‌های مخاطب و پویایی

از زمان ایجاد در невідомо، پروژه رشد سریعی داشته و 14 333 مشترک جذب کرده است.

بر اساس آخرین داده‌ها در تاریخ 25 ژوئن, 2026، کانال فعالیت پایداری دارد. در ۳۰ روز گذشته تغییر اعضا برابر -108 و در ۲۴ ساعت گذشته برابر -4 بوده و همچنان دسترسی گسترده‌ای حفظ شده است.

  • وضعیت تأیید: تأیید نشده
  • نرخ تعامل (ER): میانگین تعامل مخاطب 38.62% است و در ۲۴ ساعت نخست پس از انتشار، محتوا معمولاً 12.61% واکنش نسبت به کل مشترکان کسب می‌کند.
  • دسترسی پست‌ها: هر پست به طور میانگین 5 538 بازدید دریافت می‌کند. در اولین روز معمولاً 1 808 بازدید جمع‌آوری می‌شود.
  • واکنش‌ها و تعامل: مخاطبان به‌طور فعال حمایت می‌کنند؛ میانگین واکنش به هر پست 33 است.

📝 توضیح و سیاست محتوایی

توضیحی برای کانال ارائه نشده است.

به لطف به‌روزرسانی‌های پرتکرار (آخرین داده در تاریخ 26 ژوئن, 2026)، کانال همواره به‌روز و دارای دسترسی بالاست. تحلیل‌ها نشان می‌دهد مخاطبان به‌طور فعال با محتوا تعامل دارند و آن را به نقطه اثرگذاری مهم در دسته وبلاگ‌ها تبدیل کرده‌اند.

14 333
مشترکین
-424 ساعت
-317 روز
-10830 روز
آرشیو پست ها
"በእድሜ የገፋ ሽማግሌ ማሰቃየት ተገቢ አይደለም" በሚል ምክንያት አቦይን የፈታው አካል ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ እንዳያመልጡት እጃቸውን በካቴና አስሮ የሕክምና ወረፋ ሲያስጠብቃቸው አስበኸዋል?
"በእድሜ የገፋ ሽማግሌ ማሰቃየት ተገቢ አይደለም" በሚል ምክንያት አቦይን የፈታው አካል ጋሽ ታዲዮስ ታንቱ እንዳያመልጡት እጃቸውን በካቴና አስሮ የሕክምና ወረፋ ሲያስጠብቃቸው አስበኸዋል?

photo content

photo content

በባለፉት ጊዜያት የኦነግ ሸኔ ታጣቂ በተለያዩ ክልሎች ላይ ከፈጸማቸውና ተድበስብሰው ከታለፉት መጠነ ሰፊ ጥቃቶች መሀከል አንዷ እንኳን አማራ ክልል ውስጥ በተፈጠረ ሽፍታ ብትፈጸም ኖሮ፡- ▬▬▬▬ ➔በአማራ ብልጽግና እርምጃ ጥቃቱን ከፈጸሙት ሽፍቶች በተጨማሪ የክልሉ ወጣቶች ሕልውና አደጋ ውስጥ ይገባ ነበር፡፡ ➔በአገር አቀፍ እና በዓለም አቀፍ ሚዲያዎች መላው የአማራ ሕዝብ እየተወገዘ ነበር፡፡ ➔"ፌደራላዊት ኢትዮጵያን አጥፍተው ያለፈውን ሥርዓት መመለስ የሚሹ ኃይሎች የፈጸሙትን ጥቃት እናወግዛለን›› የሚሉ የብልጽግና አመራሮችና የተቃዋሚ መሪዎች ሶሻል ሚዲያውን ያጨናንቁት ነበር፡፡ ➔‹‹የፌደራል መንግሥት እጁን አስገብቶ አማራ ክልልን ይመንጥርልን›› የሚሉ የቁጣ ድምጾች አገር ምድሩን ይሞሉት ነበር። በሌላ መልኩ ግን በባለፈው ዘመቻ "ተደምስሷል" የተባለው ኦነግ ሸኔ ከትናንት ጀምሮ የጋምቤላ ክልል ላይ ጦርነት መክፈቱና የአዲስ አበባ ነቀምቴን መንገድ መዝጋቱ ቢታወቅም የሀገሪቱ ሚዲያዎች እንኳን የተከበረውን አሸባሪ መዳፈር አልፈለጉም።

ለ፦ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጉዳዩ፡- እኔን ወክለው እንዳይደራደሩ አሳዬ ደርቤ ▬▬▬▬ ክቡር ሚኒስትር፡- የትኛውም አገራዊ ትርምስና አለመረጋጋት የእርስዎን ሰላም ማናጋት እንደማይቻለው በማመን ‹‹ሰላም ነዎት ወይ›› ብዬ ሳልጠይቅ ወደ ዋናው ሐሳቤ ስገባ ‹‹ካለመናገር ደጃዝማችነት ይቀራል›› የሚለው አባባል እውነት የመሰላቸው ባለሥልጣናት በተናገሩ ማግስት ሲባረሩ ታይተዋል፡፡ እርስዎ ግን ‹‹ባለመናገር ምክትልነት ይጸናል›› በሚል ፍልስፍና የሚመሩ በመሆንዎ ከጎንዎ የነበሩ ጓዶችዎ ከጸረ አማራ ንቅናቄው ጋር በሚጋጭ ተግባራቸውና በአፈንጋጭ ንግግራቸው ሲቀበሩ፣ ሲታሰሩና ሲባረሩ ምክትልነትዎን እንዳስከበሩ እስካሁን ድረስ ዘልቀዋል፡፡ በእነዚያ የዝምታና የመኝታ ዓመታት ታዲያ የአማራ ሕዝብ በቀድሞው ሥርዓት ማንነቱን፣ መሬቱን፣ ክብሩን፣ ዜግነቱን ሲነጠቅ ቢኖርም እርስዎ ግን የተነጠቀውን ሊያስመልሱለት ቀርቶ ‹‹የጎንደርን ምድር ለሱዳን ፈርሞ ሰጥቷል›› እየተባለ ሲነዛብዎት የነበረውን ክስ እንኳን ማስተባበል የቻሉት ህውሓት ከተባረረ በኋላ ነበር፡፡ ያንንም የሥም ማጥፋት ዘመቻ ካስተባበሉ በኋላ በፈርዖን አንደበት ‹‹ሥልጣን ልልቀቅ›› የሚል ጥያቄ ሲያቀርቡ ብሶትዎን የተጋራው የአማራ ኤሊት ‹‹እኛ ሳንፈቅድ ንቅንቅ ማለት አይቻልም›› በሚል ጫጫታ የእርስዎ ምክትልነትና የአማራ ሕዝብ ባርነት ይቀጥል ዘንድ ይሁንታውን ቸረ፡፡ ከዚያን ጊዜ አንስቶም የፈረደበት አማራ ‹‹ነፍጠኛ ነህ›› እያለ ከሚያባርር ጠላት እና ‹‹ከተማ ታቆሽሻለህ›› ከሚል መንግሥት እጅ ወድቆ አገሩን የዘረፈውን አገር መፈለግ ጀመረ፡፡ ክልላቸውን በወረረ ጠላት የተፈናቀሉ እናቶችና ሕጻናትም ሸኖ ላይ ከሚያግት መንግሥት እጅ ወድቀው ‹‹የኢትዮጵያ ዜጎች ሆነን ሳለ የሦሪያ ስደተኞች ከሚኖሩበት የአዲስ አበባ ከተማ መግባት እንዴት ተከለከልን›› እያሉ ሲያለቅሱ ነበረ፡፡ እንዳጠቃላይም በብአዴን እና በእርስዎ የሥልጣን ዘመን የአማራ ሕዝብ ከጸሐይ በታች ያሉ ግፎችን ሁሉ እያስተናገደ ‹‹ያልፋል›› በሚለው ቀን ውስጥ እየተጨፈጨፈ ሲያልፍ ነበር፡፡ በተለይ ደግሞ በብልጽግና ዘመን ያጋጠመው ጥቃት ሕይወቱን ከመንጠቅ ባለፈ ሥነ ልቦናውን የማድቀቅ ግብ ያለው በመሆኑ እልቂትና ውርደት ይዘው የሚመጡትን መጪ ጊዜያት ሊጠብቅ ቀርቶ አባቶቹ ከእራሳቸው ባለፈ አገራቸውን አስከብረው ያሳለፉትን የትናንት ጊዜያት እንዳይናፍቅ በሚያደርጉ ዘመቻዎች አሳሩን ሲበላ ነበር፡፡ ክቡር ሚኒስትር፡- በሥልጣን ሽግግሩ ማግስት ብአዴንም ሆነ አብን በባለፈው ሥርዓት የአማራን ሕዝብ ለሰቆቃ የዳረጉና መልስ የሚፈለጉ ጥያቄዎችን ዘርዝረው ማስቀመጣቸው ይታወቃል፡፡ ሆኖም ግን ችግሮቹ ሲረቀቁና ሲጸድቁ ፊርማውን ባኖረ ድርጅት የሚፈታ ችግር ባለመኖሩ ‹‹ለሰባቱ ሕዝባዊ ጥያቄዎች መፍትሔ አመጣለሁ›› ብሎ ቃል የገባው የእርስዎ ድርጅት ሰባ ሰባት ችግሮች አምጥቶ ሲያስታቅፈን ከርሟል፡፡ ከእነዚያም ሰባት ጥያቄዎች አንዱ የወልቃይትና የራያን ሕዝብ የማንነት ጥያቄ የሚመለከት ሲሆን በእልፍ አእላፍ ወገኖች ነፍስ መልስ አግኝቶ የነበረውን የራያን ሕዝብ ደፍጥጦ ያለምንም ትግል ለቀድሞ አፋኙ ያስረከበው ድርጅት በወልቃይት ማንነት ላይም ለመደራደር መዘጋጀቱ ግልጽ ሆኗል፡፡ ይሄውም የድርድር ኮሚቴ በእርስዎ የሚመራ መሆኑ ቢነገርም በበኩሌ ግን የድርጅትዎም ሆነ የእርስዎ ያለፉ ዘመናት ትግሎች በአማራ ሕዝብ ጉዳት ላይ የአገር ቀጣይነትን ሲያረጋግጡ፣ በወገን በደል ላይ የሌሎችን ድል ሲያስጨብጡ፣ የአማራን ሕዝብ ጸጋ ነጥቀው የሕልውና አደጋ ሲያመጡ…. የኖሩ በመሆናቸው አሁንም ቢሆን በድርድር ለሌሎች የሚሰጡት ካልሆነ በስተቀር የሚያመጡት ቅንጣት ታክል በጎ ነገር ይኖራል ብዬ አላስብም፡፡ ስለሆነም አገርዎንም ሆነ ክልልዎን ወክለው የሚያደርጉት ድርድር እንደ አንድ አማራ እኔን የማይወክል መሆኑን ስገልጽ ‹‹ሕገ-መንግሥቱ ላይ ካልሆነ በቀር ለሱዳን የተሸጠው መሬት ላይ አልፈረምኩም›› ያሉትን ፊርማ ወልቃይት ላይ እንዳያስቡት በመምከር ነው፡፡

ፖሊስ ያቀረበው ይግባኝ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ተሽሮ ብርቱዋ እኅታችን በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ ተለቅቃለች። ምክንያት የለሹ አፈና ከትናንት የበለጠ እንደሚያበረታት አምናለሁ! እንኳን ከሰባት ወር ልጅ
ፖሊስ ያቀረበው ይግባኝ በፌደራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት ተሽሮ ብርቱዋ እኅታችን በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ ተለቅቃለች። ምክንያት የለሹ አፈና ከትናንት የበለጠ እንደሚያበረታት አምናለሁ! እንኳን ከሰባት ወር ልጅሽ ጋር ለመገናኘት በቃሽ ውዷ እኅቴ!

አሳዬ፡ ደርቤ ፡ ዳምጠው ፡ ገብርዬ... ዘ ዐምሐራ ፡ ሳይንት ዝንታለም፡ ዐማራ‼️
አሳዬ፡ ደርቤ ፡ ዳምጠው ፡ ገብርዬ... ዘ ዐምሐራ ፡ ሳይንት ዝንታለም፡ ዐማራ‼️

ከጅምላ ጨራሽ መሳሪያ በላይ አሳሳቢ የሆነው ጥቁር ክላሽ‼️ ኦነግ ሸኔ ለሪፑብሊክ ጋርድ የተገዙ ዘመናዊ ስናይፐሮችንና ጦር መሣሪያዎችን ታጥቆ መከላከያ ጋር ሲታኮስና የአማራዎችን ደም ሲያፈስስ ከረመ
+3
ከጅምላ ጨራሽ መሳሪያ በላይ አሳሳቢ የሆነው ጥቁር ክላሽ‼️ ኦነግ ሸኔ ለሪፑብሊክ ጋርድ የተገዙ ዘመናዊ ስናይፐሮችንና ጦር መሣሪያዎችን ታጥቆ መከላከያ ጋር ሲታኮስና የአማራዎችን ደም ሲያፈስስ ከረመ፡፡ ዋናው አሸባሪ ደግሞ የኢትዮጵያ መከላከያ ሠራዊት ላይ ሁለት ዙር ጥቃት አካሂዶ እልፍ አእላፍ ታንኮችን፣ መድፎችን፣ ሮኬቶችን፣ ሞርታሮችን እና ዲሽቃዎችን ከእጁ ካስገባ በኋላ አማራና አፋር ክልሎች ላይ ወረራ ፈጸመ፡፡ በዚያን ወቅትም የመንግሥትን ጥሪ ተቀብለው ከመከላከያ ሠራዊቱ ጎን የተሰለፉ የአማራ ፋኖዎች ባደረጉት ተጋድሎ ወራሪው ኃይል ከእጁ ካስገባቸው ጥቁር ክላሾች መሃከል የተወሰኑትን ማርከው ታጠቁ፡፡ በአሸባሪዎች እጅ ከገባው እልፍ አእላፍ ጅምላ ጨራሽ ጦር መሣሪያዎች በላይ ሕዝባቸውን ከጥቃት የሚከላከሉ ፋኖዎች የታጠቋቸው ጥቁር ክላሾች እረፍት አልባ ያደረጓቸው ጠቅላይ ሚኒስትርም በዛሬው ስብሰባ ላይ ‹‹ደበስበስ አድርጎ መንከስ›› የሚባለውን የንግግር ጥበብ በመጠቀም የፋኖን ተጋድሎ በስሱ ከተናገሩ በኋላ ‹‹መከላከያን ገድሎ መሳሪያ ነጥቋል›› የሚል ኃይለኛ ውንጀላ አቅርበውበታል፡፡ ፋኖን እና መከላከያን የሚያቃቅር ብቻ ሳይሆን የአማራ ሕዝብን ከሌሎች ኢትዮጵያውያን ነጥሎ ያለ አጋር የሚያስቀር እጅግ አደገኛና ሤረኛ ንግግር አድርገዋል፡፡ ይሄም ከአገር መሪ የማይጠበቅ አደገኛ ንግግር ያልገባቸው ወይም ደግሞ እንዲገባቸው ያልፈለጉ መናኛ ወገኖች ፍሬ ነገሩን ትተው መንደርደሪያው ላይ በማተኮር ‹‹ፋኖ በሚገባው ልክ እውቅና ተችሮታል›› እያሉ ነው፡፡

photo content

የጠቅላይ ሚኒስትሩ ንግግር ▬▬▬▬▬▬ ➔በትሕነግ እና በኦነግ የተፈጸሙ መከላከያ ሠራዊትን የመውጋት ወንጀል ለፋኖ ያከፋፈለ፤ ➔የአማራ ሕዝብን ከመከላከያ ሠራዊቱና ከብሔር ብሔረሰቦች ጋር ያቃቃረ፤ ➔ወራሪው ጦር ከመከላከያው ማርኮ የወሰዳቸውን ክላሾች ያስመለሰውን ፋኖ በመሳሪያ ነጣቂነት የወነጀለ፤ ➔የኢትዮጵያን ሕዝብ ችግሮች ወደ ጎን ገፍቶ መንግሥታዊ ቅዠቶችን ያካተተ፤ ➔ምድር ላይ ካለው መራር እውነታ ጋር የማይጣጣም፤ ➔ጸረ አማራ ንግግሮችና አሽሙሮች የተንጸባረቁበት፤ ➔በርካታ ዝባዝንኬዎች የተካተቱበት፤

ያንተን ጥያቄ ለመስማት ነበር ቲቪ የከፈትኩ። እናም አንደበቴን አንደበትህ ላይ አግኝቼዋለሁ። ከተጠያቂው አካል ግን ምንም አይነቴ መልስ ስለማልጠብቅ ቀሪውን ስብሰባ ረግጬ ወጥቻለሁ። 😆
ያንተን ጥያቄ ለመስማት ነበር ቲቪ የከፈትኩ። እናም አንደበቴን አንደበትህ ላይ አግኝቼዋለሁ። ከተጠያቂው አካል ግን ምንም አይነቴ መልስ ስለማልጠብቅ ቀሪውን ስብሰባ ረግጬ ወጥቻለሁ። 😆

photo content

ብልጽግና ካልገገመ በቀር መስኪ በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲትለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።
ብልጽግና ካልገገመ በቀር መስኪ በ30 ሺህ ብር ዋስ እንዲትለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኗል።

የጣልኩባቸውን ተስፋ ያመከኑ ሁለት ፕሮፌሰሮች‼️ አሳዬ ደርቤ ፕሮፌሰር ብርሐኑ ▬▬▬▬▬ ከህውሓት የሥልጣን ዘመን አንስቶ እስከ ለውጡ ማግስት ድረስ ‹‹የኢትዮጵያ የቁርጥ ቀን ልጆች›› ሆነኝ ከሚታዩኝ ሰዎች ዋነኛው እና ቀዳሚው ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነበር፡፡ ከሥልጣን ሽግግሩ በኋላ ግን እኒያ ፕሮፌሰር ወደ ትግል ሜዳ ይዘዋቸው የሄዱትን ታጋዮች ከሜዳ ላይ በትነዋቸው ወደ ቤተ-መንግሥት ሲያመሩ ዐየኋቸው፡፡ ➔ወንበር ተቀብለው አገር ሲሰጡ፣ ድርጅታዊ ትግልን በግላዊ ድል ሲለውጡ፣ የሕዝብ ፍቅርን በግለሰብ አምልኮ ሲሸጡ፣ ➔በመለስ ዜናዊ ላይ ደረታቸውን የሚነፉት ሰው ለወቅቱ መሪ ሲሽቆጠቆጡ፣ የዜግነት ፖለቲካ ትግላቸው ደጋፊ ሆኖ ገንዘቡን እና ጉልበቱን ሲለግሳቸው የኖረውን ዜጋ አሽቀንጥረው ከብሔርተኞች ስር ሲርመጠመጡ፣ ➔ግዙፍ ሥማቸውንና በሕዝብ ልብ ውስጥ የተቀመጠ ዙፋናቸውን ወርውረው ከቆማሪዎች ወንበር ላይ በእርካታ ሲቀመጡ…ዐየኋቸው፡፡ በህውሓት ጊዜ አገራዊ ችግሮች ከመከሰታቸው በፊት ቀድመው የሚተነብዩት ፖለቲከኛ በብልጽግና ጊዜ የተከሰተ ችግርን መመልከት ሲሳናቸው ዐየሁ፡፡ ያለፈውን ሥርዓት ‹‹አገር የሚያወድም ካንሰር ነው›› እያሉ የሚጠሩት ጉምቱ ፖለቲከኛ ሥልጣን ላይ ያለውን ሥርዓት ‹‹አገር የሚያክም ዶክተር ነው›› እያሉ ሲያወድሱት ሰማሁ፡፡ ፕሮፌሰር በለጠ ሞላ ▬▬▬▬▬▬ እንደ ሌሎች የአብን አመራሮች በሶሻል ሚዲያ ሳይሆን በአካልም ጭምር ያገኘሁትና በእርጋታው፣ በእውቀቱ፣ በብስለቱ በተለያዩ ጊዜያት እዚህ ገፄ ላይ አድናቆቴን የቸርኩት ፕሮፌሰር በለጠ በሰለጠነ መንገድ የዶክተር ደሳለኝን ሥልጣን ተረክቦ የአብን ፕሬዝዳንት ሲሆን ‹‹የተጀመረውን ድርጅታዊ ትግል ከፍ በማድረግ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጸመውን በደል እና ግፍ እንዲቀንስ ማድረግ ይችላል›› የሚል እምነት ነበረኝ፡፡ ፍልስፍና ያጠና ሰው እንደመሆኑ መጠንም ከቁሳዊ እና ግላዊ ነገሮች ይልቅ ሕዝባዊ እና ሞራላዊ ጉዳዮችን ያስቀድማል የሚል ግምት ነበረኝ። የብልጽግናን ሥልጣን በተረከበ ማግሥት ግን ይሄንን ዐየሁ! ➔የነበረውን እርጋታ ወደ መኝታ አሳድጎ በእንቅልፍ ሲስለመለም፣ የተጀመረውን ድርጅታዊ ትግል እና የተባባሰውን ሕዝባዊ በደል እርግፍ አድርጎ ትቶ ከተሰጠው ወንበር ላይ ያገኘውን ድል ሲያጣጥም፣ ➔በብልጽግና ፓርቲ ተመስጦ አብንን ሲያከስም፣ ‹‹እውነት ምንድና ናት›› ለሚለው የፍልስፍና ጥያቄ ‹‹በሕዝብ ትግል የምትገኝ ግላዊ ጥቅም ናት›› የሚል መልስ ሰጥቶ ኑሮውን ሲያጣጥም፣ ➔ከአርባ በላይ የአብን አመራሮች ጋር በሺህዎች የሚቆጠሩ ፋኖዎች መታፈናቸውን የሚደግፍ መግለጫ ላይ ሲፈርም... በደል ፈጻሚው እሱ ሆኖ ሳለ እንደተበዳይ ሲያልጎመጉም፣ ከተማረው ፍልስፍና በተቃራኒ ተሰልፎ በእራስ ወዳድ ስብዕና ሥልጣኑን ለማስረከብ ሲለግም ዐየሁ፡፡ የአማራን ሕዝብ ያለመሪ ድርጅት አስቀርቶ አምሳ ሚሊዮን ግለሰብ ሲያደርገውም ታዘብኩ፡፡

በመተከል ጥቃት ሲያልቅ ለኖረው ሕዝብ ፥ ድምጽ ስለሆነ፤ መሸለም ሲገባው በብአዴን ትዕዛዝ ፥ ታፍሶ የታፈነ። #ፍትሕ በሚያሸልማቸው ተግባር ለእስር ለተዳረጉ ሁሉ‼️
በመተከል ጥቃት ሲያልቅ ለኖረው ሕዝብ ፥ ድምጽ ስለሆነ፤ መሸለም ሲገባው በብአዴን ትዕዛዝ ፥ ታፍሶ የታፈነ። #ፍትሕ በሚያሸልማቸው ተግባር ለእስር ለተዳረጉ ሁሉ‼️

ጄኔራሉ በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ዋስ የመሆን እድሉን ባገኝ ደስታውን አልችለውም‼️
ጄኔራሉ በሰላሳ ሺህ ብር ዋስ እንዲለቀቅ ፍርድ ቤቱ ወስኗል። ዋስ የመሆን እድሉን ባገኝ ደስታውን አልችለውም‼️

ፋሲል የኔ ዓለም ሰቦቃ ▬▬▬▬▬▬ ➔ፖለቲከኞችን እና ፖለቲካን በዘር መነጽር መመልከት የተጠናወተው፤ ➔ለአማራ ፖለቲከኞች፣ አክቲቪስቶችና ጋዜጠኞች በጎ እይታ የሌለው፤ ➔የተረኝነት መንፈስ የሚሰማው፤ ➔ከብሔርተኞች ጎራ ለመቀላቀል የቋንቋ እጥረት ያጋጠመው፤ ➔ተወልዶ ላደገበት አካባቢ ቅን አመለካከት የሚጎድለው፤ ➔የክፋት አስተሳሰቡን በዜግነት ጭምብል እና በለስላሳ ቃል መጠቅለል የሚቀናው፤ ➔"የኢትዮጵያ ፖለቲካ ከሰሜን ኢትዮጵያ መራቅ አለበት" በሚል እሳቤ እነ አንዱዓለም አራጌን ሳይቀር ሲታገል የምታገኘው፤

ሶስቱ የበቀለ ልጆች ▬▬▬▬ ➔ዶክተር ስለሽ በቀለ ➔ኢንጂነር ስመኘው በቀለ ➔ሽመልስ በቀለ ሦስቱ የመኮነን ልጆች ▬▬▬▬▬ ➔ናትናኤል መኮነን ➔ደመቀ መኮነን ➔መሳይ መኮነን ጋሽ በቀለን እናመሠግናለን! ጋሽ መኮነን ግን በጣም ታናድዳለህ 😆

እራስዎን ይፈትሹ!! አሳዬ ደርቤ ታላላቅ ስብዕናዎች፡- ▬▬▬▬▬ ➔መልካሞች ሆነው ለሌሎች ይኖራሉ፡፡ ➔ከጥቅም ይልቅ መልካም ሥምን ያስቀድማሉ፡፡ ➔ለሌሎች ነጻነት የእራሳቸውን ሕይወት ይሰዋሉ፡፡ ➔በጭቆና ሜዳ ውስጥ አፈናን ሲጠየፉ፣ በቅጥፈት ፖለቲካ ውስጥ እውነትን ሲለፍፉ፣ የእራሳቸውን ግላዊ ሲሳይ ንቀው ስለ ሌሎች ስቃይ ሲባዝኑ ለአፈና እና ለካቴና ይዳረጋሉ፡፡ በባርነት የብስ ላይ ነጻ የሆነች ነፍስ ታቅፈው ሲሟገቱ በተላላኪዎች ጥይት ይቀጠፋሉ፡፡ አንዳንዶቹም የታገሉለት ዓላማ ሲሳካ የማየት እድሉን ያገኛሉ፡፡ ኖርማል ስብዕናዎች ▬▬▬▬▬▬ ➔እነሱን ነጻ የሚያወጣ መሲህ ወይም መሪ እስኪመጣ ድረስ ‹‹ሕዝብ›› በሚል ሥም ታሽገው በባርነት ዘመን ባሪያነትን፣ በአፈና ዘመን ዱዳነትን፣ በብዝበዛ ዘመን ርሐብን…. ይለማመዳሉ፡፡ ➔አቅማቸውን ሳይፈትሹት፣ ሕልማቸውን ሳይኖሩት፣ መክሊታቸውን ሳያዉቁት ከሌሎች በተሰጣቸው ነጻነትና በተፈቀደላቸው ሕይወት ልክ ይኖራሉ፡፡ ሞታቸውን የያዘ ቀን እስኪመጣ ድረስ ‹‹ይሄም ያልፋል›› ሲሉ ኖረው ያልፋሉ፡፡ (ነፍስ ይማር) 😭 ውዳቂ ስብዕናዎች ▬▬▬▬▬ ➔አንዳንዶቹ ወንበር ይዘው ሕዝብን ለእጦት፣ አገርን ለፍርሰት፣ ንጹሐንን ለእልቂት… ሲዳርጉ አብዛኞቹ ደግሞ ከመጣ ከሄደው ሥርዓት ጋር መልካቸውን እንደ እስስት እየለዋወጡ ከአምባገነኖች ጎን ተሰልፈው የነጻነት ታጋዮችን ያሳፍናሉ፡፡ ሆዳቸውን ለመሞላት ሲሉ እራሳቸውን ጨምሮ ሕዝባቸውንና አገራቸውን ይሸጣሉ፡፡ ➔በመንግሥትና በሕዝብ መሃከል የሚመላለሱ ደላላዎች እንደመሆናቸው መጠን ባርነትን፣ ጭቆናን፣ እልቂትን፣ ርሐብን፣ ግፍን… የሚያሻሽጡበት አካውንት ከፍተው የወገን ድምጽ ለመሆን የሚሞክሩትን ‹‹በአመጽ ቀስቃሽነት›› ይወነጅላሉ፡፡ ‹‹እናንተን አስሮ የጀግንነትና የታዋቂነት ካባ የሚደርብ የለም›› በሚል ተልካሻ አስተያየት የልባቸውን ንቅዘት ይፋ ያወጣሉ፡፡ ➔እንደ ታላቁ እስክንድር በርካታ መስዋዕትነት ሲከፍሉ የኖሩ ጀግኖችን ‹‹ንኮች ናቸው›› እያሉ ያጥላላሉ፡፡ እንደ ጎበዜ ሲሳይ ያሉ ጋዜጠኞች ሲታፈኑ ‹‹እራሳቸውን ደብቀው ነው›› የሚል ዘመቻ ይከፍታሉ፡፡ ከእለታት ባንዱ ቀንም ከሰፊ ጨጓራቸው ጋር ወደ መቃብር ይወርዳሉ፡፡ (ነፍስ ይማር ያላልኩት ነፍስ ስለሌላቸው ነው፡፡) 😆

ጎበዟ እኅቴ "የአማራ ሕዝብ የትግል ዳራ እና አቅጣጫዎች" የሚል እጅግ አስገራሚ ሰነድ አዘጋጀች። ብአዴንም ሰነዱን ካነበበ በኋላ ለበላይ አካል ሪፖርት አደረገ። "ከምድር ላይ መጥፋት አለበት" የሚል
ጎበዟ እኅቴ "የአማራ ሕዝብ የትግል ዳራ እና አቅጣጫዎች" የሚል እጅግ አስገራሚ ሰነድ አዘጋጀች። ብአዴንም ሰነዱን ካነበበ በኋላ ለበላይ አካል ሪፖርት አደረገ። "ከምድር ላይ መጥፋት አለበት" የሚል ውሳኔ ያስተላለፈበትን ሕዝብ የሚታደግ ሰነድ በማዘጋጀቷ የተበሳጨው የብልጽግና መንግሥትም መስኪን አፈናት። ቤቷን ሲፈትሽም ያገኘውን አምሳ የኬንያ ሽልንግ እንደ ወንጀል ቆጥሮ "በሕገወጥ የገንዘብ ዝውውር" ከሰሳት። 😆 እንኩቶዎች‼️